[ { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ2010 ጀምሮ በፋይናንሱ ዘርፍ ስኬታማ ለውጦች መመዝገባቸውን ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፋይናንስ ዘርፍ ዐበይት ስኬቶች በሚል በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ እንዳስታወቁት የታክስ ገቢ በ2010 ከነበረበት 229 ቢሊየን ብር በ2012 የ36 በመቶ ጭማሪ በማሳየት 311 ቢሊየን ማድረስ ተችሏል። \n \nጥያቄ: በ2010 ዓመታዊ የታክስ ገቢ ስንት ብር ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 229 ቢሊየን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nተቀማጭነቱ ካሊፎርኒያ ውስጥ ያደረገው ኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የተባለው የሶፍትዌር አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ፡፡ የኢ ኦ ኤን ኩባንያ መስራች ዳን ለጀርስካር ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት መኖሩን ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሂሩት በበኩላቸው የቴክኖሎጂውን አስፈላጊነትና ወቅታዊነትን በመገንዘብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኩባንያው ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የሶፍትዌር አምራች ድርጅት ማዕከሉን በኢትዮጵያ ለመክፈት ሀሰብ እንዳለው ውይይት ያደረገው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየመደመር መንገድ መጽሐፍ ሁለት ዓላማ ያነገበ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡ ይህም በአንድ በኩል ሐሳብ ማስተላለፍ በሌላ በኩል በገቢው ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል፡፡ የመጽሐፉ የነጠላ መሸጫ ዋጋ 350 ብር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አንባቢዎች ሊዳረስ የሚችል በቂ ቅጅ ስላለ ከዚህ በላይ ከሚሸጡት እንዳይገዙም አሳስበዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የመደመር መጽሐፍ ጸሐፊ ማነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፌስቡክ የሰዎችን ምስል ለማጣራት እና ለመለየት የሚጠቀምበት መሳሪያ ጋር ተያይዞ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የህግ ክርክር እልባት መስጠቱ ተገልጿል። ፌስቡክ በፈረንጆቹ 2010 የሰዎችን የፊት ገጽታ መለያዎች መሣሪያን መጠቀም በፈረንጆቹ 2010 ላይ የጀመረ ሲሆን፥ መሣሪያው የተጠቃሚውን ፊት ገጽታ በመቃኘት ስለ ደንበኛው ማንነት ሃሳቦችን የሚያቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ምንም እንኳን ተጠቃሚዎች እሱን የማጥፋት አማራጭ ቢኖራቸውም፣ በወቅቱ ቴክኖሎጂው አወዛጋቢ ሆኖ መገኘቱ ተጠቁሟል። ተቃዋሚዎቹ የፊት ገጽታ መለያ መሣሪያው በኢሊኖስ ግዛትከወጣው የግላዊነት ህጎችን ይጥሳል ብለው የተከራከሩ ሲሆን ÷በግዛቱ ለሚገኙ ቡድኖችም 550 ሚሊየን ዶላር ይከፍላልም ተብሏል። ጉዳዩ በፈረንጆቹ ከ2015 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ፥ስምምነቱም በየሩብ ዓመቱ ከሚገኝ ገቢ መሆኑም ተመላክቷል። ይህ የፊት ገጽታ እውቅናው በፖሊስ እና በአደባባይ ቦታዎችጥቅም ላይ ሲውል በጥልቀት ክትትል እንደሚደረግበትም ተገልጿል። በፈረንጆቹ ታህሳስ ወር 2017ተጠቃሚዎች ይበልጥ በቀላሉ ማብራት ወይም ማጥፋት ይችላሉ እንዲችሉ ተደርጎ የተሰራ ሲሆን ÷በ 2019 ፌስቡክ ይበልጥ በግላዊነት ላይ ያተኮረ እንዲሆን አድርጎ አዲሱ የመቆጣጠሪያ አካል አድርጎ መስራቱም ነው የተገለጸው። የማህበራዊ አውታር መረቡ ይህንን ጉዳይ ለማህበረሰባችን እና ለባለአክሲዮኖቻችን ጥቅም ስንል ለመፍታት ወስነናል ሲል አስታውቋል፡፡ ይህ ማስተካከያ የሰዎችን መረጃ እና ግላዊነትን ለመጠበቅ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሁለተኛውን ትልቁ መሆኑን የኢንቨስትመንት ባንክ ጃንስትር የሆኑት ክርስቶፎር ሮዝባች ተናግረዋል። ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: ፌስቡክ የሰዎችን የፊት ገጽታ መለያዎች መሣሪያን መጠቀም የጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በፈረንጆቹ 2010 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ የትኞቹን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወቱ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፋሲለደስ ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው አፄ ሱሰኒዮስ እና እናታቸው ልዕልት ስልጣነ ምገሴ በመገዛዝ፣ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው። አፄ ፋሲል አዘዞ ተብላ በምትታወቀው ከጎንደር ከተማ 5 ማይል ርቃ በምትገኘው ከተማ ጥቅምት18፣1667 እ.ኤ.አ. (ጥቅምት 10፣ 1660) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አስከሬናቸውም የአገሪቱ መላ ህዝብ ባዘነበት ሁኔታ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ተብላ በምትታወቀው ደሴት የዘላለም እረፍት አገኘ። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲለደስ የዙፋን ስማቸው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዓለም ሰገድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ በመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ላስመዘገበችው ውጤት ሩዋንዳ በተዘጋጀው የአፍሪካ የጤና ኮንፍራስ ላይ እውቅናን አግኝታለች :: በሀገር አቀፍ ደረጃ ሞዴል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያ የሆነችው ወ/ሮ ሰናይት 40,000 የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በመወከል ሽልማቱን ተቀብላለች:: \n \nጥያቄ: በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደረጃ ሞዴል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያ ተብላ የተመረጠችው ማናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ወ/ሮ ሰናይት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሆ ቺ ሚን ሆ ቺ ሚን ከ1890-1969 እ.ኤ.አ. የኖረ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሥራችና መሪ ነበር። ሆ ቺ ሚን ከወጣትነት ጊዜው ጀምሮ ለአብዮታዊ ተግባራት የቆመ ነበር። ሆ ቺ ሚን በሥራ ምክንያት ፈረንሳይ ውስጥ በነበረበት ወቅት የካፒታሊስት ሥርዓት ምን ያህል ሠርቶአድሩን ሕዝብ ለሥቃይና ለመከራ እንደዳረገውና የዓለም ወዛደሮች በቀለም በቋንቋና በባህል ቢለያዩም ብሶታቸው አንድ መሆኑን በቅርብ ተገነዘበ። በአፍሪካና በእስያ የኢምፔሪያሊስቶች መምጣት ምን ያህል ሥቃይና ውርደት በእነዚህ ሕዝቦች ላይ እንዳደረሰ ተረዳ። በዚህም ምክንያት ሆ ቺ ሚን የቬትናም ሕዝብ ጠላት የፈረንሳይ ኢምፔሪያሊዝም እንጂ የፈረንሳይ መላው ሕዝብ አለመሆኑን ደጋግሞ ገልጿል። ሆ ቺ ሚን በ1917 እ.ኤ.አ. በፈረንሳይ ወዝአደሮች ትግል ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊ በመሆን የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲ አባል ሆነ። ከዚህም በላይ በፈረንሳይ የቬትናም አርበኞችን ማኅበር በማቋቋም በፈረንሳይ ይኖሩ የነበሩትን ቬትናማውያን በማንቃትና በማስተማር ለሀገራቸው ነፃነትና ክብር እንዲታገሉ ያነሣሣ ነበር። የጥቅምቱ የሩሲያ አብዮት ለአያሌ ዓመታት በዓለም ሰፍኖ የነበረውን የኢምፔሪያሊዝም ብቸኛ የበላይነት ሰባብሮ አዲስ ዘመን በማብሰሩ ሆ ቺ ሚን የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ የቦልሼቪኮችን ፈለግ መከተል እንዳለበት አመነ። በሆ ቺ ሚን አስተሳሰብ የቬትናም ብቻ ሳይሆን የሌሎች ቅኝ ተገዥ የሆኑ ሀገሮች ነፃነት የሚገኘው የወዝአደሩን የአብዮት ጎዳና በመከተል ብቻ እንደሆነ አጥብቆ ያምን ነበር። የነዚህ ሀገሮች ብሔራዊ ነፃነት ከማኅበራዊ ነፃነት ጋር መያያዙንና ይህም ነፃነት ከሶሻሊዝምና ከኮሚኒዝም ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን አስገንዝቧል። ሆ ቺ ሚን ከ1924 እስከ 1930 እ.ኤ.አ. በቻይናና በቬትናም በመዘዋወር ለዚህ ውስብስብ ትግል ግንባር ቀደም አመራር ሊሰጥ የሚችለውን ማርክሳዊ ሌኒናዊ ፓርቲ ለማቋቋም ከፍተኛ ትግል አደረገ። በመጀመሪያም የቬትናም አብዮታዊ ወጣቶች ማኅበር የተባለውን በማቋቋም «ወጣት» በተባለው ጋዜጣ ወጣቱን ለትግል ቀሰቀሰ። በዚህ ዓይነት ከብዙ ጥረትና ትግል በኋላም በ1930 እ.ኤ.አ. የኢንዶቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን (ኋላ የቬትናም ሠራተኞች ፓርቲ፤ ዛሬ ደግሞ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ) መሠረተ። በ1935 እ.ኤ.አ. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደው የኮሚኒስቶች ስብሰባ አንድ ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት የሆነ ዲሞክራሲያዊ ግንባር እንዲቋቋም በወሰነው መሠረት ሆ ቺ ሚን ቬትሚን የተሰኘውን ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት ግንባር በማቋቋም መላውን ሕዝብ በትግሉ ለማሳተፍ ችሏል። ዲየን ቢየን ፉ በተባለው ታሪካዊ ስፍራ የቬትናም አርበኞች የፈረንሳይን ጦር በማሸነፋቸው ፈረንሳይ በጀኔቩ ስምምነት መሠረት የቬትናምን አንድነት በማወቅ የሰላም ውል ፈረመች። ነገር ግን ከ1955 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም በፈረንሳይ እግር በመተካት የደቡቡን ክፍል ለመቁረስ የጦር ሰፈር በመሥራትና በውስጥ አርበኞች በመጠቀም ጦርነት ከፈተ። ነገር ግን አሜሪካ ከግማሽ ሚሊዮን ወታደሮች በላይና በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ቢያፈስም ቬትናምን ሊያሸንፍ አልቻለም። \n \nጥያቄ: ሆ ቺ ሚን ትግሉን ለማሸነፍ ምን አይነት መንገድ ተጠቀመ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የቦልሼቪኮችን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና የአሻንቲ መንግሥት የቆየው ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ1662 እስከ 1949 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ የምትገኝበት አህጉር የት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሄራቅሊጠስ የዚህ ዓለም ጥንተ መሰረት ምንድን ነው ብሎ ነበር የሚያምነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እሳት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል። ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማራያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል። ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ ይኖራል። አልፎም በግራኝ አህመድ ዘመን በእሳት ጋይቶ የነበረችውን አክሱም ፂዮን በአዲስ መሰረት እንደገና ማሰራት ችሎአል። ፋሲለደስ በዘመኑ እጅግ ተወዳጅ ንጉስ ቢሆንም አመጽ መነሳቱ አልቀረም። በላስታ ለምሳሌ በ1637 መልክዓ ክርስቶስ በተባለ ሰው መሪነት ጦርነት ተነስቶ አፄ ፋሲልን ስጋት ላይ ቢጥልም በሚቀጥለው አመት በተደረገው ጦርነት አመፁ ሊገታ ችሎአል። ፋሲለደስ ፖርቱጋሎችን ቢያባርርም ከውጭው አለም ጋር ብዙ ግንኙነት ያደርግ ነበር። ለምሳሌ በ1664-5 የህንድ ንጉስ አውራንግዘብ ሲነግስ መልካም ምኞትን በመልክተኞቹ ለሙግሃሉ መሪ ልኮ ነበር። በ1666 ልጁ ዳዊት ሲያምጽ፣ ወህኒ ተብሎ ወደሚታወቀው አገር በግዞት ልኮት ነበር። ይህም ከጥንቶቹ የኢትዮጵያውን ነገሥት ተፎካካሪያቸውን ወደ አምባ ግሽን በግዞት እንደሚልኩት ስርዓት ነበር። \n \nጥያቄ: ጎንደር ከተማ በምን ትታወቃለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዳም ረታ አዳም ረታ ልቦለድና ግጥም በአማርኛ የሚጽፍ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነው። አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተመው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ”፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። ይህ የአጻጻፍ ስልቱ ሕጽናዊነት የሚባል ሲሆን ደራሲው በሌሎቹ መጻሕፍቱም ውስጥ በስፋት ተጠቅሞበታል፡፡ በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየዓመቱ አንዳንድ መፅሐፍ ለአንባቢያ ያደረሰ ሲሆን በ2002 ዓ.ም “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ በ2003 ዓ.ም “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” እና በ2004 ዓ.ም “ሕማማት እና በገና” ታትመው ለንባብ በቅተዋል። “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” በተሰኘው መፅሀፉ ድንቅ የፋንታሲ (“ፈንጠዚያ”) ሥራዎች የተካተቱ ሲሆን በ”ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” ለመጀመሪያ ጊዜ መቼቱን ከሀገር ውጭ በማድረግ የውጭውን ሕይወት በስሱ የዳሰሰ ሲሆን ከሌሎቹ ስራዎቹ በተለየ መልኩ ስለሀገራችን ፖለቲካ ወጣ-ገባ መንገድ በታዛቢ አይን ምልከታው፣ ትውስታውን … አስፍሯል፡፡ ሕማማትና በገና የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ሲሆን ለየት ያለ ቅርፅ ያላቸው አንዳንድ ልቦለዶች ተካተውበታል። ፍልስፍናውና ስልቱ ሕፅናዊነት በሚል ስያሜው ይፋ ሆኗል። \n \nጥያቄ: አዳም ረታ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1950 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በቤተክርስቲያንና በምእመናን ላይ የተለያዩ መከራዎች እንዲደርስባቸው ምክንያት የሆኑት ነገሥታት እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1828 ዓ.ም. በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ሰዎች በማን ተወረሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በንዴቤሌ ብሔር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: በቻይና ዘመናዊው የኮንግ-ፉጸ ትምሕርት መቼ ይፋ ሆነ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1360-1903 ዓም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ፈላስፋ ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ታሊዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የኢያን ስሚዝ መንግሥት በዚምባቡዌ ከሦስት መሪዎች ጋር በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የተፈራረመው ስምምነት ስለምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከኢትዮጵያውን ይልቅ በብዛት የውጪ ዜጎችን እየቀጠሩ መሆናቸውን ያሳወቁት ኃላፊ ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወ/ሮ ስምረት ግርማ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም. በሚካሄደው የአስትሮኖሚካል ሲምፖዚየም ላይ ከስንት በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይታሰባል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ200 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጎ ያስገነባቸው አራት የአየር መቆጣጠሪያ ታወሮች ነገ እንደሚመረቁ ተገለጸ፡፡ ታወሮቹ የተገነቡት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ሮቤ ከተማ፣ በአማራ ክልል ኮምቦልቻ፣ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ እና በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ መሆኑን ከባለስልጣኑ ማህበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ለአየር መቆጣጠሪያ ታወሮች ግንባታ ምን ያህል ገንዘብ አወጣ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: በሳውዲ አረቢያ ምን ያህል ህዝቦች ይኖራሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 28.7 ሚሊዬን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቴክኖ ካሞን 17 በዘጋቢ ፊልም ታግዞ ወደ ገበያ መግባቱን ኩባንያው አስታወቀ :: በዓለም አቀፍ ደረጃ በአዲሱ ትውልድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ቴክኖ ሞባይል ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም በለቀቀው አዲሱ የCAMON 17 ተከታታይ ስልክ የብዙዎችን ቀልብ መሳብ መቻሉን ኩባንያው አስታውቋል:: ይህ ፈጠራ የታከለበት ቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ማጠንጠኛውን በሰልፊ ላይ ባደረገ ዘጋቢ ፊልም የተመረቀ ሲሆን ድርጅቱ ምርቱን ከማስተዋወቅ ባለፈ በኢንዱስትሪ፣ በማኅበራዊና በሰብዓዊነት ዘርፎች ላይ የበለጠ ጥረት ለማድረግ ያለውን ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል:: “The Rise of Selfie” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ዘጋቢ ፊልም ፊልም በማስመረቂያ ፕሮግራሙ ላይ የቀረበ ሲሆን ታዳሚዎቹ በእርግጥም ቴክኖ የዚህን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት በተጨባጭ እና በስሜት እየሰራ መሆኑን ስለመገንዘባቸው ድርጅቱ ገልጿል:: አዲሱ የቴክኖ የንግድ አምባሳደር ክሪስ ኢቫንስ “ሕያው እና በስሜት የተሞላ ምስል ትፈልጉ ይሆናል፣ ነገር ግን መልካም ምስል የሚያደርገው ‘እጅግ ግለሰባዊ’ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ ሁሌም ቴክኖ በፅኑ ከሚያምንበት እና ከሚታወቅበት ሃሳብ ጋር ይጣጣማል ብለዋል፡፡ የስማርት ስልክ ፅንሰ ሃሳብ ብራንዱ ላይ ሳይሆን ተጠቃሚው ላይ ማውጠንጠን እንዳለበትም ነው የንግድ አምባሳደሯ የጠቆሙት፡፡ የፋሽን ሞዴል የሆኑት ሣራ በፊልሙ ላይ እንዳሉት እንደ ቴክኖ ካሞን 17 ያሉ የሰልፊ ስልኮች ተጠቃሚዎች የራሳቸውን ምስል ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተወዳጅ ፎቶዎችን በማንሳት ምስላቸውን እንዲቆጣጠሩ ያስችላቸዋል:: በተጨማሪም የተሻለ ማንነት እንዲኖር ለማድረግ እዲሁም በደመነብስ ወደተሻለ እኛነት እንድንመጣ ለራሳችን የምንጠቁምበት መንገድ ነው ብለዋል:: ቴክኖ ካሞን 17 ሁልጊዜ “በልባቸው ወጣት” ለሆኑ እና ለአዳዲስ ነገሮች ራሳቸውን ለሚያነሳሱ ተጠቃሚዎች ምልክት ለመሆን የተሰራ ነው ያለው ድርጅቱ፥ ሰዎች ራሳቸውን በይበልጥ ለመግለጽ እንዲችሉ ያስችላቸዋልም ብሏል፡፡ ኮቪድ19 ባስከተለው ተጽዕኖ ሰዎች ከሚወዷቸው ሰዎች ጋር ለመገናኘት ሰልፊን ማዘውተራቸው የሰልፊን ተግባር ይበልጥ አስፈላጊ ያደረገው በመሆኑ ጉዳዩን ቴክኖ እና ሌሎች የስልክ አምራቾች በአጽንኦት እንዲያጤኑት አድርጓቸዋል:: በቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ሰዎች ህይወት ያላቸው የሚመስሉ ፎቶዎችን ማጣጣም ብቻ ሳይሆን በFHD ስክሪን ላይ በጣም ግልጽ የሆነ ምስልን ማየት እንደሚያስችላቸው ነው የተገለጸው:: ይህ ከፍተኛ ጥራት ያለው ስክሪን ተጠቃሚዎች በቪዲዮ ጥሪዎች ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ተወዳዳሪ የሌለው ግልጽነት የሚሰጣቸው ሲሆን ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎችን መመልከት እና ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ጌሞችን መጫወት እንደሚችሉም ነው ኩባንያው የገለጸው፡፡ ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!   \n \nጥያቄ: ቴክኖ ኩባንያ ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ያስተዋወቀው አዲሱ ምረቱ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኢትዮጵያን በመወከል ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት መቅረባቸው ነው የተነገረው። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ለረጅም ዓመታት በመምህርነት አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ፕ/ር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ምን ክፍል ውስጥ ነው ያገለግሉ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሁዋዌ የተሰኘው ግዙፍ የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተሰምቷል። የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ሀገራቸው ከሁዋዌ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በቅንጅት ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ኩባንያው በቀጣይ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ነው የገለጹት። ሁዋዌ ቻይና ከአሜሪካ ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ መግባቷን ተከትሎ በዩናይትድ ስቴትስ አገልግሎት እንዳይሰጥ ክልከላ የተደረገበት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው አገልግሎት በሚሰጥባቸው ሀገራት በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጣልቃ ይገባል በሚል ካናዳ እና አውስትራሊያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት መሻከሩ ይታወቃል። ብሪታኒያ ከኩባንያው ጋር በቅንጀት ለመስራት እና አገልግሎቱን ለመጠቀም መፈለጓም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ሊያሻክረው እንደሚችል ተሰግቷል። ምንጭ፦ሲ ጂ ቲኤ ን \n \nጥያቄ: ሁዋዌ በአሜሪካ አገልግሎቱን ያቋረጠው ቻይናና አሜሪካ ወደ ምን በመሄዳቸው ምክንያት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የንግድ ጦርነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአቡነ ቴዎፍሎስ አቡነ ቴዌፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ጎጃም በሚገኝው በዝነኛው ደብረ ኤሊያስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ማርያም ውቤ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘርትሁን አደላሁ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፲፱፻፪ ዓ/ም ተወለዱ። ሲወለዱም የተሰጣቸው ስም መልእክቱ ወልደ ማርያም ነበር። በልጅነታቸው ንባብ እና ዜማን በመምህር መሪ ጌታ ረዳኸኝ እና ግራ ጌታ ሣህሉ እዚያው የተወለዱበት አካባቢ ተምረዋል። ኋላ የቅኔ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ዝንባሌ ስላደረባቸው እዚያው ደብረ ኤሊያስ ደብር መምህር ገብረ ሥላሴ በሚባሉ ሊቅ ሥር መማር ጀመሩ። በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው ፍትሐ ነገሥትና አዲስ ኪዳንን በመምህር ተክሌ (ነቡረ ዕድ በኋላ ቢትወደድ አቡነ ዮሐንስ) በመባል የሚታወቁት መሪነት ሲከታተሉ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የኃይማኖት ችግሮችን ለማወቅ ይፈልጉ እንደነበርና ሰፋ ያለ ዕውቀት እንደነበራቸው ይነገራል። በተጨማሪ የኃይማኖት ችግሮችን የሚመለከቱ መጻሕፍትን ሳይታክቱና ሳይሰለቹ ያነቡም ነበር። መልእክቱ ወልደ ማርያም በ፲፱፻፴ ዓ/ም ይህን ዓለም በቃኝ ብለው ደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰው ገቡ። ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀሳውስቱ በዘመናዊ የኃይማኖት ትምህርት እንዲሠለጥኑ በነበራቸው ሀሳብ መሠረት ፳ የሚሆኑ ሊቃውንት መርጠው በቤተ መንግሥቱ አካባቢ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። ከነኚህም አንዱ አባ መልእክቱ ወልደ ማርያም ናቸው። ቀደም ብሎ በኢትዮጵያና በግብጽ በተደረገው ስምምነት መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ጳጳሶች ሲሾሙ ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ ወልደ ማርያም ለሹመት ከተመረጡት አምስት አባቶች አንዱ ሲሆኑ ወደግብጽ ተጉዘው በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ እጅ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ “ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ” ተብለው የሐረርጌ ጳጳስ ሆኑ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ የነበሩት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አቡነ ቴዎፍሎስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን የማስተርስ ዲግሪውን መቼ አገኘ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ትራምፕ በስንት አመቱ ስልጣን ላይ ወጣ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ70 ዓመቱም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ young men’s Cristian association tinning school በአሁኑ መጠሪያው spring filed college ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ YMCA ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን FYBA አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ Czechoslovakia ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ lasiva፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡ \n \nጥያቄ: የሴቶች ባስኬት ቦል ውድድር የተጀመረው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በስሚዝ ኮሌጅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመንግሥት እና ፖለቲካ ናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ሲሆን መንግሥቷ በአሜሪካ መንግሥት ላይ ነው የተመረኮዘው። የህግ አውጪው አካል አወቃቀር የዌስትሚኒስትር ሥርዓትን ይከተላል። በአሁኑ ጊዜ ጉድላክ ጆናታን ፕሬዝዳንት ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ለሁለት የአራት ዓመት ጊዜ ሲያገለግል በሕዝቡ ነው የሚመረጠው። የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት አካሎች አሉት። እነዚህም ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ናቸው። ሴኔቱ 109 መቀመጫዎች ሲኖሩት እያንዳንዱ ክልል በሶስት አባሎች ይወከላል። የአቡጃ ርዕሰ አካባቢም አንድ ተወካይ አለው። የሴኔት አባላት በሕዝብ ይመረጣሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 360 መቀመጫዎች ሲኖሩት የእያንዳንዱ ክልል ወካዮች በሕዝብ ብዛት ነው የሚወሰነው። የውጭ ግንኙነቶች ነፃነቷን በ1960 እ.ኤ.አ. ካገኘች በኋላ ናይጄሪያ ለአፍሪካ ነፃነትና ክብር መታገል ዋና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አድርጋለች። የደቡብ አፍሪካን አፓርታይድ ሥራዓት በመቃወም ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በ1960ዎቹ እ.ኤ.አ. ናይጄሪያ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ሲሆን እስራኤል የናይጄሪያ ፓርላማ ህንጻዎችን አሰርታለች። ናይጄሪያ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራች አገር ናት። በምዕራብ አፍሪካም ሆነ በአፍሪካ በጠቅላላ ትልቅ ተጽዕኖ አላት። በተጨማሪም እንደ ኤኮዋስ ያሉ የምዕራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅቶች መሥራች ናች። ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ጀምሮ ናይጄሪያ ዋና የነዳች አምራች ስትሆን የኦፔክ አባል ሀገር ናት። በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ናይጄሪያውያን በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ናይጄሪያውያን በአሜሪካን እንደ ሚኖሩ ይገመታል። \n \nጥያቄ: የምእራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅት ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኤኮዋስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: የጣና ሐይቅ መጋቢ ወንዞች እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ596 ዓ.ም. በጃፓን 17 አንቀጽ ያለ ሕገ መንግሥት በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ ይታመናል። እንዲሁም በ614 ዓ.ም. ከነቢዩ መሐመድ የወጣው የመዲና ሕገ መንግሥት ዕጅግ ጥንታዊ ምሳሌ ነው። በዌልስ በ940 ዓ.ም. አካባቢ ንጉስ ህወል ዳ ሕጎቹን ጻፉ። በዛሬው ሩሲያ ደግሞ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ጥበበኛው ፕራቭዳ ያሮስላቫ የተባለውን ሕገ መንግሥት በ1009 ዓ.ም. ያህል ሠሩ። ይህ ሕግ በ1046 ታድሶ በኪዬቭ ሩስ በሙሉ ህጝ ሆነ። በስሜን አሜሪካ የኖሩ ኗሪ ጎሣ ሆደነሾኒ 'የአፈ ቃል' ሕገ መንግሥት «ጋያነሸጎዋ» የነበራችው ከ1080-1140 ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ሕግ በከፊል ለአሜሪካ ሕገ መንግሥት ተጽእኖ እንደነበረው ይታመናልና የአሜሪካ ምክር ቤት በ1981 ዓ.ም. ይህንን ግንዛቤ አስታወቀ። በእንግሊዝ አገር በ1092 ዓ.ም. ንጉስ 1 ሄንሪ የነጻነት ሥርአት የተባለውን ሰነድ አዋጀ። ይህ መጀመርያ የንጉሱን ሥልጣን ወሰኖ ንጉሡ ለቤተ ካህናትና ለቤተ መሳፍንት ወገኖች የሚገባውን እንቅብቃቤ ገለጸ። ይህም መሰረት በመኳንንቱ ሲዘረጋ በ1207 ዓ.ም. የእንግሊዝ ንጉሱን ዮሃንስ (ጆን) ማግና ካርታ («ታላቅ ሥርዓት») የሚባለውን ሰነድ እንዲፈርሙት አስገደዱዋቸው። ከዚሁ መሃል ቁም ነገር የሆነው ንጉሡ ያለ ሕጋዊ ሂደት ማንንም ሰው እንዳይገድሉ፣ ከአገር እንዳያሳደዱ፣ ወይም እስር ቤት እንዳያስገቡ ከለከላቸው። በዚያ ወቅት ያ ሰነድ በእንግሊዝ አገር የነጻነት መሠረት ሆነ። በ1212 እና 1222 ዓ.ም. መካከል አንድ የሳቅሰን አስተዳዳሪ አይከ ቮን ረፕጎቭ ያቀነባበረው ሕግጋት ሳቅሰንሽፒግል በአንዳንድ ጀርመን ክፍላገር እስከ 1892 ዓ.ም. ድረስ ላይኛ ሕገ መንግሥት ሆነ። በ1228 ዓ.ም. ሱንዲያታ ከይታ ማሊ መንግሥትን ለማወሐድ የ'አፈ ቃል' ሕገ መንግሥት አወጡ። ይህ ሕግ 'ኩሩካን ፉጋ' ተብሎ ነበር። \n \nጥያቄ: በ1009 ዓ.ም. ተዘጋጅቶ በሩሲያ ጥቅም ላይ የዋለው ሕገ መንግሥት ያዘጋጀው ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ያሮስላቭ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ለመጀመሪያ ጊዜ ምድር ጸሓይን ትዞራለች እንጂ ፀሓይ መሬትን አትዞርም ብሎ ያስተማረው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ16ኛው ምእት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማይክሮሶፍት በዊንዶውስ 10 የመተግበሪያ ስርዓት አጋጥሞ የነበረውን ችግር መፍታቱን አስታወቀ። በርካታ ተጠቃሚዎች መተግበሪያው ከትናንት ጀምሮ መስራት ማቆሙን ገልጸው ነበር። ተጠቃሚዎች እንደገለጹት በዴስክቶፕ መረጃ መፈለጊያ ትዕዛዝ ሲጠይቁ የሚፈልጉትን ነገር ከማግኘት ይልቅ ባዶ ሳጥን ያገኙ ነበር። ኩባንያውም የተጠቃሚዎችን ሪፖርት ካገኘ ከሰዓታት በኋላ የብዙ ተጠቃሚዎችን ችግር መቅረፍ መቻሉን አስታውቋል። ይሁን እንጅ አሁንም አንዳንድ ተጠቃሚዎች ኮምፒተሮቻቸውን እንደገና ማስጀመር ወይም ሪስታርት ማድረግ ሊያስፈልጋቸው ይችላል ብሏል። ኩባንያው ምን ያህል ሰዎች ይህ ችግር እንዳጋጠማቸው ግን ያለው ነገር የለም፡፡ ዊንዶውስ 10 መተግበሪያ ሥርዓት በዓለም ዙሪያ 800 ሚሊየን የሚሆኑ ተጠቃሚዎች አሉት። \n \nጥያቄ: ዊንዶውስ 10 በዓለም ላይ ምን ያህል ሰዎች ይጠቀሙታል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 800 ሚሊየን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማውሳ ትራዎሬ ወደ ማሊ ሪፐብሊክ መሪነት የመጣው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1968 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ. ጋምቢያና ማን ናቸው በኮንፌደሬሽን የተዋሐዱት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሴኔጋል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ፓርላማ ውስጥ ካሉት ምክር ቤቶች አንዱ ሴኔት ምን ያህል መቀመጫዎች አሉት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፻ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ እና ጠባቂው ተሳፍረውበት ወደ እንግሊዝ ያቀኑባት መርከብ ማን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፌሬዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ማዕከል መሥራች ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮሮና ቫይረስ ፅኑ ህክምና ማዕከል ውስጥ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዘሚ የኑስ በአሁኑ ሰአት ከ200 በላይ ለሚሆኑ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: የኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦቲዝም መስራች ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወይዘሮ ዘሚ የኑስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: አባይ ጣናን አቋርጦ ካለፈ ከምን ያህል ርቀት አባይ ፏፏቴ የሚፈጠረው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አርባ ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት የጀመረው የምን ሀገር ኩባንያ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የኮሎምቢያ ኩባንያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. በላይቤሪያ የተከሰተው የእርስ በእርስ ግጭት ምን ያህል ሰዎችን ለስደት ዳረገ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: በብራዚል ለተካሄደው ለ2014ቱ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ስንቱ ስቴድየሞች አዲስ የተገነቡ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሰባቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ የብእር ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ማርክ ትዌይን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: በአናብስት ቤተሰብ ላይ በቤት ውስጥ አመራር የሚሰጡት እናማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሴቶቹ ናቸው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ1913 በፕሬዝዳንት ዋረን ሃርዲንግ ዘመን ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ሆኑ። በሃርዲንግ ተከታይ በፕሬዝዳንት ካልቪን ኩሊጅ ዘመን ደግሞ እንዲህ ያለን ማዕረግ ይዘው አገለገሉ። የንግድ ሚኒስትር እየሆኑ ሃይለኛ ሰው ነበሩ። የንግድ ዘርፍና መንግሥት አንድላይ ይሠሩ የሚለውን ተስፋ በመያዛቸው በዚህ አንጻር ብዙ አደረጉ። በማዶ ባሕርና በውጭ አገር ለባለጉዳዮች ምክርና እርዳታ የሚሰጡ መሥርያ ቤቶች በማስከፈቱ የአለም አቀፍ ንግድ በጉልበት አስለሙ። በተለይም የሆሊዉድ ፊልም ማዶ ባሕር ለመግፋፋት ጉጉ ነበሩ። ዜጎችም ቤት እንዲያገነቡና የራሳቸው መሬት ባለአባት እንዲሆኑ አበረታቷቸው። ስለ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የክላርክ ሰነድ በ1920 ተጽፎ ሁቨር ፕሬዝዳንት እየሆኑ በ1922 ግልጽ ሆኖ ወጣ። በዚህ ሰነድ ዘንድ፥ አውሮጳ በላቲን አሜሪካ ላይ ዛቻ ካልጣለች በተቀር አሜሪካ በውጭ አገር ጥልቅ ለማለት ሕጋዊ መብት አልነበራትም የሚል ማስታወሻ ነበር። በዚያን ጊዜ አሜሪካ ሠራዊት በኒካራጓና በሃይቲ ነበራት። ስለዚህ ሁቨር ከነዚህ አገራት የሠራዊቱን ቁጥር ቀነሱ። በላቲን አሜሪካ ውስጥ የጦርነት መሣርያ እንዳይደርስ ማዕቀብ ለመጣል አሠቡ። በ1924 ጃፓን ማንቹርያን በወረረ ጊዜ አዲስ ፖሊሲ አወጡ። እሱም በግፍና በወረራ የሚገኝ የመሬት ለውጥ ሁሉ አናከብርም የሚል ነበር። ከታላቁ ጭፍግግ የተነሣ ብዙ ባንክ ቤቶች ስለወደቁ አንዳችም ብድር ለማግኘት ከባድ ሆነ። ብዙ ሰዎች ሥራ ፈት ሆኑ። በአውሮፓም ምጣኔ ሃብቱ ችግር ውስጥ ስለ ገባ ሁቨር ጀርመን ስለመጀመርያው ጦርነት ለፈረንሳይ ከምትከፍል ካሣ ለአንድ አመት ይቅር ትበል የሚል ዕቅድ አዋጁ። በሚከተለውም አመት የጀርመን ዕዳ በሙሉ ተሰረዘ። በ1925 ምርጫ ተቃራኒው ፍራንክሊን ሮዘቨልት በሰፊ መጠን አሸነፉና በሳቸው ፈንታ ፕሬዚዳንት ሆኑ። ሁቨር ፕሬዚዳንት ከሆኑ በኋላ ረጀም ዕድሜ ነበራቸው። እስከ 1957 ዓ.ም. ድረስ ኖሩ። ከ2ኛ አለማዊ ጦርነት ቀጥሎ በ1939 ስለ ቀድሞው ልምዳቸው ፕሬዚዳንት ሃሪ ትሩማን የአውሮፓ ምግብ ፍላጎት ለመወሰን ወደ አውሮፓ ላኳቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨርን ተቃርኖ በምርጫ የተወዳደረው ሰው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፍራንክሊን ሮዘቨልት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ከሚገኙ ስደተኞች ብዛት ያላቸው የተሰደዱት ከየት ሀገር ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከሞሪታኒያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: የበርሊኑ ጉባኤ መች ነበር የፖርቱጋልን የቅኝ ግዛት ድንበር የወሰነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1885 እ.ኤ.አ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የሰለሞናዊ መንግስትን የመለሱት የመጀመሪያው ንጉስ ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ይኵኖ አምላክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ የመጀመሪያ ድርሰቷ የት ኩባንያ ውስጥ ታተመላት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በጆን ዴይ ኩባንያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ናጊብ ማህፉዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ትራምፕ የት ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፌስቡክ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም እያበለፀገ መሆኑን ከሰሞኑ የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል። ኩባንያው የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም የሚሰራውም ከጎግል አንድርይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እና ከአይፎን አይ.ኦ.ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ አንደሆነም ታውቋል። አዲሱ የፌስቡክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ሙሉ በሙሉ ከዜሮ ተነስቶ በራሱ መንገድ እየበለፀገ መሆኑንም ኩባንያው አስታውቋል። ኦፕሬቲንግ ሲስተሙ በምን መልኩ ይሰራል የሚለው ነገር በግልፅ ባይታወቀም የፌስቡክ የቪዲዮ የስልክ ጥሪን ጨምሮ ሌሎች የኩባንያው አገልግሎቶች ግን ተጠቃሚ ይሆናሉ ነው የተባለው። ፌስቡክ አሁን በሚያመርታቸው መገልገያዎች ላይ በብዛት የጎግል አንድሮይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተመን የሚጠቀም ሲሆን፥ ይህም ጎግል በአብዛኛው የፌስቡክ አገልግሎቶች ላይ በበላይነት እንዲቆጣጠር እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ፌስቡክ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም መስራቱም ከጎግል አንድሮይድ ጥገኝነት የሚያላቅቀው መሆኑን እና በሚያመርታቸው መገልገያዎችን ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር ስልጣን እንዲኖረው እንደሚያደርገውም ተገልጿል። ምንጭ፦ www.techworm.net \n \nጥያቄ: ፌስቡክ ከጎግል አንድርይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እና ከአይፎን አይ.ኦ.ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ ምን ዘዴ ቀየሰ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም እያበለፀገ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ለአርካንሳው አስተዳዳሪነት ተወዳድረው የተሸነፉት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1980 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔዎች በመንጋ ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ሲሆኑ በአነድ መንጋ ምን ያህል ይኖራሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ2 እስከ 50 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዋትስ አፕ የተሰኘው የፅሁፍ እና የምስል መልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያ በሚሊየን በሚቆጠሩ ዘመናዊ ስልኮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት ሊያቋርጥ መሆኑን አስታወቀ። ዕቅዱ በተለይም ኦፕሬቲንግ ሲስተማቸውን ማዘመን ባልቻሉ የአንድሮይድ እና አይፎን ስልኮች ላይ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ ነው የተገለጸው። እርምጃው የደንበኞችን የመረጃ ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንም ኩባንያው ገልጿል። በዚህ መሰረት መተግበሪያው አይፎን ኦፕሬቲንግ ሲስተም አይ ኦ ኤስ 8ን ጨምሮ ከዚያ በፊት በተመረቱ ተመሳሳይ መለያ ባላቸው ስልኮች ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት እንደሚያቆም ተገልጿል። እንዲሁም አንድሮይድ 2፣3፣7 እና ከዚያ በፊት ያሉትን ያልዘመኑ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮች ላይ የሚሠጠውን እንደሚያቋርጥም ተነግሯል። በመተግበሪያው ላይ ማሻሻያ እያደረገ መሆኑን የገለጸው ኩባንያው፥ ይህም የመረጃ ደህንነትን ከማስጠበቅ ባለፈ ደንበኞች ሀሰተኛ ገጽ በመክፈት የተዛቡ መረጃዎችን እና የጥላቻ ንግግሮችን እንዳያሰራጩ የሚያግዝ ነው መሆኑን አስታውቋል።   ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision   \n \nጥያቄ: ዋትስ አፕ መተግበሪያው አንድሮይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ከዓይነት ስንት በታች ባላቸው ስልኮች ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማቆም አቅዷል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አንድሮይድ 2፣3፣7 እና ከዚያ በፊት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: ከደአማት መንግሥት ቀጥሎ ስልጣን ላይ የወጣው መንግስት ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አክሱም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር። ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች ኮሞዲቲ ገንዘብ መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ ከብትና እህል (ገብስ) መደበኛ ነበሩ። በተለይ ዛጎል በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። መዳብ፣ ብረት፣ ብርና ወርቅ በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረታብረት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ። በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ የፈተና ደንጊያ ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሳንቲም እና የብር ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ልድያውያን ነበር።. በኢትዮጵያም በአክሱም ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል። ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው ተወካይ ገንዘብ የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። ሆኖም ስዊድን የወረቀት ብር ያወጣው ምክንያት ጦርነት ለማድረግ ፈልጎ በቂ ወርቅ ወይም ሌላ ገንዘብ በአገሩ ስላልነበረው ነው። አሁን ወዲያው የስዊድን መንግሥት ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ሥራተኖች መክፈል ቻለ። በጥቂት ዓመት ውስት የስዎድን ወረቀት ገንዘብ ወደቀ። ነገር ግን ከትንሽ በኋላ የእንግላንድ መንግሥት በፈረንሣይ ላይ በጦርነት ተይዞ ለጦርነትም ያህል በቂ ሀብት ባለመኖሩ እንዲህ አይነት መፍትሄ መረጡ፤ የኢንግላንድ ፓውንድ ድፍን ጀመሩ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አገራት ፈቃዳቸውን ለመፈጽም አዲስ የወርቅ ወይም የብር ማዕድን ማግነት አስፈላጊ አልነበረም። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ይህ በወርቅ የተደገፈ የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በይፋ በመላው ዓለም ተንሰራፋ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብሬቶን ውድስ ስብሰባ፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች ፊያት ገንዘብን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር። በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታት እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው። \n \nጥያቄ: የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሶንግ ስርወ መንግስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም የሕይወት ዘመናቸው ከመቼ እስከ መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ዓለምና በውስጧ ያሉ ነገሮች ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን የነበረው ፈላስፋ ማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ታሊዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፕል ኩባንያ ተጠቃሚዎች በድምፅ ማዘዝ የሚችሉት ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ወይንም ኢርፎን ይፋ አደረገ፡፡ ይህም ተጠቃሚዎች ምንም አይነት ነገር ሳይጫኑ ሃይ ሲሪ የሚል ድምፅ በማሰማት ብቻ የድምፅ ማዳመጫውን ማዘዝ እንደሚችሉ ነው የተነገረው፡፡ ከዚህ ባለፈ ኤርፖድስ የተባለው ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ተጠቃሚዎች ባትሪ ካለቀባቸው እንዲያስተካክሉ ተጨማሪ ሰዓትን በቅድሚያ እንደሚሰጥ ነው የተነገረው፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት የሰጡ ባለሙያዎች ኤርፖድስ የተሰኘው የድምፅ ማዳመጫ በእጅጉ እየዘመነ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ ይህ አዲሱ ድምፅ ማዳመጫ 159 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ሲሆን ገመድ አልባ ቻርጀርን የሚያካትት ከሆነ ተጨማሪ 40 ዶላር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ኤርፓድስ የተባለ ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ መጀመሪያ ያቀረበው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አፕል ኩባንያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ከስንት ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንአግኝቷል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ በየት አካባቢ የሚነገር ቋንቋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመጋቢት ፳፮ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት የመጀመሪያው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፱ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል። ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅት መሠረቱ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (የዓለም የንግድ ማዕከል) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል። ፲፱፻፷ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በሜምፊስ ከተማ በነፍሰ-ገዳይ እጅ ተገደለ። \n \nጥያቄ: የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅትን አሥራ ሁለቱ ምዕራባውያን አገሮች መቼ መሰረቱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፵፩ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: ለ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዮሀንስ ሳህሌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የሚተዳደር በኢትዮጵያ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበዚህ በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. ላይ የቱርክ፣ የመስኮብ፤ የጀርመን፤ የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይና የኤስፓኝ መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት መቆጠራቸው አልቀረም። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ የፖርቱጋል መንግሥት በሌላው እንኳን ባይሆን በመርከብና አገር በመያዝ ከቀሩት ይበልጥ ነበር። የቀሩት የኤውሮፓ መንግሥታት እዚያው ወሰናቸው ላይ ገዥነታቸውን ለማጽደቅ እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ የፖርቱጋል መንግሥት ግን ደኅና ደኅና መርከቦችን አዘጋጅቶ እየላከ ከመንግሥቱና ከኤውሮፓ ርቆ የሚገኘውን የአሜሪካን፤ የእስያን፤ የአፍሪካን አገሮች ያስመረምር ነበር። መርማሪዎቹም እነቫስኮ ደጋማ፤ እነፔሬዝ፤ እነአንድራድ፤ እነካብራል በመርከብ እየሄዱ ለመከላከል ጉልበት የሌለውንና በጠባዩ ሀብት ያለበትን አገር መርምረው ሲመለሱ መንግሥቱ ወታደር በመርከብ እየላከ ብዙ አገር ያዘ። በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ. ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል የተባለው የፖርቱጋል መኮንን በትልቅ መርከብ ሄዶ ይን ጊዜ ለቀረው ዓለም ያልታወቀውን የብራዚልን አገር አስገበረና በፖርቱጋል መንግሥት ስም ቅኝ አገር አደረገው። ከዚያም አገር በተገኘው ወርቅ መንግሥቱ ሀብታም ሆነ። እንደዚሁም የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ ወደ ህንድ አገር ሄዶ አገሩን ያዘ። ከተማውንም በጎአ አድርጎ ህንድንም የፖርቱጋል የቄሣር ግዛት አደረገና አገር ገዥውም የንጉሥ እንደራሴ ይባል ጀመር። ከዚያም በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን የሚባለውን አገር በየጊዜው በጦር ኃይል አስገበራቸው። በዚሁ አኳኋን ወደ ኢትዮጵያም እነኮቪልሐኦ ቀደም ብለው በዓፄ እስክንድር ዘመን መጥተው እንደመረመሩትና የኢትዮጵያ መንግሥት በዚያ ጊዜ በነሱ አጠራር የቄሱ የዮሐንስ መንግሥት አለ ብለው አውርተው እንደነበረ ሌላ የፖርቱጋል የጦር መርከብ በአፍሪካ ድንበር በቀይ ባሕር ላይም እየተመላለሰ አስቀድሞ ከያዙት ከቱርኮችና ከግብጾች እየተዋጋ አንድ ጊዜም እየተሸነፈ አንድ ጊዜም እያሸነፈ ብዙ ጊዜ ተመላለሰ። በዚህ ሁሉ ምክንያት የፖርቱጋል መንግሥት ታላቅነት በሌላው ዓለም እንደ ታወቀ እንደዚሁም ፩ኛ ትልቅ መንግሥት መሆኑ ፪ኛ ክርስቲያን መሆኑ ኢትዮጵያ ባሉት የውጭ አገር ሰዎች አፍ እየተነገረ ዝናው በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ዘንድ መሰማት ቻለ። \n \nጥያቄ: የፖርቱጋል መኮንን የሆነው በትልቅ መርከብ ሄዶ በራዚልን ቅኝ ሀገር እንድትሆን ያደረጋት ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: አብዱ ዲዮፍ ከመቼ እስከ መቼ የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአማርኛ ውክፔዲያ የአማርኛው ውክፔዲያ ጥር 18፣ 1996 ዓ.ም. (27 January 2004 እ.ኤ.አ.) ተጀመረ። አሁን ገጽ ስራዎች በውስጡ ይገኛሉ። ውክፔዲያ ዓለም-ዓቀፍ የዕውቀት ማከማቻ ድረ-ገጽ ነው። ውክፔዲያ የጋራ ነው። ሁሉም ሰው በመዝገበ ዕውቀቱ እንዲሳተፍ ተፈቅዷል። አዳዲስ ተሳታፊዎች፣ የጀማሪዎች ማያያዣን በመጫን በፍጥነት ስለ ድረ-ገጹ መረጃ ማግኘት ይችላሉ። አዲስ ጽሑፍ ለመጻፍ ወይንም ነባር ጽሑፍ ለማስተካከል ደፍሮ መሞከር ጥሩ ልምድ ነው። ከሌሎች ውክፔዲያዎች የተተረጎሙ ጽሑፎች እንዲያቀርቡ ይበረታታሉ። ለዚህ ተግባር እነዚህን መዝገበ ቃላት ማማከር ይችላሉ ። የሚያቀርቡት ጽሑፍ ያልተሟላ ወይንም ያልተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳ መጨነቅ አያስፈልግም። ጅምር ጽሑፍ በተፈለገ ጊዜ ሊሻሻል ይችላልና። \n \nጥያቄ: የአማርኛ ውክፔዲያ መቼ መስራት ጀመረ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጥር 18፣ 1996 ዓ.ም. (27 January 2004 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: የፀሀይ የሚታየው ገጽ ስኂን ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 6,000 ኬ (ኬልቪን) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሚያዝያ ፲፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፳፰ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፳፫ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፴፰ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፴፯ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ። ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ታሽኬንት በትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ክስተት ስትወድም ሰብ ስምንት ሺ መኖሪያ ቤቶች በመጥፋታቸው ከሦስት መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎቿ መኖሪያ ቢስ ሆነዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በሼክ ሞሀመድ ማህሙድ ኤል ሳዋ የተመራ የሳዑዲ አረቢያ\tልዑካን ቡድን ለአጭር ጉብኝት አዲስ አበባ ገባ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ከደርግ በተላለፈ ትእዛዝ መሠረት፣ የፖሊስ አለቆች፤ የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ታሠሩ። ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር። \n \nጥያቄ: የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ታሽኬንት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንክን መች ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ማዕከል መሥራች ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮሮና ቫይረስ ፅኑ ህክምና ማዕከል ውስጥ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዘሚ የኑስ በአሁኑ ሰአት ከ200 በላይ ለሚሆኑ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ወይዘሮ ዘሚ የኑስ የምንና የምን ማዕከላት መስራች ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎግል የተወሰኑ ደንበኞችን የግል ተንቀሳቃሽ ምስል በስህተት ለሌሎች በማጋራቱ ይቅርታ ጠይቋል። ችግሩ ደንበኞች የግል ገፃቸውን ለመለየት የሚስችለውን ምስል ለመጫን በሚያስችለው ክፍል ላይ የተፈጠረ መሆኑ መሆኑን ኩባንያው አስታውቋል። ስህተቱ ለአራት ቀናት ማለትም ካሳለፍነው ጥቅምት 21 እስከ 25 ቀን 2019 ድርስ የቆየ መሆኑ ነው የተገለጸው። በዚህ ወቅትም በችግሩ የተጠቁ ደንበኞች የራሳቸው ያልሆነ አሊያም ተገቢውን ጥራት ያላሟላ ተንቀሳቃሽ ምስል የደረሳቸው መሆኑ ተጠቁሟል። ይሁን እንጂ ኩባንያው ችግሩ በምን ያህል ደንበኞቹ ላይ ተከስቶ እንደነበር ከመግለፅ ተቆጥቧልል። አሁን ላይ ችግሩ መስተካከሉን የገለጹት የኩባንያው ቃል አቀባይ፥ለተፈጠረው ስህተት ደንበኞችን ይቅታ ጠይቀዋል። በቀጣይ መሰል ችግሮች እንዳይከሰቱ ጥልቅ ምርመራዎችን በማካሄድ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅ የሚደረግ መሆኑ ተጠቁሟል። ምንጭ፡-ቢቢሲ   \n \nጥያቄ: የደንበኞችን የግል ተንቀሳቃሽ ምስል በስህተት ለሌሎች ያጋራው ጎግል ይህ ችግር ያጋጠመው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጥቅምት 21 እስከ 25 ቀን 2019 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። ባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሕንድ አምባሳደር ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አኑራንግ ስትራቫስታቫ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዶናልድ ትራምፕ ከኒው ዮርክ ከአምስቱ ቀጠናዎች አንዱ በሆነው በክዊንስ በእ.ኤ.አ. ጁን 14 1946 ተወለደ። ለእናቱ ሜሪ አን እና ለአባቱ ፍሬድ ትራምፕ ከአምስት ልጆች መሃል አራተኛው ልጃቸው ነበር። እናቱ የተወለደችው በስኮትላንድ ሉዊስ ኤንድ ሃሪስ ደሴት ላይ ቶንግ በተባለው ስፍራ ነው። በእ.ኤ.አ. 1930 በ18 ዓመቷ ዩናይትድ ስቴትስን ጎበኘች እናም ከፍሬድ ትራምፕ ጋር ተገናኘች። በእ.ኤ.አ. 1936 ትዳር ይዘው በጃማይካ ኢስቴትስ ክዊንስ መኖር ጀመሩ። በዚህም ስፍራ ፍሬድ ትራምፕ ታላቅ የሪል ኢስቴት ገንቢ ሆኖ ነበር። ዶናልድ ትራምፕ፥ ሮበርት የተባለ አንድ ወንድም፣ ሜሪአን እና ኤሊዛቤት የተባሉ ሁለት እህቶች አሉት። ፍሬድ ጁኒየር የተባለ ወንድሙ ደግሞ ከአልኮል ሱስ ጋር በተያያዘ ምክንያት ሕይወቱ አልፏል ፤ ይህም ከአልኮሆል መጠጥ እና ከትምባሆ እንዲታቀብ እንዳደረገውም ዶናልድ ትራምፕ ይናገራል። የዶናልድ ትራምፕ አባት ከካልሽታት ጀርመን በስደት ከመጡት ከፍሬድሪክ እና ከኤሊዛቤት ትራምፕ በዉድሄቨን ክዊንስ ተወለደ። ዶናልድ ትራምፕ በእ.ኤ.አ. 1976ቱ የኒው ዮርክ ታይምስ የሕይወት ታሪክ መዛግብት ላይ እንዲሁም በእ.ኤ.አ. 1987 በታተመው ዘ አርት ኦፍ ዲል በተሠኘው መጽሐፉ ውስጥ በተሳሳተ መልኩ ፍሬድሪክ የስዊድን ዝርያ እንዳለው ገልጿል። ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ የቤተሰብ ታሪክ ጸሐፊ ነው ብሎ የጠራው የወንድም ልጅ እንዳለው ከሆነ ፍሬድሪክ ትራምፕ ይህንን አቋም ለረጅም ጊዜያት የያዘው \"ብዙ አይሁዳዊያን ጓደኛሞች ስለነበሩት እና ጀርመናዊ መሆን ጥሩ ስላልሆነ ነበር\" ነው ብሏል። ኋላ ግን ዶናልድ ትራምፕ በቅድመ አያቶቹ ጀርመን መሆኑን አምኖ በእ.ኤ.አ. 1999 በኒው ዮርክ ከተማ በተካሄደው በጀርመን - አሜሪካን ስቱበን ሰልፍ ላይ በግራንድ ማርሻልነት አገልግሏል። \n \nጥያቄ: የትራምፕ አባትና እናት እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እናቱ ሜሪ አን እና ለአባቱ ፍሬድ ትራምፕ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: ቻይና በምን እና በምን ግዛቶቿ መካከል ያለውን የባቡር መስመር ለአገልግሎት ክፍት ልታደርግ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: ቱርክመንኛ በላቲን ፊደላት እንዲጻፉ ያወጀው የቱርክመኒስታን መሪ ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ መቼ ተሰወሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጥቅምት አሥራ አራት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: የራስ መኮንን አርባ በአዲስ አበባ እንዲደረግ የወሰነው ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዐፄ ምኒልክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: 1688-1678 ዓክልበ. በአሦር ላይ የተሾመው የንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ ልጅ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ እሽመ-ዳጋን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: የሳተርን ሮኬት አፖሎ 11 ሚሲዮንን ይዞ ጉዞ የጀመረበት ጠፈር ማእከል ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ ምን ዓይነት ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በቴሌቪዥን ለመላክ ቻለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በኢትዮጵያ የነዳጅ አቅርቦት ምን ያህል ድርሻ አለው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 24 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: በሳውዲ ቅዱስ ስፍራ የሚባለው የትኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መካ እና መዲና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከደቡብ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: የእቴጌ ዘውዲቱ አባት ማናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዳግማዊ ሚኒሊክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአንድ ወጣት ተማሪ ከወዳደቁ ቁሳቁሶች በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ መስራቱ ተገለጸ፡፡ ጌታባለው መኩሪያው የተባለው ወጣት በባህርዳር ዩኒቨርስቲ 3ኛ ዓመት የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሲሆን ወጣቱ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች እንዲሁም አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የብስክሌት አካላትን ተጠቅሞ ነው የብስክሌት ጀልባ (Pedal-Boat) መስራት የቻለው፡፡ ጌታባለው መኩሪያው ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የሰራውን የብስክሌት ጀልባ በውሃ ላይ በመንዳት ሙከራ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: በዉሃ ላይ የሚሄድ ብስክሌት ፈጠራ ባለቤት ጌታባለው መኩሪያ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስንተኛ ዓመት ተማሪ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 3ኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: ኮንግ-ፋጸ (ኮንፉክዩስ) ማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ቻይናዊ ፋላስፋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኢትዮጵያን በመወከል ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት መቅረባቸው ነው የተነገረው። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ለረጅም ዓመታት በመምህርነት አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም በሚንስቲር ማዕረግ የማን አማካሪ ሆነው ሰርተዋል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኩባንያው በ124 ሚሊዮን ብር የሞተር ዘይቶችና ቅባቶች ማምረቻ ለማቋቋም፣ የቡታ ጋዝ ማከፋፈል ሥራ ለመጀመር፣ የሬንጅ አቅርቦት ሥራውን ለማሳደግና የኢንዱስትሪ ኬሚካሎች ለማቅረብ ማቀዱንም ገልጸዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በአውሮፕላን ነዳጅ አቅርቦት ላይ በስፋት እየሠራ እንደሆነ አቶ ዘካሪያስ ተናግረዋል፡፡ በአውሮፕላን ነዳጅ ገበያ የ42 በመቶ የገበያ ድርሻ እንዳለው ጠቁመው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ለ30 ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ እንደሚያቀርብ ገልጸዋል፡፡ ኩባንያው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚገኘውን የአውሮፕላን ነዳጅ ዴፖ ማስፋፋቱን፣ አምስት ዘመናዊ የአውሮፕላን ነዳጅ መሙያ ማሽኖች ገዝቶ ጥቅም ላይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ለቀለምና ፕላስቲክ ፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች ለማቅረብ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ‹‹ለጊዜው ኬሚካሎቹን ከውጭ በማስገባት የምናከፋፍል ሲሆን፣ በሒደት አገር ውስጥ የማምረት ዕቅድ አለን፤›› ብለዋል አቶ ዘካሪያስ፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በኢትዮጵያ የአውሮፕላን ነዳጅ ሽያጭ ምን ያህል ድርሻ አለው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የ42 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ያገኙት ነጂብ ማኅፉዝ የምን ሀገር ዜጋ ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ግብፅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ ቦታ የገዙት ከማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከናፖሌዎን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በ29ኛው የእግር ኳስ የአፍሪካ ዋንጫ ስትጫወት አዳነ ግርማ ማን ላይ ግብ አስቆጠረ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዛምቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ስንት ብሔረሰቦች ይገኛሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ ፹ (80) በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) የተሸነፈው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1441 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: በልጅ ኢያሱና በራስ ተፈሪ መካከል ተደርጎ የነበረው ስምምነት የተሻረው በምን ምክንያት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ከ100 ዓመታት በፊት በአፍሪካና በአውሮፓ ለከብቶች እልቂት ምክንያት የሆነው በሽታ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የደስታ በሽታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ግብይት የሚያስፈጽመው ግዥና ሻጭን መድረክ ላይ በማገናኘት በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው፡፡ ይህ የተለመደው አሠራር የበለጠ ውጤታማ የሚሆነው ግን በድረ ገጽ ግብይት ሲደረግ በመሆኑ ይህንን የድረ ገጽ ግብይት ለማስጀመር ከሦስት ዓመት በፊት ሥራው የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ችሏል፡፡ በተለመደው የመድረክ የግብይት አሠራር በቀን የሚፈጸመው የግብይት መጠን ከ200 እስከ 300 የሚደርስ ነው፡፡ ይህም የግብይት መጠኑ ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የድረ ገጽ ግብይት መጀመሩ ግን ይህንን በመለወጥ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል፡፡ ይህም አሠራሩን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው ተቋም ጭምር ዕውቅና አግኝቶበታል፡፡ እንደ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያሉ ተቋማትም ይህንን አገልግሎት ፈትሸው ማረጋገጫ ተሰጥቶት እየተሠራበት ስለመሆኑም የምርት ገበያው የሥራ ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህንን ዘመናዊ አገልግሎት ሥራ ለማስጀመር ከመጀመሪያው ጀምሮ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) የተባለው ተቋም ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮጀክት 2.2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ይህ ግብይት በቡና የተጀመረ ሲሆን፣ ሁሉም በዚህ የግብይት ሥርዓት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ የግብይት ሥርዓቱ አዲስ በመሆኑ በዚህ ለመጠቀም ተገበያዮች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም 380 ተገበያዮች በድረ ገጽ ለመገበያየት ሥልጠና ወስደው ብቁ መሆናቸው ተረጋግጦ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የድረ ገጽ የግብይት ሥርዓት ለመጠቀም ምን ያህል ገዥና ሻጮች ሰለጠኑ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 380 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት ሲሆን ወገናቸው ከእንስሳት መካከል የትኛው ወገን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የድመት ወገን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየደቡብ ክልል ምክር ቤት ዛሬ ማካሄድ በጀመረው 5ኛ ዙር 4ኛ አመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ የ2012 በጀት አመት 40 ቢሊዮን 56 ሚሊዮን 938 ሺህ ብር በጀት አጸደቀ፡፡ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሄለን ደበበ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የምክር ቤቱ ጉባኤው ለመዘግየቱ ይቅርታ ጠይቀዋል። በዋናነት በ3 አጀንዳዎች ላይ እየመከረ የሚገኘው ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችንም ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ \n \nጥያቄ: የደቡብ ክልል የ2012 በጀት አመት ስንት ብር አፀደቀ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 40 ቢሊዮን 56 ሚሊዮን 938 ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአረማይክ አረማይክ ወይም አራማይስጥ፣ የሶርያ ቋንቋ ከሴማዊ ቋንቋዎች አንዱ ሲሆን በመካከለኛ ምሥራቅ ከጥንት ጀምሮ ታውቋል። መጀመርያ የአረማይክ ጽሑፎች ከ1000 ዓክልበ. ግድም በፊንቄ አልፋቤት ነበሩ፤ ይህም የአራም ሕዝብ የተናገሩት ጥንታዊ አራማይስጥ ነበር። በአንድ አስተሳሰብ ቋንቋቸው ከ1100 ዓክልበ. አስቀድሞ ሑርኛ ይሆን ነበር፤ የአሦርም መንግሥት ከገዙአቸው በኋላ እንደ አካድኛ ሴማዊ ሆነ። ከ800 ዓክልበ. አካባቢ በኋላ የራሱ አረማይክ አልፋቤት ከፊንቄ አልፋቤት ተለማ። በ740 ዓክልበ. የአሦር ንጉሥ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር አረማይስጥ ከአሦርኛ (አካድኛ) ጋር ይፋዊና መደበኛ ቋንቋ አደረገው። ከዚያ ጀምሮ የአረማይስጥ ጥቅም እየተስፋፋ የአካድኛ ጥቅም በየጊዜ ይቀነስ ነበር። ከአሦር ውድቀት (617 ዓክልበ.) በኋላ በባቢሎኒያ መንግሥት፣ ከባቢሎኒያም ውድቀት (547 ዓክልበ.) በኋላ በፋርስ አሓይመኒድ መንግሥት ውስጥ፣ አረማይክ መደበኛና ይፋዊ ቋንቋ ተደረገ፣ ስለዚህ ጥቅሙ በሰፊ ከግብጽ እስከ ባክትሪያ ድረስ ይዘረጋ ነበር። በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ የተገኘው አራማይክ በተለይ በትንቢተ ዳንኤል ከዚሁ ዘመን ነው። \n \nጥያቄ: አረማይክ ቋንቋ ይፋዊ ቋንቋ መቼ ተደረገ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ740 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: ኒጄርና ቤንዌ የት ሀገር የሚገኙ ወንዞች ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በናይጄሪያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: በሀገራችን ታሪክ የመጀመሪያው ሕገ መንግሥት እንዲዘጋጅ የተደረገው በማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዓጼ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ አነሳሽነት በ12ኛው ክፍለ ዘመን በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ የተሰራ ቤተክርስቲያንና በዚያው ዋሻ ውስጥ ከቤተርክስቲያኑ ፊትለፊት ያለ ቤተ መንግስት ህንጻ በአንድነት የሚጠሩበት ስም ነው። ዋሻው ከላሊበላ የ6 ሰዓት የእግር ጉዞ ርቀት ላይ ይሚገኝ ሲሆን 45ሜትር ርዝመት በ6 ሜትር ቁመትና 50ሜትር ጉድጉደት አለው። በዋሻው ውስጥና ውጭ ለጸበል የሚያገለግሉ ምንጮች ይፈልቁበታል። ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ ከሮሃ ሆኖ አገሩን ያስተዳድር እንጂ ይሄው ቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ሲታነጽ መኖሪያውን ወድዚህ ዋሻ እንዳዛወረ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ የህይወት ታሪኩ ይገልጻል። የቤተክርስቲያኑ ህንጻ 3 መግቢያዎች ሲኖሩት በሰሜን(ለወንዶች)፣ ደቡብ(ለሴቶች) እና ምሥራቅ (ለካህናት) ይገኛሉ። በግድግዳው ላይ የሚገኙ፣ ነገር ግን በአቧራ የተሸፉኑት ምስሎች ከዚሁ ዘመን የሚመነጩ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የግድግዳ ምስላት ቀደምት ናቸው። ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ይህን ቤተክርቲያን በ16ኛው ክፍለዘመን መግቢያ ላይ የጎበኘው ሲሆን፣ እንደርሱ ዘገባ በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኑ 200 ደብተራዎች የነበሩት ሲሆን አጠቃላይ ቤቱ በሊቀ ካህናት ይመራ እንደነበር ሲጠቅስ፤ በወቅቱ መነኮሳት እንደማይኖሩበትም ዘግቧል። ከይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ጀርባ 3 መቃብሮች ሲኖሩ፣ የራሳቸው የዓፄ ይምርሃነ፣ የሴት ልጃቸው እና ከእስክንድርያ ንጉሱን ሊጠይቁ የመጡ ፓትሪያርክ እንደሆኑ ይጠቀሳል። ወደዋሻው ውስጥ በጣም ርቆ ደግሞ የብዙ ምዕመናን አጽም የሚታይበት ሰፊና ጨለማ ክፍል አለ። \n \nጥያቄ: ዋሻ ውስጥ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በማን እና መቼ ተሰራ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ12ኛው ክፍለ ዘመን በአቡነ ዮሴፍ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየቻይና ስነ ፈለክ ተመራማሪዎች የመጀመሪዋን ከፀሀይ ስርዓት ውጪ የሆች ኤክሶፕላኔት ማግኘታቸው ተገለፀ። በቻይና የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች የተገኘችው ይህች ፕላኔት “ወንግሹ” እና “ዢሂ” የሚል ስያሜ ተሰቷታል። ይህም ማለት የጨረቃ አምላክ ወይም የጸሃይ አምላክ የሚል ትርጉም አለው። ሁለቱ ስሞች የሚያሳዩት የኮኮብ እና ፕላኔትን ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ዩንቨርስን የማሳስ ሂደት የሚወክል ወይም ምሳሌ የሚሆን ነው ተብሏል። የፕላኔትዋ መጠን ከፀሐይ ሁለት እጥፍ የሚበልጥ ሲሆን፥ ከጁፒተርም በ2 ነጥብ 7 እጥፍ ትበልጣለች፤ በዚህም ከጸሃይ ስርዓት ውስጥ ትልቋ ነው የተባለችው በብሔራዊ የሥነ ፈለክ ምርምር ተቋም። የቻይና የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች በአውሮፓውያኑ በ2008 ከቻይና 10 ምርጥ የሥነ ፈለክ እድገቶች መካከል አንዱ ሆነው የተመረጡት ትልቁን ኤክስፕላኔት HD173416b’ን አገኝታለች። ምንጭ፡-ሲጂቲኤን በፌቨን ቢሻው \n \nጥያቄ: የቻይና ስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ያገኟት ኤክሶፕላኔት መጠን ከጁፒተር ምን ያህል ይበልጣል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ2 ነጥብ 7 እጥፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መቼ ተቀበረ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nለሴት ልጆች ትምህርትን አጥብቃ በመስራቷ እ.ኤ.አ. በ 2003 በደቡብ አፍሪካ የተቀበለችውን የአማኒታሪ ሽልማትን (አፍሪካዊ አጋርነት ለወሲባዊ እና ስነተዋልዶ ጤና እና የሴቶች መብቶች ) ጨምሮ ለፀረ-ኤድስ እንቅስቃሴ ባገለገለችበት ወቅት በርካታ ብሔራዊ እና ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አግኝታለች ። ፡፡ ወ / ሮ የትነበርሽ ከአካዳሚክ ህይወቷ ባሻገር በበጎፈቃደኝነት ከ 20 በላይ ድርጅቶች ውስጥ ያገለገለች ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን የሴቶች ክንፍ ማህበር ለ 4 ዓመታት (እ.ኤ.አ. ከ 2003 እስከ 2007) መርታለች ፡፡ ከዚያም በመቀጠል የአካል ጉዳተኞች ኢኮኖሚያዊ መብትን ጨምሮ በተለያዩ የልማት መርሃ ግብሮች ውስጥ እንዲካተቱ ለማበረታታት የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና የልማት ማዕከል (ኢ.ሲ.ዲ.ዲ.) የተባለ አገር በቀል ድርጅት ለማቋቋም ወሰነች ፡፡ከ2016 ጀምሮ ደግሞ ቀደም ሲል በዓለምአቀፍ አምባሳደሮች ቦርድ አባልነት ወክላው ከነበረው የአካል ጉዳተኞች እና ልማት ብርሃን ለኣለም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ላይ ትሰራለች ፡ የትነበርሽ ንጉሴ የአካል ጉዳተኞችን መብትና ማካተት በማስተዋወቋ እና ሙሉ አቅማቸውን እንዲገነዘቡ የሚያስችላቸው አነቃቂ ሥራ በመስራት በማህበረሰቡ ውስጥ የአስተሳሰብ ለውጥ በመፍጠሯ እ.ኤ.አ. በመስከረም ወር 2017 ላይ የተባበሩት መንግስታት ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ ፣ “አማራጭ የኖቤል ሽልማት” ፡ እና የአሜሪካ የአካባቢ ጠበቃ ጋር በመጋራት ተሸላሚ ሆናለች። ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን በማሸነፏ እና በሄለን ኬለር ሽልማት መንፈስ የተበረታታችው የትነበርሽ ንጉሴ በህይወታቸው እና በስራ መስካቸው ታላቅ ውጤት ያስመዘገቡ የአካል ጉዳተኛ ሴቶችን ለማክበር ከብርሃን ለኣለም ጋር በመሆን ‹የእርሷ ችሎታዎች ሽልማትን› ኣስጀምራለች፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ በ2017 ምን ተሸለመች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መቼ ታሰሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nባቢሌ የዝሆን መጠለያ ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከአዲስ አበባ ወደ ጅጅጋ መስመር፣ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ይህ መጠለያ በቆዳ ስፋት ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር የሚመዘን ሲሆን፣ ከጠቅላላ ስፋቱም ውስጥ ፸፯ ከመቶ ያህሉ በአሁኑ አጠራር ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ይገኛል። የአካባቢው የኦሮሚያ ብሔር ተወላጆች ‹‹ወረ-ሃርባ›› (ባለዝሆኖቹ) በማለት የሚጠሩትና በፌዴራል የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሥር የሚተዳደረው የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት፣ በ፲፱፻፷፪ ነው የተመሠረተው። የምሥረታውም ዋነኛ ዓላማ፥ በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ ሲሆን ባሁን ጊዜ መጠለያው በተጨማሪም ከ፴ በላይ ጡት አጥቢ የዱር እንስሳት፣ ከ፪መቶ ፶ በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች፣ ፫መቶ ያህል የዕፅዋት ዝርያዎች የሚገኙበት ነው። ከሌሎች አዕዋፍ እና የዱር አራዊት ዝርያዎች ደግሞ ከገጸ ምድር የመጥፋት አደጋ ላይ ያለው የሳልቫዶሪ ዘረ-በል ወፍ እና ባለጥቁር ጎፈር አንበሳ በዚህ መጠለያ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከአዲስ አበባ በስንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የብሪታንያው ድርጅት ሰሜናዊ ሮዴዢያ ብሎ ይጠራው የነበረው የዛምቤዚያን አካባቢ አሁን ምን ተብሎ ይታወቃል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዛምቢያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዎችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀው አፓሎ 11 መንኮራኩር የሰራው የጠፈር ምርምር ጣቢያ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ናሳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ የሚለው ቃል ምንጩ ከምን ቋንቋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከዓረብኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ በሰሜን-ምሥራቅ የምትዋሰነው ከየትኛው ባህር ጋር ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከቀይ ባህር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ወደዚህ ምድር ከመምጣታቸው ከስንት ጊዜ በፊት ነው አባታቸው የሞቱት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሶስት ወር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ የትዳር አጋራቸው ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኢንጂነር ሰይፉ ለማ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሚያዝያ ፲፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፳፰ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፳፫ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፴፰ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፴፯ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ። ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ታሽኬንት በትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ክስተት ስትወድም ሰብ ስምንት ሺ መኖሪያ ቤቶች በመጥፋታቸው ከሦስት መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎቿ መኖሪያ ቢስ ሆነዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በሼክ ሞሀመድ ማህሙድ ኤል ሳዋ የተመራ የሳዑዲ አረቢያ\tልዑካን ቡድን ለአጭር ጉብኝት አዲስ አበባ ገባ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ከደርግ በተላለፈ ትእዛዝ መሠረት፣ የፖሊስ አለቆች፤ የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ታሠሩ። ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር። \n \nጥያቄ: ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው ሲዋሃዱ የተፈጠረቸው ሀገር መጠሪያ ስሟን ማን ብለው ሰየሙ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ታንዛኒያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየጥምቀት በዓል በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው ያሳልፋሉ።በከተሞች ግን ሰው ሰራሽ ግድብ ይሰራል። ጥር ፲፩ ቀን የጥምቀት ዕለት፤ በገጠር፣ ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት መሪነት ሁሉም ወደከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል። ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬ፣ ወንዱ በሆታ፤ ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው ይመለሳሉ። በየዓመቱ በመላ ኢትዮጵያ የሚከበረው የጥምቀት በዓል፣ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው፣ በየጥምቀተ ባሕሩ የሚከበሩ በመኾናቸው፣ ሀገሬውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መስህብ በመፍጠሩ፣ ቱሪስቶችን መሳቡ አልቀረም። ጥቁርና ነጭ፣ ቀይና ብጫ ያለም ዘር፣ ከአዲስ አበባ እስከ ላሊበላ፣ ከአክሱም እስከ ጎንደር በሁሉም ሥፍራዎች በዚሁ ዓይነት ደምቆ ይከበራል። የምእመናኑም ሆነ የካህናትና ዲያቆናት አለባበስ ፍፁም በሚማርክ ባህላዊ አልባሳት የተዋበ በመሆኑ ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ ለሚመጡ ጎብኚዎች ሁል ጊዜ አዲስ ነው። ሊቃውንቱ እንደሚናገሩት፣ ዘመነ አስተርእዮ የሚባለው፣ ከጥር ፲፩ ቀን ጀምሮ እስከ ጾመ ነነዌ ያለው ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ አምላክ ሰው ሆኖ በሥጋ መገለጡ፣ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር መታወቁ፣ በቃና ዘገሊላ በተደረገው ሠርግ ላይ የመጀመሪያው ተዐምር በመፈጸሙ፣ አምላካዊ ኃይሉ መገለጡ፣ እየታሰበ ምስጋና ይቀርባል። ይህ ሁነት ኢትዮጵያ ብሂልን ከባህል ጋር አዛምዳ ከሌላው የክርስቲያን ዓለም በተለየ አከባበር በዓሉን ማክበሯ፣ አያሌ ቱሪስቶችን ለመሳብ አስችሏታል። \n \nጥያቄ: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በማን ተጠመቀ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር በየት ዩንቨርስቲ ተማረ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ የተጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት አደጋ የሟቹች ቁጥር ስንት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፬ ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: የፀሓይ ብርሃን መሬት ለመድረስ ምን ያህል ጊዜ ይወስድበታል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 8.5 ደቂቃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመንግሥት መንግሥት በአንድ አገር ወይም ተቋም ውስጥ ሕጎችን ለማውጣትና ለማስፈጸም ስልጣን ያለው አካል ነው። መንግሥት አንድ ሃገር ወይም ማህበረሰብ የሚስተዳደርበት ሥርዓትና ለዚህም ሲባል የተቋቋመ ኃይል ያለው አካል ነው ፡፡ ይህም ህግ አውጪውን፣ ህግ አስፈጻሚውን እና ህግ ተርጓሚውን ማለትም የዳኝነት አካላትን የያዘ ነው፡፡ ድርጅቶች ሁሉ እንደ መንግሥት ያለ አስተዳደር ሲኖራቸው ፣ መንግሥት የሚለው ቃል በተለይ በግምት 200 የሚሆኑ አገራዊ መንግስታትን በበለጠ ያመለክታል፡፡ የመንግስት አመሠራረት መቼ እንደተጀመረ በእርግጠኝነት መናገር ይቸግራል ፡፡ ሆኖም ታሪክ የጥንታዊ መንግስታትን ምስረታ ይመዘግቧል ፡፡ ከ 5,000 ዓመታት በፊት የመጀመሪያዎቹ ትናንሽ የከተማ መንግስታት ብቅ ብቅ እንዳሉ ይገመታል ፡፡ ከሶስተኛው እስከ ሁለተኛው ዓመተ ዓለም ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ወደ ትልልቅ አካባቢዎች በማደግ እንደ ሱመር ፣ የጥንቷ ግብፅ ፣ የኢንዲስ ሸለቆ ስልጣኔ እና ቢጫ ወንዝ ስልጣኔ የሚባሉትን ፈጥረዋል ። ግብርና ልማት እና የውሃ ቁጥጥር ለመንግስት ማደግና መጠናከር እንደ ዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ የአንዳንድ ነገድ አለቆች የእነሱን ጎሳ ለማስተዳደር በተለያዩ የአምልኮ ሥርዓቶች ወይም ባላቸው ጥንካሬ ተመርጠው አስተዳድረዋል፣ አንዳንዴም ከጎሣው ሽማግሌዎች ጋር በመሆን መንግሥት ሆነዋአል፡፡ በግብርና የበለጠ ውጤታማ እየሆኑ መሄድ በአንድ አካባቢ የሚኖረው ህዝብ ብዛቱ እንዲጨምር አስችሏል። ይህም በተለያዩ ቡድኖች መካከል የሚደረጉ ግንኙነቶች እየጨመሩ እንዲሄዱና የሚፈጠረውንም መሥተጋብር የሚቆጣጠር አካል (መንግሥት) እንዲኖር አድርጓል። እ.ኤ.አ. ከ 17 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ የሪፖብሊካዊ መንግስት ተስፋፍቷል፡፡ የእንግሊዝ፣ የአሜሪካና የፈረንሳይ አብዮቶች ለተወካይ የመንግስት ምሥረታ እድገት አስተዋጽኦ አበርክቷል ፡፡ የኮሚኒስት መንግስት የተመሠረተበት የመጀመሪያው ሠፊ ሀገር ሶቪዬት ህብረት ነው። የበርሊን ግንብ ከተደረመሰ ጊዜ ጀምሮ የሊበራል ዴሞክራሲ የተስፋፋ የመንግሥት መስተዳድር ሆኗል ። \n \nጥያቄ: በዓለም ላይ የሪፐብሊካዊ መንግሥት መስፋፋት የጀመረው ከስንተኛው ክፍለ ዘመን አንስቶ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እ.ኤ.አ. ከ 17 ኛው ክፍለ ዘመን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) ኡበርና ሃዩንዳይ በራሪ ታክሲዎችን በጋራ ሊሰሩ መሆኑን አስታወቁ። ሁሉቱ ኩባንያዎች አዲስ የሚሰሩትን በራሪ ተሽከርካሪ በላስ ቬጋሱ የንግድ ትርኢት ይዘው እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል። አራት ተሳፋሪዎችን የሚይዘው በራሪ ታክሲ በሰዓት እስከ 320 ኪሎ ሜትር መጓዝ እንደሚችል ተገልጿል። ሁለቱ ኩባንያዎች በዚህ ሳምንት በላስ ቬጋስ በሚደረገው የንግድ ትርኢት ላይ የታክሲ አገልግሎት ይሰጣል ያሉትን በራሪ ተሽከርካሪ ሞዴል ይፋ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። ኡበር በፈረንጆቹ 2023 ለደንበኞቹ የበራሪ ታክሲ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ነው የገለጸው። \n \nጥያቄ: በራሪ ታክሲዎችን በጋራ ለመስራት የወሰኑት ኩባንያዎች እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኡበርና ሃዩንዳይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: ከተማዋ በምን ያህል የባህር ወለል ከፍታ ላይ ትገኛለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል። ባለፈው አመት የመጠቀችው “ETRSS-1” የሚል ስያሜ የተሰጣት ምድርን እየቃኘች ፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው ሳተላይት በሀገራችን የዕድገት ጉዞ ላይ ቁልፍ ሚና እንደሚኖራት መነገሩ አይዘነጋም። መረጃ መላክ የጀመረችው ይች ሳተላይት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ አሁን ደግሞ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን ነው ኢንስቲትዩቱ ያስታወቀው። \n \nጥያቄ: ETRSS-1 የተሰኘችውን ሳተላይት ወደ ህዋ ያመጠቀችው ሀገር ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ከሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምን ያህሉ ሲሚንቶ ማምረት ጀምረዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 12ቱ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የፐርል በክ የትውልድ ስፍራ ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ያገኙት ናዲን ጎርዲመር የምን ሀገር ዜጋ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደቡብ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋሊልዮ ለእስር ያበቃው ምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየጥምቀት በዓል በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው ያሳልፋሉ።በከተሞች ግን ሰው ሰራሽ ግድብ ይሰራል። ጥር ፲፩ ቀን የጥምቀት ዕለት፤ በገጠር፣ ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት መሪነት ሁሉም ወደከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል። ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬ፣ ወንዱ በሆታ፤ ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው ይመለሳሉ። በየዓመቱ በመላ ኢትዮጵያ የሚከበረው የጥምቀት በዓል፣ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው፣ በየጥምቀተ ባሕሩ የሚከበሩ በመኾናቸው፣ ሀገሬውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መስህብ በመፍጠሩ፣ ቱሪስቶችን መሳቡ አልቀረም። ጥቁርና ነጭ፣ ቀይና ብጫ ያለም ዘር፣ ከአዲስ አበባ እስከ ላሊበላ፣ ከአክሱም እስከ ጎንደር በሁሉም ሥፍራዎች በዚሁ ዓይነት ደምቆ ይከበራል። የምእመናኑም ሆነ የካህናትና ዲያቆናት አለባበስ ፍፁም በሚማርክ ባህላዊ አልባሳት የተዋበ በመሆኑ ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ ለሚመጡ ጎብኚዎች ሁል ጊዜ አዲስ ነው። ሊቃውንቱ እንደሚናገሩት፣ ዘመነ አስተርእዮ የሚባለው፣ ከጥር ፲፩ ቀን ጀምሮ እስከ ጾመ ነነዌ ያለው ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ አምላክ ሰው ሆኖ በሥጋ መገለጡ፣ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር መታወቁ፣ በቃና ዘገሊላ በተደረገው ሠርግ ላይ የመጀመሪያው ተዐምር በመፈጸሙ፣ አምላካዊ ኃይሉ መገለጡ፣ እየታሰበ ምስጋና ይቀርባል። ይህ ሁነት ኢትዮጵያ ብሂልን ከባህል ጋር አዛምዳ ከሌላው የክርስቲያን ዓለም በተለየ አከባበር በዓሉን ማክበሯ፣ አያሌ ቱሪስቶችን ለመሳብ አስችሏታል። \n \nጥያቄ: የጥምቀት በዓል መች ይከበራል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጥር ፲፩ ቀን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ ቤተመንግሥቱ የሚገኘው የት ከተማ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በፕሪቶሪያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ ያረፈው በምን ምክንያት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በልብ ምታት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: አፋር በየት ሀገር የሚገኝ ክልል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየእብድ ውሻ በሽታ የእብድ ውሻ በሽታ የየቫይረስ በሽታ ሆኖ ከፍተኛ የየአንጎል መጉረብረብን በሰዎች እና በሌሎች ደመ-ሞቃት እንስሳት ላይ የሚያስከትል ነው። ቅድሚያ ምልክቶቹ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠልን ያካትታል። እነዚህ ምልክቶች ከሚከተሉት አንድ ወይም የበለጡ ምልክቶች አስከትለው ይመጣሉ- ሃይል የታከለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች፣ ከቁጥጥር ወጭ የሆ መሸበር፣ የውሀ ፍራቻ, የሰውነት ክፍለን ለማንቀሳቀስ አለመቻል፣ ግራ መጋባት፣ እና ህሊናን መሳት። ምልክቶቹ ከታዩ በኋላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ በአብላጫው ሁልጊዜ ሞትን ያስከትላል። በበሽታው በመያዘዎ እና ምልክቶቹ መታየት የሚጀምሩበት የጊዜ ገደብ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የጊዜ ገደብ ከሳምንት ባነሰ እና ከአመት በበለጠ ጊዜ ሊለያይ ይችላል። የጊዜ ገደቡ የሚወስነው የበሽታ አምጭው ረቂቅ ህዋስ ወደ የማዕከላዊ የነርብ ስርዓትለመድረስ በሚፈጅበት እርቀት ነው። የእብድ ውሻ በሽታ በአለም ዙሪያ በአመት ከ26,000 እሰከ 55,000 ሞቶች ምክንያት ነው። ከ95% በላይ እነዚህ ሞቶች የተከሰቱት በኢሲያ እና አፍሪቃነው። የእብድ ውሻ በሽታ ከ150 ሀገራት በላይ እና ከአንታርቲካ በቀር በሁሉም አሀጉራት ይገኛል። ከ3 ቢሊዮን ሰዎች በላይ የእብድ ወሻ በሽታ በሚከሰትበት የአለማችን ከፍሎች ውስጥ ይኖራሉ። እጅግ በአብዛኛው አውሮፓ እና አውስትራሊያ፣ የእብድ ወሻ በሽታ የሚገኘው በሌሊት ወፎች ላይ ነው። \n \nጥያቄ: በአብዛኛው በአውሮፓ በአውስትራሊያ የእብድ ውሻ በሽታ የሚገኘው በምን ላይ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሌሊት ወፎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና በፊት የማን ቅኝ ግዛት ነበረች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የብሪታንያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው ያስተማሩት የት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጀስትን ቢበር ጀስትን ድሩ ቢበር (ተወለደ በ፲፻፱፻፹፮ በመጋቢት)፣ ካናዳዊ ዘፋኝ። ጀስትን ቢበር ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለመለው በአሜሪካዊው የቅጂ ድርጅት ባለቤት እስኩተር ብሮን ሲሆን የፈረመው ደግሞ ከአርቢኤምጂ የቅጂ ድርጅት በ፪፲፻ አመተ ምህረት ነው። በቀጣዩ አመት ማለትም በ፪፲፻፩ የመጀመሪያ ኢፒ(EP)ውን ለቆ እውቅናን እየተጎናፀፈ ብዙም ሳይቆይ እራሱን መገንባት እንደ ምርጥ ታዳጊ። የጀስትን ቢበር የመጀመሪያ አልበም (ማይ ወርልድ 2.0) በሁለት ሺ ሁለት ተለቀቀ፤ አልበሙም ቁጥር አንድ ሆኖ ላለፉት አርባ ሰባት አመታት (ማለትም ከሁለት ሺ ሁለት አመተ ምህረት ወዲያ ባሉ ጊዜያት) በማንም ታዳጊ ወጣት ሊያዝ ያልተቻለውን ደረጃ ይዞ አሳየ በዪናይትድ እስቴትስ። አልበሙም በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኘውን \"ቤይቢ\" የተሰኘውን ነጠላ ዘፈን ይይዛል፣ ይህም ዘፈን የምንጊዜም ከፍተኛ የምስክር \"ወረቀቶች\" ያገኘ ሊሆን ችሏል በተመሳሳይ ሀገር። የጀስትን ቢበር ቀጣይ አልበም (አንደር ዘ ሚስትልተው) በሁለት ሺ ሶስት ፡ የመጀመሪያው የገና አልበም ነበር በወንድ አንደኛ ለመሆን ከቢልቦርድ መቶ አልበሞች። በቀጣይ አመት (ሁለት ሺ አራት) ሶስተኛ አልበሙን ተከትሎ ጀስትን ቢበር ከህዝብ ጋር ያለው ግንኙነት በሻካራ ሁኔታ ተቀየረ የተለያዩ ክርክሮች በመነሳታቸው እና በህጋዊ ጉዳዮቹ ምክኛት (በሁለት ሺ አምስት እና ስድስት አመት ውስጥ) ፡ እንዲያውም ሮልንግ እስቶን የተባለ ታዋቂ የመረጃ ድርጅርት ጀስትን ቢበርን \"መጥፎ ልጅ\" ብሎ ሰየመው በመጋቢት ሁለት ሺ ስድስት ጉዳዩ። ይሁን እንጂ ከሁለት ሺ ስምንት ጀምሮ ጀስትን ቢበር ተቀዳሚነቱን ለዳግም ህዝባዊ ግንኙነቱ ሲያውል ነበር ፡ ሲያውል ነበር ለአይምሮው ጤንነት። የካቲት ሁለት ሺ ስምንት ጂኪው የተባለ ታዋቂ የመረጃ ተቋም ስለ ጀስትን ቢበር ራስ ማደስ ተነሳሽነት አስመልክቶ ፅሑፍ ይዞ ሊወጣም ችሏል። \n \nጥያቄ: ጀስቲን ቢበር ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለመለው በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአሜሪካዊው የቅጂ ድርጅት ባለቤት እስኩተር ብሮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት የሆነ እንስሳ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ቀጭኔ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የሮዴዢያን ግዛት ከብሪታንያ ነጻነቷን ያገኘችው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1958 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአንኮበር በ፲፯፻፳ ዓ/ም በሸዋው ነጋሲ በመርድ አዝማች አብዬ የተመሠረተችና በአልጋ ወሪሹ መርድ አዝማች አምኀ ኢየሱስ የተስፋፋች የሸዋ ከተማ ስትሆን ከደብረ ብርሃን ምስራቃዊ አቅጣጫ ፵፫ ኪሎ ሜትር ርቀት የስምጥ ሸለቆው አፋፍ ላይ ትገኛለች። አንኮበር ከዓፄ ይኵኖ አምላክ (፲፪፻፸-፲፪፻፹፭ ዓ/ም) ዘመን ጀምሮ ለኢትዮጰያ ነገሥታት በማረፊያነት አገልግላለች። ዓፄ አምደ ጽዮን ፲፫፻፲፬-፲፫፻፵፬ ዓ/ም የድንኳን ከተማቸውን እንደተከሉባት ይነገራል። አስቲት ኪዳነ ምሕረት የርሳቸው ትክል ናት። ጦረኛዉ ዓፄ አምደ ጽዮን በ፲፫፻፴፭ ዓ/ም አዳልን ለማስገበር የዐማራን፣ የዳሞትን፣ የጐዣምን ሠራዊት ይዘው አንኮበር ሠፈሩ።ለ፬ ወራት ያህል እስከ ዘይላና በርበራ ድረስ በመዝለቅ ድል አድርገው አስገብረውታል። ዓፄ ልብነ ድንግል (፲፭፻፰-፲፭፻፵ ዓ/ም) ደግሞ በተሻለ ሁኔታ በቦለድ የባለወልድን ቤተ ክርስቲያን ለማነጽ ጀምረው እንደነበር የሚጠቁሙ መረጃዎች አሉ። የከተማነት ታሪኳ የጐላው ግን ከግራኝ ወረራ በኋላ ተበታትኖ የቆየውን የጥንታዊ ሸዋን ግዛት አንድ ለማድረግ የሸዋ ስርወ-መንግሥት በአቤቶ ነጋሲ በመንዝ አጋንቻ ላይ በ፲፮፻፷፭ ዓ/ም ተጀምሮ በተከታታይ እስከ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም የጥንት ኢትዮጶያ ግዛትን ለማስመለስ በተደረገው እንቅስቃሴ ነው። የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ወደ ፲፫ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሥር መሠረቱ የረር | እንጦጦ እስከዞረበትና በኋላም አዲስ አበባ እስከተቆረቆረችበት ጊዜ ድረስ በቀዝቃዛ አየሯ የምትታወቀው አንኮበር ለአምስት የሸዋ ነገሥታት በማእከልነት አገልግላለች። \n \nጥያቄ: አንኮበር ከተማ መቼ ተቆረቆረች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፯፻፳ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር ከመቼ ጊዜ አንስቶ ነበር ሲጋጩ የነበሩት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ1982 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ከተማ ማናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አዲስ አበባ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: ላይቤሪያ የምትገኝበት አህጉር የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሳ በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ የሚታወቅ ነው አሁን የሚገኘው በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: 29ኛውን የእግር ኳስ የአፍሪካ ዋንጫ ያዘጋጀችው ማናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ደቡብ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: ፍትሐ ነገሥት ወደ ግእዝ ተተርጉሞ ኢትዮጵያ የገባው መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1450 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፌስቡክ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም እያበለፀገ መሆኑን ከሰሞኑ የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል። ኩባንያው የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም የሚሰራውም ከጎግል አንድርይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እና ከአይፎን አይ.ኦ.ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ አንደሆነም ታውቋል። አዲሱ የፌስቡክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ሙሉ በሙሉ ከዜሮ ተነስቶ በራሱ መንገድ እየበለፀገ መሆኑንም ኩባንያው አስታውቋል። ኦፕሬቲንግ ሲስተሙ በምን መልኩ ይሰራል የሚለው ነገር በግልፅ ባይታወቀም የፌስቡክ የቪዲዮ የስልክ ጥሪን ጨምሮ ሌሎች የኩባንያው አገልግሎቶች ግን ተጠቃሚ ይሆናሉ ነው የተባለው። ፌስቡክ አሁን በሚያመርታቸው መገልገያዎች ላይ በብዛት የጎግል አንድሮይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተመን የሚጠቀም ሲሆን፥ ይህም ጎግል በአብዛኛው የፌስቡክ አገልግሎቶች ላይ በበላይነት እንዲቆጣጠር እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ፌስቡክ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም መስራቱም ከጎግል አንድሮይድ ጥገኝነት የሚያላቅቀው መሆኑን እና በሚያመርታቸው መገልገያዎችን ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር ስልጣን እንዲኖረው እንደሚያደርገውም ተገልጿል። ምንጭ፦ www.techworm.net \n \nጥያቄ: በኡበር የታክሲ አገልግሎት ውስጥ ለረጅም ጊዜ በቦርድ አባልነት ያገለገሉት ትራቪስ ካላኒክ መቼ በተስተዋለው የሙስና ችግር ምክንያት ነው ከኃላፊነታቸው ለመልቀቅ ያሰቡት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከጎግል አንድርይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እና ከአይፎን አይ.ኦ.ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴት ተማሪዎች በትርፍ ጊዜያቸው ችግር ፈቺ የሞባይል አፕሊኬሽን እና ኮዲንግ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ የሚያግዝ ስምምነት መፈረሙን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ስምምነቱ የተፈረመውም ከኮኖቬሽን ኢንተርፕረንርሺፕ ዲቨሎፕመንት ከተባለ ድርጅት ጋር መሆኑ ተነግሯል፡፡ ስምምነቱን የፈረሙት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ÷ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ሲመደቡላቸው ተቀብሎ ከማስተማር ጎን ለጎን በአከባቢያቸው ካሉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር ትስስር በመፍጠር ፣ተማሪዎችን በቀጣይ የዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ውጤታማ የሚያደርጉና በሳይንስ ዘርፉም ፍላጎት እንዲያድርባቸው የሚያግዙ ስራዎችን ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲዎች በአይሲቲ ዘርፍ ያላቸውን አቅርቦት ለስልጠናው በማመቻቸትና መምህራንንም በማሳተፍ ሴት ተማሪዎች በሞባይል አፕሊኬሽን እና ኮዲንግ ላይ የሚሰጣቸውን ስልጠና ይደግፋሉ፡፡ ይህ ስምምነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዩኒቨርሲቲዎች ባሉበት አከባቢ የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ ለሚሰራው ስራ እና የሳይንስ ባህል ግንባታ ላይ የሰጠው ትኩረት አንድ አካል ነው ብለዋል፡፡ የኮኖቬሽን ኢንተርፕረንርሺፕ ዲቨሎፕመንት በኢትዮጵያ አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ገብረሚካኤል÷ ሴት ተማሪዎች በሳይንስ ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆኑን አንስተዋል። ፕሮጀክቱ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸው ጀምሮ ሳይንስ ውስጥ እንዲገቡ የሚያግዙ ስልጠናዎችን በማመቻቸት በሳይንስ ዘርፍ የሚመረቁ ሴት ተማሪዎችን ቁጥር ከፍ የማድረግ ዓላማ አለው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱን እውን ለማደረግ የዩኒቨርሲቲዎች ድጋፍ ወሳኝ መሆኑንና በፕሮግራሙ ታቅፈው ስልጠናውን ተከታትለው ጥሩ ውጤት ለሚያስመዘግቡ ሴት ተማሪዎችም የነፃ ትምህርት እድሎችን እንደሚያመመቻቹ ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቱን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመረጡ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚጀምሩና ከዚያም በመነሳት በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የማስፋፋት እቅድ እንዳላቸውም አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል፡፡ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ተማሪዎች የአይ ሲ ቲ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ ማመቻቸቱን አስታውቀዋል፡፡ በተለይም ዲጂታል ሊትሬሲ በሚል የክረምት የስልጠና ፕሮግራም በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች በማካሄድ የተለያዩ የማህበረሰብ አካላት መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል። በቀጣይም የዚህ አይነት ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ፕሮፌሰር አፈወርቅ መግለጻቸውን ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: ሴት ተማሪዎች በትርፍ ጊዜያቸው ችግር ፈቺ የሞባይል አፕሊኬሽን እና ኮዲንግ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ የሚያግዝ ስምምነት የተፈረመው ለምን ዓላማ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሳይንስ ዘርፍ የሚመረቁ ሴት ተማሪዎችን ቁጥር ከፍ የማድረግ ዓላማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት ያለው ወይራ የምን ምልክት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሰላም ምልክት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: ዓርብና ሮብን የሚያሽር በዓል ሲኖር በዋዜማው የሚጾመው ጾም ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጾመ ገሀድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየህንዱ ኩባንያ በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን ጉማሬ ወረዳ ጥቅጥቅ ደን ውስጥ 3,012 ሔክታር መሬት ለሻይ ቅጠል ልማት ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ቦታ መሰጠቱ አግባብ አለመሆኑ ተጠቅሶ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስን ጨምሮ የአካባቢው ነዋሪዎችና የአካባቢ ጉዳይ ተሟጋቾች ቅሬታ ቢያቀርቡም፣ መሬቱን የሰጠው ግብርና ሚኒስቴር ቦታው ላይ ያሉት ዛፎች ትልልቅ ሳይሆኑ ቁጥቋጦ ናቸው በማለት ሲቀርብ የነበረውን ቅሬታ ውድቅ አድርጓል፡፡ ነገር ግን ኩባንያው ጣውላ በሕገወጥ መንገድ ሲያመርት በመገኘቱ የኩባንያው ሥራ አስኪያጅ ሰኔ 14 ቀን 2004 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሦስት ዓመታት በኋላ ቬርዳንታ ሐርቨስት በዓለም አቀፍ ሕግጋትም ሆነ በኢትዮጵያ ሕግ በፅኑ የተከለከለውን የሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ማካሄዱ፣ በአካባቢው ባለሥልጣናት ቁጣ መቀስቀሱ እየተነገረ ነው፡፡ ‹‹ሠራተኛ መቅጠር ከፈለገ በሠራተኛና በአሠሪ ሕግ መሠረት መሆን ይኖርበታል፤›› በማለት አቶ ዮናስ ኩባንያው የፈጸመው ተግባር ሕገወጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋት ሉዋክ ቱሉና ምክትላቸው ኢንጂነር ኦሌሮ ኤፒዮ በጉዳዩ ላይ መረጃው እንዳልቀረበላቸው ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በቬርዳንታ ሐርቨስት ትላልቅ ዛፎችን ጨፍጭፏል ተብሎ የቀረበበትን ክስ የነበሩት ትላልቅ ዛፎች ሳይሆኑ ቁጥቋጦዎች ናቸው ብሎ የገለጸው መስሪያ ቤት ማነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ግብርና ሚኒስቴር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአንድ ወጣት ተማሪ ከወዳደቁ ቁሳቁሶች በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ መስራቱ ተገለጸ፡፡ ጌታባለው መኩሪያው የተባለው ወጣት በባህርዳር ዩኒቨርስቲ 3ኛ ዓመት የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሲሆን ወጣቱ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች እንዲሁም አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የብስክሌት አካላትን ተጠቅሞ ነው የብስክሌት ጀልባ (Pedal-Boat) መስራት የቻለው፡፡ ጌታባለው መኩሪያው ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የሰራውን የብስክሌት ጀልባ በውሃ ላይ በመንዳት ሙከራ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: ጌታባለው መኩሪያ የፈጠራ ሥራውን የት ፈጠረው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ሣህሌ ደጋጎ በክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራ እፁብ ድንቅ በማድረግ የበኩላቸውን ሚና የተጫውቱት ከነማን ጋር ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nማርኮ ፖሎ ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ 600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል። ይህ ተጓዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል። በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል። \n \nጥያቄ: ማርኮ ፖሎ በኩብላ ካህን ቤተመንግስት ሥልጣን ተሰጥቶት ስንት ዓመት ቆየ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 17 ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፕል ኩባንያ ተጠቃሚዎች በድምፅ ማዘዝ የሚችሉት ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ወይንም ኢርፎን ይፋ አደረገ፡፡ ይህም ተጠቃሚዎች ምንም አይነት ነገር ሳይጫኑ ሃይ ሲሪ የሚል ድምፅ በማሰማት ብቻ የድምፅ ማዳመጫውን ማዘዝ እንደሚችሉ ነው የተነገረው፡፡ ከዚህ ባለፈ ኤርፖድስ የተባለው ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ተጠቃሚዎች ባትሪ ካለቀባቸው እንዲያስተካክሉ ተጨማሪ ሰዓትን በቅድሚያ እንደሚሰጥ ነው የተነገረው፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት የሰጡ ባለሙያዎች ኤርፖድስ የተሰኘው የድምፅ ማዳመጫ በእጅጉ እየዘመነ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ ይህ አዲሱ ድምፅ ማዳመጫ 159 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ሲሆን ገመድ አልባ ቻርጀርን የሚያካትት ከሆነ ተጨማሪ 40 ዶላር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ኤርፓድስ የተባለው ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ለተጠቃሚዎች ልዩ የሚያደርገው ነገር ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በድምፅ ማዘዝ የሚችሉት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ የተወለደባት የአሜሪካ ግዛት ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሚዙሪ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1881 ዓ.ም. ለብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ የማዕድን ማውጣት ፈቃድ የሰጠው ንጉሥ ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሎቤንጉላ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኋንግ ዲ ኋንግ ዲ (ቢጫው ንጉሥ) በቻይና ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ የቻይና ሕዝብ አባትና ንጉሥ ነበረ። የቤተሠቡ ስም «ጎንግሱን» የተሰጠው ስም «ሽወንዩወን» ነበር ይባላል። አባቱ ሻውድየን ተባለ። የተወለደው ሾው ጪው በተባለ ሥፍራ በጩፉ ሲሆን በኋላ ነገዱን ወደ ዥዎሉ ወሰደው፤ በዚያ ገበሬ ሆኖ ድብ፣ ነብርና ባለክንፍ አንበሣ የመሰለ ፍጡር አንዳስለመደ የሚል ትውፊት አለ። ያንጊዜ የኋንግ ዲ ወገን እና የያንዲ (ዩዋንግ) ወገን ለቢጫው ወንዝ ሸለቆ ተወዳዳሪዎች ነበሩ። ሦስተኛ ወገን - የሊ ሕዝብና ንጉሣቸው ቺ ዮው - ደግሞ ጠላቶቻቸው ሆኑ። ሦስት ውግያዎች ተከተሉ። በመጀመርያው የቺ ዮው ሥራዊት ያንዲውን አሸነፈው። ከዚያ ያንዲው ተሸንፎ ወደ ኋንግ ዲ ሸሸ። በሁለተኛው የዥዎሉ ውግያ ኋንግ ዲ እና ቺ ዮው ተጋጠሙ። በዚህ ውግያ ቺ ዮው ጉምን በጥንቆላ ፈጥሮ ኋንግ ዲ እንደገና በተነው፣ ብዙም ሌሎች ጉድ ሥራዎች እንደ ተከሠቱ የሚል ትውፊት አለ። ቺ ዮው በዚህ ውግያ ቢሸነፍም፣ የኮርያ ሕዝብና የህሞንግ ሕዝብ ዛሬውንም እንደ ቅድማያታቸው ይቆጥሩታል። በሦስተኛው የባንጯን ውግያ፣ ኋንግ ዲ በያንዲው ላይ ድል አደረገ። ከዚያ በኋላ ወገኖቻቸው ተባብረው የኋሥያ ብሔር (የቻይና ሕዝብ ቅድማያቶች) ፈጠሩ። ኋንግ ዲ በይፋ የቻይና ንጉሥነት ማዕረግ ወሰደ፤ የዘውድና ቤተ መንግሥት ሥርዓት ጀመረ። ከዚህ በተረፈ ኋንግ ዲ ጋሪና መርከብ እንደ ፈጠረ ይጻፋል። ደግሞ ምኒስትሩ ጻንግችየ መጀመርያ የቻይና ጽሕፈት ፈጠረ፤ የኋንግ ዲ ሚስት ሌዙም ልብስ ከሃር ትል እንዴት እንደሚሠራ አሳየች። የህክምና መጽሓፍ ኋንግዲ ኔጂንግ ሌሎችንም መጻሕፍት እንደ ጻፈ ይታመናል። ከዚህ በላይ የቻይና ስነ ፈለክና የቻይና ዘመን አቆጣጠር ፈጠረ። ስለ ኋንግ ዲ ብዙ ሌሎች ትውፊቶች አሉ። መጀመርያ ሚስቱ ሌዙ ተከታዩን ሻውሃውን ወለደች። 3 ሌሎች ሚስቶች እነርሱም ፋንግሌ፣ ቶንግዩ እና ሞሙ ነበሩት። በተለመደው ታሪክ ዘንድ ለ99 አመት ነገሠ። ታላቅ መቃብሩ በያንአን ከተማ ሲገኝ እስከ ዛሬ ድረስ በየአመቱ በሥነ ስርአት ይከብራል። \n \nጥያቄ: ኋንግ ዲ የተወለደው በየት ስፍራ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሾው ጪው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቅዱስ ላሊበላ ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ ሕንዓዎችን ለመገንባት አሰበ ከዚያም በጊዜው ከነበሩት አባቶች በተለይ ቀይት ከምትባል ባለአባት የጠየቀውን 40 ጊደር ለመግዛት በሚያስችለው ወርቅ ቦታውን ገዝቶ በከርሰ ምድር ውስጥ ያሉትን ሕንዓዎቸ ሊያወጣ ተዘጋጅ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ የሚገነባባቸውን መሳሪያዎችለ 10 አመታት አዘጋጅቶ ማለትም በ 1157 አ.ም ነግሶ በ1166 አ.ም ሕንዓውን ገንብቶ ጨረሰ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ከ 40 አመታት የንግስና ዘመን በኋላ በተወለደ በ 97 አመቱ ሰኔ12 ቀን ከዚህ አለም በሞት ተለየ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ ያስገነባቸው 1.ቤተ መድሃኒያለም፤ ቤተማርያም ፡ቤተ መስቀል፡ ቤተ ደናግል እና ቤተ ሚካኤል ፤ 2.ለየት ብሎ እሚታየው ከላይ እስከ ታች ድረሰስ በመስቀል ቅርዕ የተቀረዐው ቤተ ጊዮርጊስ፤ 3.ቤተ ገብር፤ልና ቤተ መርቆሪዮስ፤ ቤተ አማኑኤል እና ቤተ ሊባኖስ ይገኛሉ እነዚህንም ታሪክ ለ ሁለት ይከፍላቸዋል ቤተ መድሃኒአለም፤ ቤተ ማሪያም፤ ቤተ መስቀል፤ ቤተ ደናግል፤ ቤተ ሚካኤል፤ ቤተ ጊዮርጊስ በ ምድራዊ እየሩሳሌም በማለት ቤተ ገብርኤል፤ ቤተ መርቆሪስ፤ ቤተ አማኑኤል፤ ቤተ ሊባኖስ በ ሰማያዊ ፤የሩሳሌም ይላቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ቅዱስ ላሊበላ ከዚህ ዓለም በስንት ዓመቱ አረፈ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ 97 አመቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: የጣና ሐይቅ ርዝመት ምን ያህል ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 84 ከ.ሜ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመንግሥት እና ፖለቲካ ናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ሲሆን መንግሥቷ በአሜሪካ መንግሥት ላይ ነው የተመረኮዘው። የህግ አውጪው አካል አወቃቀር የዌስትሚኒስትር ሥርዓትን ይከተላል። በአሁኑ ጊዜ ጉድላክ ጆናታን ፕሬዝዳንት ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ለሁለት የአራት ዓመት ጊዜ ሲያገለግል በሕዝቡ ነው የሚመረጠው። የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት አካሎች አሉት። እነዚህም ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ናቸው። ሴኔቱ 109 መቀመጫዎች ሲኖሩት እያንዳንዱ ክልል በሶስት አባሎች ይወከላል። የአቡጃ ርዕሰ አካባቢም አንድ ተወካይ አለው። የሴኔት አባላት በሕዝብ ይመረጣሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 360 መቀመጫዎች ሲኖሩት የእያንዳንዱ ክልል ወካዮች በሕዝብ ብዛት ነው የሚወሰነው። የውጭ ግንኙነቶች ነፃነቷን በ1960 እ.ኤ.አ. ካገኘች በኋላ ናይጄሪያ ለአፍሪካ ነፃነትና ክብር መታገል ዋና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አድርጋለች። የደቡብ አፍሪካን አፓርታይድ ሥራዓት በመቃወም ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በ1960ዎቹ እ.ኤ.አ. ናይጄሪያ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ሲሆን እስራኤል የናይጄሪያ ፓርላማ ህንጻዎችን አሰርታለች። ናይጄሪያ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራች አገር ናት። በምዕራብ አፍሪካም ሆነ በአፍሪካ በጠቅላላ ትልቅ ተጽዕኖ አላት። በተጨማሪም እንደ ኤኮዋስ ያሉ የምዕራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅቶች መሥራች ናች። ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ጀምሮ ናይጄሪያ ዋና የነዳች አምራች ስትሆን የኦፔክ አባል ሀገር ናት። በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ናይጄሪያውያን በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ናይጄሪያውያን በአሜሪካን እንደ ሚኖሩ ይገመታል። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ ነዳጅ በማምረት የኦፔክ አባል ሀገር የሆነችው ከመቼ ጀምሮ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nናይጄሪያ ናይጄሪያ በይፋ የናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ አገር ናት። በሕዝብ ብዛትም ከአፍሪቃ አንደኛ ናት። ከቤኒን ፣ ቻድ ፣ ካሜሩን ፣ ኒጄር ፣ እና ከጊኒ ባሕረ ሰላጤ ጋር ድንበር ትካለላለች። በናይጄሪያ ውስጥ ትልቁ ብሔሮች ሀውዛ ፣ ኢግቦ እና ዮሩባ ናቸው። ግማሹ ሕዝብ እስላም ሲሆን ሌላው ግማሽ ደግሞ የክርስትና እምነት ይከተላል። ትንሽ የሕዝቡ ክፍልም ባህላዊ ሃይማኖቶችን ይከተላል። የሳይንስ ጥናት እንደሚያሳየው ናይጄሪያ ከ፱ሺህ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ ነዋሪዎች እንደነበሩባት ያሳያል። በቤንዌ እና ክሮስ ወንዞች አካባቢ ያለው ሥፍራ የባንቱ ፍልሰቶች መነሻ እንደ ነበረ ይታመናል። የናይጄሪያ ስም ከኒጄር ወንዝ ነው የተወሰደው። ናይጄሪያ በአፍሪካ በሕዝብ ቁጥር አንደኛ ስትሆን ከዓለም ደግሞ ሰባተኛ ናት። የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በዓለም ላይ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። የዓለም አቀፍ ገንዘብ ፈንድ እንደሚገምተው የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በ2011 እ.ኤ.አ. በ8% ያድጋል። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት ከዓለም ስንተኛ ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሰባተኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ጣልያንን ያሸነፈችበት የአድዋ ጦርነት የተካሄደው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1880 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: በአንጎላ ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን የያዘው አካል ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nህንድ ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ሰርታለች፡፡ ሃገሪቱ የሰራችው መመርመሪያ ልክ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ውጤቱን በፍጥነት ሊያሳይ የሚችል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ከአንድ ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ ውስጥ ውጤቱን እንደሚያደርስ ነው የተነገረው፡፡ በ2 ሺህ ህሙማን ላይ ምርመራ ተደርጎም ውጤታማነቱ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ ፌሉዳ የተባለው ይህ መመርመሪ ኪት ዋጋው 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የህንድ መንግስት ዋና የሳይንስ አማካሪ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን እንዳሉትም ሙከራው ቀላል ፣ ትክክለኛ፣ አስተማማኝ እና ወጪ ቆጣቢ ነው ፡፡ ህንድ በአሁኑ ጊዜ ከ1 ሺህ 200 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሏት ሲሆን በቀን 1 ሚሊየን ናሙናዎችን እየመረመረች ትገኛለች፡፡ \n \nጥያቄ: የሕንድ መንግስት የሳይንስ አማካሪ ማናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ዋናው ሃይማኖት ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ እስልምና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስንተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፯ተኛው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በህፃናት ልብ ህክምን ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ዶክተር በላይ አበጋዝ እና 30ኛ አመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል ያላቸውን አስተዋፅኦ በማድነቅ ሽልማት አበረከቱ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ዶ/ር አብይ አህመድ ዶ/ር በላይ አበጋዝን በምን ዘርፍ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ነው የሸለሟቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በህፃናት ልብ ህክምን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: በ628 ዓክልበ. ማን የአቴና ሕግጋትን ጻፈ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ድራኮ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: ግራኝ መሃመድ በኢትዮጵያ ወረራ ሲያካሄድ ንጉሱ ማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአጼ ልብነድንግል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበመረጃ መንታፊዎች የተያዘባቸዉን መረጃ ለማስለቀቀ የራንስም ክፍያ ከከፈሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል 80 ከመቶ የሚሆኑት ድርጅቶች ለዳግም ጥቃት መጋለጣቸዉን የሳይበርሰን ጥናት ጠቁሟል ሳይበርሰን የተሰኘው የሳይበር ደህንነት ምርት አቅራቢ የሆነዉ ተቋም ባካሄደዉ አዲስ ጥናት እንዳመለከተዉ ከሆነ ተቋማቱ ብዙውን ጊዜ በተመሳሳይ የመረጃ መንታፊዎች ጥቃት እንደሚሰነዘርባቸዉ ነዉ ያመለከተዉ። ‘የራንሰም’ ክፍያ መክፈል የቅጅ ወንጀሎችን ከማበረታታት በተጨማሪ እነዚህ ኩባንያዎች በፍጥነት ወደ ተለመደው ንግድ ሥራቸዉ የመመለስ ዋስትና አለመኖሩን ነው ሳይበርሰን የገለጸው። ከዚህ ባሻገር ወደ ግማሽ የሚጠጉ የጥናቱ ተሳታፊዎች የሳይበር ጥቃት ሰለባ የሆኑ ድርጅቶች ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ መረጃዉን የማግኘት እድል ቢፈጠርም አንዳንዶቹ ወይም ሁሉም መረጃዎች እንደሚበላሹ ሳይበርሰን በጥናቱ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ይህም በመረጃ መንታፊዎች የሚጠየቁ የመረጃ ማስለቀቂያ ክፍያዎችን መፈጸም ለተቋማቱ በትክክል መረጃዎቻቸዉን እንደሚያስገኝላቸው ዋስትና አለመሆኑን ማሳያ እንደሆነ እና የመረጃ መንታፊዎች በተጎጂው ድርጅት ላይ እንደገና ጥቃት ከመሰንዘር አያግዳቸውም ተብሏል። ከዚያ ይልቅ የራንሰም ክፍያ መፈጸም የመረጃ መንታፊዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እንዲያደርሱ የሚገፋፋ መሆኑን ሳይበርሰን መጠቆሙን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በመሆኑም የራንሰምዌር ጥቃቶችን ቀድሞ ለመለየትና ለመከላከል የቅድመ መከላከል ስትራቴጂ መኖር ኩባንያዎች ላይ የሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች እና በድርጅቶቹ ላይ ያንዣበቡ የራንሰምዌር ጥቃት እንቅስቃሴዎችን ቀድሞ ለመግታት ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: የምን ክፍያ መፈጸም ነው የመረጃ መንታፊዎች የበለጠ ተደጋጋሚ ጉዳት እንዲያስከትሉ የሚያደርገው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የራንሰም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ካርቱም የየትኛው ሀገር ዋና ከተማ ናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሱዳን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ዘመነ መሳፍንት ያስቆሙት ንጉሥ ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አፄ ቴዎድሮስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: አሸናፊ ከበደ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የጨረሱት የት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ የአስትሮኖሚካል ሲምፖዚየም ያዘጋጀች ስንተኛዋ አፍሪካዊ ሀገር ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሶስተኛዋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: ጣና ሐይቅ በዓመት ሊሰጠው ከሚችለው የዓሳ ምርት እየተመረተ የሚገኘው ምን ያህል እጁ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 15 በመቶው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: አዲስ አበባ የተቆረቆረችው ማን በመረጠው ቦታ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እቴጌ ጣይቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ዘ ኢትዮጵያ ካረፉ በኋላ ተከታዩን ፓትርያርክ ለመሾም በተደረገው ምርጫ በዕለቱ ተገኝተው የመረጡት ፻፵፮ አባላት ሲሆኑ ሦስቱ ዕጩዎች፦ ፩) አቡነ ቴዎፍሎስ (የሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ) - ፻፳፫ ድምጽ ፪) አቡነ ያዕቆብ (የወለጋ ሊቀ ጳጳስ) - ፰ ድምጽ ፫) አቡነ ጢሞቲዎስ (የሲዳሞ ሊቀ ጳጳስ - ፲፫ ደምጽ አግኝተዋል። በዚህም መሠረት የፓትርያርኩ ስርዓተ ሲመት ግንቦት ፩ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ/ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናውኗል። በ፲፱፻፷፮ ዓ/ም በኢትዮጵያ ወታደራዊው አብዮት ተለኩሶ ንጉሠ ነገሥቱ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ከሥልጣን ሲወርዱ ወዲያው የቤተ ክርስቲያኗም ንብረት ተወረሰ። ፓትርያርኩንም ከሥልጣን ከማውረዱ በፊት ደርግ “የተሐድሶ ጉባዔ” የሚል ኮሚቴ አቋቁሞ በተለያየ ክፍል በሳቸው ላይ የማይገታ አመጽና አድማ መነሳሳት ጀመረ። በዚህ ሁኔታ ለአንድ ዓመት ያኡል በትዕግስት ከቆዩ በኋላ በየካቲት ወር ፲፱፻፷፰ ዓ/ም የደርግ መንግሥት “ሲጠበቅ የቆየ ፍርድ” በሚል አዋጅ ከሥልጣን አውርዶ እሳቸውንና በመጨረሻ በእሳቸው የተሾሙትን ሦስት ጳጳሳት (ያሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አንዱ ናቸው) አሰራቸው። በኋላም ሐምሌ ፯ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም እኒህ የቤተ ክርስቲያን መሪ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ርዕሰ ሊቃና ጳጳሳት ወፓትርያርክ ዘ ኢትዮጵያ በደርግ እጅ ተገደሉ። ቀደም ሲል “የተቀባ ፓትርያርክን ሞት ብቻ ነው የሚሽረው” የሚለውን እምነት በሚቃረን ሁኔታ ከሥልጣን አውርደው “የተቀባ ፓትርያርክ ሳይሞት በላዩ ላይ ሌላ ፓትርያርክ አይሾምም” የሚለውን ሁለተኛውን እምነት ጥሰው ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ሦስተኛው ፓትርያርክ እንዲሾሙ አደረጉ። \n \nጥያቄ: አቡነ ቴዎፍሎስ በማን ተገደሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በደርግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየሕገ መንግሥት ታሪክ የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና በ2093 ዓክልበ. ያሕል ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው። ሰነዱ እራሱ ገና አልተገኘም፤ ነገር ግን ለዜጎቹ አንዳንድ መብት እንደ ፈቀደላቸው ይታወቃል። ለምሳሌ ለመበለትና ለደሀ አደጎች ቀረጥ እንዳስቀረላቸው ድሆችንም ከሃብታሞች አራጣ እንደጠበቃቸው ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ብዙ መንግሥታት በተጻፈ ሕግ እንዲገዙ ልዩ ስርዓት ነበራቸው። ከተገኙት ሕግጋት ሁሉ ጥንታዊ የሆነው በ1983 ዓክልበ. የገዙ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው። በተለይ ዕውቅ የሆኑ የጥንት መንግሥት ሕጎች የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት (1832 ዓክልበ.) ፤ የኤሽኑና ሕግጋት (ምናልባት 1775 ዓክልበ. ግድም)፤ የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ.) እና፤ ሕገ ሙሴ ለእስራኤል (1661 ዓክልበ.) ናቸው። ሕገ ሙሴ በተለይ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 ያህዌ አስተካክሎ ከነዚህ ሁሉ የተሻሸሉት ብያኔዎች ይጠቅልላል። በኋላ ኬጢያውያን (1488 ዓክልበ. ግድም) እና አሦር (1080 ዓክልበ. ግድም) በበኩላቸው ለራሳቸው ሕግጋት አወጡ። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ተመዝግቦ የተገኘው ሕገ-መንግሥት የታወጀው በማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኡሩካጊና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: በ350ዓክልበ. ስለ ሕገ መንግሥት ያወቀው ግሪካዊ ፈላስፋ ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አሪስጣጣሊስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ ከሴኔጋል ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በደቡብ-ምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመጋቢት ፳፮ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት የመጀመሪያው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፱ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል። ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅት መሠረቱ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (የዓለም የንግድ ማዕከል) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል። ፲፱፻፷ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በሜምፊስ ከተማ በነፍሰ-ገዳይ እጅ ተገደለ። \n \nጥያቄ: ፲፰፻፺፯ ዓ/ም በሕንድ ግዛት ውስጥ ተከስቶ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ያጠፋው እሳተ ገሞራ የተከሰተው በየትኛው ሸለቆ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የካንግራ ሸለቆ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ እ.ኤ.አ. በ1971 ሥልጣን የያዘው ማን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኢዲ አሚን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: በ1720 ዓክልበ. ግ. ከነአሦር ከተማን ያቀናው የአሞራዊው ንጉሥ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየኢትዮጵያ ሙዚቃ የመጀመሪያውን ግራማፎን ወይም የሸክላ ማጫወቻ በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ሊዋንቲቭ ለዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አመጡላቸው። ይኸውም ማጫወት ብቻ እንጂ ድምጽ አይቀዳም ነበር። በኋላ ግን በዓመቱ በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ከንግሥት ቪክቶሪያ የተላኩ የእንግሊዝ መልዕክተኞች በመጡ ጊዜ ግራማፎኑንና ድምፅ መቅጃውን ይዘውላቸው መጡ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸው በዲስክ የተቀረፁት ዓፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ናቸው። ዛሬ በእንግሊዝ አገር በለንደን ከተማ ብሪቲሽ ኢንስቲቲውት ኦፍ ሪኮርድ ሳውንድ በተባለው ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ በሸክላ የተቀረፀው የመጀመሪያው ዜማ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ስራዎች ሲሆኑ ዘመኑም በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ነበር። ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በጀርመን ቆይታቸው ወቅት የጀርመን የሙዚቃ ድርጅት ጠይቋቸው የኢትዮጵያ መዲናና ዘለሰኛ ዜማዎች በ፲፯ አይነት ስልት እየተጫወቱ ተቀርፀዋል። ኩባንያው የተሰማ እሸቴን ዜማዎች በ፲፯ ሸክላዎች የቀረፀው ሲሆን ለዜማው ባለቤት የድካም ዋጋ እንዲሆን በወቅቱ ፲፯ ሺህ የጀርመን ማርክ ከፍሏቸዋል። በዘመኑ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያም አሁንም እነዚህ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ብርቅዬ ሸክላዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ። እነዚህ በተቋሙ እጅ ያሉት ፲፮ ሸክላዎች እያንዳንዳቸው ሁለት ዜማዎችን የያዙ ሲሆኑ ባጠቃላይ ፴፪ ዜማዎች ተቀርፀውባቸዋል። እያንዳንዱ የሸክላው ገፅ ላይ A ወይም B ተብሎ ተሰይሟል፣ የዜማው ስም ተፅፎበታል፣ የዜማው ባለቤት ተሰማ እሸቴ ስም አለ፣ ሸክላው ጀርመን ሀገር መሰራቱ እንዲሁም የሸክላው ቁጥር ተጠቅሷል። በ፲፱፻፳፭-፳፮ ዓ.ም. አካባቢ የእነ ፈረደ ጎላ፣ ንጋቷ ከልካይና ተሻለ መንግሥቱ የዜማ ሸክላዎች ብቅ እስከሚሉ ድረስ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ሸክላዎች ከ፳ ዓመታት በላይ አቅም ባላቸው ቤተሰቦች ዘንድ በብቸኝነት በግራማፎን ሲደመጡ ቆይተዋል። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያውን የሸክላ ማጫዋች ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ሊዋንቲቭ ለአፄ ሚኒልክ ያመጡላቸው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር የሕይወት ዘመናቸው ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1866 - 1957 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ አዲስ የዲዛይን ክፍተት መገኘቱ ተገለፀ። የቦይንግ ኩባንያ እና የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍ.ኤ.ኤ) በትናንትናው እለት እንዳረጋገጡት በ737 ማክስ አውሮፕላን ዲዛይን ላይ የተገኘው አዲስ ክፍተት የኤሌክትሪክ ሽቦ መቀራረብ ችግር እንደሆነ አረጋግጠዋል። የቦይንግ ቃል አቀባይ ጎርዶን ጆንድሮ “ጉዳዩ የቦይንግ አስቸጋሪ ሂደት አካል ቢሆንም፤ ተገቢውን ትንተና ለማከናወን ከአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር ጋር በጋራ እየሰራን ነው፤ አሁን የተገኘው ክፍተት የዲዛይን ለውጥ ለማድረግ ያስገድዳል የሚያስብል ደረጃ ላይ ግን አልደረሰም”ብለዋል። የቦይንግ አውሮፕላን ላይ የተገኘው አዲሱ የዲዛይን ክፍተት የሁለት ሽቦዎች በጣም መቀራረብ መሆኑን በመግለጽ፤ አብራሪዎች ችግሩን ተረድተው በአፋጣኝ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋን ሊያስከትል ይችላል” ሲል የኒው ዮርክ ታይምስ አስነብቧል። የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሰጠው መግለጫ፥ በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ሊደረግ በታቀደው የዲዛይን ማሻሻያ ዙሪያ ኤጀንሲው እና የቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ ግኝቶችን እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል። ኤጀንሲው አክሎም “በዚህ ሂደት ወቅት ተለይተው የሚታወቁ የደህንነት ችግሮች በሙሉ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ይደረጋል ” ሲልም አስታውቋል። ቦይንግ በአሁኑ ጊዜ ተቀራርበዋል የተባሉ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ለመለየት እና ስህተቱን ተከትሎ የሚደርሰውን አደጋ በተመለከተ ሰፋ ያለ ትንተና እየሰራ መሆኑን አንድ የኩባንያው ባለስልጣን አስረድተዋል። ቦይንግ በአምስት ወራት ውስጥ በሁለት አደጋዎች 346 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የማክስ 737 አውሮፕላን ማምረት ማቆሙ ይታወሳል።   ምንጭ፡- ሲጂቲኤን \n \nጥያቄ: በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ በተገኘው የዲዛይን ክፍተት ምክንያት በአምስት ወር ውስጥ ምን ያህል አደጋ አጋጠመ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ በዛምቢያ ከየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ የወደቀው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፱፻፶፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም እናታቸው ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቱርክመንኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nግሥላ ግሥላ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኝ አጥቢ አውሬ ነው። በእስያ የተገኘው ነብር የግስላ ቅርብ ዘመድ ሆኖ፣ በአነጋገር «ግስላ»ና «ነብር» የሚሉ ስሞች ሊለዋወጡ ይችላሉ። የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደት ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ሲደርስ በርዝመት ከ90 ሴ.ሜ እስከ 1,60 ሜ.ና በአፍሪካ የሚገኘው ዘር እስከ 1,90 ሜ ይደርሳል ። ከመሬት እስከ ሆዱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖረው ጭራው ደግሞ እስከ 100 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያሳያል ። ሴቲቱ ከወንዱ አነስ ትላለች ። በዱር ሲኖር እስከ 10 አመት እንደሚኖር ሲታወቅ በሰው ተይዘው ሲኖሩ እስከ 20 አመት እድሜ ያስመዘገቡ ግሥሎች አሉ። \n \nጥያቄ: ግስላ በሰው ተይዘው በእንክብካቤ ሲኖሩ ለምን ያህ፤ ጊዜ ይኖራሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 20 አመት እድሜ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ልጃቸውን አጼ ኃይለ ሥላሴን የወለዱት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና የመጀመሪያ ዲግሪዋን በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያገኘችው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1964 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: ‹‹ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ›› በሚል ቅፅል ስም የሚታወቁት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እቴጌ ጣይቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ከ100 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጎ ያስገነባቸው አራት የአየር መቆጣጠሪያ ታወሮች ነገ እንደሚመረቁ ተገለጸ፡፡ ታወሮቹ የተገነቡት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ሮቤ ከተማ፣ በአማራ ክልል ኮምቦልቻ፣ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ እና በሶማሌ ክልል ጎዴ ከተማ መሆኑን ከባለስልጣኑ ማህበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ለአየር መቆጣጠሪያ ስንት ታወሮች ገነባ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አራት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ተርሚናል ዛሬ ተመረቀ። ተርሚናሉ በ12 ሂክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ 800 ከባድ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑ ተገልጿል። የዲቾቶ የከባድ ተሽከርካሪ ተርሚናል 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ወጭ ተደረጎበት መገንባቱ ተነግሯል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የጭነት መቆያ ተርሚናል ለመገንባት ምን ያህል ወጪ ወጣ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: አይዛክ ኒውተን ፕሪዝም በመጠቀም ምን አሳየ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ መቼ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nካሣ አያሌው ገና የአራት ዓመት ህፃን ልጅ ሳለ በወቅቱ የትምህርት ገበታን መቋደስ የሚጀመርበት የቄስ ትምህርት ቤት ተልኮ ፊደል መቁጠር ጀምሯል። በዚህ ቆይታው ከፊደል ቆጠራ እስከ ዳዊት ንባብ በአግባቡ ለመማር በቅቷል። በኋላም በጊዜው እንጦጦ አምባ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተብሎ ይጠራ የነበረው ት/ቤት በመዝለቅ ዘመናዊ ትምህርቱን አንድ ብሎ ጀምሯል። ካሣ በዚህ ት/ቤት ሳለ ነበር ውስጡ ከነበረው የህይወት መክሊቱ ጋር የተገናኘው። የሦስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በት/ቤታችን የሚገኘውን ሚኒ ሚዲያ የምቀላቀልበት ዕድል ተፈጠረ። ይህ ዕድል የተገኘው በክፍሌ ውስጥ ተማሪዎች ፊት ቆሜ ጋዜጣ ሳነብ ድንገት ክፍላችን በተገኙት የት/ቤታችን ም/ርዕሰ መምህር አማካኝነት ነው። ስማቸው መምህር ግርማ ይገዙ ይባላል። አነባበቤን አይተው ስለወደዱት እርሳቸው ይመሩት የነበረውን የሚኒ ሚዲያ ክበብ እንድቀላቀል አደረጉ። በዚህ ክበብ ውስጥ ሆኜ በትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮሩ ዜናዎችን እየዘገብኩ ዘወትር ማለዳ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር እየተዘመረ ሰንደቅ ዓላማ በሚሰቀልበት የተማሪዎች ሰልፍ ላይ ማንበብ ጀመርኩ» በማለት ካሣ የጋዜጠኝነት ህይወት መስመሩ አንድ ብሎ የተጀመረበትን ሁኔታ ያስታውሳል። ካሣ አያሌው ካሣ የዘጠነኛ ክፍል ትምህርቱን በእንጦጦ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት /ቲ ኤም ኤስ/ ከጀመረ አንስቶ ሙሉ ትኩረቱን የቀለም ትምህርቱ ላይ አድርጎ ቆይቷል። በዚህ ቆይታው ከማህበራዊ ሳይንስ ይልቅ የተፈጥሮ ሳይንስን ምርጫው አድርጎ ትምህርቱን ተከታትሏል። የአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ አገር ዓቀፍ ፈተና ሲወስድም እንደ ተለመደው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ከፍተኛ ትምህርት የሚሸጋገርበት ዕድል አግኝቷል። በወቅቱ የከፍተኛ ትምህርት ምደባ የሚሰጠው በዕጣ ስለነበር ካሣ በዚህ አመዳደብ መሰረት የኢንጂነሪንግ ትምህርት እንዲማር የአዳማ ቴክኒክ ኮሌጅን እንዲቀላቀል ምደባ ወጥቶለታል። ምደባውን ተከትሎ ወደ አዳማ በማቅናት የቴክኖሎጂ ትምህርቱን መከታተል ቢጀምርም ቅሉ ሁኔታው ምቾት እንዳሳጣውና እንዳሎደደው ካሣ ይናገራል። ካሣ በ2005ዓ.ም ላይ ከፍቅረኛው ሊና ኑር አሕመድ ጋር በጋብቻ የተሳሰረ ሲሆን ቀዳማዊትና ለዕልና የተባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዷል። በትዳር ህይወቱ እጅግ የተሳካለት እንደሆነ በቅርበት የሚያውቁት ጓደኞቹ ይመሰክራሉ። ከስራ ውጪ ያለ ሰዓቱን ሁሉ ከቤተሰቦቹ ጋር ማሳለፍ እንደሚያስደስተው ሁሉም ይመሰክሩለታል። \n \nጥያቄ: ካሳ እንዴት የጋዘጠኝነት ሙያውን አንድ ብሎ የጀመረው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የሚኒ ሚዲያ ክበብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ የተቀበረበት ቤተክርስቲያን የት ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አረፎ አንኮበር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: የቀጭኔ ልብ በደቂቃ ምን ያህል ይመታል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ እስከ 170 ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: እበ ለገሰ ለተጨማሪ ለስንት ወጣቶች የሥራ እድል ፈጠረ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 10 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: ናዋትል ቋንቋ በሜክሲኮ በምን ያህል ሰዎች ይገራል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1.5 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ራስ ተፈሪ መኮንን የሐረርጌ አውራጃ አስተዳዳሪ የሆኑት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፱፻፫ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአንድ ወጣት ተማሪ ከወዳደቁ ቁሳቁሶች በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ መስራቱ ተገለጸ፡፡ ጌታባለው መኩሪያው የተባለው ወጣት በባህርዳር ዩኒቨርስቲ 3ኛ ዓመት የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሲሆን ወጣቱ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች እንዲሁም አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የብስክሌት አካላትን ተጠቅሞ ነው የብስክሌት ጀልባ (Pedal-Boat) መስራት የቻለው፡፡ ጌታባለው መኩሪያው ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የሰራውን የብስክሌት ጀልባ በውሃ ላይ በመንዳት ሙከራ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: በዉሃ ላይ የሚሄድ ብስክሌት ፈጠራ ባለቤት የሆነው ጌታባለው መኩሪያ በየት ዩኒቨርሲቲ ይማራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በባህርዳር ዩኒቨርስቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከአፍሪካ ህዝብ ውስጥ 24 በመቶ ብቻ የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆናቸውን ዓለም ባንክ አስታወቀ፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት አለመስፋፋት በአህጉሪቱ አዳዲስ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ የስራ ዕድል ፈጠራዎችን ለማስፋፋት አዳጋች እንደሚሆን ነው ባንኩ የገለጸው፡፡ በአፍሪካ እኤአ ከ2015 እስከ 2035 ባለው ጊዜ ውስጥ 450 ሚሊዮን ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የዓለም ባንክና የአፍሪካ ልማት ባንክ በጥምረት ያወጡት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ እንደ ኢኮሜርስ እና ፋይናንስ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የስራ ዘርፎችን በአፍሪካ በማስፋፋት ከፍተኛ የስራ እድልን መፍጠር እንደሚቻል ተጠቅሷል፡፡ በዚህም፣ ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በቂ እውቀት እንዲኖራቸው በማድረግ ማሰማራት እንደሚገባ ተነግሯል፡፡ \n \nጥያቄ: በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ከ2015-2035 እ.ኤ.አ ምን ያህል ስራ ፈላጊ ሰዎች ይኖራሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 450 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nስታምፎርድ ብሪጅ (የእግር ኳስ ሜዳ) ስታምፎርድ ብሪጅ በፉልሃም ለንደን የሚገኝ የቼልሲ እግር ኳስ ቡድን የእግር ኳስ ሜዳ ነው። የእግር ኳስ ሜዳው የሚገኘው በሙር ፓርክ ኢስቴት (በሌላ አጠራር በዋልሃም ግሪን) ወይም በተለምዶ ዘ ብሪጅ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ነው። ይህ የእግር ኳስ ሜዳ 41,798 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ ከፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ትልቅ የእግር ኳስ ሜዳ ያደርገዋል። የተከፈተው እ.ኤ.አ በ1877 ሲሆን እስከ 1905 ድረስ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ይጠቀምበት ነበር። ሜዳው ብዙ ለውጦችን አካሂዷል። በቅርቡ ደግሞ (እ.ኤ.አ 1990ዎቹ) ወደ ዘመናዊና ለሁሉም ተመልካቾች መቀመጫ ያለው ሆኖ ተሠርቷል። ስታምፎርድ ብሪጅ የተለያዩ የእንግሊዝ ዓለም አቀፋዊ ጨዋታዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ግማሽ ፍጻሜዎችን እና የቻሪቲ ፊልድ ጨዋታዎችን አስተናግዷል። ለተለያዩ ስፖርቶችም እንደ ክሪኬት ፣ ራግቢ ዩኒየን ፣ ስፒድዌይ ፣ ግሬይሃውንድ ሬሲንግ ፣ ቤዝቦል እና የአሜሪካን ፉትቦል ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ጥቅም ላይ ውሏል። የስታዲየሙ ትልቁ ኦፊሲዬላዊ የታዳሚዎች ቁጥር 82,905 ሲሆን ፤ ይህ የሆነው ቼልሲ ከአርሰናል እ.ኤ.አ በኦክቶበር 12 1935 ባካሄዱት የሊግ ጨዋታ ነበር። ስታምፎርድ ብሪጅ ፤ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ስታዲየም ሆኖ እ.ኤ.አ በ1877 ተከፈተ። በዚያ ሜዳ ላይ ታላላቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት የፈለጉ ገስ እና ጆሴፍ ሚየርስ የተባሉ ወንድማማቾች ኮንትራቱን እስካገኙበት ጊዜ ድረስ ለለንደን አትሌቲክስ ክለብ እስከ እ.ኤ.አ 1904 ድረስ አገልግሏል። \n \nጥያቄ: ስታምፎርድ ብሪጅ የእግር ኳስ ሜዳ ስንት ስዎችን ማስተናገድ ይችላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 41,798 ሰዎችን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ዓለም አቀፋዊ የአስትሮኖሚካል ሲምፖዚየም ለማዘጋጀት እድል ያገኘችው ሀገር ማናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን የተገደሉት በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአሜሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፋሽስት ቅዲስቲቱዋን ኢትዮጵያን ለማዋረድ ለመዝረፍና ለመግዛት ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ዝግጅቱን አጠናቆ በ1928 ዓም 300, 000 ሰራዊት 160 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች 450 ታንኮች 2000 የመጉዋጉዋዣ መኪናዎችን በማሰማራት ድንበር አልፎ ጦርነት በመክፈት ከገጠር እስከ ከተማ ህዝቡን ያለ እርህራሄ ጨፈጨፈ። በዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ላይ የመጀመሪያውን ህይወት ያለዉን ነገር ሁሉ የሚያጠፋውን “ማስተርድ ጋዝ” የሚባል ኬሚካል መሳሪያ በመጠቀም ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል ፈጸመ። በዚያን ክፉ ቀን የነጻነትና የሀገር ትርጉም የገባቸው የቁርጥ ቀን ልጆች በየአካባቢያቸው ፋኖዎችን በመምራት የእብሪተኛዉን የፋሽ ስት ጦር መግቢያ መዉጫ በማሳጣት ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰላም መኖር እንደማይችል ተስፋ አስቆርጠዉታል። ከነዚህ ነበልባል የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች መካከል ጠላትን በተከታታይ ዝርክርኩን አዉጥተው ከደቡብ ያሳደዱትና በመጨረሻው ዉጊያ ላይ ኢትዮጵያዊ በሚመስሉ የትግሬ ስርጎ ገብ ባንዶች ቆሰለው የተያዙትና በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ዉዱ የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ልጅ ራስ ደስታ ዳምጠው ነበሩ። ራስ ደስታ ዳምጠዉን ያስያዛቸው የባንዳ ጦር መሪ ደግሞ የትግሬው ተክሉ መሸሻ የሚባል የጣሊያን ሎሌ ሲሆን የስብሃት ነጋ አጎት የናቱ ታላቅ ወንድም መሆኑ ተረጋግጦአል ተክሉ መሸሻ በጣሊያን ደጃዝማችነት ተሰጥቶት በደቡብ ኢትዮጵያ የኢጣልያ ባንዳ ጦር አዛዥ ሆኖ በአካባቢው ኢትዮጵያ ጦር አዛዥ የነበሩት ራስ ደስታ ዳምጠው ከበርካታ አስደናቂ ጀብዱ በሁዋላ ቆስለው በጉራጌ አካባቢ መስቃ ከተባለው ሥፍራ ተኝተው በስቃይ ላይ እያሉ ተክሉ የስለላ መረቡን ዘርግቶ እግር በግር ተከታትሎ በመያዝ ከግንድ ጋር አስሮ በጭካኔ ደብድቦ ከገደላቸው በኋላ ራሳቸውን ረግጦ በመቆም ፎተግራፍ በመነሳት ለጣልያኑ ጌታው ግዳይ ካቀረቡት እርካሽ የትግሬ ከሃዲዎች አን ዱ ነበር። የፋሽስት ጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን ወሮ መናገሻ ከተማዋን አዲስ አበባን ለመያዝ ሲገሰግስ ጀምሮ ሶስቱ ቆራጥ የኢትዮጵያ ሌጆች (የሸንቁጥ) ልጆች አበበ ሸንቁጥ ተሾመ ሸንቁጥና ጥላሁን ሸንቁጥ በመርሃቤቴ በጅሩና በዠማ ወንዝ አካባቢ በመንቀሳቀስ “ዱሩ ቤቴ” በማለት ብዙ የአካባቢውን ጀግኖች አስከትለው የጣሊያንን ሀይል በመመከትና ከአገር በማባረር ከፍተኛ ገድል ፈጽመዋል። \n \nጥያቄ: ፋሺሽት ጣልያን ሁለተኛ ዙር ኢትዮጵያን ለመውረር በመጣ ጊዜ ምን ያህል ተዋጊ አውሮፕላኖችን ተጠቅሟል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 160 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም አዲሱን ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ምን ብለው ሰየሙት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ተክለ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ለአሜሪካ ፕሬዝደንትነት ለመጀመሪያ ጊዜ የተወዳደሩት መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1992 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በመጽሐፍ ቅዱስ ለሚገኙት መጻሕፍት ርእስ የተሰጠው በየት በተደረገ ጉባኤ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በኒቂያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: አፍሪካን ከእስያ የሚለያት ባህር ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በኤርትራ ባሕር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በኮትዲቯር የቀለም ቴሌቭዥን ስርጭት የተጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1962 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ596 ዓ.ም. በጃፓን 17 አንቀጽ ያለ ሕገ መንግሥት በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ ይታመናል። እንዲሁም በ614 ዓ.ም. ከነቢዩ መሐመድ የወጣው የመዲና ሕገ መንግሥት ዕጅግ ጥንታዊ ምሳሌ ነው። በዌልስ በ940 ዓ.ም. አካባቢ ንጉስ ህወል ዳ ሕጎቹን ጻፉ። በዛሬው ሩሲያ ደግሞ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ጥበበኛው ፕራቭዳ ያሮስላቫ የተባለውን ሕገ መንግሥት በ1009 ዓ.ም. ያህል ሠሩ። ይህ ሕግ በ1046 ታድሶ በኪዬቭ ሩስ በሙሉ ህጝ ሆነ። በስሜን አሜሪካ የኖሩ ኗሪ ጎሣ ሆደነሾኒ 'የአፈ ቃል' ሕገ መንግሥት «ጋያነሸጎዋ» የነበራችው ከ1080-1140 ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ሕግ በከፊል ለአሜሪካ ሕገ መንግሥት ተጽእኖ እንደነበረው ይታመናልና የአሜሪካ ምክር ቤት በ1981 ዓ.ም. ይህንን ግንዛቤ አስታወቀ። በእንግሊዝ አገር በ1092 ዓ.ም. ንጉስ 1 ሄንሪ የነጻነት ሥርአት የተባለውን ሰነድ አዋጀ። ይህ መጀመርያ የንጉሱን ሥልጣን ወሰኖ ንጉሡ ለቤተ ካህናትና ለቤተ መሳፍንት ወገኖች የሚገባውን እንቅብቃቤ ገለጸ። ይህም መሰረት በመኳንንቱ ሲዘረጋ በ1207 ዓ.ም. የእንግሊዝ ንጉሱን ዮሃንስ (ጆን) ማግና ካርታ («ታላቅ ሥርዓት») የሚባለውን ሰነድ እንዲፈርሙት አስገደዱዋቸው። ከዚሁ መሃል ቁም ነገር የሆነው ንጉሡ ያለ ሕጋዊ ሂደት ማንንም ሰው እንዳይገድሉ፣ ከአገር እንዳያሳደዱ፣ ወይም እስር ቤት እንዳያስገቡ ከለከላቸው። በዚያ ወቅት ያ ሰነድ በእንግሊዝ አገር የነጻነት መሠረት ሆነ። በ1212 እና 1222 ዓ.ም. መካከል አንድ የሳቅሰን አስተዳዳሪ አይከ ቮን ረፕጎቭ ያቀነባበረው ሕግጋት ሳቅሰንሽፒግል በአንዳንድ ጀርመን ክፍላገር እስከ 1892 ዓ.ም. ድረስ ላይኛ ሕገ መንግሥት ሆነ። በ1228 ዓ.ም. ሱንዲያታ ከይታ ማሊ መንግሥትን ለማወሐድ የ'አፈ ቃል' ሕገ መንግሥት አወጡ። ይህ ሕግ 'ኩሩካን ፉጋ' ተብሎ ነበር። \n \nጥያቄ: በጃፓን 17 አንቀጽ ያለው ሕገ መንግስት በልዑል ሾታኩ የተጻፈው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ596 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: አፈወርቅ ተክሌ የምህንድስና ትምህርታቸውን ትተው ኪነጥበብ ለማጥናት ለመጀመሪያ ጊዜ የገቡበት ትምህርት ቤት ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሶች በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ስንት አባላትን ይይዛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ዶ/ር ውለታ ለማ ያሸነፉበት የውድድር ዓይነት ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nረጅሙ የቦይንግ አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን በስኬት አጠናቋል። ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው ይህ አውሮፕላን ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ርዝመት እንዳለው ተገልጿል። አዲሱ አውሮፕላን በኩባንያው ምርቶች ላይ በሚፈጠሩ እክሎች ምክንያት የሚደርሱ አደጋዎችን ለመቀነስ ያስችላል ነው የተባለው። የአውሮፕላኑ የተሳካ የበረራ ሙከራ ሲያትል ከተማ አካባቢ የተከናወነ ሲሆን፥ ይህ ሙከራ ከመካሄዱ በፊት በአየር ፀባይ ችግር ምክንያት ሊካሄዱ የነበሩ ሁለት የሙከራ በረራዎች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ኩባንያው እስካሁን 309 የሚሆኑ 777 ኤክስ አውሮፕላኖችን የሸጠ ሲሆን፥ የአንዱ ዋጋም 442 ሚሊየን ዶላር ነው ተብሏል። ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዢያ የሆኑ ሁለት አውሮፕላኖች ተከስክሰው የ346 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሚያመርታቸው አውሮፕላኖች ደህንነት አስተማማኝ አይደለም በሚል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና በባለሙያዎች ከፍተኛ ወቀሳ ሲቀርብበት ቆይቷል። ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን   \n \nጥያቄ: ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ እና የኢንዶኔዢያ የሆኑ ሁለት አውሮፕላኖች ተከስክሰው የምን ያህል ሰዎች ሕይወት ተቀጠፈ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የ346 ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: ዝናሽ ማሞ የት ተወለደች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አዲስ አበባ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፌስቡክ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም እያበለፀገ መሆኑን ከሰሞኑ የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል። ኩባንያው የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም የሚሰራውም ከጎግል አንድርይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም እና ከአይፎን አይ.ኦ.ኤስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ አንደሆነም ታውቋል። አዲሱ የፌስቡክ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ሙሉ በሙሉ ከዜሮ ተነስቶ በራሱ መንገድ እየበለፀገ መሆኑንም ኩባንያው አስታውቋል። ኦፕሬቲንግ ሲስተሙ በምን መልኩ ይሰራል የሚለው ነገር በግልፅ ባይታወቀም የፌስቡክ የቪዲዮ የስልክ ጥሪን ጨምሮ ሌሎች የኩባንያው አገልግሎቶች ግን ተጠቃሚ ይሆናሉ ነው የተባለው። ፌስቡክ አሁን በሚያመርታቸው መገልገያዎች ላይ በብዛት የጎግል አንድሮይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተመን የሚጠቀም ሲሆን፥ ይህም ጎግል በአብዛኛው የፌስቡክ አገልግሎቶች ላይ በበላይነት እንዲቆጣጠር እያደረገ መሆኑ ይታወቃል። ፌስቡክ የራሱን ኦፕሬቲንግ ሲስተም መስራቱም ከጎግል አንድሮይድ ጥገኝነት የሚያላቅቀው መሆኑን እና በሚያመርታቸው መገልገያዎችን ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር ስልጣን እንዲኖረው እንደሚያደርገውም ተገልጿል። ምንጭ፦ www.techworm.net \n \nጥያቄ: ፌስቡክ በአዲሱ የራሱ የኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ምን ምን አካቷል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የቪዲዮ የስልክ ጥሪን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nድረ ገጽ መረብ የድረ ገጽ መረብ (ወይም ኢንተርኔት) በጣም ብዙ የኮምፒዩተር አውታሮችን የያዘ የመገናኛ መረብ ነው። በመረቡ ውስጥ ብዙ ድረ ገጽ ይገኛሉ። ከዚያ በላይ በርካታ የመነጋገርና መገናኘት መንገዶች አሉ። ከሁሉ አስቀድሞ የተፈጠረ ክፍለ-ኢንተርኔት «USENET» የሚባለው አገልግሎት ነው። ይህ በ1973 ዓ.ም. (1980 እ.ኤ.አ.) አካባቢ ሲጀመር በተለይ ለዩኒቨርሲቴዎችና ኮሌጆች ብቻ የታወቀ መገናኛ ሆኖ ቆየ። ይህ ጽሑፍ በተገናኙት ኮምፒውተሮች ላይ መልጠፍ የሚፈቅድ ሥርዓት ብቻ እንጂ ስዕል ወይም ሌላ ነገር አልነበረም። መጀመርያው e-mail አድራሳዎች የተሰጡት ከዚያ ዘመን ነው። ዛሬም ብዙዎች ተጠቃሚዎቹ ግን ስንኳ ስለ USENET መኖሩን አያውቁም። መጀመርያው ድረ ገጽ የተፈጠረው በ1983 ዓ.ም. (1990 እ.ኤ.አ.) ሆነ። \n \nጥያቄ: ድረ ገጽ ተግባር ላይ የዋለው ከመቼ ጀምሮ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1983 ዓ.ም. (1990 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የፐርል በክ የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ ርዕሱ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ East Wind, West Wind ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ የተባለችው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1962 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ የምን ሀገር ሰው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኢትዮጵያዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: ሉሲ በአፋር ክልል የተገኘችው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: የአንጎላ ጦር ሰራዊት ብዛት ምን ያህል ይሆናል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፻፲ ሺህ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nካሣ አያሌው ገና የአራት ዓመት ህፃን ልጅ ሳለ በወቅቱ የትምህርት ገበታን መቋደስ የሚጀመርበት የቄስ ትምህርት ቤት ተልኮ ፊደል መቁጠር ጀምሯል። በዚህ ቆይታው ከፊደል ቆጠራ እስከ ዳዊት ንባብ በአግባቡ ለመማር በቅቷል። በኋላም በጊዜው እንጦጦ አምባ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተብሎ ይጠራ የነበረው ት/ቤት በመዝለቅ ዘመናዊ ትምህርቱን አንድ ብሎ ጀምሯል። ካሣ በዚህ ት/ቤት ሳለ ነበር ውስጡ ከነበረው የህይወት መክሊቱ ጋር የተገናኘው። የሦስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በት/ቤታችን የሚገኘውን ሚኒ ሚዲያ የምቀላቀልበት ዕድል ተፈጠረ። ይህ ዕድል የተገኘው በክፍሌ ውስጥ ተማሪዎች ፊት ቆሜ ጋዜጣ ሳነብ ድንገት ክፍላችን በተገኙት የት/ቤታችን ም/ርዕሰ መምህር አማካኝነት ነው። ስማቸው መምህር ግርማ ይገዙ ይባላል። አነባበቤን አይተው ስለወደዱት እርሳቸው ይመሩት የነበረውን የሚኒ ሚዲያ ክበብ እንድቀላቀል አደረጉ። በዚህ ክበብ ውስጥ ሆኜ በትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮሩ ዜናዎችን እየዘገብኩ ዘወትር ማለዳ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር እየተዘመረ ሰንደቅ ዓላማ በሚሰቀልበት የተማሪዎች ሰልፍ ላይ ማንበብ ጀመርኩ» በማለት ካሣ የጋዜጠኝነት ህይወት መስመሩ አንድ ብሎ የተጀመረበትን ሁኔታ ያስታውሳል። ካሣ አያሌው ካሣ የዘጠነኛ ክፍል ትምህርቱን በእንጦጦ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት /ቲ ኤም ኤስ/ ከጀመረ አንስቶ ሙሉ ትኩረቱን የቀለም ትምህርቱ ላይ አድርጎ ቆይቷል። በዚህ ቆይታው ከማህበራዊ ሳይንስ ይልቅ የተፈጥሮ ሳይንስን ምርጫው አድርጎ ትምህርቱን ተከታትሏል። የአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ አገር ዓቀፍ ፈተና ሲወስድም እንደ ተለመደው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ከፍተኛ ትምህርት የሚሸጋገርበት ዕድል አግኝቷል። በወቅቱ የከፍተኛ ትምህርት ምደባ የሚሰጠው በዕጣ ስለነበር ካሣ በዚህ አመዳደብ መሰረት የኢንጂነሪንግ ትምህርት እንዲማር የአዳማ ቴክኒክ ኮሌጅን እንዲቀላቀል ምደባ ወጥቶለታል። ምደባውን ተከትሎ ወደ አዳማ በማቅናት የቴክኖሎጂ ትምህርቱን መከታተል ቢጀምርም ቅሉ ሁኔታው ምቾት እንዳሳጣውና እንዳሎደደው ካሣ ይናገራል። ካሣ በ2005ዓ.ም ላይ ከፍቅረኛው ሊና ኑር አሕመድ ጋር በጋብቻ የተሳሰረ ሲሆን ቀዳማዊትና ለዕልና የተባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዷል። በትዳር ህይወቱ እጅግ የተሳካለት እንደሆነ በቅርበት የሚያውቁት ጓደኞቹ ይመሰክራሉ። ከስራ ውጪ ያለ ሰዓቱን ሁሉ ከቤተሰቦቹ ጋር ማሳለፍ እንደሚያስደስተው ሁሉም ይመሰክሩለታል። \n \nጥያቄ: ካሳ ስንት ልጆች ወለደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ራስ መኮንን የት ተቀበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሊቢያ ኦይል ሊሚትድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ ሥራ ለማስፋፋት መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ዱባይ ከሚገኘው የሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ ዋና መሥሪያ ቤት ወደ አዲስ አበባ የመጣው ኮርፖሬት ማኔጅመንት፣ ከሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል የአንድ ሳምንት ጉባዔ አካሂዷል፡፡ ከ18 የአፍሪካ አገሮች የሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ የሽያጭና ማርኬቲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካሪያስ ወሊቃ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ማኔጅመንቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ዕድገት በመገምገም ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ እንቅስቃሴ ለማስፋፋት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ካፀደቁት ኢትዮጵያ ውስጥ የ150 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ለማካሄድ አቅዷል፡፡ \n \nጥያቄ: የ18 የአፍሪካ ሀገራት ሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች የተሳተፉበት ውይይት ምን ያህል ጊዜ ቆይታ ነበረው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአንድ ሳምንት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: መባጃ ሐመር መሰረት ተደርጎ የሚጀምሩበት ጊዜ የሚወሰነው አጽዋማት እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመጠነ እንቅፋት የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት (ሬዚስታንስ) የሚባለው አንድ ኤሌክትሪክ አባል በውስጡ ሊያልፍ የሚሞክር የኤሌክትሪክ ጅረትን የሚያደናቅፍበት መጠን ልኬት ነው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት ከሰበቃ ጋር ተመሳሳይ ባህርይ አለው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት የተደረሰበት በ1819 ዓ፣ም በጆርጅ ኦም ሲሆን፤ በዚህ ሰው ጥናት መሰረት የአንድ ነገር ኤሌክትሪካዊ መጠነ እንቅፋት በዚያ ነገር ላይ ያለ የቮልቴጅ ለ በውስጡ የሚያልፍ ጅረት ሲካፈል ጋር እኩል ነው። በሒሳብ ቋንቋ፡ ለብዙ ቁሶችና ሁኔታዎች፣ የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት R ጸንቶ የሚቆይ ቋሚ ቁጥር ነው። ማለት በኤሌክትሪክ ጅረትና በቮልቴጅ መጠን አይቀየርም። እነዚህ ነገሮች ኦማዊ ቁሶች ይባላሉ። የአንድ ሽቦ መጠነ እንቅፋት መጠን በርዝመቱና በስፋቱ ይወሰናል። የሽቦው ርዝመት በጨመረ ቁጥር እንቅፋቱ እየጨመረ ይሄዳል፣ በአንጻሩ ስፋቱ ሲጨምር እንቅፋቱ ይቀንሳል። ልክ ውሃ በሰፊ ቱቦ ውስጥ በቶሎ ሊሄድ እንደሚችልና፣ በረጅም ቱቦ ውስጥ ብዙ ሰበቃ ስለሚገጥመው በቀስታ እንደሚጓዝ ሁሉ። ከዚህ በተጨማሪ የሽቦው መጠነ እንቅፋት ሽቦው ከተሰራበት ዕቃ ተፈጥሮ ጋር ይዛመዳል። ስለሆነም የአንድ ሽቦን መጠነ እንቅፋት በሒሳብ ለማስላት የሚከተለው ቀመር ይጠቅማል፡ ሽቦው የተሰራበት ቁስ ልዩ መጠነ እንቅፋት ሲሆን የሚለካውም በ ኦም-ሜትር ነው። \n \nጥያቄ: የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት በምን ይለካል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ ኦም-ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ሴኔጋልና ጋምቢያ በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ. ባደረጉት ስምምነት የፈጠሩት ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት እስከ ስንተኛ ክፍል ተማረች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: ከመጀመሪያው የአቴና ሕግ ቀጥሎ አዲስ ሕገ መንግሥት የፈጠረው የአቴና አለቃ ማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሶሎን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ ተውኔት መንግስቱ ለማ ምን ብሎ ተርጉሞታለ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዳንዴዎ ጨቡዴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nስታምፎርድ ብሪጅ (የእግር ኳስ ሜዳ) ስታምፎርድ ብሪጅ በፉልሃም ለንደን የሚገኝ የቼልሲ እግር ኳስ ቡድን የእግር ኳስ ሜዳ ነው። የእግር ኳስ ሜዳው የሚገኘው በሙር ፓርክ ኢስቴት (በሌላ አጠራር በዋልሃም ግሪን) ወይም በተለምዶ ዘ ብሪጅ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ነው። ይህ የእግር ኳስ ሜዳ 41,798 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ ከፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ትልቅ የእግር ኳስ ሜዳ ያደርገዋል። የተከፈተው እ.ኤ.አ በ1877 ሲሆን እስከ 1905 ድረስ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ይጠቀምበት ነበር። ሜዳው ብዙ ለውጦችን አካሂዷል። በቅርቡ ደግሞ (እ.ኤ.አ 1990ዎቹ) ወደ ዘመናዊና ለሁሉም ተመልካቾች መቀመጫ ያለው ሆኖ ተሠርቷል። ስታምፎርድ ብሪጅ የተለያዩ የእንግሊዝ ዓለም አቀፋዊ ጨዋታዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ግማሽ ፍጻሜዎችን እና የቻሪቲ ፊልድ ጨዋታዎችን አስተናግዷል። ለተለያዩ ስፖርቶችም እንደ ክሪኬት ፣ ራግቢ ዩኒየን ፣ ስፒድዌይ ፣ ግሬይሃውንድ ሬሲንግ ፣ ቤዝቦል እና የአሜሪካን ፉትቦል ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ጥቅም ላይ ውሏል። የስታዲየሙ ትልቁ ኦፊሲዬላዊ የታዳሚዎች ቁጥር 82,905 ሲሆን ፤ ይህ የሆነው ቼልሲ ከአርሰናል እ.ኤ.አ በኦክቶበር 12 1935 ባካሄዱት የሊግ ጨዋታ ነበር። ስታምፎርድ ብሪጅ ፤ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ስታዲየም ሆኖ እ.ኤ.አ በ1877 ተከፈተ። በዚያ ሜዳ ላይ ታላላቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት የፈለጉ ገስ እና ጆሴፍ ሚየርስ የተባሉ ወንድማማቾች ኮንትራቱን እስካገኙበት ጊዜ ድረስ ለለንደን አትሌቲክስ ክለብ እስከ እ.ኤ.አ 1904 ድረስ አገልግሏል። \n \nጥያቄ: ስታምፎርድ ብሪጅ የየትኛው እግር ኳስ ቡድን ሜዳ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የቼልሲ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አራት ግዙፍ ድመቶች በመባል ከሚታወቁት ውስጥ አንዱ የሆነው አራዊት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አንበሳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ቅኝ ገዢ የነበረችው ፈረንሳይ በመላው ሀገሪቱ ግዛቷን ያስፋፋችው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1850ዎቹ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየፌስቡክ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን የሶስተኛ ወገን የትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም (Third-Party Fact-Checking Program) መጀመሩን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ፕሮግራሙን ካስጀመረባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛምቢያ፣ ሶማሊያ፣ ቡሪኪና ፋሶ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኮትዲቯር፣ ጊኔ ኮናክሪ እና ጋና ይገኙበታል፡፡ ሶስተኛ ወገን የመረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት የሚያስችል እንደሆነ ተነግሯል፡፡ በዚህም የፌስቡክ ተጠቃሚዎች በማህበራዊ ሚዲያው ጥራት ያለው መረጃ የሚያገኙበትን አሰራር የሚያሻሽል እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: የፌስቡክ ኩባንያ ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን ምን አይነት ፕሮግራም አስተዋወቀ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የሶስተኛ ወገን የትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ቱባ ከተማ ምን ያህል ነዋሪ አላት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፭፻ ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: አባይ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተገለጸው ምንጩ ከየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከኤደን ገነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቅልልቦሽ ቅልልቦሽ የኢትዮጵያ ህጻናት በጠጠር የሚጫወቱት ሲሆን አጨዋወቱም አንዱዋን ጠጠር ወደአየር በማጉናት እሱዋ ባየር ላይ እያለች የተቻለን ያክል ጠጠር ከመሬት ማፈስ ነው። ባየር ላይ ያለችው ጠጠር ስትመለስ በተጫዋቹ እጅ \"መቀለብ\" ወይም \"መያዝ\" ይኖርባታል። ሳትያዝ መሬት ላይ ከወደቀች፣ ጨዋታው አለቀ ማለት ነው። ጨዋታው \"ጠጠር\" በመባልም ይጠራል። ብዙ አይነት የቅልልብልቦሽ ጨዋታዎች ሲኖሩ፡ በጣም የታወቀው \"ዓይጥ አለብሽ\" በመባባል የሚጫወቱት ነው። ልጆቹ ሁለት ወይም ሶስት ይሆኑና፡ አምስት ቆንጆ ድብልብል ጠጠሮች፡ ስፋትና ርዝመታቸው ከግማሽ ኢንች የማይበልጡ፡ ይለቅሙና መሬት ይቀመጣሉ። ቀድሞ \"ብጀ\" ያለ መጀመርያ ይጀምራል። ብጀ ማለት ብጀምር ማለት ነው። ያንን ለማለት እሽቅድምድም ነው።\"ብቀ\" ያለ ከርሱ የሚከተል ነው ማለት ነው፡፡ ብቀ ማለት ብቀጥል ማለት ነው። ሁለት ልጆች እኩል \"ብቀ\" ካሉ በድምጽም ቢሆን ቀድሞ \"ብ!\" ከአፉ የወጣው ሰው ሁለተኛነቱን ያገኛል። \"ብቀጣጥል!\" ያለ ሶስተኛ ነው። \"እንጀራ ብጋግር!\" ያለ አራተኛ ነው። አምስተኛ ካለ \"ወጥ ብሰራ!\" ብሎ ተራውን ያሳውቃል። በዚህ ተራ ተስማምተው ጀማሪው ይጀምራል። \n \nጥያቄ: በቅልብልቦሽ ጨዋታ ብቀጣጥል ማለት ምን ማለት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሶስተኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ የሚለው ቃል ምንጩ ከምን ቋንቋ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከዓረብኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ በቆዳ ስፋት ከዓለም ስንተኛ ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 23ኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nናሚቢያ ናሚቢያ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ፣ በስሜን በአንጎላና በዛምቢያ፣ በምስራቅ በቦትስዋና፣ በደቡብም በደቡብ አፍሪቃ ትካለላለች። በ1982 አመተ ምኅረት ነጻነትዋን ከደቡብ አፍሪቃ ስላገኘች በጣም አዲስ አገር ነች። ዋና ከተማዋ ዊንድሁክ ነው። የናሚቢያ በረኅ አውራጃ ከጥንት ጀምሮ በሳን (ቡሽማን)፣ በዳማራና በናማቋ ሕዝቦች ተሰፈረ። በ14ኛው መቶ ዘመን፣ የባንቱ ወገኖች ባስፋፉ ጊዜ አገሩን ሠፈሩ። ክልሉ ግን ከ19ኛው መቶ ዘመን በፊት በአውሮጳውያን አልተዘለቀም። በዚያን ጊዜ ጀርመን ደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ አገሪቱ የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። ዳሩ ግን ዋልቪስ በይ የተባለው ትንሽ ወደብ ብቻ የእንግሊዝ ግዛት ነበር። \n \nጥያቄ: በምስራቅ አቅጣጫ ናሚቢያ በማን ሀገር ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቦትስዋና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዋሽ ብሔራዊ የመዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል በ፲፱፻፶፰ ዓ/ም የተመሠረተ ክልል ሲሆን ከአዲስ አበባ በስተ ምሥራቅ አቅጣጫ በ፪መቶ ፲፩ ኪሎሜትር ርቀት ፤ በአፋርና በኦሮሚያ አዋሳኝ ክልሎች ሥር ይገኛል። ይህ ክልል ሲመሠረት በ ፱፻፮ ካሬ ኪሎሜትር የቆዳ ስፋት (ቦልቶን ፲፱፻፷፰) የነበረው ቢሆንም፤ ባሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ማስረጃ እንዳስቀመጠው የክልሉ የቆዳ ስፋት ፯መቶ ፶፮ ካሬ ኪሎ-ሜትር ነው። የክልሉ ደቡባዊ ድንበር የአዋሽ ወንዝ ሲሆን፣ የተሠየመውም በዚሁ ታላቅ ወንዝ ስም ነው። ክልሉ የብዙ ዓይነት አራዊት እና አዕዋፍ መጠለያ ከመሆኑም ባሻገር ፍል-ውሓ እና የፋንታሌ ተራራ ይገኙበታል። የአገሪቱ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥልጣን ሲመሠረት ለንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በአማካሪነት የተመደበው እንግሊዛዊ ባቀረበው ኃሣብ መሠረት የመጀመሪያው ብሔራዊ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥጣን ከተመሠረተ በኋላ የቅድሚያ ሥራ የተደረገው፤ በታቀዱት ክልሎች የሚገኙትን የአገሪቱን የዱር አራዊት ኃብት መጠን ማረጋገጥ ነበር። ለዚህም ሥራ ከብሪታኒያ ተመልምሎ የተቀጠረው ባለ-ሙያ እንግሊዛዊው የሥነ-ሕይወት ባለሙያ ሜልቪን ቦልቶን ነበር። የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የበርካታ የዱር አራዊት፤ አዕዋፋት እና የውሐ አራዊት መኖሪያ ነው። በደቡብ አዋሳኙ በሆነው የአዋሽ ወንዝ አዞ እና ጉማሬ ሲገኝበት፤ በሰሜን ክፍሉ ደግሞ ጦጣና ዝንጀሮ፤ እንዲሁም ጅብ እና አጋዘን ይገኙበታል። በክልሉ ከሚገኙት የዱር አራዊት በከፊሉ፦ ጉሬዛ፤ ተራ ዝንጀሮ፤ ነጭ ዝንጀሮ፤ ጦጣ፤ ሳላ፤ የሜዳ ፍየል፤ ሚዳቋ፤ ትልቁ የቆላ አጋዘን ፤ አምባራይሌ፤ ከርከሮ፤ ቆርኪ በብዛት የሚገኙ ሲሆን አንበሣ፤ ነብር፤ ጀርባ-ጥቁር እና ተራ ቀበሮ፤ዳልጋ አንበሣ፤ አነር እና የዱር ድመት ደግም አልፎ-አልፎ ይታያሉ። ባለፉት አሥር ዓመታት ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ምዝገባ እንደተረጋገጠው፣ በክልሉ ውስጥ ፬መቶ ፷፪ ዓይነት የወፍ ዝርያዎች ተመዝግበዋል። ከነዚህም መኻል ስድስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ ናቸው። እነዚህም መንቆረ-ጥቁር ጋርደም፤ ግንደ-ቆርቁር፤ ክንፈ-ነጭ የገደል-ቻት፤ ጅራተ-ረጅም ወማይ፤ ቁራ እና ጋጋኖ ናቸው። \n \nጥያቄ: በክልሉ ስድስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙት የወፍ ዝርያዎች ስማቸውን ጥቀስ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ መንቆረ-ጥቁር ጋርደም፤ ግንደ-ቆርቁር፤ ክንፈ-ነጭ የገደል-ቻት፤ ጅራተ-ረጅም ወማይ፤ ቁራ እና ጋጋኖ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን የገዛው የትኛው ኩባንያ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የፈረንሣይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nብጫ ሱማራ ብጫ ሱማራ በ1960 ዓም ዘ ቢተልስ ሙዚቃ ቡድን የሠሩት ዝንኛና ተወዳጅነት ያገኘ የልጆች ካርቶን ፊልም ነበር። በርካታ ዘ ቢተልስ ዘፈኖች በካርቶኑ ሕልም ታሪክ ውስጥ ይሰማሉ። \n \nጥያቄ: ዘ ቢተልስ ሙዚቃ ቡድን የሠሩት ዝንኛና ተወዳጅነት ያገኘ የልጆች ካርቶን ፊልም ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ብጫ ሱማራ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን ስንት ልጆች ነበሩዋቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 4 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: የፓራዳይዝ መጽሐፍ ደራሲ ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አብዱልራዛቅ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: አሪስጣጣሊስ የየት ሀገር ፈላስፋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የግሪክ ፈላስፋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት የጾሙት ጾም ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጾመ ፍልሰታ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: ወጣት ዕበ ለገሠ የሠራው የወርቅ መፈለጊያ ማሽን በስንት ሜትር ጥልቀት ይፈልጋል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአንድ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \n125ኛውን የአድዋ ድል በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለማክበር የባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ሂሩት ካሳው አሶሳ ከተማ ገቡ። በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሌ ሀሰን የተመራው የክልሉ ከፍተኛ አመራርም ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በዓሉም ከዛሬ ጀምሮ በፓናል ውይይት እና ታሪካዊ ቦታዎችን በመጎብኘት እንደሚካሄድ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ማነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አቶ አሻድሌ ሀሰን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከ2009 ዓ.ም ህዳር ወር ጀምሮ ሲዘጋጅ የነበረው አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡ ዝርዝር እቅዱን ለመተግበር ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡ ገንዘቡ በኢትዮጵያ መንግስትና በአጋር ድርጅቶች እንደሚሸፈንም ተነግሯል፡፡ አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ የሚቆይ ነው ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ለሀገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ የሚያስፈልገው ገንዘብ በማን ይሸፈናል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በኢትዮጵያ መንግስትና በአጋር ድርጅቶች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: የፀሓይ ክብደት ከመሬት ጋር ሲነጻጸር ስንት እጥፍ ይበልጣል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 1.3 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: ባቢሎን ለካሣውያን የወደቁት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1507 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የሰጠው የመጀመሪያው ሰሌዳ ቁጥር ስንት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ በ1986 አፍሪካዊ የኖቤል ተሸላሚ ማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዎሌ ሾይንካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የቲቢ በሽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት ምን ያህል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዛሬው ዕለት ኡጋንዳ ገብተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ኡጋንዳ መግባታቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለከተው፡፡ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ባለፈው ጥር ወር ላይ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለ6ኛ ዙር ሀገሪቱን ለመምራት ዛሬ ቃለ መሃላ ይፈፅማሉ። \n \nጥያቄ: ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኔ ጥር ወር ላይ የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያሸነፉት ለስንተኛ ጊዜ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ለ6ኛ ዙር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናይጄሪያ ናይጄሪያ በይፋ የናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ አገር ናት። በሕዝብ ብዛትም ከአፍሪቃ አንደኛ ናት። ከቤኒን ፣ ቻድ ፣ ካሜሩን ፣ ኒጄር ፣ እና ከጊኒ ባሕረ ሰላጤ ጋር ድንበር ትካለላለች። በናይጄሪያ ውስጥ ትልቁ ብሔሮች ሀውዛ ፣ ኢግቦ እና ዮሩባ ናቸው። ግማሹ ሕዝብ እስላም ሲሆን ሌላው ግማሽ ደግሞ የክርስትና እምነት ይከተላል። ትንሽ የሕዝቡ ክፍልም ባህላዊ ሃይማኖቶችን ይከተላል። የሳይንስ ጥናት እንደሚያሳየው ናይጄሪያ ከ፱ሺህ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ ነዋሪዎች እንደነበሩባት ያሳያል። በቤንዌ እና ክሮስ ወንዞች አካባቢ ያለው ሥፍራ የባንቱ ፍልሰቶች መነሻ እንደ ነበረ ይታመናል። የናይጄሪያ ስም ከኒጄር ወንዝ ነው የተወሰደው። ናይጄሪያ በአፍሪካ በሕዝብ ቁጥር አንደኛ ስትሆን ከዓለም ደግሞ ሰባተኛ ናት። የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በዓለም ላይ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። የዓለም አቀፍ ገንዘብ ፈንድ እንደሚገምተው የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በ2011 እ.ኤ.አ. በ8% ያድጋል። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ ስያሜዋ የተወሰደው ከምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከኒጄር ወንዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በ1923 ዓ.ም. ታውጆ የነበረው ሕገ መንግሥት እስከ መቼ አገልግሎት ላይ ዋለ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እስከ 1948 አ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና ከልብ-ወለድ ደራሲነት በተጨማሪ እውቅናን ያተረፈችው በምንድነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: እቴጌ ጣይቱ በስንት ዓ.ም. ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nከአድዋ ሽንፈት በኋላ ጣሊያኖች ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራርመው አዲስ ገዢ፣ ፈርዲናንዶ ማርቲኒ፣ 1897 ላይ በመሾም ግዛታቸውን ማጽናት ጀመሩ። በዚህ ወቅት የቀደመው ወታደራዊ ስርዓት እንዲቋረጥ ተደርጎ አገሪቱ የብሔር ልዩነትን \"በሚያከበር\" አስተዳደር ተከፍሎ እንዲቋቋም ተደረገ። ዳህላክ፣ አፋር እና ሰምሃር አንድ ላይ \"ምስራቃዊ ክፍል\" ተብለው ከምጽዋ እንዲተዳደሩ ተደረገ። \"ምዕራባዊ ክፍል\" ከአቆርዳት እንዲተዳደር ሲደረግ ቤኒ አሚርን፣ ናራንና ኩናማ ምድርን ያጠቃልል ነበር። ከከረን ሆኖ የሚተዳደረው ደግሞ ሰሜናዊ ሐማሴን (የእስልምና ተከታይ የሆነ)፣ ቤት አሰገደና ዓድ ሼኽ ነበሩ። ቀሪው ሐማሴን ከአስመራ፣ ሰራየ ከመንደፈራ(አዲ ወግሪ) እንዲተዳደር ሲደረግ አካለ ጉዛይ ከሳሆ ጋር ተዋህዶ ከአዲ ቀይሕ ይገዛ ጀመር። ከላይ ወደታች በተዘርጋ መዋቅር የጣሊያን ባለስልጣኖች እያንዳንዱን ክፍል ያስተዳድሩ ጀመር። የአገሪቱ ዋና ከተማ ከምጽዋ ወደ አስመራ የተዛወረው በዚህ ወቅት፣ በ1898 ነበር። ከ1898 እስከ 1908 በተደረጉ ውሎች (ከኢትዮጵያ፣ ከአንግሎ-ግብጻዊ ሱዳንና ከጅቡቲ ጋር) መሰረት የቅኝ ግዛቱ ድንበር ታወቀ። ኢትዮጵያን ስለ ድንበሩ ለማሳመን 3 አመትና 5ሚሊዮን ሊሬ ፈጅቶባቸው ግንቦት 1900 ላይ ያሰቡት ሊሳካላቸው ቻለ። ድንበሩ ከሞላ ጎደል የመረብ፣ በለሳና ሙና ወንዞችን የታከከ ነበር። \n \nጥያቄ: አስመራ የኤርትራ ዋና ከተማ የተደረገችው መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1898 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ዚምባቡዌያውያን ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ንግድ የጀመሩት መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 10ኛው ክፍለ-ዘመን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: የኮንግ-ፉጸ ትምህርትን የማን ሥርወ መንግሥት ይፋ አደረገው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሃን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን የባችለር ሳይንስ ዲግሪውን ያገኘው ከየትኛው ዩኒቨርሲቲ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ታኅሣሥ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲፯ ዓ/ም በአንዲት “ብርሃንና ሰላም” በተሰኘች አነስተኛ ጋዜጣ ሕትመት ሥራውን ጀመረ። በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መጻሕፍት ፣ ጋዜጦች ፣ መጽሔቶችና የምስጢራዊ ሕትመት ሥራዎች በተለያዩ ቋንቋዎች እያተመ ይገኛል። ማተሚያ ቤቱ በርካታ የመንግሥት እና የግል ጋዜጦችን የሚያትም ሲሆን ፥ በተጨማሪም በየዓመቱ በርካታ የፈተና ሥራዎችን በማተም ይታወቃል። ጥንታዊ ኢትዮጰያውያን ሊቃውንት የሚጽፏቸው መጻሕፍት ለሕዝብ የሚቀርቡት ብራና ተፍቆ ፣ ቀለም ተቀምሞ በእጅ ተፅፎ ነበር። በዳግማዊ ምኒልክ ዘመነ-መንግሥት የተጀመረው የዘመናዊ ሕትመት ሥራ በሀገሪቱ ቁጥራቸውና መጠናቸው በርከት ያሉ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች፣ መጻሕፍት፣ እንዲሁም ሌሎች የሕትመት ውጤቶች መታተም በመጀመራቸው የትምህርትና የሥልጣኔ መሰፋፋት ላይ የበኩሉን ሚና መጫወት ጀመረ። የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትም ምሥረታ ዋና ዓላማ የአገሪቱን መንፈሳዊ መጻሕፍት በብዛት እና በዘመናዊ መልክ ከእጅ ጽሑፍ ወደ ሕትመት ለማሸጋገር ሲሆን፤ ምሑሩ ተክለጻድቅ መኩሪያ (፲፱፻፷፩ ዓ/ም)፣ ማተሚያ ቤቱ መስከረም ፫ ቀን ፲፱፻፲፬ ዓ/ም መቋቋሙን እና ብዙ ሥጋዊና የመንፈሳዊ መጻሕፍት እንዲሁም ምክርና ተግሣጽ፣ የለት ወሬ፣ የሹም-ሽር አዋጆችን ያትም እንደነበር ዘግበዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ረዳት መምህር መኩሪያ መካሻ፤ “የፕሬስ ታሪክ” በተሰኘ ጽሑፋቸው ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ፣ ራስ ተፈሪ መኮንን በ፲፱፻፲፫ ዓ/ም የማተሚያ መሣሪያ አስመጥተው “ትንሹ ግቢ” (በኋላ ገነተ ልዑል — አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ) ይባል በነበረው መኖሪያቸው ውስጥ አስተክለው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት የተባለውን እንደመሠረቱ ዘግበዋል። ከሁለት ዓመት በኋላ በ፲፱፻፲፭ ዓ/ም አራት ተጨማሪ ማተሚያዎች ተገዝተው ከተተከሉ ከአንድ ዓመት በኋላ ሣምንታዊው ‘ብርሃንና ሰላም’ የተሰኘው ጋዜጣ እየታተመ፣ አስቀድሞ በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን ከተጀመረችው ‘አዕምሮ’ ጋዜጣ ጋር እስከ ጠላት ወረራ ዘመን ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ይሠራጩ ነበር። የወቅቱ ማተሚያ መሣሪያዎች በእግር እየተረገጡ የሚንቀሳቀሱ መሣሪያዎች ሲሆኑ የሠራተኞቹ ቁጥር ከሰባት እስከ አሥራ-ሁለት እንደነበር ተዘግቧል። ራስ ተፈሪም አልፎ-አልፎ በብርሃን እና ሰላም ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ይረዱ እንደነበረና ጽሑፎቻቸውንም ለሕትመት ያበቁ እንደነበር ተምዝግቧል። \n \nጥያቄ: ጥንታዊ ኢትዮጰያውያን ሊቃውንት መጻሕፍት የሚጻፈው እንዴት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ብራና ተፍቆ ፣ ቀለም ተቀምሞ በእጅ ተፅፎ ነበር። ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: ኦሮሚኛና ሱማሊኛ ቋንቋ በምን መደብ ይካተታሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኩሻዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበኢትዮጵያ የተለያዩ የቤተሰብ ሕግጋት ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ሕግጋት በሰው ፊት ዋጋ ያለው ግንኙነት የሚፈጠርበትን ጥምረት በተለያየ መንገድ ይደነግጋሉ፡፡ በቤተሰብ ሕግ ዕውቅና የተሰጣቸው የተቃራኒ ፆታዎች ጥምረት ሦስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያውና ዋናው ጋብቻ ሲሆን፣ አሥራ ስምንት ዓመት የሞላቸው ወንድና ሴት ጥንዶች ለዘለቄታው አብረው በትዳር ለመኖር በማሰብ የሚመሠርቱት ተቋም ነው፡፡ ይህ ተቋም በሕገ መንግሥቱ ዕውቅና የተሰጠው ሲሆን፣ ወጣቶች በሕጉ የተቀመጡትን የዕድሜ፣ የፈቃድና የዝምድና ሁኔታዎችን ካከበሩ ሊመሠርቱት የሚችሉት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ጥምረት በክብር በመዝገብ ሹም ፊት፣ በሃይማኖት ሥርዓት ወይም በባህል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ሁለተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው ጥምረት፣ ጋብቻ ሳይፈጸም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ነው፡፡ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድና አንዲት ሴት በሕግ በሚጸና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈጽሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ግንኙነት አለ የሚባለው ሰዎቹ እንደተጋቡ ዓይነት ሰዎች ዓይነት አኗኗር ማሳየታቸው እንደሆነ እንጂ በታወቀና በተደጋገመ ሁኔታ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸማቸው ብቻ አለመሆኑ በሕጉ በግልጽ ተመልክቷል፡፡ ሦስተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው መተጫጨትን ነው፡፡ መተጫጨት በተወሰኑ የክልል የቤተሰብ ሕግጋት ዕውቅና የተሰጠው እጮኛውና እጮኛይቱ ለወደፊት በመካከላቸው ጋብቻ ለመፈጸም የሚያደርጉት ስምምነት ነው፡፡ መተጫጨት ወደፊት በሚጋቡት ሰዎች ነፃ ፈቃድና ስምምነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚቆይ ጥምረት ነው፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ቤተሰብ ሕግ መሰረት እውቅና ያገኘው የተለያዩ ጾታዎች ጥምረት ስንት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሦስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን የትውልድ ስፍራው ማን በመባል ይታወቃል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ በስንት አመቱ ነበር ከዚህ አለም በሞት የተለየው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ19 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: የአብርሃም ሊንከን የስራ ዘርፋቸው ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሕግ ባለሙ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ አነሳሽነት በ12ኛው ክፍለ ዘመን በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ የተሰራ ቤተክርስቲያንና በዚያው ዋሻ ውስጥ ከቤተርክስቲያኑ ፊትለፊት ያለ ቤተ መንግስት ህንጻ በአንድነት የሚጠሩበት ስም ነው። ዋሻው ከላሊበላ የ6 ሰዓት የእግር ጉዞ ርቀት ላይ ይሚገኝ ሲሆን 45ሜትር ርዝመት በ6 ሜትር ቁመትና 50ሜትር ጉድጉደት አለው። በዋሻው ውስጥና ውጭ ለጸበል የሚያገለግሉ ምንጮች ይፈልቁበታል። ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ ከሮሃ ሆኖ አገሩን ያስተዳድር እንጂ ይሄው ቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ሲታነጽ መኖሪያውን ወድዚህ ዋሻ እንዳዛወረ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ የህይወት ታሪኩ ይገልጻል። የቤተክርስቲያኑ ህንጻ 3 መግቢያዎች ሲኖሩት በሰሜን(ለወንዶች)፣ ደቡብ(ለሴቶች) እና ምሥራቅ (ለካህናት) ይገኛሉ። በግድግዳው ላይ የሚገኙ፣ ነገር ግን በአቧራ የተሸፉኑት ምስሎች ከዚሁ ዘመን የሚመነጩ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የግድግዳ ምስላት ቀደምት ናቸው። ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ይህን ቤተክርቲያን በ16ኛው ክፍለዘመን መግቢያ ላይ የጎበኘው ሲሆን፣ እንደርሱ ዘገባ በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኑ 200 ደብተራዎች የነበሩት ሲሆን አጠቃላይ ቤቱ በሊቀ ካህናት ይመራ እንደነበር ሲጠቅስ፤ በወቅቱ መነኮሳት እንደማይኖሩበትም ዘግቧል። ከይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ጀርባ 3 መቃብሮች ሲኖሩ፣ የራሳቸው የዓፄ ይምርሃነ፣ የሴት ልጃቸው እና ከእስክንድርያ ንጉሱን ሊጠይቁ የመጡ ፓትሪያርክ እንደሆኑ ይጠቀሳል። ወደዋሻው ውስጥ በጣም ርቆ ደግሞ የብዙ ምዕመናን አጽም የሚታይበት ሰፊና ጨለማ ክፍል አለ። \n \nጥያቄ: ዋሻው በምን አይነት ጉዞ ነው ከላሊበላ 6 ሰአት የሚፈጀው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የእግር ጉዞ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: የአስትኖሚካል ሲምፖዚየም መድረክ ምን አይነት ትስስር ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \n67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ አንጋፎቹ ገጣሚያን ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ዶ/ር ሙሉአለም ተገኝወርቅ፣ መርድ ተስፋዬና ቤዛ ትዕዛዙ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ዲስኩር እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ \n \nጥያቄ: በ67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት ላይ አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ ምን ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አጭር ተውኔት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በ84ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ላይ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የአባት አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተገኝተዋል። በሰመዕታት መታሰቢያ ቀን የካቲት 12 ቀን በየአመቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፤አባት አርበኞች፤ እና የህብረተሰብ ክፍሉ በስድስት ኪሎ ታስቦ ይውላል፡፡ \n \nጥያቄ: በስንተኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ በዓል ላይ ነው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ የተገኙት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ84ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: የኃይሌ ገብረሥላሴ የትውልድ ሥፍራ የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ቅኝ ገዢ የነበረችው ሀገር ማን ነበረች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፈረንሣይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ጋሊሊዮ በቴሌስኮፕ የታገዘ የፀሓይ ምርምር የጀመረው መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ17ኛው ምእት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ በምእራብ አቅጣጫ የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በአዳማ ሳይንስ ቴክኖሎጂ የባህል መድኃኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ ኢንዱስትሪ ለማስገባት እየሰራ ያለው የትኛው ክፍል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በ1923 ዓ.ም. ጀምሮ ሲያገለግል የነበረው ሕገ መንግሥት መች ተሻሻለ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1948 አ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: የአባይ ወንዝ ምንጭ ሀገር ማናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቴምፕላርስ ቴምፕላር ወይም በሙሉ ስማቸው የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች የሚባሉት በጣም ታላቅ እና ሃይለኛ ከነበሩት ክርስቲያናዊ ወታደራዊ ስርአቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው። ይህ ስርዓት በ1088 ዓ.ም. ከተካሄደው አንደኛው የመስቀል ጦርነት በኋላ ማለትም በ1110 ዓ.ም. አዲስ የተቋቋመውን የእየሩሳሌም መንግስት ከእስላሞች ለመከላከልና ወደ ከአውሮፓ ወደ እየሩሳሌም የሚጎርፉትን ተሳላሚዎች ደህንነት ለመጠበቅ የተመሰረተ ነው። ቴምፕላሮች የተዋቀሩት በገዳማዊ ስርዓት ሲሆን ይኸውም የሲሰተርሲያን ስርዓት መስራች የነበረው የክላርቮው በርናርድ በዘረጋላቸው ህግጋት መሰረት ነው። ቴምፕላሮች ከብዙ መሳፍንት ጋር ግንኙነት ስለነበራቸው እና ጳጳሱም እነሱ ከሚቆጣጠሩዓቸው ቦታዎች ሁሉ ግብርና አስራት እንዲሰበስቡ ስለፈቀደላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝነኛና ሃይለኛ ለመሆን ችለዋል። ቴምፕላሮቹ አራት ዋና ክፍሎች የነበሩአቸው ሲሆን እነዚሁም ዋነኞቹ ወታደሮች ወይም ናይትስ የሚባሉት ሙሉ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ከዝቅተኛ የህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡት ወይም ሰርጀንትስ በመባል የሚታወቁት፤ መለስተኛ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ገበሬዎች ዋነኛው ስራቸው የስርዓቱን ንብረት ማስተዳደር የነበረ፤ እንዲሁም ካህናት ስራቸው የስርዓቱን መንፈሳዊ ህይወት መከታተል የነበረ ናቸው። \n \nጥያቄ: የቴምፕላርስ በሌላ ስማቸው ምን ተብለው ይታወቃሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዛሬው ዕለት ኡጋንዳ ገብተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ኡጋንዳ መግባታቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለከተው፡፡ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ባለፈው ጥር ወር ላይ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለ6ኛ ዙር ሀገሪቱን ለመምራት ዛሬ ቃለ መሃላ ይፈፅማሉ። \n \nጥያቄ: ለ6ኛ ዙር ኡጋንዳን ለመምራት ዛሬ ቃለመሀላ የፈፀሙት ማናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዮዌሪ ሙሴቬኒ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: የኃይሌ ገብረሥላሴ የልደት ቀኑ መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኮንታ የኮንታ ብሔረሰብ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ኮንቲኛ ሲሆን፣ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ከንግግር ቋንቋነት ባሻገር የትምህርትና የሥራ ቋንቋ በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አብዛኛው የብሔረሰቡ አባላት ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ዳውሮኛ፣ ጋሞኛ፣ ወላይትኛና አማርኛ ይናገራሉ። የኮንታ ብሔረሰብ ባህላዊ አስተዳደር መዋቅር ተዋረዳዊ ኃላፊነትና ተግባር ባላቸው የተለያዩ ክፍሎች የተደራጀ ነው፡፡ በእዚህ መዋቅር የሁሉም የበላይ ካዎ ወይም ንጉስ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ከማላ ጎሳ ይመረጣል፡፡ በኮንታ ብሔረሰብ ስድስት ባህላዊ የጋብቻ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህም በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ቦሣ) የለፋ ጋብቻ (ላታ) በተጋቢዎች ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ማቆ) የቃል ጋብቻ (ያኤኤኩዎ) እና ሚሽቶ (የምትክ ጋብቻ) በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ ዓይነቶች በብዛት ሲከናወን የሚስተዋለው በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸመው የቦሣ ጋብቻ ነው፡፡ ከብሔረሰቡ ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ፂፄ፣ ጫቻ፣ ዛይ፣ዲንኬ እና ኡልዱዶ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ የትንፋሽና የምት የሙዚቃ መሣሪያዎች ለለቅሶና ለደስታ ጊዜ ያገለግላሉ፡፡ በተለይ ኡላዱዶ የተሰኘው የትንፋሽ መሣሪያ ከድኩላ ቀንድ ተበስቶ የሚሠራ ሲሆን ከብቶቻቸው ሆራ (ጨውነት ያለው ውሃ) ሊያጠጡ የሚወስዱ እረኞች ይነፉታል፡፡ የኮንታ ባህላዊ የቤት አሠራር ከፍልጥ እንጨት፣ ከቀርከሀ ከሰንበሌጥና ከሣር የሚዘጋጅ ሲሆን በደጋውና በቆላው አካባቢ ልዩነት አለው፡፡ ሱልሶ፣ ሲሊሶ፣ ኡስታ፣ ጨዲያ፣ ኩበዋ፣ ቦሩዋ (ዱቢያ) እና ባጨራ የኮንታ ብሔረሰብ ዋነኛ ባህላዊ ምግቦች ናቸው፡፡ ሲልሶ ለአብነት ከምን እንደሚሠራ እንይ፡፡ ሲልሶ ከጥሬ ሥጋ፣ ከቅቤ፣ ከደም፣ ከሀሞት እና ከተለያዩ የማጣፈጫ ቅመሞች ከተዘጋጀ በኋላ ከተለበለበና በክብ በተቆረጠ የእንሰት ቅጠል ላይ ለቤተሰቡ አባላት ይቀርብና በቡላ ወይም በቆጮ ይበላል፡፡ በብሔረሰቡ ወንዶች ከአቡጀዲ በእጅ የተሰፋ እጀ ጠባብ ሸሚዝና ሱሪ እንዲሁም ሀሲያ የተባለ በእጅ የተፈተለ ልብስ ሲለብሱ ሴቶች በኋላ በኩል ባለወጥ ጥለት የሆነውን ማዳ የተባለ የእጅ ፈትል ይለብሳሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የኮንታ ብሔረሰብ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኮንቲኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል። ባለፈው አመት የመጠቀችው “ETRSS-1” የሚል ስያሜ የተሰጣት ምድርን እየቃኘች ፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው ሳተላይት በሀገራችን የዕድገት ጉዞ ላይ ቁልፍ ሚና እንደሚኖራት መነገሩ አይዘነጋም። መረጃ መላክ የጀመረችው ይች ሳተላይት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ አሁን ደግሞ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን ነው ኢንስቲትዩቱ ያስታወቀው። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በ2013 ምን የምትባለዋን ሳተላይት አመጠቀች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ET-Smart-RSS ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል ጋብቻ የመሰረቱበት ዓመት መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማርኮ ፖሎ ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ 600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል። ይህ ተጓዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል። በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል። \n \nጥያቄ: ወደ ሞንጎሊያና ቻይና ከተጓዙ አውሮፓውያን ቀደምት የሆነው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ማርኮ ፖሎ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የአክሱም ግዛት የመንን ያካትት የነበረበት ጊዜ መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፮ኛው ምእት ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መቼ ተከፈተ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1957 አ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፄ ይስሐቅ ቀዳማዊ አጼ ይሥሓቅ በዙፋን ስማቸው \"ዳግማዊ ገብረ መስቀል\" ሲባሉ እ.ኤ.አ ከ1414-1429 የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የነበሩ ናቸው። የቀዳማዊ አጼ ዳዊት ሁለተኛ ወንድ ልጅ ሲሆኑ የቀዳማዊ ቴዎድሮስ ታናሽ ወንድም ናቸው። ከአክሱም ነገሥታት በኋላ የመጀመሪያውን ከአውሮጳውያን መሪወች ጋር ግንኙነት ያደረገው ይሄው ንጉስ ነበር። ለምሳሌ ለአራጎን መሪ ለነበርው አልፎንሶ አምስተኛ በ1428 ዓ.ም. በእስላሞች ላይ የተባበረ ሃይልን ለመመስረት ደብዳቤ ልኳል። በዚሁ ደብዳቤ የጋብቻን ነገር ያወሳ ሲሆን ህጻኑ ዶን ፔድሮ ከእጅ ጥበብ አዋቂወች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የይስሓቅን ሴት ልጅ እንዲያገባ ያትታል። አልፎንሶ ለይስሓቅ የመለሰለት ደብዳቤ ባይገኝም ለይስሓቅ ተከታ ለአጼ ዘርዓ ያዕቆብ በ1450 በደረሰ ደብዳቤ ደህንነታቸው እስከተጥበቀ ድረስ እጅ ጥበበኞችን በደስታ ወደኢትዮጵያ እንደሚልክና ከአሁን በፊት የላካቸው 13 ጥበበኞቹ በመንገድ ላይ እንደጠፉ ሳይጠቅስ አላለፈም። በኒሁ ንጉስ ዘመን በፈላሾች በተነሳ አመጽ ምክንያት ንጉሱ ወደወገራ ዘምተው አመጸኞቹን ኮሶጌ ላይ በማሸነፍ አመጹን አረገቡ። በዚያውም ደብረ ይሥሓቅ የተሰኘውን ቤተክርስቲያን ለድሉ ማስታወሻ ኮሶጌ ላይ አሰሩ። . ንጉሱ ተመልሰው ከአገው ምድር ባሻገር ያለውን የሻንቅላ ምድር ላይ ዘመቻ አካሂደዋል። በደቡብ ምስራቅ ደግሞ ከአረብ አገር የተመለሱትን የሳድ አዲን ፪ኛ ልጆች ወግተዋል። ታሪክ አጥኝው ታደሰ ታምራት ይስሓቅ ከመስሊሞች ጋር ሲዋጋ ወደቀ ይበል እንጂ ዋሊስ በድጅ በርግጥም በወንጀል እንደተገደለና በተድባባ ማርያም እንደተቀበረ ይናገራል። \n \nጥያቄ: አፄ ይስሐቅ ያሰሩት ደብረ ይሥሓቅ የሚባለው ቤተክርስቲያን በየት ተሰራ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኮሶጌ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የሆነው የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም በአሜሪካ ዶላር ላይ እና ፓስፖርት ላይ መታየት የጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን የባችለር ሳይንስ ዲግሪውን መቼ አገኘ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማይክሮሶፍት በዊንዶውስ 10 የመተግበሪያ ስርዓት አጋጥሞ የነበረውን ችግር መፍታቱን አስታወቀ። በርካታ ተጠቃሚዎች መተግበሪያው ከትናንት ጀምሮ መስራት ማቆሙን ገልጸው ነበር። ተጠቃሚዎች እንደገለጹት በዴስክቶፕ መረጃ መፈለጊያ ትዕዛዝ ሲጠይቁ የሚፈልጉትን ነገር ከማግኘት ይልቅ ባዶ ሳጥን ያገኙ ነበር። ኩባንያውም የተጠቃሚዎችን ሪፖርት ካገኘ ከሰዓታት በኋላ የብዙ ተጠቃሚዎችን ችግር መቅረፍ መቻሉን አስታውቋል። ይሁን እንጅ አሁንም አንዳንድ ተጠቃሚዎች ኮምፒተሮቻቸውን እንደገና ማስጀመር ወይም ሪስታርት ማድረግ ሊያስፈልጋቸው ይችላል ብሏል። ኩባንያው ምን ያህል ሰዎች ይህ ችግር እንዳጋጠማቸው ግን ያለው ነገር የለም፡፡ ዊንዶውስ 10 መተግበሪያ ሥርዓት በዓለም ዙሪያ 800 ሚሊየን የሚሆኑ ተጠቃሚዎች አሉት። \n \nጥያቄ: የዊንዶውስ ሶፍትዌር አምራች ድርጅት ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማይክሮሶፍት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ለሁለት ሣምንት የሚጾመው ጾም ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጾመ ፍልሰታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ የተወለደበት ቦታ ቀድሞ በየት ክፍለ ሃገር ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አርሲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ለመጀመሪያ ጊዜ ጾመ ፍልሰታን የጾሙት እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሐዋርያት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የዓለም ጤና ድርጅት በቲቢ በሽታ የሚያዙ ሰዎችን በ2032 ወደ ስንት ለመቀነስ አስቧል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ100 ሺህ አስር ብቻ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጁፒተር እና ሳተርን ጁፒተር እና ሳተርን ከ4 መቶ አመት በሆላ ትላንት ምሽት በአንድ ላይ ገጥመው አንድ ፕላኔት መስለው ታይተዋል፡፡ ፕላኔቶቹ ከቀን ቀን እየተቀራረቡ መጥተው ትላንት ምሽት በአንድ ላይ በመግጠም ደማቅ ብርሃን ፈንጥቀዋል፡፡ የሁለቱ ግዙፍ ፕላኔቶች ምህዋር በየ20 ዓመቱ የሚገናኙ ሲሆን ክስተቱ በብዛት በቀን ውስጥ ስለሚሆን በዓይን ለማየት ከባድ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ‘ዘ ስታር ኦፍ ቤቴልሄም’ ወይም የቤቴልሄም ኮከብ ተብሎ በሚጠራው በዚህ ክስተት ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ሰማይ ላይ እጅግ ደማቅ ብርሃን ታይቶ እንደነበር ሳይንቲስቶች መናገራቸውን ዘ ጋርዲያን አስነብቧል፡፡ \n \nጥያቄ: በየ20 አመቱ በመግጠም አንድ የሚሆኑ ፕላኔቶች እነማ ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጁፒተር እና ሳተርን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመርያው ሦስት ወራት፣ ከ12.2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ቢሮው እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ የሚዘልቅ ግብር የማሳወቅና የመሰብሰብ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጾ፣ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጨረሻ ሳምንት ባለው ጊዜ ከግብር አሰባሰቡ የተገኘው ገቢ ከታቀደው በላይ እንደሆነ አስታወቋል፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊነትን አዲስ በተመረጠው የከተማ አስተዳደር እንዲመሩ በድጋሚ የተመረጡት አቶ ሙሉጌታ ተፈራ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ ገቢዎች ቢሮው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የተጀመሩትን የከተማዋን ገቢ በተጠናከረ ሁኔታ የመሰብሰብ ሥራ ዘመናዊ በሆነ ሥርዓትና ቅንጅታዊ አተገባበር እየተከናወነ ነው፡፡ በተያዘው በሩብ ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ የታቀደው የግብር ገቢ 11.5 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ያስታወቁት ኃላፊው፣ ከሦስት ያላነሱ ቀናት የገቢ አሰባሰብ መረጃ ሳይካተት እስከ መስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ 12.26 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየሆሊውዱ የፊልም ኩባንያ ዋርነር ብሮስ የቦክስ ኦፊስን የደረጃ ሰንጠረዥ በሰው ሰራሽ መሳሪያ (አርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ) መገመት ሊጀምር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ሰው ሰራሽ መሳሪያው ዋርነር ብሮስ የሚያዘጋጃቸው ፊልሞች ምን ያህል ስኬታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ ግምቱን ያስቀምጣል ተብሏል፡፡ ይህ አሰራር የተዋናይ አመራረጥን፣ የማከፋፈሉን ሂደት እና የሚለቀቅበትን ጊዜ መነሻ በማድረግ ትርፋማነቱን ይገመግማል ነው የተባለው፡፡ በሆሊውድ መንደር ከስድስት ትልልቅ የፊልም ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ዋርነር ብሮስ ይህን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ከኤልኤ ስታርት አፕ ሲኔለይቲክ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ የመገመቻ መሳሪያው ባለፈው ዓመት ይፋ የሆነ ሲሆን ለዘርፉ አዲስ ይዘት እና አሰራርን ይዞ መምጣቱ ሲኔለይቲክ በድረ ገፁ አስነብቧል፡፡ መሳሪያው የተለያዩ መረጃዎችን በመጠቀም የቦክስ ኦፊስ የደረጃ ሰንጠረዥን በትክክል እንደሚገምት ተጠቁሟል፡፡ አንዱ የዚህ መሳሪያ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ተዋንያን የሚመርጡበት ሂደት እንዴት በፊልሙ ትርፋማነት ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር መመልከት እንዲችሉ ያደርጋል ነው የተባለው፡፡ ምንጭ፡-ስካይ ኒውስ \n \nጥያቄ: ዋርነር ብሮስ በአርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ መሰረት ያደረገ የቦክስ ኦፊስን ደረጃ ሰንጠረዥ መገመቻ መሳሪያ ለማሰራት የተዋዋለው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከኤልኤ ስታርት አፕ ሲኔለይቲክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ ጡረታ ከወጡ በኋላ ምን በማድረግ ጊዜቸውን ያሳልፉ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በማንበብ እና በምርምር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ አንበሶች ምን ያደርጋሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ያገሣሉ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: የኤዎስጣጤዎስ ተከታዩች እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል። ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማራያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል። ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ ይኖራል። አልፎም በግራኝ አህመድ ዘመን በእሳት ጋይቶ የነበረችውን አክሱም ፂዮን በአዲስ መሰረት እንደገና ማሰራት ችሎአል። ፋሲለደስ በዘመኑ እጅግ ተወዳጅ ንጉስ ቢሆንም አመጽ መነሳቱ አልቀረም። በላስታ ለምሳሌ በ1637 መልክዓ ክርስቶስ በተባለ ሰው መሪነት ጦርነት ተነስቶ አፄ ፋሲልን ስጋት ላይ ቢጥልም በሚቀጥለው አመት በተደረገው ጦርነት አመፁ ሊገታ ችሎአል። ፋሲለደስ ፖርቱጋሎችን ቢያባርርም ከውጭው አለም ጋር ብዙ ግንኙነት ያደርግ ነበር። ለምሳሌ በ1664-5 የህንድ ንጉስ አውራንግዘብ ሲነግስ መልካም ምኞትን በመልክተኞቹ ለሙግሃሉ መሪ ልኮ ነበር። በ1666 ልጁ ዳዊት ሲያምጽ፣ ወህኒ ተብሎ ወደሚታወቀው አገር በግዞት ልኮት ነበር። ይህም ከጥንቶቹ የኢትዮጵያውን ነገሥት ተፎካካሪያቸውን ወደ አምባ ግሽን በግዞት እንደሚልኩት ስርዓት ነበር። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲል በ1664-5 ማን የተባለው የህንድ ንጉስ ሲነግስ መልካም ምኞታቸውን ገለጹ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አውራንግዘብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ ኢትዮጵያዊው ሊቅና ጻድቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ የተወለዱት በ፲፫፻፶፯ ዓ.ም. በወሎ ክፍለ ሀገር በቦረና ወረዳ ሸግላ/ሰግላ በተሰኘች ቦታ ነው። አባታቸው ሕዝበ ጽዮን ከተከበሩ መምህራን ወገን የሆኑ የቤተ መንግሥት ባለሟል ፤ መጽሐፍትን የሚያውቁ ጥበብ የተሞሉ ሲሆን የሰግላ አገረ ገዢም ነበሩ ። እናታቸው እምነጽዮንም ከወለቃ ሹማምንት ወገን የሆኑ ደግ ሰው ነበሩ። ሲጀመር እናታቸው ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማሩ በጥበብና በዕውቀት አሳደጓቸው ። አባ ጊዮርጊስ የተመረጠ የሆነ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በመማፀን የተወለዱ ልጃቸው ስለሆኑ እንደሰማዕቱ የእውነት ምስክር እንዲሆኑላቸው በመመኘት ስማቸውን ጊዮርጊስ ብለው ጠርተዋቸዋል ። ከተወለዱበትም ሀገር በመነሳት ጊዮርጊስ ሰግላዊ ተብለው ሲጠሩ በጊዮርጊስ ዘጋስጭና በጊዮርጊስ ሰግላዊ መካከል ምንም ልዩነት የለም። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ እንደ ሰማዕት ግርፋትንና እሥራትን የተቀበሉ ፣ እንደ ሊቃውንት የመናፍቃንና የከሀድያንን ክርክር የረቱ ፣ እንደ መሐንዲስ ሐናጺ ፣ የሕግና የሥርዐት የሚስጥራትና የትርጉዋሜያት መምህር ፣ የጸሎትና የትምህርት መጻሐፍት ደራሲ ፣ የሥርዓተ ገዳምና ማኅበረ መነኰሳት አባት እንዲሁም ቢያንስ የአንድ ትምህርት መሥራች ሲሆኑ በግዞት በሄዱባቸውና በታሰሩባቸው ቦታዎችም ሆነ በተሾሙባቸው እንደ ደብረዳሞ ገዳም በመሰሉ ቦታዎች ሁሉ ሲያስተምሩና ሲገስጹ ኖረዋል ። በድርሰቱም እስካሁን በሃገራችን ተወዳዳሪ የላቸውም ። እጃቸው ከብዕር ተጨማሪ ከጠንካራ ሥራ ሳይቦዝኑ ዋሻ ሲፈለፍሉ የውሃ ጉድጉዋድ ሲቆፍሩ ድልድይ ሲሠሩ ኖረዋል ። አንደበታቸውና ሕሊናቸው ከምስጋና ሳያቁዋርጡ ለቤተክርስቲያን ጸሎትና ምስጋና ሥርዓት ሲተጉ ኖረው በፅድቅና በቅድስና ሕይወት እንዳጌጡ ለተዋህዶ ኮከብ ሆነው በተወለዱ በ፷ ዓመታቸው በ፲፬፻፲፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፯ ቀን አርፈዋል ። ተማሪዎቻቸውም በመረረ ሐዘን ሆነው አፅማቸውን በጋስጫ ራሳቸው ፈልፍለው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በሠሩት ገዳም ውስጥ አስቀምጠውታል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ አባት ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሕዝበ ጽዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም የዚምባቡዌ ፓርቲዎች የላንካስተር ቤት ስምምነትን የተፈራረሙት በየት ከተማ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በለንደን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት የኒው ዮርክ አገረ ገዥ የሆኑት መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1920 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዕዝራ ዕዝራ ወይም ሱቱኤል በብሉይ ኪዳን ዘንድ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ የአይሁድ ካህን ነበረ። የሠራያ ልጅ ሲሆን በፋርስ ንጉስ አርጤክስስ 7ኛው አመት (464 ክ.በ.) ከ5000 ከወገኖቹ ጋራ ወደ ኢየሩሳሌም ለመመለስ ፈቃድ ተቀበለ። ከዚህ 13 አመት በኋላ ነህምያ የከተማውን ቅጥር ሲጠግነው ዕዝራ ኦሪት በሙሉ ለሕዝብ አነበበ (መጽሐፈ ነህምያ ምዕ. 8)። በአይሁዳዊው ታሪክ ጸሐፊ በዮሴፉስ ዘንድ ይህ የፋርስ ንጉስ አርጤክስስ ሳይሆን አሕሻዊሮስ ነበረ። አርጤክስስ የአሕሻዊሮስ ልጅ ሲሆን እነዚህ 2 ነገስታት ስሞች ብዙ ጊዜ በተለያዩ ቅጂዎች ተደናገሩ። ዮሴፉስ ደግሞ ዕዝራ የሞተበት ወራት ኤልያሴብ ታላቁ ካህን በሆኑበት ወቅት ገደማ እንደ ነበር ይመሰክራል። የአሕሻዊሮስ ዘመን ከሆነ 7ኛው አመት 486 ክ.በ. ነበር። ዕዝራ መጽሐፈ ዕዝራንና መጽሐፈ ነህምያ ከመጻፉ በላይ በዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ክፍል የሚገኙት መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤልና መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ እንደ ጻፈ ይባላል። መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ ለመጽሐፈ ዕዝራ በጣም ተመሳሳይ በመሆኑ በዕዝራ ካልዕ 81 ግን ሠራያ ሳይል በግድፈት የአዛርያስ ልጅ ይለዋል። ዕዝራ ሱቱኤል በሚባለው ትንቢት ደግሞ በ11 የጻፈው ኢየሩሳሌም ከጠፋች 30 አመት በባቢሎን መሆኑን ይላል። ይህም 565 ክ.በ. ማለት ነው። በዚህ መጽሐፍ 1344 መሠረት 24 መጻሕፍት በ40 ቀን ውስጥ ጻፈ ቢለን፥ በሌሎች ልሣናት ሕትመት ግን ስለ 94 መጻሕፍት እየተናገረ ከነዚህ መሀል ተጨማሪው 70 መጻሕፍት በምስጢር እንዲቆዩ ነበረባቸው ይላል። \n \nጥያቄ: በብሉይ ኪዳን ዘመን በባቢሎን ምርኮ ጊዜ የአይሁድ ካህን የነበረው ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዕዝራ ወይም ሱቱኤል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዛሬው ዕለት ኡጋንዳ ገብተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ኡጋንዳ መግባታቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለከተው፡፡ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ባለፈው ጥር ወር ላይ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለ6ኛ ዙር ሀገሪቱን ለመምራት ዛሬ ቃለ መሃላ ይፈፅማሉ። \n \nጥያቄ: ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የዩዌሪ ሙሴቬኒ በዓለ ሲመት ለመገኘት የት ሀገር ሄዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኡጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nደስታ ተክለወልድ አለቃ ደስታ ተክለወልድ የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ነበሩ። ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ የተወለዱት አለቃ ደስታ፣ ያረፉት ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን ከአጥቢያቸው ጀምሮ እስከ ደብረ ሊባኖስ የቅኔና የዜማ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ቀለምን ፈጥኖ በመቀበልና በማስተዋል ችሎታቸው የተመሰከረላቸው አለቃ ደስታ የመጻሕፍት አንድምታ ትርጓሜን አደላድለዋል፡፡ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የሠሩ ሲሆን፣ በእርሳቸው አረጋጋጭነት በርካታ መጸሕፍት ለሕትመት በቅተዋል፡፡ በሀገረ ጀርመን በታተመው ኢንሳይክሎፔዲያ ኢትዮፒካ እንደተዘገበው፣ ወደ ድሬዳዋ በመሄድ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ሥራቸውን የቀጠሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው ከሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መተዋወቃቸው ነበር፡፡ ከ30 ዓመት በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምን እየሠሩ ዐምድ አጋጣሚውን እንዲህ ያስታውሰዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የጣልያን ፋሺስት ጦር ኢትዮጵያን በመውረሩ ምክንያት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በስደት ስንት ዓመት ቆዩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አምስት ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ የት ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኤሮስፔስና ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ ዘርፎች ዙሪያ ከኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ጋር በቅንጅት ለመስራት እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታውቋል። በዚህ መሰረት ሚኒስቴሩ በሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ እና ኤሮስፔስ ላይ ለመስራት ከተሰማራው ፋሪስ ከተሰኘ ኢንስቲቲዩት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ እና የፋሪስ ቴክኖሎጅ ኢንስቲቲዩት መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ይርዳው ተፈራርመውታል። ስምምነቱ ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ፣ ኤሮስፔስና ሌሎች የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መስኮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑ ነው የተገለጸው። ፋሪስ በወጣት ኢትዮጵያውያን ኢንጅነሮች እና የፈጠራ ባለሙያዎች የተቋቋመ ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ፣ ኤሮስፔስና መሰል ዘርፎች ላይ የሚሰራ ኢንስቲቲዩት መሆኑን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። \n \nጥያቄ: ፋሪስ የቴከረኖሎጂ ኢንስቲቲዩት መስራች ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አቶ ኤልያስ ይርዳው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአቡነ ባስልዮስ ቀዳማዊ አቡነ ባስልዮስ (፲፰፻፹፬ዓ/ም (ሚዳ ሚካኤል) - ፲፱፻፷፫ ዓ/ም (አዲስ አበባ)) የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመጀመሪያው ፓትርያርክ ነበሩ። አቡነ ባስልዮስ ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም ገብረ ጊዮርጊስ ሲሆን መጋቢት ፲፬ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ/ም ከደብተራ ወልደጻድቅ ሰሎሞንና ከወይዘሮ (በኋላ እማሆይ) ወለተማርያም ባዩ በሸዋ አውራጃ ሚዳ ሚካኤል ተወለዱ። ደብተራ ወልደጻድቅ የይፋት ቀውትጌስ ማርያም ተወላጅ ሲሆኑ፣ እማሆይ ወለተማርያም ደግሞ በመንዝ ላሎ ምድር የተወለዱ ነበር። በሕጻንነታቸው ዘመን መንፈሳዊ ትምህርትን እየተማሩና የኮሶ ማርያምን ቤተ ክርስቲያን እያገለገሉ አድገዋል። አቡነ ባስልዮስ የአሥራ-አራት ታዳጊ ወጣት እያሉ በ፲፰፻፺፱ ዓ/ም ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገብተው ትምህርታቸውን ከመምህር ገብረ ኢየሱስ ሲከታተሉ ቆይተው በዚያው ገዳም መዓርገ-ምንኩስናቸውን እስከተቀበሉበት ድረስ ለሦስት ዓመታት በእርድና አገልግለዋል። በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመን በ፲፱፻፱ ዓ/ም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ትዕዛዝ በመናገሻ ግርጌ ለሚሠራው የማርያም ቤተ ክርስቲያን ለሚጠጉ መነኮሳትና ባሕታውያን የሚሠሩትን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳደር ረዳት እንዲሆኑ በተጠየቁት መሠረት፣ እያገለገሉና ቅዳሴ እያስተማሩ ለሦስት ዓመታት በመናገሻ ማርያም ደብር ቆዩ። እዚሁም ገዳም መምህር (አበ ምኔት) ሆነው ሲኖሩ ወደሐዋርያዊነት ሥራ በመሠማራት ቆዩ። \n \nጥያቄ: አቡነ ባስልዮስ በ14 አመታቸው በደብረ ሊባኖስ ገዳም ያስተማሯቸው መምህር ማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መምህር ገብረ ኢየሱስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ አብላጫው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚደረገው የት አካባቢ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በኒጅር ወንዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበዚህ በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. ላይ የቱርክ፣ የመስኮብ፤ የጀርመን፤ የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይና የኤስፓኝ መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት መቆጠራቸው አልቀረም። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ የፖርቱጋል መንግሥት በሌላው እንኳን ባይሆን በመርከብና አገር በመያዝ ከቀሩት ይበልጥ ነበር። የቀሩት የኤውሮፓ መንግሥታት እዚያው ወሰናቸው ላይ ገዥነታቸውን ለማጽደቅ እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ የፖርቱጋል መንግሥት ግን ደኅና ደኅና መርከቦችን አዘጋጅቶ እየላከ ከመንግሥቱና ከኤውሮፓ ርቆ የሚገኘውን የአሜሪካን፤ የእስያን፤ የአፍሪካን አገሮች ያስመረምር ነበር። መርማሪዎቹም እነቫስኮ ደጋማ፤ እነፔሬዝ፤ እነአንድራድ፤ እነካብራል በመርከብ እየሄዱ ለመከላከል ጉልበት የሌለውንና በጠባዩ ሀብት ያለበትን አገር መርምረው ሲመለሱ መንግሥቱ ወታደር በመርከብ እየላከ ብዙ አገር ያዘ። በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ. ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል የተባለው የፖርቱጋል መኮንን በትልቅ መርከብ ሄዶ ይን ጊዜ ለቀረው ዓለም ያልታወቀውን የብራዚልን አገር አስገበረና በፖርቱጋል መንግሥት ስም ቅኝ አገር አደረገው። ከዚያም አገር በተገኘው ወርቅ መንግሥቱ ሀብታም ሆነ። እንደዚሁም የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ ወደ ህንድ አገር ሄዶ አገሩን ያዘ። ከተማውንም በጎአ አድርጎ ህንድንም የፖርቱጋል የቄሣር ግዛት አደረገና አገር ገዥውም የንጉሥ እንደራሴ ይባል ጀመር። ከዚያም በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን የሚባለውን አገር በየጊዜው በጦር ኃይል አስገበራቸው። በዚሁ አኳኋን ወደ ኢትዮጵያም እነኮቪልሐኦ ቀደም ብለው በዓፄ እስክንድር ዘመን መጥተው እንደመረመሩትና የኢትዮጵያ መንግሥት በዚያ ጊዜ በነሱ አጠራር የቄሱ የዮሐንስ መንግሥት አለ ብለው አውርተው እንደነበረ ሌላ የፖርቱጋል የጦር መርከብ በአፍሪካ ድንበር በቀይ ባሕር ላይም እየተመላለሰ አስቀድሞ ከያዙት ከቱርኮችና ከግብጾች እየተዋጋ አንድ ጊዜም እየተሸነፈ አንድ ጊዜም እያሸነፈ ብዙ ጊዜ ተመላለሰ። በዚህ ሁሉ ምክንያት የፖርቱጋል መንግሥት ታላቅነት በሌላው ዓለም እንደ ታወቀ እንደዚሁም ፩ኛ ትልቅ መንግሥት መሆኑ ፪ኛ ክርስቲያን መሆኑ ኢትዮጵያ ባሉት የውጭ አገር ሰዎች አፍ እየተነገረ ዝናው በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ዘንድ መሰማት ቻለ። \n \nጥያቄ: ብራዚል በፖርቹጋል ቅኝ ሀገር የሆነችው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ የምትችል ተሸከርካሪ በኢትዮጵያዊ ወጣት መሰራቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ነዋሪ የሆነው ታዳጊ አጃዬ ማጆር ተሸከርካሪዋን ከወዳደቁ ብረቶች እንደሰራት ተነግሯል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባደረገለት ድጋፍ የተሰራችው የባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ ሞተርን በመጠቀም የተሰራች ሲሆን ወደ ኋላ መሄድ እንድትችል ተደርጋ ተሻሽላ ተሰርታለች፡፡ አራት ኩንታል ክብደት ያላት ተሽከርካሪዋ እስከ 4 ሰዎች የመጫን አቅም ያላት ሲሆን በአንድ ሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ ትችላለች ተብሏል፡፡ ታዳጊው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ መኪና መስራቱ ተገልጿል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለታዳጊው የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያዊው ወጣት የተሰራው ተሽከርካሪ ምን ያህል ክበደት አለው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አራት ኩንታል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: የስዋሂሊ ቋንቋ የአፍ መፍቻቸው የሆኑ ምን ያህል ሕዝቦች አሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፭ ፡ ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመስከረም ፩ መስከረም ፩ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ የመጀመሪያው ዕለት ነው። በመሆኑም ቀኑ የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓል ወይም ዕንቁጣጣሽ በመባል ይታወቃል። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፫፻፷፭ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ዮሐንስ፤ ማቴዎስ፤ እና ማርቆስ ደግሞ ፫፻፷፬ ቀናት ይቀራሉ። ==ታሪካዊ ማስታወሻዎች== ፲፭፻፯ ዓ/ም - የፖሎኝ ሠራዊት በኦርሻ ውግያ በሩስያ ላይ አሸነፈ። ፲፮፻፺፮ ዓ/ም - በጎንደር ትልቅ አውሎ ነፋስ ተነስቶ ብዙ የሕዝብ እና የንጉሥ ቤቶችን ሲያወድም፣ የሸዋው ታላቅ መኮንን አቤቶ ወልደ ብርሃን እና ፵ ሰዎች ሞተዋል። ፲፰፻፮ ዓ/ም - የአሜሪካ መርከቦች በኤሪ ሐይቅ በእንግሊዝ አሸነፉ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በላቲመር ፔንሲልቬኒያ ፖሊሶች 19 የማዕደን ሰራተኞች በእልቂት ገደሉ። ፲፱፻፲፭ዓ/ም - የእንግሊዝ አስተዳደር በፍልስጤም ጀመረ። ፲፱፻፴፮ ዓ/ም - የጀርመን ሃያላት ሙሶሊኒን ከእስር በት እንዲያመልጥ ነጻ አወጡት። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - የብረት መጋረጃ በኰሙኒስት ሃንጋሪና በኦስትሪያ መሃል ተከፍቶ ወዲያው ብዙ ሺህ የቀድሞው የምሥራቅ ጀርመን ዜጋዎች ወደ ምዕራብ ፈለሱ። ፲፱፻፺፬ ዓ/ም - አራት አውሮፕላኖች በአረብ ተዋጊዎች ተሰርቀው በአለም ንግድ ሕንጻና በፔንታጎን ተጋጭተው 3000 ያህል ሰዎች ተገደሉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት በዓል ወይም እንቁጣጣሽ መች ይከበራል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መስከረም ፩ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስን በ70 ዓመቱ የከሰሰው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአቴና መንግስት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nናሚቢያ ናሚቢያ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ፣ በስሜን በአንጎላና በዛምቢያ፣ በምስራቅ በቦትስዋና፣ በደቡብም በደቡብ አፍሪቃ ትካለላለች። በ1982 አመተ ምኅረት ነጻነትዋን ከደቡብ አፍሪቃ ስላገኘች በጣም አዲስ አገር ነች። ዋና ከተማዋ ዊንድሁክ ነው። የናሚቢያ በረኅ አውራጃ ከጥንት ጀምሮ በሳን (ቡሽማን)፣ በዳማራና በናማቋ ሕዝቦች ተሰፈረ። በ14ኛው መቶ ዘመን፣ የባንቱ ወገኖች ባስፋፉ ጊዜ አገሩን ሠፈሩ። ክልሉ ግን ከ19ኛው መቶ ዘመን በፊት በአውሮጳውያን አልተዘለቀም። በዚያን ጊዜ ጀርመን ደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ አገሪቱ የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። ዳሩ ግን ዋልቪስ በይ የተባለው ትንሽ ወደብ ብቻ የእንግሊዝ ግዛት ነበር። \n \nጥያቄ: ናሚቢያ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዓረብኛ ዓረብኛ የሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ አባል ሆኖ የዕብራይስጥ የአረማያ እንዲሁም የአማርኛ ቅርብ ዘመድ ነው። ፪፻፶ (250) ሚሊዮን የሚያሕሉ ሰዎች እንደ እናት ቋንቋ ይናገሩታል። ከዚህም በላይ በጣም ብዙ ሰዎች እንደ ፪ኛ ቋንቋ ተምረውታል። የሚጻፈው በዓረብኛ ፊደል ነው። በዓረብ አለም ውስጥ አያሌ ቀበሌኞች ይገኛሉ። ቋንቋው በእስልምና ታላቅ ሚና አጫውቷል። እስላሞች አላህ ለሙሐማድ ቁርዓንን ሲገልጽ በዓረብኛ እንደ ሆነ ስለሚያምኑ እንደ ቅዱስ ቋንቋ ይቆጥሩታል። አብዛኛው ዓረብኛ ተናጋሪዎች ሙስሊሞች ናቸው። ዛሬ በምዕራብ ዓለም ደግሞ ብዙ ሰዎች አረብኛ እያጠኑ ነው። በታሪክ ከፍተኛ ሚና በማጫወቱ መጠን ፤ ብዙ የዓረብኛ ቃላት ወደ ሌሎች ቋንቋዎች ገብተዋል። \n \nጥያቄ: ዓረብኛ ዓረብኛ ከየትኛው ቋንቋዎች ቤተሠብ ውስጥ ይመደባል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሴማዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመንግሥት እና ፖለቲካ ናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ሲሆን መንግሥቷ በአሜሪካ መንግሥት ላይ ነው የተመረኮዘው። የህግ አውጪው አካል አወቃቀር የዌስትሚኒስትር ሥርዓትን ይከተላል። በአሁኑ ጊዜ ጉድላክ ጆናታን ፕሬዝዳንት ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ለሁለት የአራት ዓመት ጊዜ ሲያገለግል በሕዝቡ ነው የሚመረጠው። የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት አካሎች አሉት። እነዚህም ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ናቸው። ሴኔቱ 109 መቀመጫዎች ሲኖሩት እያንዳንዱ ክልል በሶስት አባሎች ይወከላል። የአቡጃ ርዕሰ አካባቢም አንድ ተወካይ አለው። የሴኔት አባላት በሕዝብ ይመረጣሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 360 መቀመጫዎች ሲኖሩት የእያንዳንዱ ክልል ወካዮች በሕዝብ ብዛት ነው የሚወሰነው። የውጭ ግንኙነቶች ነፃነቷን በ1960 እ.ኤ.አ. ካገኘች በኋላ ናይጄሪያ ለአፍሪካ ነፃነትና ክብር መታገል ዋና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አድርጋለች። የደቡብ አፍሪካን አፓርታይድ ሥራዓት በመቃወም ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በ1960ዎቹ እ.ኤ.አ. ናይጄሪያ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ሲሆን እስራኤል የናይጄሪያ ፓርላማ ህንጻዎችን አሰርታለች። ናይጄሪያ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራች አገር ናት። በምዕራብ አፍሪካም ሆነ በአፍሪካ በጠቅላላ ትልቅ ተጽዕኖ አላት። በተጨማሪም እንደ ኤኮዋስ ያሉ የምዕራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅቶች መሥራች ናች። ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ጀምሮ ናይጄሪያ ዋና የነዳች አምራች ስትሆን የኦፔክ አባል ሀገር ናት። በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ናይጄሪያውያን በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ናይጄሪያውያን በአሜሪካን እንደ ሚኖሩ ይገመታል። \n \nጥያቄ: በናይጄሪያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስንት መቀመጫ አለ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 360 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ስለፀሀይ ሳይንሳዊ መግለጫ ከሰጡ ፈላስፎች ቀዳሚው የሆነው አናክሳጎራስ የየት ሀገር ፈላስፋ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ግሪካዊው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የትዳር አጋር ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እቴጌ መነን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: አዲ ዘመን ጋዜጣ ስራውን በይፋ ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በማን ታሰሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በማርክሲስት አብዮት ደርግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን በማን ትእዛዝ ሰጪነት ተገደሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ የመቃብር ስፍራ ስሙ ምን በመባል ይታወቃል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፔንሲልቬንያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ስንት አልበም ሰርቷል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 13 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአኩሪ አተር አኩሪ አተር የአባዝርት አትክልት ዝርያ ነው። በየጊዜው አኩሪ አተርን መመገብ ለሴቶች ጉዳት ባያደርግም፣ ለወንዶች ጤናማ እንደማይሆን በሰፊ ቢታወቅም በአንዳንድ አገር ባሕል አመጋገብ በብዛት ይጨመራል። ከ20ኛዉ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ አሜሪካን ዉስጥ ወርቃማዉ ወይም ተዓምረኛዉ እህል የሚል ስያሜ አግኝቷል። አኩሪ አተር በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር የለም። ባለሙያ ካገኘም ለመጠጣትም ለመበላትም የሚችል የእህል ዘር ነዉ። ስለአኩሪ አተር ሲወሳ ብዙዎች የሚያስታዉሱት ለሕፃናት አካል ግንባታ ጠቃሚ መሆኑ ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአኩሪ አተር ወተት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በኢትዮጵያዉያን የምግብ ጣዕም ለዛ ተላብሶ በተለያየ ምግብነት መቅረብ እንደሚችል እየታየ ነዉ። አኩሪ አተር ወደኢትዮጵያ የገባዉ በ1950ዎቹ መሆኑን ነዉ በእህሉ ላይ ምርምር የሚያደርጉት ባለሙያዎች የሚያስረዱት። በአኩሪ አተር ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተደረገዉ ዝርያ የማዉጣት ምርምርም 22 ዓይነት ዘሮች እስካሁን ተገኝተዋል። አኩሪ አተርን በሀገር ዉስጥ በ12 የምርምር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ፤ መካከለኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ እና ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርምሩ ይካሄዳል። አኩሪ አተር ሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረተዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነዉ። አኩሪ አተርን በብዛት ከሚያመርቱ ሃገራት ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ቀዳሚዎቹ ናቸዉ። ከአኩሪ አተር ወተት ለማዘጋጀት ሲታሰብ እህሉን ከአንድ ቀን በፊት ለቅሞና አጥቦ ለ15 ደቂቃ ያህል መቀቀል ያስፈልጋል። ከዚያም አዉጥቶ ተዘፍዝፎ ያድራል። ከዚያም የራሰዉን አኩሪ አተር ልጣጩን በሚገባ በዉኃ አስለቅቆ በትንሽ በትንሹ እየቆነጠሩ ፈጭቶ እንደእህሉ መጠን ዉኃ ጨምሮ መቀቀልና መጭመቅ ነዉ። እንደባለሙያዉ ከሆነም ለአንድ ኪሎ አኩሪ አተር ስምንት ሊትር ዉኃ ያስፈልጋል። ተፈጥሮን ተከትሎ የማይበቅል እህልም ሆነ በተፈጥሮ ሥርዓት ያላደጉ እንስሳትን መመገብ ለጤና አደገኛ መሆኑን በተግባር የተረዳዉ ምዕራቡ ዓለም በአሁኑ ጊዜ ፊቱን ከእንስሳት ተዋፅኦ ወደተክሎችና ሰብሎች አዙሯል። በዚህ ምክንያትም ከአኩሪ አተር የሚገኙ የምግብ ተዋፅኦዎች ተመራጭነትን እያገኙ ነዉ። ከአኩሪ አተር ወተት እና አይቡ እንደሚገኝ ሁሉ የአኩሪ አተር ሥጋም አለዉ። \n \nጥያቄ: አኩሪ አተር በኢትዮጵያ ውስጥ በብዛት የት ይመረታል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል የሚያስችል መሳሪያ ሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የፈጠረው በስንት ዓ.ም. ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1911 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዐምደ ጽዮን ቀዳማዊ አጼ ዐምደ ጽዮን (የዙፋን ስም ገብረ መስቀል) ከ1314 እስከ 1344 ዓ.ም. የነገሡ ሲሆን በጥንቱ ዘመን ከተነሱ ነገሥታት ውስጥ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ሰፋ ያለ አሻራ ትተው ካለፉት (ለምሳሌ፦ ዘርአ ያዕቆብ) ጎን ወይም በላይ ስማቸው ይጠቀሳል። አጼ ዐምደ ጽዮን የአጼ ይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅና የአጼ ወድም አራድ ልጅ እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ይኩኖ አምላክ አዲሱን የሰሎሞን ስርወ መንግስት ቢመሰርቱም፣ በልጅ ልጆቻቸው የነበረው ፉክክርና አዲስ ከሚስፋፋው የእስልምና ሃይማኖት የሚሰነዘረው ጥቃት ስርዓቱን ስጋት ላይ የጣለ ነበር። አጼ አምደ ጽዮን ይህን ፉክክር በማስቆምና በዘመናት በማይደበዝዘው ጀግንነታቸው የኢትዮጵያን ድንበር ከሞላ ጎደል አሁን በሚታወቀው መልኩ በማስቀመጥ፣ የአዲሱን ስርወ መንግስት መሰረት በማጽናት እንዲሁም በማረጋጋት ዝናቸው በጥንቱ አለም ክአፍሪቃ ቀንድ እስከ አውሮጳ የተንሰራፋ ነበር። \n \nጥያቄ: አጼ ዐምደ ጽዮን ምን ያህል ጊዜ ነገሱ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1314 እስከ 1344 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: በፈረንሳይ ስንት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጣለ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል ከሞሪታንያ ጋር የምትዋሰነው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከሰሜን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ የምትችል ተሸከርካሪ በኢትዮጵያዊ ወጣት መሰራቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ነዋሪ የሆነው ታዳጊ አጃዬ ማጆር ተሸከርካሪዋን ከወዳደቁ ብረቶች እንደሰራት ተነግሯል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባደረገለት ድጋፍ የተሰራችው የባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ ሞተርን በመጠቀም የተሰራች ሲሆን ወደ ኋላ መሄድ እንድትችል ተደርጋ ተሻሽላ ተሰርታለች፡፡ አራት ኩንታል ክብደት ያላት ተሽከርካሪዋ እስከ 4 ሰዎች የመጫን አቅም ያላት ሲሆን በአንድ ሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ ትችላለች ተብሏል፡፡ ታዳጊው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ መኪና መስራቱ ተገልጿል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለታዳጊው የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ውስጥ በሊትር 40 ኪ.ሜ መጓዝ የምትችል መኪና የሰራው ወጣት ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አጃዬ ማጆር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጨረቃ ላይ መውጣት ጨረቃ ላይ መውጣት የምንለው ማናቸውም ሰው ሰራሽ መንኮራኩሮች ጨረቃ ገጽ ላይ ሲያርፉ ያለውን ክንውን ነው። ይህ እንግዲህ ሰውንም ሆነ ያለሰው የተደረጉ በጨረቃ የማረፍ ክንውኖችን ይጠቀላላል። ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰራሽ የሆነ ነገር ጨረቃ ላይ ያረፈው በመስከረም 13፣ 1959 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውም የሶቭዬት ህብረት ሉና 2 ሚሲዮን ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ልጅ እራሱ ጨረቃ ላይ የወጣው ሐምሌ 20፣ 1969 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውን በአሜሪካው የአፖሎ 11 ሚሲዮን መንኮራኩር ነበር። ባጠቃላይ 24 አሜሪካውያን ወደጨረቃ ተጉዘዋል፣ 12ቱ የጨረቃን ምድር በእግራቸው ረግጠዋል። በዚህ ወቅት ሶቪየት ህብረትም የራሷን ጠፈርተኞች ለመላክ ሞክራለች። ለዚህ እንዲረዳት ጨረቃ ላይ አራፊ LK የተሰኘ መንኮራኩር ሰራች፣ ሆኖም ግን ይህን መንኮራኩር ወደ ጨረቃ የሚወስድ ከባድ ሃይል ያለው ሮኬት ከአሜሪካ ቀድማ መስራት ስላልቻለች ተቀደመች። ዩጂን ከርናን የጨረቃን ምድር የረገጠው የመጨረሻው ሰው ነው። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃ ላይ ያረፈው ሰው ሰራሽ ነገር የማን ሀገር ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የሶቭዬት ህብረት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሶቪዬት ሕብረት ሶቭየት ሕብረት ሰብአዊ ሪፐብሊክ በ፲፱፻፲ ዓ.ም. የተከሰተውን የሩሲያ አብዮት ፍንዳታ፤ እንዲሁም ያንን ተከትሎ ለሦስት ዓመታት የተከናወነውን የሩሲያ «ውስጣዊ ሕዝባዊ የርስ በርስ ግጭት» ተከትሎ በኅብረተስብአዊ ሕገ መንግሥት (socialist constitution) በአራት ሪፑብሊኮች ቅንብርነት የተመሠረተ አገር ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ከቀድሞው የናዚ ጀርመን እጅ የተወሰዱ አገሮችን በማቀላቀል እንዲሁም በ፲፱፻፵፱ ዓ.ም በጉልበት ሌሎች የምሥራቅ አውሮፓ አገሮችን በመቀላቀል ኅብረቱ ዓሥራ ስድስት ሪፑብሊኮችን ያካተተ ነበር። በዘመን ቆይታና በጥንካሬም የጎለበተ ሕዝባዊ አብዮታዊ የኅብረት ሪፑብሊክ በመሆኑም በተለይ በ«ቀዝቃዛ ጦርነት» በሚባለው በ«ምዕራብና በምሥራቅ» ዓለም ተከስቶ በነበረው ፍጥጫ ጊዜ፣ በዓለም ላይ ለሚመሠረቱ ሕዝባዊ መንግሥታት ዋና የሽከታ አርአያ የነበረ መንግሥት ነበር። በ ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጀምሮ ይሄ ኅብረት እስከፈረሰበት እስከ ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ድረስ በተካሄደው የ«ቀዝቃዛ ጦርነት» ዘመን የሶቪየት ኅብረት በዓለም ከነበሩት ሁለቱ ተቃራኒ ኃያላን መንግሥታት አንዱ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ላይ በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም የተመሠረተውን የአብዮት ወታደራዊ የደርግ መንግሥት በጦር መሣሪያ፤ በአማካሪነት፤ በገንዘብ፤ ወዘተረፈ፤ ዋነኛ ደጋፊና ታላቅ ተዋናይ አገር ነበር። የቀድሞው የሶቪዬት ኅብረት መጨረሻ ላይ ታኅሣሥ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ተደምስሶ በዓለም መንግሥታት እውቀትና ስምምነት ሕጋዊ ወራሽነት የሩሲያ መንግሥት እንደሆነ ታወጀ። ሩሲያም በዚህ መሠረት የቀድሞውን የሶቪዬት ሕብረት የውጭ ዕዳዎች እንዲሁም የውጭ ንብረቶች በፈቃዱ ተቀበለ። በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ተፈርመው የነበሩም ዓለም አቀፍ ስምምነቶችንም ሩሲያ መቀበሏን አስታውቃለች። \n \nጥያቄ: የሶቭየት ሕብረት መቼ ፈረሰ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ታኅሣሥ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ የት ከተማ ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሞንሮቪያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር ከመቼ ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር ሆነ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: አማርኛ የስራ ቋንቋ የሆነባት ሀገር ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአራት ማዕዘን አራት ማዕዘን ማናቸውም አራት ቀጥተኛ መስመር የሆኑ \"ጎኖች\"ና አራት መገናኛወች ያላቸውን የሚወክል የሂሳብ ስያሜ ነው። እኒህ ጎኖች መነባበር ወይም አንዱ ባንዱ ላይ መንሳፈፈ የለባቸውም አለዚያ አራት ማዕዘን አይባሉም። የአራት ማዕዘን አራቱ ውስጣዊ ማዕዘኖች ሲደመሩ ምንጊዜም ውጤታቸው 360 ዲግሪ ነው። ፓራላሎግራም ሁለቱ ጎኑ ትይዩ የሆነ አራት ማዕዘን ፓርላሎግራም ይባላል። በፓራላሎግራም ስር የሚተድዳደሩ እንግዲህ ካሬ፣ ሬክታንግል፣ ሮምበስና ሮምባቶይድ ይባላሉ። ሮምበስ ማለት አራቱም ጎኑ እኩል የሆነ ፓራልላሎግራም ነው። በሌላ አነገጋገር ተጻራሪ ጎኖቹ ትይዩ ሲሆኑ ተጻራሪ ማዕዘኖቹ ደግሞ እኩል ናቸው፣ ወይም ደግሞ ዲያጎናሎቹ በ90 ደጊሪ እኩል ለኩል ይቋረጣሉ። ወይም በሌላ አባባል ወደጎን የተገፋ ካሬ ማለት ነው። ሮምባቶይድ ማለት ፓራሎግራም ሆኖ ተነካኪ ጎኖቹ እኩል ያልሆኑና ማዕዘኖቹ ኦብሊክ የሆኑ ማለት ነው። በሌላ አባባል የተገፋ ሬክታንግል ማለት ነው። ሬክታንግል ማለት አራቱም ማዕዘኖቹ 90ዲግሪ የሆነ አራት ማዕዘን ማለት ነው። በሌላ አባባል ዲያጎናሎቹ እኩል ሆነው እኩል የሚቋረጡ ማለት ነው። ካሬ አራቱም ጎኖቹ እኩል የሆኑ እንዲሁም አራቱም ማዕዘኖቹ 90 ዲግሪ የሆኑ ማለት ነው። በአንድ ጊዜ ሮምበስ እና ሬክታንግል የሆነ አራት ማዕዘን ምንጊዜም ካሬ ነው። \n \nጥያቄ: የአራት ማዕዘን ዉስጣዊ ማዕዘኖች ድምር ስንት ዲግሪ ይሆናል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 360 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ የሥራ ፈጠራ ይዘው በመቅረብ በጤና ዘርፍ አሸናፊ የሆኑት ግለሰብ ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ፕሬዝዳንት አብዱ ዲዮፍ በምርጫ ተሸንፎ ስልጣኑን ያስረከበው ለማን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አብዱላይ ዋዲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ ለ25 ዓመታት ያገለገሉት ብርጋዴር ጄነራል መአሾ ሀጎስ ስዩም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ተልእኮ አዛዥ ሆነው ተሰየሙ። ብርጋዴየር ጄነራል መአሾ በተመድ የላይቤሪያ እንዲሁም ዳርፉር ሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ማገልገላቸውም ታውቋል። አዲሱን ሹመት ከጥር 04 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደተሰጣቸውም በተመድ መረጃ ላይ ተገልጿል። \n \nጥያቄ: ብርጋዴር ጄነራል መአሾ በኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ ለስንት ጊዜ አገልግለዋል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለ25 ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ ታዋቂ የሆኑት ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ሙያቸው ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሙዚቀኞች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በአውስትራሊያ የቀለም ቴሌቭዥን ስርጭት የተጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1967 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየናሳ ተመራማሪዎች ሱፐር ኧርዝ ሲሉ የሰየሟትን አዲስ ፕላኔት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡ በመጠኗ የመሬትን እጥፍ ታክላለች የተባለችው አዲሷ ፕላኔት ከከዋክብቷ አንፃር ለህይወት ተስማሚ በሆነ ርቀት ውስጥ እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡ ይህም በፕላኔቷ ላይ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚል ተስፋ አሳድሯል ነው የተባለው፡፡ ፕላኔቷ አለታማ አሊያም እንደኔፕቲዩን በጋዝ የበለፀገች ልትሆን እንደምትችል የናሳ ተመራማሪዎች የገለጹ ሲሆን ፕላኔቷ ያልተለመደችና ከቀድሞ ፕላኔቶች ልዩ እንደሆነች በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ \n \nጥያቄ: የናሳ ተመራማሪዎች ያገኝዋትን አዲስ ፕላኔት ምን ብለው ሰየምዋት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሱፐር ኧርዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: ሙሴ ሌስፖስ ሱዝ ካናልን ለምን አሰራው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መርከብ እንዲተላለፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1945 ዓ.ም. ደቡብና ሰሜን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ ጋር አንድ ላይ በማድረግ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽንን ማን ፈጠረው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ብሪታኒያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የውጪ ሀገር ዜጎች ሠራተኞች በብዛት የሚሳተፉት በምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከአፍሪካ ህዝብ ውስጥ 24 በመቶ ብቻ የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆናቸውን ዓለም ባንክ አስታወቀ፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት አለመስፋፋት በአህጉሪቱ አዳዲስ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ የስራ ዕድል ፈጠራዎችን ለማስፋፋት አዳጋች እንደሚሆን ነው ባንኩ የገለጸው፡፡ በአፍሪካ እኤአ ከ2015 እስከ 2035 ባለው ጊዜ ውስጥ 450 ሚሊዮን ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የዓለም ባንክና የአፍሪካ ልማት ባንክ በጥምረት ያወጡት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ እንደ ኢኮሜርስ እና ፋይናንስ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የስራ ዘርፎችን በአፍሪካ በማስፋፋት ከፍተኛ የስራ እድልን መፍጠር እንደሚቻል ተጠቅሷል፡፡ በዚህም፣ ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በቂ እውቀት እንዲኖራቸው በማድረግ ማሰማራት እንደሚገባ ተነግሯል፡፡ \n \nጥያቄ: ዲጂታል ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ የሥራ እድል ፈጠራዎች አዳጋች ያደረጉ ነገሮች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኢንተርኔት አገልግሎት አለመስፋፋት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: በናይጄሪያ ትልልቆቹ ወንዞች ማንና ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኒጄር እና ቤንዌ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nስታምፎርድ ብሪጅ (የእግር ኳስ ሜዳ) ስታምፎርድ ብሪጅ በፉልሃም ለንደን የሚገኝ የቼልሲ እግር ኳስ ቡድን የእግር ኳስ ሜዳ ነው። የእግር ኳስ ሜዳው የሚገኘው በሙር ፓርክ ኢስቴት (በሌላ አጠራር በዋልሃም ግሪን) ወይም በተለምዶ ዘ ብሪጅ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ነው። ይህ የእግር ኳስ ሜዳ 41,798 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ ከፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ትልቅ የእግር ኳስ ሜዳ ያደርገዋል። የተከፈተው እ.ኤ.አ በ1877 ሲሆን እስከ 1905 ድረስ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ይጠቀምበት ነበር። ሜዳው ብዙ ለውጦችን አካሂዷል። በቅርቡ ደግሞ (እ.ኤ.አ 1990ዎቹ) ወደ ዘመናዊና ለሁሉም ተመልካቾች መቀመጫ ያለው ሆኖ ተሠርቷል። ስታምፎርድ ብሪጅ የተለያዩ የእንግሊዝ ዓለም አቀፋዊ ጨዋታዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ግማሽ ፍጻሜዎችን እና የቻሪቲ ፊልድ ጨዋታዎችን አስተናግዷል። ለተለያዩ ስፖርቶችም እንደ ክሪኬት ፣ ራግቢ ዩኒየን ፣ ስፒድዌይ ፣ ግሬይሃውንድ ሬሲንግ ፣ ቤዝቦል እና የአሜሪካን ፉትቦል ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ጥቅም ላይ ውሏል። የስታዲየሙ ትልቁ ኦፊሲዬላዊ የታዳሚዎች ቁጥር 82,905 ሲሆን ፤ ይህ የሆነው ቼልሲ ከአርሰናል እ.ኤ.አ በኦክቶበር 12 1935 ባካሄዱት የሊግ ጨዋታ ነበር። ስታምፎርድ ብሪጅ ፤ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ስታዲየም ሆኖ እ.ኤ.አ በ1877 ተከፈተ። በዚያ ሜዳ ላይ ታላላቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት የፈለጉ ገስ እና ጆሴፍ ሚየርስ የተባሉ ወንድማማቾች ኮንትራቱን እስካገኙበት ጊዜ ድረስ ለለንደን አትሌቲክስ ክለብ እስከ እ.ኤ.አ 1904 ድረስ አገልግሏል። \n \nጥያቄ: ስታምፎርድ ብሪጅ የእግር ኳስ ሜዳ የት ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በፉልሃም ለንደን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከአድዋ ሽንፈት በኋላ ጣሊያኖች ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራርመው አዲስ ገዢ፣ ፈርዲናንዶ ማርቲኒ፣ 1897 ላይ በመሾም ግዛታቸውን ማጽናት ጀመሩ። በዚህ ወቅት የቀደመው ወታደራዊ ስርዓት እንዲቋረጥ ተደርጎ አገሪቱ የብሔር ልዩነትን \"በሚያከበር\" አስተዳደር ተከፍሎ እንዲቋቋም ተደረገ። ዳህላክ፣ አፋር እና ሰምሃር አንድ ላይ \"ምስራቃዊ ክፍል\" ተብለው ከምጽዋ እንዲተዳደሩ ተደረገ። \"ምዕራባዊ ክፍል\" ከአቆርዳት እንዲተዳደር ሲደረግ ቤኒ አሚርን፣ ናራንና ኩናማ ምድርን ያጠቃልል ነበር። ከከረን ሆኖ የሚተዳደረው ደግሞ ሰሜናዊ ሐማሴን (የእስልምና ተከታይ የሆነ)፣ ቤት አሰገደና ዓድ ሼኽ ነበሩ። ቀሪው ሐማሴን ከአስመራ፣ ሰራየ ከመንደፈራ(አዲ ወግሪ) እንዲተዳደር ሲደረግ አካለ ጉዛይ ከሳሆ ጋር ተዋህዶ ከአዲ ቀይሕ ይገዛ ጀመር። ከላይ ወደታች በተዘርጋ መዋቅር የጣሊያን ባለስልጣኖች እያንዳንዱን ክፍል ያስተዳድሩ ጀመር። የአገሪቱ ዋና ከተማ ከምጽዋ ወደ አስመራ የተዛወረው በዚህ ወቅት፣ በ1898 ነበር። ከ1898 እስከ 1908 በተደረጉ ውሎች (ከኢትዮጵያ፣ ከአንግሎ-ግብጻዊ ሱዳንና ከጅቡቲ ጋር) መሰረት የቅኝ ግዛቱ ድንበር ታወቀ። ኢትዮጵያን ስለ ድንበሩ ለማሳመን 3 አመትና 5ሚሊዮን ሊሬ ፈጅቶባቸው ግንቦት 1900 ላይ ያሰቡት ሊሳካላቸው ቻለ። ድንበሩ ከሞላ ጎደል የመረብ፣ በለሳና ሙና ወንዞችን የታከከ ነበር። \n \nጥያቄ: በ1898 የኤርትራ ዋና ከተማ ከምጽዋ ወደ የት ተዘዋወረ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ወደ አስመራ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በምን በምን ውድድሮች ክብረ ወሰን አሻሻለ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር ከተማ ከጢስ አባይ በምን ያህል ርቀት ላይ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ30 ኪሎሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: አፕል የምን ዘርፍ ኩባንያ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቴክኖሎጂ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኮምፒዩተር ኮምፕዩተር ማለት ማንኛውንም ኢንፎርሜሽን ፕሮሰስ የሚያደርግ ማሽን ነው። ይህንም የሚያደርገው በተርታ የተቀመጡ ትዕዛዞች በመፈጸም ነው። ለብዙ ሰዎች ኮምፒዩተር ሲባል ዐዕምሯቸው ላይ የሚመጣው የግል (ፐርሰናል) ኮምፒዩተር ነው። ነገር ግን ኮምፒዩተር ሲባል በጣም ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። ላፕቶፕ ፣ ዴስክቶፕ ፣ ማይክሮ-ኮምፒዩተር ፣ ሱፐር-ኮምፒዩተር ፣ ካልኩሌተር ፣ዲጂታል ካሜራ እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ቀድሞ አስሊ ማለት አንድ በሒሳባዊ ትዕዛዝ የተለያዩ የጥንት መሣሪያዎችን እየተጠቀመ ቁጥሮችን የሚያሰላ ሰው ነበር። እስከ 20ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የተለያዩ ጠቃሚ መሣሪያዎች ተሰርተዋል። ከዛ በኋላ ትልልቅ ማሸኖች መሠራት ጀመሩ። እነዚህ ማሽኖች ከዛሬው ኮምፒዩተሮች(አስሊዎች) ጋር ሲወዳደሩ በጣም ትልቅና ቀርፋፋ ናቸው። የኮምፕዩተር የውስጥ ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1.ሞኒተር - የምንሰራውን ነገር እንዲያሳየን፤ምስል፣ጽሑፍ፣ ቪዲዮ ወይም ማንኛውም ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ሞኒተር 14 ኢንች፣ 15 ኢንች፣ ወዘተ. እየተባለ ይገላጻል፡፡ 2.ማዘርቦርድ - እናት ሰሌዳ ሁሉም የኮምፕዩተር ክፍሎች(ዕቃዎች)የሚቀዳጁበት 3.ሲፒዩ - የኮምፕዩተሩ አእማሮ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሲፒዩን ከሰው አእምሮ ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ 4.ሜሞሪ - የምንሰራውን ስራ ወይም ፋይል በጊዚያዊነት አስቀምጠንበት የምንሰራበት፡፡ ሜሞሪበባይት (Bytes) ይለካል፡፡ ከ Bytes ፊት Kilo፣ ማለትም ኪሎባይት (kilobytes)([1,024 ባይቶች ወይም Bytes ማለት ነው፡፡ ] ፣ Mega[1,048,576 ባይቶች ወይም Bytes ] ፣ Giga [1,073,741,824 ባይቶች ወይም Bytes]፣ ወዘተ የሚሉትን ቃላት በመጠቀም ኪሎባይት(kilobyte)፣ ሜጋባይት (megabyte)፣ ጊጋባይት (gigabyte) እያልን የኮምፒዩተር ሜሞሪ መግለፅ እንገልጻለን፡፡ ለምሳሌ 10 MegaBytes ወይም ባጭሩ ሲጸፍ 10MB ይህ ማለት 10,485,760 Bytes ይሆናል ማለት ነው፡፡ 5.ኤክስፓንሽ ስሎት 6.የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረቢያ (power supply) 7.የሲዲ ማሰሪያ (cd drive) 8.ሀርድ ዲስክ (የምንሰራውን ወይም የምንጠቀምበትን ፋይል በቋሚነት ለማስቀመጥ) 9. መሎጊያ (ማውስ) 10.የፊደል ገበታ (ኪቦርድ) የመጀመሪያቹ ኮምፕዩተሮች የሚሠሩት በእንግሊዝኛ ፊደል ብቻ ነበር። ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ኣገሮች ሊቃውንት በየራሳቸው ፊደላት እንዲሠሩ ኣደረጉ። ኮምፕዩተር በእያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኣበራ ሞላ ነው። በቅርቡም አያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት ዩኒኮድ የሚባል የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ መግባት ቀጥሏል። \n \nጥያቄ: ኮምፒዩተር ላይ የሚታዩ ነገሮችን ለማሳየት የሚጠቅመው ክፍል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሞኒተር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nክዋሜ ንክሩማህ የተወለዱት በ1909 እ.ኤ.አ. ደቡባዊ ምዕራብ ጋና (ቀደም ሲል ጎልድ ኮስት) ንክሮፉል በምትባል ከተማ ነው። ንክሩማህ በካቶሊክ ሚሽነሪ ትምህርት ቤት ይማሩበት በነበረ ወቅት ብሩህ አዕምሮ እንደነበራቸው የተመሰከረላቸው ሲሆን ገና በአሥራዎቹ እድሜ ውስጥ እያሉ ነው በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ የሆኑት። ይሁንና ያለሥልጠና የጀመሩትን ትምህርት በ1926 እ.ኤ.አ. የአክራውን አቺሞታ ኮሌጅ ተቃለቅለው የመምህርነት ምሥክር ወረቀት በማግኘት በተለያዩ የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች አስተምረዋል። በ1935 እ.ኤ.አ. ወደ አሜሪካ በማቅናትም የፔንሴልቬኒያውን ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተቀላቅለው በኢኮኖሚክስና ሶሲዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በ1939 የተቀበሉ ሲሆን በ1942ም በሥነ-መለኮት ሌላ ድግሪ ከዚሁ ዪኒቨርሰቲ አግኝተዋል። በ1942 እና በ1943ም የማስተርስ ድግሪያቸውን ከፔንሴልቬኒያ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ትምህርትና በፍልስፍና ሠርተዋል። በአሜሪካ ቆይታቸውም በግራ ዘመም አሰተሳሰቦች በመማረከቸው የተነሳ በወቅቱ በሥርነቀል ለውጥ ፈላጊነታቸው ከሚታወቁ ምሁራን ጋር ቅርብ ግንኙነት መሥርተው ነበር። አፍሪካውያንን ያሰባሰበ የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሥራችና ግንባር ቀደም ተናጋሪ እንዲሁም የአፍሪካ አገራት ነፃ እንዲወጡና የአውሮፓ ቅኝ ግዛት እንዲያበቃ ቁርጠኛ አቋም ነበራቸው። ከዚሁ ጎን ለጎንም የተባበረች አፍሪካ አስፈላጊነትን በማመን አፍሪካውያንና የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው ሕዝቦች በአንድነት እንዲቆሙ የሚሰብከው ፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ነበሩ። በ1945 ወደ ለንደን ሕግና ኢኮኖሚክስ ለማጥናት ባመሩበት ወቅትም በማንችስተር እንግሊዝ የተካሄደውን 5ኛው የፓን አፍሪካን ጉባዔ እንዲካሄድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የአፍሪካን ከቅኝ ግዛት የመውጣት እንቅስቃሴ ለማስተባበርና ቅኝ አገዛዝን ለመቃውም የተደራጀው ጉባዔ ንክሩማህ ታዋቂ የጥቁር መብት ታጋዮችና የፀረ-ቅኝ ግዛት ንቅናቄ መሪዎች ጋር እንዲገናኙ ዕድል የሰጣቸው ሲሆን በ1946ም ጥናታቸውን ትተው በ5ኛው ጉባኤ የተቋቋመው የምዕራብ አፍሪካ ብሔራዊ ጽ/ቤት ዋና ጸኃፊና የምዕራብ አፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: በ1935 የትኛውን ዩንቨርሲቲ ተቀላቀለ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የፔንሴልቬኒያውን ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: አልፍሬድ ኢልግ በየት ሀገር ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በስዊትዘርላንድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nግሪክ ግሪክ ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋ አንድ ትንሽ አገር ነው። ከምሥራቅ ወደ ትንሽ እስያ፤ ከምዕራብ ወደ ኢጣሊያ አገር ከሁለቱም ወገን ርቀቱ ትክክል ነው። ግሪክ በሰሜን ወገን ከመቄዶንያ ይዋሰናል። ግሪክ ኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው። በደቡብና በምሥራቅ ወገን አያሌ ደሴቶች አሉ። ከእነርሱም በአያሌዎቹ መንደሮችና ከተሞች ተሠርተውባቸዋል። አንዱ አንቲፖሮስ ይባላል። በእዚህም ስፍራ ያለው ታላቅ ያጌጠ ዋሻ የታወቀ ስመ ጥሩ ነው። እኩሌቶቹም የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እየተወረወሩ የወጡ ይመስላሉ። እኩሌቶቹም ከጥንት ጀምረው ይታዩ የነበሩት ያሉበት አይታወቅም ጠፍተዋል። ይህ እንግዳ ነገር እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ከባሕር በታች የተነሳው እሳተ ገሞራ ነው። በደቡብ ግሪክ ወገን ባሉት ደሴቶች አየሩ በአሜሪካ እንዳለው እንደ ቨርጂኒያ ግዛት አየር ቀላል ነው። በዚህ አገር ብዙ አይነት ፍሬ ሁሉ ሞልቶዋል። በሰሜን በኩል ደግሞ አየሩ ቅዝቃዜ ያለበት ነው። በየጠረፉ የመርከብ መቋሚያዎች ወደቦች ይገኛሉ። ብዙዎቹ የአገሩ ሰዎችም መርከበኞች ናቸው። በደኑም ፓይን (ጥድ) የተባለው ጠንካራ ዛፍ ይገኛል። በላይኛው አውራጃ ኦክ የተባለው ዛፍ ይገኛል። ወደታች ባለው ክፍልም ቸስትነትና ዋልነት የሚባሉት ዕንጨቶች ይገኛሉ። በዚህ ስፍራ የሚገኘው ዋናው ነገር ደረቅ ፍራፍሬ፣ ዘቢብ፣ ጥጥ፣ ሐር ጠጉር፣ ሩዝ፣ ትንባሆና በቆሎ ነው። የእጅ ሥራ ጥቂት ነው። በቤት የተለመደ ሥራ እንደ ጥጥ እንደ ጠጉር እንደ ሐር የመሰለ ነገር ነው። ቀለም ማግባት ወይም መቀባት በጣም የተለመደ ከሆነ ብዙ ጊዜው ሆነው። ከዛፎች ፍሬ ዋነኛው ወይራ ሲሆን በብዛት ይተከላል። ወይን፣ በኽረ? ሎሚ፣ በለስ፣ አልሞንድ (ለውዝ)፣ ተምር፣ ሴትሮን፣ ፓሜግራኔት (ሮማን)፣ ኩሬንትም ይበቅላሉ። \n \nጥያቄ: ግሪክን በሰሜን ወገን የምታዋስናት ሀገር ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መቄዶንያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ በራድዮ የላከው ወደ የት ከተማ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nታሊየም የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ መረጃ መዝባሪዎች ቡድን ሚስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር እንደተቆጣጠረው ማይክሮ ሶፍት አስታወቀ፡፡ መቀመጫው ሰሜን ኮሪያ እንደሆነ የታመነው ይህ መረጃ መዝባሪ ቡድን የመንግስት ሰራተኞችን ፣ የዩኒቨርሲቲ ሰራተኞችን ፣ የኒውክሌር ሙያተኞችን እና የጥናት ተቋማንን ኢላማ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የመረጃ መዝባሪ ቡድኑ በዋነኝነት ኢላማ ያደረገው በአሜሪካ የሚገኙ ተቋማትን ሲሆን በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚገኙ ተቋማንንም ኢላማ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡ ታሊየም በመጀመሪያ እይታ ትክክለኛ ሆነው የሚታዩ የኢሜል አድራሻዎችን በመጠቀም መረጃ ሲመዘብር ነበር ተብሏል፡፡ ማይክሮሶፍትም በአሁን ወቅት መረጃ መዝባሪ ቡድኑ የሚጠቀምባቸውን 50 የድር ጎራዎች መቆጣጠሩን የገለፀ ሲሆን በምሥራቃዊ ቨርጂኒያ አውራጃ በሚገኝ ፍርድ ቤት በጠለፋ ቡድን ላይ ክስ መመስረቱን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡-ሮይተርስ \n \nጥያቄ: ማይክሮሶፍት ታሊየም የመዘበራቸውን ስንት የድር መደቦችን ተቆጣጠረ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 50 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየኢትዮጵያ ሙዚቃ የመጀመሪያውን ግራማፎን ወይም የሸክላ ማጫወቻ በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ሊዋንቲቭ ለዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አመጡላቸው። ይኸውም ማጫወት ብቻ እንጂ ድምጽ አይቀዳም ነበር። በኋላ ግን በዓመቱ በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ከንግሥት ቪክቶሪያ የተላኩ የእንግሊዝ መልዕክተኞች በመጡ ጊዜ ግራማፎኑንና ድምፅ መቅጃውን ይዘውላቸው መጡ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸው በዲስክ የተቀረፁት ዓፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ናቸው። ዛሬ በእንግሊዝ አገር በለንደን ከተማ ብሪቲሽ ኢንስቲቲውት ኦፍ ሪኮርድ ሳውንድ በተባለው ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ በሸክላ የተቀረፀው የመጀመሪያው ዜማ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ስራዎች ሲሆኑ ዘመኑም በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ነበር። ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በጀርመን ቆይታቸው ወቅት የጀርመን የሙዚቃ ድርጅት ጠይቋቸው የኢትዮጵያ መዲናና ዘለሰኛ ዜማዎች በ፲፯ አይነት ስልት እየተጫወቱ ተቀርፀዋል። ኩባንያው የተሰማ እሸቴን ዜማዎች በ፲፯ ሸክላዎች የቀረፀው ሲሆን ለዜማው ባለቤት የድካም ዋጋ እንዲሆን በወቅቱ ፲፯ ሺህ የጀርመን ማርክ ከፍሏቸዋል። በዘመኑ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያም አሁንም እነዚህ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ብርቅዬ ሸክላዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ። እነዚህ በተቋሙ እጅ ያሉት ፲፮ ሸክላዎች እያንዳንዳቸው ሁለት ዜማዎችን የያዙ ሲሆኑ ባጠቃላይ ፴፪ ዜማዎች ተቀርፀውባቸዋል። እያንዳንዱ የሸክላው ገፅ ላይ A ወይም B ተብሎ ተሰይሟል፣ የዜማው ስም ተፅፎበታል፣ የዜማው ባለቤት ተሰማ እሸቴ ስም አለ፣ ሸክላው ጀርመን ሀገር መሰራቱ እንዲሁም የሸክላው ቁጥር ተጠቅሷል። በ፲፱፻፳፭-፳፮ ዓ.ም. አካባቢ የእነ ፈረደ ጎላ፣ ንጋቷ ከልካይና ተሻለ መንግሥቱ የዜማ ሸክላዎች ብቅ እስከሚሉ ድረስ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ሸክላዎች ከ፳ ዓመታት በላይ አቅም ባላቸው ቤተሰቦች ዘንድ በብቸኝነት በግራማፎን ሲደመጡ ቆይተዋል። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸው በዲስክ የተቀረፁት እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዓፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ የነገሱበት ዘመን ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ዋና መዲና ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዳካር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ በብራዚል በስንት ከተሞች ይካሄዳል ይዘጋጃል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 15/2012 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሰራተኞቹ ጋር በሬድዬ ግንኙነት በመፍጠር አገልግሎቱን የሚያቀላጥፍበት የአስትሮ ሞቶሮላ የሬድዬ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት አስመረቀ። የፕሮጀክቱ ምረቃ ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር በተገኙበት በእንጦጦ ማሪያም የቴሌ ማይክሮዌቭ ማሰራጭያ ጣቢያ ተካሂዷል። በሁለት ምዕራፍ የተከፈለውን ፕሮጀክት ወደ ሥራ ለማስገባት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ሐምሌ 15 /2017 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና በሞቶሮላ ሶሉሽን ኩባንያ መካከል ስምምነት ተፈርሞ ነበር። የመጀመሪያው ምዕራፍ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአዲስ አበባና ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ኦሮሚያ ዞን ላይ ተግባራዊ ሆኗል። የኤሌክትሪክ የአገልግሎት አሰራሩን በማቀላጠፍ ለዜጎች የተሻለ አገልግሎት እንደሚሰጥ የታመነበት ይሄው ፕሮጀክት 6 ቡድኖችን በመያዝ በ 8 የግንኙነት ቻናሎች በጋራ እና በእኩል ሁኔታ እንዲጠቀሙ የሚያግዝ ነውም ተብሏል። የአስቸኳይ ጥገና ሥራን ማቀላጠፍ፣ ከሰብ ስቴሽን ጋር የሚኖረውን ግኝኑነት ማሳለጥ፣ በግንኙነት ክፍተት ሊፈጠሩ የሚችሉ የሰውና የንብረት አደጋን መቀነስ እንዲሁም የኃላፊዎችን መረጃ የመቀበልና መልዕክት የማስተላለፍ ሥራውን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገልጿል። በኤሌክትሪክ አገልግሎት የአውቶሜሽንና ኢነርጂ ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደመቀ ሮቢ አገልግሎቱ ስራውን የሚያከናውነው በስልክ እንደነበር አስታውሰው ይህም የሚሰጠው አገልግሎት ቅልጥፍና እንዳይኖረው አድርጎት ቆይቷል ይላሉ። ዛሬ የተመረቀው የሬድዮ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት መስክ የወጡ የጥገና ሰራተኞች ቢሮ ካሉ ሰራተኞች ጋር በፍጥነት እንዲገናኙ ከማድረጉም ባለፈ ከፍተኛና ዝቅተኛ ኃይል መስመር ላይ ካሉ ኦፕሬተሮች ጋርም በቀላሉ በመገናኘት ፍጥነት ያለው የጥገና አገልግሎቶች እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። በዚሁ የመጀመሪያው ምዕራፍም በአዲስ አበባና ዙሪያ በእጅ የሚያዙ 300 እንዲሁም 200 መኪና ላይ የሚገጠሙና 100 በጥሪ ማዕከልና በአስቸኳይ ጥገና ማዕከላት ላይ የሚገጠሙ ዲጂታል ሬዲዮኖች ጥቅም ላይ ውለዋል። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ ምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክቱንም ለማካሄድ ከአዲስ አበባ ውጪ 8 ከተሞች የተመረጡ ሲሆን ለዚህም ከ4 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት ተይዞለታል። \n \nጥያቄ: የሬዲዮ መገናኛው የመጀመሪያ ምዕራፍ ምን ያህል ገንዘብ አስወጥቷል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: የኮንግ-ፉጸ ትምህርት በመንግስት ይፋ የሆነው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ148 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበጀት በጀት ማለት ለወደፊቱ የሚመጣን ገቢና ወጪ የሚተነብይ የንዋይ/ገንዘብ እቅድ ነው። በዚህ እቅድ ውስጥ ቁጠባ፣ ብድር እና ወጪ ይካተታሉ ። ግለሰቦች ወይንም ቢዝነሶች ገቢና ወጪያቸው ሲመረመር ከሞላ ጎደል ቋሚ ሆኖ ስለሚገኝ የበጀት ጥቅም ከዚህ ይመነጫል። ማለት፣ ቋሚ ገቢ ወጪ፣ ለወደፊት ይሚሆነን ለመተንበይ አመቺ ነው። ተንብዮ በበጀት መመራት ግለሰቦብ በገንዘባቸው/ንዋያቸው ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖራቸው ያደርጋል። አላስፈላጊ ወጭወችን ለመለየት እና በአቅም መኖርን ለማወቅ ይረዳል። የበጀት ዋናው ጥቅም አንድ ግለሰብ በራሱ ገቢና ወጪ ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖረው ማስቻሉ ነው። ስለሆነም ግለሰቦች ዕዳ ውስጥ መግባት ሲጀምሩ በቶሎ እንዲያውቁ ይሆናሉ። ስለሆነም ችግሩ ከመባባሱ በፊት አስቀድመው እርምጃ ለመውሰድ ይችላሉ። አንድ ግለሰብ ዕዳ ውስጥ እየገባ መሆኑን መረዳት ሲጀመር መጀመሪያውኑ የዕዳውን አይነት መለየት አስፈላጊ ነው። ቅድሚያ ትኩረት አግኝተው መከፈል ያለባቸው እማይለወጡ ዕዳወች (ምሳሌ ሞርጌጅ፣ የቤት ኪራይ ..) እና ቀስ ብለው ሊከፍሉ የሚችሉ ተለዋዋጭ ዕዳዎች (ምግብ፣ የኤሌክትሪክ፣ ውሃ ና ሌሎች በጥንቃቄ ሊቀነሱ የሚችሉ ቢሎች) ተለየተው ሊታወቁ ይገባል። ዕዳዎቹ ከተለዩ በሗላ፣ ዕዳዎቹን ለማስወገድ መንገድ ማበጀት ተገቢ ነው። ለዚህ ተግባር እንዲረዳ «በደህና ጊዜ» በትንሽ በትንሹ ማጠራቀም ጥሩ ነው። ነገር ግን ይህ ተደርጎ ካልሆነ፣ ቀሪ እዳን ቀስ በቀስ ለመክፍል የሚያስችል ስምምነት ከዕዳ-ሰጪው ጋር መግባት ጥሩ ነው። ባንኮች የአንድ ግለሰብ ዕዳ ባለቤት ከሆኑ፣ ግለሰቡን ለመርዳት ፍላጎት ይኖራቸዋል፣ ምክንያቱም ከርሱ ነውና ገንዘብ የሚያገኙት። ለዚህ ተግባር እንዲረዳ ኮንሶሊዴሽን (ሁሉን ዕዳን በአንድ ላይ መሰብሰብ) እና ሪፋይናንሲንግ (ብድርን፣ በተራዘመ ጊዜ እንዲከፍሉ ማስቻል) የሚባሉ ሁለት መሳሪያወችን ባንኮች ይጠቀማሉ። እኒህን ማግኘት እዳ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይወጣ ይረዳሉ። ሆኖም እኒህ እድሎች ካልተገኙ ዴቢት ስፔሻሊስት የተሰኙ መካሪዎችን ማነጋገር ይቻላል። \n \nጥያቄ: አንድ ግለሰብ ዕዳ ውስጥ እየገባ መሆኑን መረዳት ሲጀመር መጀመሪያ ምን ማረግ አለበት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የዕዳውን አይነት መለየት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፋሽስት ቅዲስቲቱዋን ኢትዮጵያን ለማዋረድ ለመዝረፍና ለመግዛት ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ዝግጅቱን አጠናቆ በ1928 ዓም 300, 000 ሰራዊት 160 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች 450 ታንኮች 2000 የመጉዋጉዋዣ መኪናዎችን በማሰማራት ድንበር አልፎ ጦርነት በመክፈት ከገጠር እስከ ከተማ ህዝቡን ያለ እርህራሄ ጨፈጨፈ። በዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ላይ የመጀመሪያውን ህይወት ያለዉን ነገር ሁሉ የሚያጠፋውን “ማስተርድ ጋዝ” የሚባል ኬሚካል መሳሪያ በመጠቀም ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል ፈጸመ። በዚያን ክፉ ቀን የነጻነትና የሀገር ትርጉም የገባቸው የቁርጥ ቀን ልጆች በየአካባቢያቸው ፋኖዎችን በመምራት የእብሪተኛዉን የፋሽ ስት ጦር መግቢያ መዉጫ በማሳጣት ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰላም መኖር እንደማይችል ተስፋ አስቆርጠዉታል። ከነዚህ ነበልባል የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች መካከል ጠላትን በተከታታይ ዝርክርኩን አዉጥተው ከደቡብ ያሳደዱትና በመጨረሻው ዉጊያ ላይ ኢትዮጵያዊ በሚመስሉ የትግሬ ስርጎ ገብ ባንዶች ቆሰለው የተያዙትና በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ዉዱ የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ልጅ ራስ ደስታ ዳምጠው ነበሩ። ራስ ደስታ ዳምጠዉን ያስያዛቸው የባንዳ ጦር መሪ ደግሞ የትግሬው ተክሉ መሸሻ የሚባል የጣሊያን ሎሌ ሲሆን የስብሃት ነጋ አጎት የናቱ ታላቅ ወንድም መሆኑ ተረጋግጦአል ተክሉ መሸሻ በጣሊያን ደጃዝማችነት ተሰጥቶት በደቡብ ኢትዮጵያ የኢጣልያ ባንዳ ጦር አዛዥ ሆኖ በአካባቢው ኢትዮጵያ ጦር አዛዥ የነበሩት ራስ ደስታ ዳምጠው ከበርካታ አስደናቂ ጀብዱ በሁዋላ ቆስለው በጉራጌ አካባቢ መስቃ ከተባለው ሥፍራ ተኝተው በስቃይ ላይ እያሉ ተክሉ የስለላ መረቡን ዘርግቶ እግር በግር ተከታትሎ በመያዝ ከግንድ ጋር አስሮ በጭካኔ ደብድቦ ከገደላቸው በኋላ ራሳቸውን ረግጦ በመቆም ፎተግራፍ በመነሳት ለጣልያኑ ጌታው ግዳይ ካቀረቡት እርካሽ የትግሬ ከሃዲዎች አን ዱ ነበር። የፋሽስት ጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን ወሮ መናገሻ ከተማዋን አዲስ አበባን ለመያዝ ሲገሰግስ ጀምሮ ሶስቱ ቆራጥ የኢትዮጵያ ሌጆች (የሸንቁጥ) ልጆች አበበ ሸንቁጥ ተሾመ ሸንቁጥና ጥላሁን ሸንቁጥ በመርሃቤቴ በጅሩና በዠማ ወንዝ አካባቢ በመንቀሳቀስ “ዱሩ ቤቴ” በማለት ብዙ የአካባቢውን ጀግኖች አስከትለው የጣሊያንን ሀይል በመመከትና ከአገር በማባረር ከፍተኛ ገድል ፈጽመዋል። \n \nጥያቄ: ፋሺሽት ጣልያን ድጋሚ ኢትዮጵያን ሲወር የተጠቀመበት መርዛማ ኬሚካል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማስተርድ ጋዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: ጋቦን ነፃነቷን ከተቀዳጀች በኋላ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት የሆኑት ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሊዮን ምባ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዩናይትድ ኪንግደም ዩናይትድ ኪንግደም ማለት የተባበረው ግዛት በተለመደው እንግሊዝ አገር ሲባል፣ እንዲያውም እንግሊዝ አገር ወይም ደግሞ «ኢንግላንድ» ከዩናይትድ ኪንግደም ዋና ክፍላገሮች አንዱ ብቻ ነው። ሌሎቹም፦ ስኮትላንድ ዌልስ ሰሜን አይርላንድ ናቸው። ከነዚህም እንግሊዝ፣ ስኮትላንድና ዌልስ አብረው «ታላቋ ብሪታንያ» የምትባል ደሴት ናቸው። ከ1699 ዓ.ም. (1707 እ.ኤ.አ.) አስቀድሞ፣ እንግሊዝና ስኮትላንድ የተለያዩ ንጉዛት ነበሩ። ከ1595 ዓ.ም. ጀምሮ ግን 2ቱ አገራት አንድ ንጉሥ ነበራቸውና በ1699 በመዋሐዳቸው አንድ ላይ «ዩናይትድ ኪንግደም» ሆነዋል። \n \nጥያቄ: እንግሊዝ፣ ስኮትላንድና ዌልስ አብረው በመሆን የፈጠሯት ደሴት ማን በመባል ትታወቃለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ታላቋ ብሪታንያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: ከኢትዮጵያ በፊት ሲምፖዚየሙን ያዘጋጁ ሁለት አፍሪካዊ ሀገራትን ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሆ ቺ ሚን ሆ ቺ ሚን ከ1890-1969 እ.ኤ.አ. የኖረ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሥራችና መሪ ነበር። ሆ ቺ ሚን ከወጣትነት ጊዜው ጀምሮ ለአብዮታዊ ተግባራት የቆመ ነበር። ሆ ቺ ሚን በሥራ ምክንያት ፈረንሳይ ውስጥ በነበረበት ወቅት የካፒታሊስት ሥርዓት ምን ያህል ሠርቶአድሩን ሕዝብ ለሥቃይና ለመከራ እንደዳረገውና የዓለም ወዛደሮች በቀለም በቋንቋና በባህል ቢለያዩም ብሶታቸው አንድ መሆኑን በቅርብ ተገነዘበ። በአፍሪካና በእስያ የኢምፔሪያሊስቶች መምጣት ምን ያህል ሥቃይና ውርደት በእነዚህ ሕዝቦች ላይ እንዳደረሰ ተረዳ። በዚህም ምክንያት ሆ ቺ ሚን የቬትናም ሕዝብ ጠላት የፈረንሳይ ኢምፔሪያሊዝም እንጂ የፈረንሳይ መላው ሕዝብ አለመሆኑን ደጋግሞ ገልጿል። ሆ ቺ ሚን በ1917 እ.ኤ.አ. በፈረንሳይ ወዝአደሮች ትግል ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊ በመሆን የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲ አባል ሆነ። ከዚህም በላይ በፈረንሳይ የቬትናም አርበኞችን ማኅበር በማቋቋም በፈረንሳይ ይኖሩ የነበሩትን ቬትናማውያን በማንቃትና በማስተማር ለሀገራቸው ነፃነትና ክብር እንዲታገሉ ያነሣሣ ነበር። የጥቅምቱ የሩሲያ አብዮት ለአያሌ ዓመታት በዓለም ሰፍኖ የነበረውን የኢምፔሪያሊዝም ብቸኛ የበላይነት ሰባብሮ አዲስ ዘመን በማብሰሩ ሆ ቺ ሚን የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ የቦልሼቪኮችን ፈለግ መከተል እንዳለበት አመነ። በሆ ቺ ሚን አስተሳሰብ የቬትናም ብቻ ሳይሆን የሌሎች ቅኝ ተገዥ የሆኑ ሀገሮች ነፃነት የሚገኘው የወዝአደሩን የአብዮት ጎዳና በመከተል ብቻ እንደሆነ አጥብቆ ያምን ነበር። የነዚህ ሀገሮች ብሔራዊ ነፃነት ከማኅበራዊ ነፃነት ጋር መያያዙንና ይህም ነፃነት ከሶሻሊዝምና ከኮሚኒዝም ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን አስገንዝቧል። ሆ ቺ ሚን ከ1924 እስከ 1930 እ.ኤ.አ. በቻይናና በቬትናም በመዘዋወር ለዚህ ውስብስብ ትግል ግንባር ቀደም አመራር ሊሰጥ የሚችለውን ማርክሳዊ ሌኒናዊ ፓርቲ ለማቋቋም ከፍተኛ ትግል አደረገ። በመጀመሪያም የቬትናም አብዮታዊ ወጣቶች ማኅበር የተባለውን በማቋቋም «ወጣት» በተባለው ጋዜጣ ወጣቱን ለትግል ቀሰቀሰ። በዚህ ዓይነት ከብዙ ጥረትና ትግል በኋላም በ1930 እ.ኤ.አ. የኢንዶቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን (ኋላ የቬትናም ሠራተኞች ፓርቲ፤ ዛሬ ደግሞ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ) መሠረተ። በ1935 እ.ኤ.አ. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደው የኮሚኒስቶች ስብሰባ አንድ ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት የሆነ ዲሞክራሲያዊ ግንባር እንዲቋቋም በወሰነው መሠረት ሆ ቺ ሚን ቬትሚን የተሰኘውን ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት ግንባር በማቋቋም መላውን ሕዝብ በትግሉ ለማሳተፍ ችሏል። ዲየን ቢየን ፉ በተባለው ታሪካዊ ስፍራ የቬትናም አርበኞች የፈረንሳይን ጦር በማሸነፋቸው ፈረንሳይ በጀኔቩ ስምምነት መሠረት የቬትናምን አንድነት በማወቅ የሰላም ውል ፈረመች። ነገር ግን ከ1955 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም በፈረንሳይ እግር በመተካት የደቡቡን ክፍል ለመቁረስ የጦር ሰፈር በመሥራትና በውስጥ አርበኞች በመጠቀም ጦርነት ከፈተ። ነገር ግን አሜሪካ ከግማሽ ሚሊዮን ወታደሮች በላይና በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ቢያፈስም ቬትናምን ሊያሸንፍ አልቻለም። \n \nጥያቄ: ሆ ቺ ሚን የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲን መቼ ተቀላቀለ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1917 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች አሉ። እነዚህም መሣሪያዎች የጅማት፣ የትንፋሽና የምት ተብለው ወደ ሶስት ይከፈላሉ። የክር ሙዚቃ መሣሪያዎች ድምጽ የሚሰጡት በንዝረት ነው፤ ክራር መሰንቆ ከዚህ የሙዚቃ መሳርያዎች ወገን ይመደባሉ፡፡ የትንፋሽ ሙዚቃ መሣሪያዎች ድምጽ የሚሰጡት በትንፋሽ ኃይል ነው ምሳሌ ዋሽንት። የምት የሙዚቃ መሣርያ እንደ ከበሮ ሲመቱ ድምጽ የሚያወጡ ናቸው። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የባህል ሙዚቃ መሳሪያዎች ስንት መደብ አላቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሶስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: በሳውዲ በነዳጅ ምርቱዋ ከአለም ስንተኛ ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሁለተኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት ጣልያንን ስታሸንፍ ንጉሡ ማን ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ወላጅ አባታቸው ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደጃዝማች ወልደሚካኤል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ላይ የሚሰራውን የተ.መ.ድ አካል (UNAIDS) ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ እና የዩኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን በኢትዮጵያ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተያዙ ዕቅዶች ላይ መምከራቸውን ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴና የዩኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ የተመካከሩት በምን ዙሪያ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በኢትዮጵያ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተያዙ ዕቅዶች ላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና በጣም ትንሽ በሆነ ርቀት ማለትም በመቶ ሜትሮች በሚቆጠር የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከዛምቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ የመጀመሪያው መጽሐፍ ምን ይባል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያውያኑ የልዑል አለማየሁ ሞግዚቶች ስማቸው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: የቶማስ ጄፈርሰን ወላጅ እናት ማናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጄን ራንዶልፍ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ596 ዓ.ም. በጃፓን 17 አንቀጽ ያለ ሕገ መንግሥት በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ ይታመናል። እንዲሁም በ614 ዓ.ም. ከነቢዩ መሐመድ የወጣው የመዲና ሕገ መንግሥት ዕጅግ ጥንታዊ ምሳሌ ነው። በዌልስ በ940 ዓ.ም. አካባቢ ንጉስ ህወል ዳ ሕጎቹን ጻፉ። በዛሬው ሩሲያ ደግሞ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ጥበበኛው ፕራቭዳ ያሮስላቫ የተባለውን ሕገ መንግሥት በ1009 ዓ.ም. ያህል ሠሩ። ይህ ሕግ በ1046 ታድሶ በኪዬቭ ሩስ በሙሉ ህጝ ሆነ። በስሜን አሜሪካ የኖሩ ኗሪ ጎሣ ሆደነሾኒ 'የአፈ ቃል' ሕገ መንግሥት «ጋያነሸጎዋ» የነበራችው ከ1080-1140 ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ሕግ በከፊል ለአሜሪካ ሕገ መንግሥት ተጽእኖ እንደነበረው ይታመናልና የአሜሪካ ምክር ቤት በ1981 ዓ.ም. ይህንን ግንዛቤ አስታወቀ። በእንግሊዝ አገር በ1092 ዓ.ም. ንጉስ 1 ሄንሪ የነጻነት ሥርአት የተባለውን ሰነድ አዋጀ። ይህ መጀመርያ የንጉሱን ሥልጣን ወሰኖ ንጉሡ ለቤተ ካህናትና ለቤተ መሳፍንት ወገኖች የሚገባውን እንቅብቃቤ ገለጸ። ይህም መሰረት በመኳንንቱ ሲዘረጋ በ1207 ዓ.ም. የእንግሊዝ ንጉሱን ዮሃንስ (ጆን) ማግና ካርታ («ታላቅ ሥርዓት») የሚባለውን ሰነድ እንዲፈርሙት አስገደዱዋቸው። ከዚሁ መሃል ቁም ነገር የሆነው ንጉሡ ያለ ሕጋዊ ሂደት ማንንም ሰው እንዳይገድሉ፣ ከአገር እንዳያሳደዱ፣ ወይም እስር ቤት እንዳያስገቡ ከለከላቸው። በዚያ ወቅት ያ ሰነድ በእንግሊዝ አገር የነጻነት መሠረት ሆነ። በ1212 እና 1222 ዓ.ም. መካከል አንድ የሳቅሰን አስተዳዳሪ አይከ ቮን ረፕጎቭ ያቀነባበረው ሕግጋት ሳቅሰንሽፒግል በአንዳንድ ጀርመን ክፍላገር እስከ 1892 ዓ.ም. ድረስ ላይኛ ሕገ መንግሥት ሆነ። በ1228 ዓ.ም. ሱንዲያታ ከይታ ማሊ መንግሥትን ለማወሐድ የ'አፈ ቃል' ሕገ መንግሥት አወጡ። ይህ ሕግ 'ኩሩካን ፉጋ' ተብሎ ነበር። \n \nጥያቄ: በዛሬው ሩሲያ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ሕገ መንግሥቱን ያዘጋጀው መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1009 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ ለስንት አመት በእስር ቆዩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ለሦስት ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንጉሠ ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ ከመቼ ጀምሮ በመሪነት ኢትዮጵያን መሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ የተወለደው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: አልፍሬድ ኢልግ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ ውስጥ በየዓመቱ ስንት ማደያዎች ለመክፈት አቅዷል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዘጠኝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nግሪክ ግሪክ ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋ አንድ ትንሽ አገር ነው። ከምሥራቅ ወደ ትንሽ እስያ፤ ከምዕራብ ወደ ኢጣሊያ አገር ከሁለቱም ወገን ርቀቱ ትክክል ነው። ግሪክ በሰሜን ወገን ከመቄዶንያ ይዋሰናል። ግሪክ ኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው። በደቡብና በምሥራቅ ወገን አያሌ ደሴቶች አሉ። ከእነርሱም በአያሌዎቹ መንደሮችና ከተሞች ተሠርተውባቸዋል። አንዱ አንቲፖሮስ ይባላል። በእዚህም ስፍራ ያለው ታላቅ ያጌጠ ዋሻ የታወቀ ስመ ጥሩ ነው። እኩሌቶቹም የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እየተወረወሩ የወጡ ይመስላሉ። እኩሌቶቹም ከጥንት ጀምረው ይታዩ የነበሩት ያሉበት አይታወቅም ጠፍተዋል። ይህ እንግዳ ነገር እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ከባሕር በታች የተነሳው እሳተ ገሞራ ነው። በደቡብ ግሪክ ወገን ባሉት ደሴቶች አየሩ በአሜሪካ እንዳለው እንደ ቨርጂኒያ ግዛት አየር ቀላል ነው። በዚህ አገር ብዙ አይነት ፍሬ ሁሉ ሞልቶዋል። በሰሜን በኩል ደግሞ አየሩ ቅዝቃዜ ያለበት ነው። በየጠረፉ የመርከብ መቋሚያዎች ወደቦች ይገኛሉ። ብዙዎቹ የአገሩ ሰዎችም መርከበኞች ናቸው። በደኑም ፓይን (ጥድ) የተባለው ጠንካራ ዛፍ ይገኛል። በላይኛው አውራጃ ኦክ የተባለው ዛፍ ይገኛል። ወደታች ባለው ክፍልም ቸስትነትና ዋልነት የሚባሉት ዕንጨቶች ይገኛሉ። በዚህ ስፍራ የሚገኘው ዋናው ነገር ደረቅ ፍራፍሬ፣ ዘቢብ፣ ጥጥ፣ ሐር ጠጉር፣ ሩዝ፣ ትንባሆና በቆሎ ነው። የእጅ ሥራ ጥቂት ነው። በቤት የተለመደ ሥራ እንደ ጥጥ እንደ ጠጉር እንደ ሐር የመሰለ ነገር ነው። ቀለም ማግባት ወይም መቀባት በጣም የተለመደ ከሆነ ብዙ ጊዜው ሆነው። ከዛፎች ፍሬ ዋነኛው ወይራ ሲሆን በብዛት ይተከላል። ወይን፣ በኽረ? ሎሚ፣ በለስ፣ አልሞንድ (ለውዝ)፣ ተምር፣ ሴትሮን፣ ፓሜግራኔት (ሮማን)፣ ኩሬንትም ይበቅላሉ። \n \nጥያቄ: ግሪክ በደሴቶቿ ከሰራቻቸው ከተሞች መካከል የሆነው ከተማ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አንቲፖሮስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ የሰዎች ስብስብ ምን በመባል ይታወቃል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። ባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። \n \nጥያቄ: ኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ዋና ዓላማው ምንድን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር ሕይወቱን ያጠፋው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት ሰባት ወራት 169 ቢሊየን 501 ሚሊየን 789 ሺህ 893 ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ አፈፃጸሙ ከዕቅድም ሆነ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ የታየበት መሆኑን ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው አስታውቀዋል፡፡ ሚኒስቴሩ 169 ቢሊየን ብር 408 ሚሊየን 889 ሺህ 4 ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የእቅዱን 100 ነጥብ 5 በመቶ ማሳካት መቻሉንም ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የገቢዎች ሚኒስቴር አቶ ላቀ አያሌው ለመሰብሰብ ከታቀደው ግብር በመቶኛ ምን ያህል እንደተሰበሰበ ገለጹ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 100 ነጥብ 5 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: የላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት አንዷ መስራችና ዋና ኃላፊ ስማቸው ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: ወጣት እበ ለገሰ ስንት ሰዎች የሚያሳፍር ሔሊኮፕተር ሰርቶ አሳየ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሶስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት ያገለገለው በየትኛው ትምህርት ቤት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ከሠራቸው አንዱ አዋሽ ወንዝ ላይ ያቆመው ድልድይ ነው። ስለዚህ ድልድይ ሥራ ኢልግ ሲጽፍ፤ የመጀመሪያው የድልድይ ሥራ እንደነበረና የድልድዩ ቋሚዎች በሰው ሸክም አሥራ አምስት ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንደመጡ ይተርክና ሥራውን በሐሩር እና በዶፍ እንዲሁም በማታ የዱር አራዊትን በመቋቋም እራሱ ድንጋይ እየጠረበ፣ ምስማር፣ ችንካር እና ብሎን እያቀለጠ እየቀጠቀጠ እንደሠራው ይነግረናል። ምኒልክ በሸዋ ንጉሥ ከሆኑ በኋላ ሐዲድ አዘርግተው ባቡር ለማስገባት አሰቡ። ይህም ሀሳባቸው እንዲፈቀድላቸው የበላያቸውን ንጉሠ ነገሥቱን አጤ ዮሐንስን ፈቃድ ጠየቁ። በአጤ ዮሐንስ አካባቢ የነበሩ መኳንንቶች መክረው ምኒልክ ከግዛታቸው ከሸዋ ውጭ ሐዲድ ለመዘርጋት እንደማይችሉ ተነገራቸው። በሳቸው መቸኮልና መጓጓት ምክንያት አልፍሬድ ኢልግ በሥራና በሀሳብ ተጠምዶ እንደነበር ወዲያውም ለጃንሆይ ምኒልክ የሞዴል ባቡር ተጎታች ጋሪዎችን እየጎተተ በሐዲድ ላይ ሲሄድ የሚያሳይ ሠርቶ ሲያሳያቸው በጣም እንደተደሰቱ ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፋቸው ዘግበዋል። ከዓፄ ዮሐንስ ሞት በኋላ ምኒልክ የንጉሠ ነግሥትነትን ዘውድ በጥቅምት ወር ጭነው ወዲያው በኅዳር ወር ላይ የምድር ባቡርን ሥራ አንቀሳቅሰዋል። ለዚህም ኢልግ ከማንኛውም ኩባንያ ጋር ተዋውሎ ሐዲዱን ለማሠራት የሚችልበትን ፈቃድና የሚዋዋልበትን የውል ዓይነት መጋቢት ፩ ቀን ፲፰፻፹፮ ዓ/ም አስጽፈው በማህተማቸው አትመው ሰጡት። ኢልግም ፓሪስ ከተማ ላይ ቢሮ ከፍቶ ለሥራው የሚያስፈልገውን መዋእለ ነዋይ፤ ሥራውን የሚኮናተሩ ድርጅቶችን እና ሌላም ጥናቶችን ማቀናበር ጀመረ። የዚህ የምድር ባቡር መሥመር ከጂቡቲ ወደብ ተነስቶ አዲስ አበባ ድረስ ፯፻፹፬ ኪሎ ሜትር ሲሆን ሥራው በ፲፰፻፺ ዓ/ም ተጀምሮ ከሀያ ዓመታት በኋላ በ ፲፱፱፻፲ ዓ/ም ተገባደደ። መቸም የኃሳቡ ጸንሳሽ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክም ሆኑ ሕልማቸውን ዕውን በማድረግ ብዙ አስተዋጽዖ ያስመዘገበው ኢልግም ፍጻሜውን ባያዩትም በኢትዮጵያ የምድር ባቡርን ስናስብ የነዚህ የሁለቱ ሰዎች ትዝታ በታሪክ ተመዝግቦ ይኖራል። \n \nጥያቄ: የምድር ባቡር መስመር መሰራት የተጀመረው ከስንት ዓ.ም ጀምሮ ነው ምን ያህል ጊዜስ ፈጀ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፲፰፻፺ ዓ/ም ተጀምሮ ከሀያ ዓመታት በኋላ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1981 ዓ.ም. ንጉሥ ሌቤንጉላ የማዕድን ማውጣት ፈቃድ የሰጠው ለማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሴሲል ሮድስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ላይ የሚሰራውን የተ.መ.ድ አካል (UNAIDS) ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ እና የዩኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን በኢትዮጵያ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተያዙ ዕቅዶች ላይ መምከራቸውን ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: የዩኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ በኢትዮጵያ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ስርጭት የሚገታበትን ሁኔታ ከማን ጋር ተመካከሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የብሪታንያ ደቡብ አፍሪካ ድርጅት የዛምቤዚያን ስም ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ብሎ ቀየረው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1887 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳምሱ-ዲታና ሳምሱ-ዲታና ከ1538 እስከ 1507 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር) ድረስ የባቢሎን ንጉሥ ነበር። የአሚ-ሳዱቃ ልጅና ወራሽ ሲሆን፣ ሳምሱ-ዲታና የባቢሎን (የሃሙራቢ ሥርወ መንግሥት) መጨረሻ ንጉሥ ነበረ። የዘመኑ አመት ስሞች ምንም ዘመቻ ስለማይጠቅሱ ሰላማዊ ዘመን ይመስል ነበር፣ ወደ ደቡቡ ግን የባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት ንጉሥ ጉልኪሻር ከሳምሱ-ዲታና ጋር እንደ ታገለ በአንድ ታሪክ ጽላት ተቀረጸ። በ1507 ዓክልበ. የሐቲ (ኬጥያውያን) ንጉሥ 1 ሙርሲሊ እስከ ባቢሎን ድረስ ዘመተና ከተማውን ዘርፎ አቃጠለው። የኬጥያውያን ሠራዊት የባቢሎን ምስሎች (ጣኦታት) ወደ ሐቲ አገር ወሰዱ፤ ሳምሱ-ዲታናም እንደ ተገደለ ይመስላል። ይህ የሚታወቀው ከባቢሎን ዜና መዋዕል «በሳምሱ-ዲታና ዘመን፣ ኬጥያውያን ወደ አካድ መጡ» ሲዘገብ፣ ደግሞ በኬጥኛ የተለፒኑ ዜና መዋዕል እንደሚለው «እርሱ (ሙርሲሊ) ወደ ሐላብ ሔዶ አጠፋው፤ የሐላብን ምርኮ ወደ ሐቱሻ ወሰደ፤ ከዚያም እስከ ባቢሎን ድረስ ሔዶ አጠፋው፣ ሑራውያንንም አሸነፋቸው፣ የባቢሎንን ምርኮ ወደ ሐቱሻ ወሰደው።» \n \nጥያቄ: የሃሙራቢ ሥርወ መንግሥት መጨረሻ ንጉሥ ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሳምሱ-ዲታና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኤንመርካር ኤንመርካር በሱመር (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የኡሩክ (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የኡቱ ልጅ መስኪያጝካሸር ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከኤአና ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል። የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። «ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ» በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የጸሓይ አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በኤሪዱም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ አራታ እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል። በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት ሹቡር፣ ሐማዚ፣ ሱመር፣ ኡሪ-ኪ (የአካድ ዙርያ) እና የማርቱ አገር ናቸው። ከዚህ በላይ የኤንመርካርን መንግሥት የሚገልጹ ሦስት ተጨማሪ ጽሑፎች አሉ። «ኤንመርካርና ኤንሱሕጊርዓና» የሚባል ተረት የኤንመርካርና የአራታ መቀያየም ሲገልጽ፣ ሐማዚ ተሸንፎ እንደ ነበር ይጠቅሳል። በ«ሉጋልባንዳ በተራራ ዋሻ»፣ ኤንመርካር በአራታ ላይ ዘመቻ ሲመራ ይታያል። አራተኛውና መጨረሻውም ጽላት፣ «ሉጋልባንዳና የአንዙድ ወፍ» ኤንመርካርና ሠራዊቱ በአራታ ዙሪያ ለ1 አመት እንደ ከበቡት ይላል። ለመሆኑ ኤንመርካር 50 አመት ከነገሰ በኋላ፣ የማርቱ ሕዝብ (አሞራውያን) በሱመርና በአካድ ሁሉ ተነሥተው ኡሩክን ለመጠብቅ ግድግዳ በበረሃ መስራት እንደ ነበረበት ይጠቅሳል። በነዚህ መጨረሻ 2 ጽላቶች፣ ከኤንመርካር ጦር አለቆች አንድ የሚሆን ሉጋልባንዳ የሚባል ሰው ይተረታል። በሱመር ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ፣ ይህ ሉጋልባንዳ «እረኛው» ኤንመርካርን ወደ ኡሩክ ዙፋን ተከተለው። ይህ ሉጋልባንዳ ደግሞ በጊልጋመሽ ትውፊት በተባለው ግጥም ዘንድ የኋለኛው ኡሩክ ንጉሥ የጊልጋመሽ አባት ነበረ። ዴቪድ ሮኅል የሚባል አንድ የታሪክ ሊቅ የኤንመርካርና የናምሩድ ተመሳሳይነት አመልክቷል። «-ካር» የሚለው ክፍለ-ቃል በሱመር ቋንቋ ማለት «አዳኝ» ነው። ኡሩክ ከተማ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ነበር ሲባል፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በሌላ ትውፊቶች ዘንድ ይህ ናምሩድ የባቢሎን ግንብ መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪም አቶ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም «ባቤል» እንደ ነበር ያምናል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ። «ባቢሎን» ማለት የኤሪዱ መጠሪያ እንደ ነበር የሚል ማስረጃ በሌሎችም ጥናቶች አለ። ሮማዊው ጸሐፊ ክላውዲዩስ አይሊያኑስ በጻፈ አንድ ትውፊት ዘንድ (200 ዓ.ም. ግድም)፣ የባቢሎን ንጉስ «ኤወኮሮስ» የተከታዩን «ጊልጋሞስ» አያት ይባላል። ይህ «ጊልጋሞስ» ማለት የኡሩክ ንጉስ ጊልጋመሽ መሆኑን የአሁኑ ሊቃውንት ስለ ገነዘቡ፣ እንዲሁም «ኤወኮሮስ» ማለት ኤንመርካር ሳይሆን አይቀርም የሚል አስተሳሰብ ያቀርባሉ። ከዚህ በላይ የከላውዴዎን ታሪክ ጸሐፊ ቤሮሶስ በጻፈው ዝርዝር መሰረት፣ ከማየ አይህ ቀጥሎ የከላውዴዎንና የአሦር መጀመርያው ንጉስ «ኤወኮዮስ» ይባላል፤ ስለዚህ የዚሁ «ኤወኮዮስ»ና የናምሩድ መታወቂያ አንድ ናቸው የሚለው አሳብ ለረጅም ዘመን የቆየ ነው። \n \nጥያቄ: የሱመር ንጉሥ የነበረው ኤንመርካር ያሰራው ታላቅ መስጊድ በየት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በኤሪዱም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ፕሬዝዳንት አብዱ ዲዮፍ በምርጫ ስንት ዙር አሸነፈ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ለአራት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር፣ በጠላት ወረራ ዘመን የተመሠረተ ድርጅት ሲሆን፤ እስከ አሁን ድረስ ያሉት አዛውንት አባላቱ በዚያው የአምሥት ዓመት ትግል ዘመናት፣ መኳንንቱ፤ የጦር መሪዎቻቸውና ንጉሠ ነገሥቱም ጭምር እነዚያን ወጣት ኢትዮጵያውያን አንጀታቸውን ለረሀብ፤ እግራቸውን ለሾኽ ለጠጠር፤ ግንባራቸውን ለእርሳስ አጋልጠዋቸው በካዷቸው መራር ዘመን፤ ሞትም ቢመጣ እናት አገራችንን አሳልፈን ለጠላት አንሰጥም፤ ነፃነታችንን ለጊዜያዊ ሹመት፣ ሽልማት አንለውጥም ብለው የተጋፈጡ ጀግኖች ናቸው። ደጃዝማች ከበደ ተሰማ፤ “የታሪክ ማስታወሻ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ፤ ይህ ማኅበር በአርበኝነት ዘመን በሸዋ ክፍለ ሀገር በ፲፱፻፴፩ ዓ/ም «የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር» በሚል ስም ተሠይሞ የተቋቋመ ማኅበር እንደነበርና ዓላማውም «የአርበኞችን ክብ በማበረታታትና በየሀገሩ ካሉ አርበኞች ጋር በመላላክ የሚገኘውን ሥራ ፍሬ» እርስ በርስም ሆነ በስደት ላይ ከነበሩት ንጉሠ ነገሥት ጋርም መካፈል እንደነበር ይገልጻሉ። ከመሥራች ማኅበረተኞቹ በከፊሉ፦ ራስ አበበ አረጋይ፤ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች ፀሐዩ እና ደጃዝማች ተስፋዬ ዕንቁ ሥላሴ፤ አቶ እምአእላፍ ኅሩይ፤ ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ፤ ደጃዝማች ታከለ ወልደሐዋርያት ይገኙባቸዋል። በመጀመሪያ ጊዜ የነበሩት መሥራቾች ሃያ ዘጠኝ አባላት ሲሆኑ በኋላ ጊዜ ግን ብዙ ማኅበረተኞች እየተጨመሩ የአባሎቹ ቁጥር ከሦስት መቶ በላይ ሆኖ ነበር። የጠላት ኃይል ተሸንፎ የአገሪቱ ነፃነት ከተመለሰ በኋላ፣ አርበኞቹ በየአውራጃውና በየጠቅላይ ግዛቱ ተሰማርተው ስለነበረና ማኅበሩም በመከራው ዘመናት የተቋቋመበት ዓላማ በነፃነት ጊዜ አላስፈላጊ በመሆኑ፤ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ሳያሳይ ብዙ ዓመታት አሳለፈ። ሆኖም በሚያዝያ ወር ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ጄኔራል ነጋ ኃይለ ሥላሴ «ከሥራ ባልደረቦቻቸውና ከዕውቅ አገር አፍቃሪዎች ጋራ፥ \"ጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበርን\" በታደሰ ሀገራዊ ዓላማና በተሻሻለ ደንብ አቋቋሙ። ኾኖም፥ ድርጅቱ እስከ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ድረስ ከመንግሥት ዕውቅናን ስላላገኘ ሥራው በዚሁ ምክንያት ለጊዜው ተገታ።» ጄኔራል ነጋ በዚህ ዕለት ሕጋዊ ዕውቅና ያገኘውንና ለፍጹም ሰላማዊና ሀገራዊ ዓላማ፤ ለበጎ አድራጎት የተጀመረውን የጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበር፤ ጠቅላይ ሥራ አመራር ሸንጎ ሊቀ-መንበር ኾነው የማኅበሩን ሥራ በሰፊው በማንቀሳቀስ ባጭር ጊዜ ውስጥ ፬ሺ የፈረሙ አባላትን ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ እንዳስገኙ፥ አሁንም መንግሥታዊ እንቅፋት ገጥሞት ከሕገ-ወጥ በሆነ እርምጃ ፥ የድርጅቱ ጽሕፈት ቤት በጸጥታ ኀይሎች እንዲዘጋ ተደረገ። \n \nጥያቄ: የታሪክ ማስታወሻ የተሰኘው መፅሀፍ በማን ተፃፈ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደጃዝማች ከበደ ተሰማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ ላይ ምን ያህል ወጥ የሲኒማ ድርሰቶች ለዓለም አበርክቷል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ የት ቤተክርስቲያን ተቀበረ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በ84ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ላይ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የአባት አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተገኝተዋል። በሰመዕታት መታሰቢያ ቀን የካቲት 12 ቀን በየአመቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፤አባት አርበኞች፤ እና የህብረተሰብ ክፍሉ በስድስት ኪሎ ታስቦ ይውላል፡፡ \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ማናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የብሪታንያው ድርጅት ደቡባዊ ሮዴዢያ ብሎ ይጠራው የነበረው የዛምቤዚያን አካባቢ አሁን ምን ተብሎ ይታወቃል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዚምባብዌ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ መዲና ማናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አዲስ አበባ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሶች በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ በቀን ውስጥ ያለውን ምን ያህል ሰዓት ያሳልፋሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ በስንት የአስተዳደር ክልሎች የተከፈለች ናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፵፯ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምን ያህል ምርምሮችን በታዋቂ መጽሔቶች ላይ አሳትመዋል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ124 በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በገበታ ለአገር የሚለማውን የወንጪ ፕሮጀክት እየጎበኙ ነው። የስራ ሃላፊዎቹ ጉብኝት በዋናነት ቴሌኮሙ በፕሮጀክቱ የሚያከናውነውን ስራ በተመለከተ የመስክ ምልከታ ለማድረግ ነው። ኢትዮ-ቴሌኮም በፕሮጀክቱ ከሚያከናውነው ስራ በተጨማሪ ለገበታ ለአገር ፕሮጀክቶች 500 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያሳያል። \n \nጥያቄ: የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማን ናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የፐርል በክ የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ ያገኘችው በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1935 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በ198 ሺህ ደንበኞች የሞባይል ስልኮች ላይ በተጫነ መተግበሪያ ዘመናዊ የቆጣሪ ንባብን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። አሰራሩ በመኖሪያ ቤቶች፣ የንግድ እና የመንግስት ተቋማት እና በሌሎች የውሃ አገልግሎቶች ላይ ተግባራዊ በመደረጉ ደንበኞች የሞባይል ስልኮች ላይ በተጫነ መተግበሪያ አማካኝነት ቆጣሪ ማንበብ ይችላሉ ተብሏል፡፡ ይህም ግምታዊ አሞላልን ከማስቀረት ባለፈ ደንበኞች የውሃ ፍጆታቸውን በተጠቀሙበት ወር ለመክፈል የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። ከዚህ ወር ጀምሮም በአራት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በሚስተናዱ 198 ሺህ 428 ደንበኞች ዘመናዊ የቆጣሪ ንባብ ስርዓት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ የክፍያ ስርዓቱ ደንበኞች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል በተዘረጉ የተለያዩ የክፍያ አማራጮች በመጠቀም የታህሳስ እና የጥር ወር የውሃ አገልግሎት ክፍያ መፈጸም የሚችሉ መሆኑንም ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ዘመናዊ የቆጣሪ ንባብን መተግበሪያ ምን ዓይነት ጥቅም ለማኅበረሰቡ ይሠጣል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ግምታዊ አሞላልን ከማስቀረት ባለፈ ደንበኞች የውሃ ፍጆታቸውን በተጠቀሙበት ወር ለመክፈል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: ዝናሽ ማሞ መቼ ተወለደች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የዚህ ዓለም ጥንተ ፍጥረቱ ከእሳት እንደሆነ የሚያምን የነበረው ፈላስፋ ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሄራቅሊጠስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል የፕሬዘንዳቶች ምርጫ ከ2001 ዓ.ም. በፊት በየስንት ዓመቱ ታደርግ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በየሰባት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የኢያን ስሚዝ መንግሥት በዚምባቡዌ ከሦስት መሪዎች ጋር በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የተፈራረመው ስምምነት ላይ የነበሩት ጳጳስ ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nክሪስታል ራዲዮ የክሪስታል ራዲዮ የሚሰኘው ከሁሉ በላይ በጣም ቀላል ራዲዮ ተቀባይ ሲሆን፣ በድሮው የራድዮ ዘመን ታዋቂነት ያገኘ ነበር። ክሪስታል ራዲዮ ባትሪም ሆነ ሌላ የኤሌክትሪክ ኃይል አይፈልግም። ይልቁኑ ከሚተላለፍ የራዲዮ ሞገድ አቅም በመውሰድ በራሱ ይሰራል። ለዚህ ተግባር ሲባል ክሪስታል ራዲዮ ረጅም የሽቦ አንቴና ይፈልጋል። ክሪስታል መባሉ ድሮ ይሰራበት ከነበርው ወሳኝ ክሪስታል ጋሌና የተባለ ክፍል የመጣ ስም ነው። በአሁኑ ዘመን ይህ ክፍል በዳዮድ ተተክቷል። ክሪስታል ራዲዮ በጣም ቀላል ከመሆኑ የተነሳ ማንም ሰው ሊሰራው ይችላል። የሚያስፈልጉትም እቃወች አንቴና ሽቦ (ረጅም መሆነ አለበት)፣ ጣቢያ መቀየሪያ ጥቅል ሽቦ (መዳብ) ፣ ክሪስታል ጠቋሚ ወይንም ዳዮድ እና የጆሮ ስልክ (ማለቱ ማናቸውም በጆሮ ላይ ተደርጎ ሙዚቃ ለመስማት የሚያገለግል ኢር ፎን) ናቸው። በርግጥ የክሪስታል ራዲዮ የተወሰነ ጣቢያወችና በዚያው ልክ ድምፁም ከፍተኛ ስላልሆነ ኢር ፎን መጠቀም ግድ ይላል። ይህ የሚታየው የክሪስታል ራዲዮ የሽቦ ዑደት፣ ቀላል ልዲዛይን ሲያሳይ ነገር ግን የሚያቀበለው ጣቢያ ከአጭር ሞገዶች በላይ መሻገር አይችልም። ከምስሉ እንደምንረዳ ጣቢያ መቀየሪያው ከትይዩእና ተያያዥ አንድ ወጥ ጥቅልል ሽቦወችና ከተለዋዋጭ ካፓሲተር የተሰራ ነው። አንቴናውና መሬቱ በትዩዩ መንገድ የተገናኙ ናቸው። ክሪስታል ራዲዮኖች አንቴናቸው ቢያንስ ቢያንስ 20 ሜትር ርዝመትና 6 ሜትር ከፍታ ሊኖረው ያስፈልጋል። ይህ ጉዳይ በሚፈጥረው የካፓሲተር ውጤት ከተወሰኑ ራዲዮ ጣቢያወች በላይና በታች ለመቀበል አዳጋች እንዲሆን ያደርጋል። ሆኖም ግን ከካፓሲተሩ ይልቅ የሽቦ ጥቅልሉን ተለዋዋጭ በማድረግ ብዙ የራዲዮ ጣቢያወችን መቀብል ይቻላል። \n \nጥያቄ: ክርስታል ሬዴዎች አንቴናቸው እና ከፍታቸው በያንስ ስንት መሆን አለበት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 20 ሜትር ርዝመትና 6 ሜትር ከፍታ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኩባንያው በ124 ሚሊዮን ብር የሞተር ዘይቶችና ቅባቶች ማምረቻ ለማቋቋም፣ የቡታ ጋዝ ማከፋፈል ሥራ ለመጀመር፣ የሬንጅ አቅርቦት ሥራውን ለማሳደግና የኢንዱስትሪ ኬሚካሎች ለማቅረብ ማቀዱንም ገልጸዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በአውሮፕላን ነዳጅ አቅርቦት ላይ በስፋት እየሠራ እንደሆነ አቶ ዘካሪያስ ተናግረዋል፡፡ በአውሮፕላን ነዳጅ ገበያ የ42 በመቶ የገበያ ድርሻ እንዳለው ጠቁመው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ለ30 ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ እንደሚያቀርብ ገልጸዋል፡፡ ኩባንያው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚገኘውን የአውሮፕላን ነዳጅ ዴፖ ማስፋፋቱን፣ አምስት ዘመናዊ የአውሮፕላን ነዳጅ መሙያ ማሽኖች ገዝቶ ጥቅም ላይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ለቀለምና ፕላስቲክ ፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች ለማቅረብ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ‹‹ለጊዜው ኬሚካሎቹን ከውጭ በማስገባት የምናከፋፍል ሲሆን፣ በሒደት አገር ውስጥ የማምረት ዕቅድ አለን፤›› ብለዋል አቶ ዘካሪያስ፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ለምን ያህል አየር መንገድ አውሮፕላኖች ነዳጅ ያቀርባል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለ30 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኒጋል ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር በስልጣን ሳሉ በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. መፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ ያደረገባቸው ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማማዱ ዲያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሩሲያዊ-አሜሪካዊ የሆነው ጉግልን የፈጠረው ግለሰብ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየሕገ መንግሥት ታሪክ የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና በ2093 ዓክልበ. ያሕል ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው። ሰነዱ እራሱ ገና አልተገኘም፤ ነገር ግን ለዜጎቹ አንዳንድ መብት እንደ ፈቀደላቸው ይታወቃል። ለምሳሌ ለመበለትና ለደሀ አደጎች ቀረጥ እንዳስቀረላቸው ድሆችንም ከሃብታሞች አራጣ እንደጠበቃቸው ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ብዙ መንግሥታት በተጻፈ ሕግ እንዲገዙ ልዩ ስርዓት ነበራቸው። ከተገኙት ሕግጋት ሁሉ ጥንታዊ የሆነው በ1983 ዓክልበ. የገዙ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው። በተለይ ዕውቅ የሆኑ የጥንት መንግሥት ሕጎች የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት (1832 ዓክልበ.) ፤ የኤሽኑና ሕግጋት (ምናልባት 1775 ዓክልበ. ግድም)፤ የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ.) እና፤ ሕገ ሙሴ ለእስራኤል (1661 ዓክልበ.) ናቸው። ሕገ ሙሴ በተለይ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 ያህዌ አስተካክሎ ከነዚህ ሁሉ የተሻሸሉት ብያኔዎች ይጠቅልላል። በኋላ ኬጢያውያን (1488 ዓክልበ. ግድም) እና አሦር (1080 ዓክልበ. ግድም) በበኩላቸው ለራሳቸው ሕግጋት አወጡ። \n \nጥያቄ: ሕገ ሙሴ ለእስራኤል መቼ ነበር የተሰጣቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1661 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ የመጀመሪያ ድርሰቷ የት ኩባንያ ውስጥ ታተመላት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በጆን ዴይ ኩባንያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ አዲስ የዲዛይን ክፍተት መገኘቱ ተገለፀ። የቦይንግ ኩባንያ እና የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍ.ኤ.ኤ) በትናንትናው እለት እንዳረጋገጡት በ737 ማክስ አውሮፕላን ዲዛይን ላይ የተገኘው አዲስ ክፍተት የኤሌክትሪክ ሽቦ መቀራረብ ችግር እንደሆነ አረጋግጠዋል። የቦይንግ ቃል አቀባይ ጎርዶን ጆንድሮ “ጉዳዩ የቦይንግ አስቸጋሪ ሂደት አካል ቢሆንም፤ ተገቢውን ትንተና ለማከናወን ከአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር ጋር በጋራ እየሰራን ነው፤ አሁን የተገኘው ክፍተት የዲዛይን ለውጥ ለማድረግ ያስገድዳል የሚያስብል ደረጃ ላይ ግን አልደረሰም”ብለዋል። የቦይንግ አውሮፕላን ላይ የተገኘው አዲሱ የዲዛይን ክፍተት የሁለት ሽቦዎች በጣም መቀራረብ መሆኑን በመግለጽ፤ አብራሪዎች ችግሩን ተረድተው በአፋጣኝ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋን ሊያስከትል ይችላል” ሲል የኒው ዮርክ ታይምስ አስነብቧል። የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሰጠው መግለጫ፥ በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ሊደረግ በታቀደው የዲዛይን ማሻሻያ ዙሪያ ኤጀንሲው እና የቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ ግኝቶችን እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል። ኤጀንሲው አክሎም “በዚህ ሂደት ወቅት ተለይተው የሚታወቁ የደህንነት ችግሮች በሙሉ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ይደረጋል ” ሲልም አስታውቋል። ቦይንግ በአሁኑ ጊዜ ተቀራርበዋል የተባሉ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ለመለየት እና ስህተቱን ተከትሎ የሚደርሰውን አደጋ በተመለከተ ሰፋ ያለ ትንተና እየሰራ መሆኑን አንድ የኩባንያው ባለስልጣን አስረድተዋል። ቦይንግ በአምስት ወራት ውስጥ በሁለት አደጋዎች 346 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የማክስ 737 አውሮፕላን ማምረት ማቆሙ ይታወሳል።   ምንጭ፡- ሲጂቲኤን \n \nጥያቄ: የቦይንግ ቃል አቀባይ ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጎርዶን ጆንድሮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዝግመተ ለውጥ የአንድ ሕይወት ያለው ማህብረሰብ የዘር ውርስ ባህሪይ ከትውልድ ወደትውልድ እየተቀየረ መሄዱ ዝግመተ ለውጥ ይባላል። ቻርለስ ዳርዊን ይህን ኩነት በማስተዋልና በሳይንሳዊ አመክንዮ አሰደግፎ በመተንተኑ የመጀመሪያው ሰው ነው። ዳርዊን በተጨማሪ የተፈጥሮ ምርጫ ባለው ኅልዮቱ ሕይወት ያላቸው ማህበረሰቦች ዝግመተ ለውጥ እሚያካሂዱት ምንም እንኳ በዘፈቀደ ስህተት እየፈጸሙ ቢሆንም፣ ተፈጥሮ እራሷ በምትፈጥረው መሰናክሎች እኒህን መሰናክሎች አልፈው የሚሄዱትን በመምረጧ ነው። ዳርዊን የተፈጥሮ ምርጫን አስተሳሰብ ከ፫ የሚታዩ ነገሮች አንጥሮ ነበር ያወጣው፦ ፩) እንስሳትም ሆነ እጽዋት ወደፊት ሊኖር ከሚችሉ ዘሮች በላይ አተረፍርፈው ነው እሚራቡት ፪) ሕይወት ያላቸው እያንዳንዳቸው ነገሮች ሁልጊዜ የተለያየ ጸባይ ነው ያላቸው፣ ስለሆነም እያንዳንዳንቸው በቀጣይ የመኖር ዕድላቸው የተለያየ ነው ፫) ስለሆነም የአንድ ማህበረሰብ አባላት ሲሞቱ፣ የሚገላቸውን ነገር ጠንክረው እሚቋቋሙት ግለሰቦች ብቻ በሕይወት ቆይተው ወደፊት መራባች ይችላሉ። ስለሆነም ቀስ በቀስ እነዚህ በህይወት ያሉ፣ በህይወት የሌሉትን አይነቶች እየተኩ ይሄዳሉ። በ፳ኛው ክፍለ ዘመን ጄኔቲክስ (ሥነ በራሂ) እና ዝግመተ ለውጥ ተዋህደው ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ እሚባለውን ጥናት ለመፍጠር ችለዋል። አንድ ማህበርሰብ ለየት ያለ ግለሰቦችን ለመፍጠር ከሚያስችሉት መንገዶች አንዱ ሙቴሽን የተባለው ሂደት ሲሆን፣ ሙቴሽን እሚፈጠረው የዚያ ግለሰብ ዲ ኤን ኤ ከወላጆች ሲወረስ በሚደረግ ስህተት (ወይም እቅድ) ነው። \n \nጥያቄ: ዝግመተ ለውጥን ለመጀመርያ ጊዜ በሳይንሳዊ መልኩ የተነተነው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቻርለስ ዳርዊን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ከሊዎፖልድ ሴንግሆር ቀጥሎ ፕሬዝዳንት የሆነው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አብዱ ዲዮፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ የቆሣ ቋንቋ በተናጋሪ ብዛት ስንተኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 2ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ ለዓለም ገበያ በምታቀርበው የፔትሮሊየም ምርት ስንተኛ ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 12ኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። \n \nጥያቄ: በ18ኛው ክፍለ ዘመን ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ የአባይ ወንዝ መነሻ ጣና ሐይቅ ነው ያለው ጄምስ ብሩስ የምን ሀገር ዜጋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የስኮትላንድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ በምስራቅ የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከዩጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ደቡብ ሱዳን ነጻ ሀገር የሆነች መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በተለያዩ አፍሪካ ሀገራት ስንት ነዳጅ ማደያዎች አሉት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1,015 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ምን ያደርጋሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ያገሣሉ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ዘ ኢትዮጵያ ካረፉ በኋላ ተከታዩን ፓትርያርክ ለመሾም በተደረገው ምርጫ በዕለቱ ተገኝተው የመረጡት ፻፵፮ አባላት ሲሆኑ ሦስቱ ዕጩዎች፦ ፩) አቡነ ቴዎፍሎስ (የሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ) - ፻፳፫ ድምጽ ፪) አቡነ ያዕቆብ (የወለጋ ሊቀ ጳጳስ) - ፰ ድምጽ ፫) አቡነ ጢሞቲዎስ (የሲዳሞ ሊቀ ጳጳስ - ፲፫ ደምጽ አግኝተዋል። በዚህም መሠረት የፓትርያርኩ ስርዓተ ሲመት ግንቦት ፩ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ/ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናውኗል። በ፲፱፻፷፮ ዓ/ም በኢትዮጵያ ወታደራዊው አብዮት ተለኩሶ ንጉሠ ነገሥቱ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ከሥልጣን ሲወርዱ ወዲያው የቤተ ክርስቲያኗም ንብረት ተወረሰ። ፓትርያርኩንም ከሥልጣን ከማውረዱ በፊት ደርግ “የተሐድሶ ጉባዔ” የሚል ኮሚቴ አቋቁሞ በተለያየ ክፍል በሳቸው ላይ የማይገታ አመጽና አድማ መነሳሳት ጀመረ። በዚህ ሁኔታ ለአንድ ዓመት ያኡል በትዕግስት ከቆዩ በኋላ በየካቲት ወር ፲፱፻፷፰ ዓ/ም የደርግ መንግሥት “ሲጠበቅ የቆየ ፍርድ” በሚል አዋጅ ከሥልጣን አውርዶ እሳቸውንና በመጨረሻ በእሳቸው የተሾሙትን ሦስት ጳጳሳት (ያሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አንዱ ናቸው) አሰራቸው። በኋላም ሐምሌ ፯ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም እኒህ የቤተ ክርስቲያን መሪ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ርዕሰ ሊቃና ጳጳሳት ወፓትርያርክ ዘ ኢትዮጵያ በደርግ እጅ ተገደሉ። ቀደም ሲል “የተቀባ ፓትርያርክን ሞት ብቻ ነው የሚሽረው” የሚለውን እምነት በሚቃረን ሁኔታ ከሥልጣን አውርደው “የተቀባ ፓትርያርክ ሳይሞት በላዩ ላይ ሌላ ፓትርያርክ አይሾምም” የሚለውን ሁለተኛውን እምነት ጥሰው ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ሦስተኛው ፓትርያርክ እንዲሾሙ አደረጉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ሁለተኛውን ፓትርያርክ ለመሾም በተደረገው ምርጫ አቡነ ቴዎፍሎስ በስንት ድምፅ ተመረጡ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፻፳፫ ድምጽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: የሶቅራጥስ አባት ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሶፍሮኒስከስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ ከሶማሊያ ጋር የምትዋሰነው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሰሜን-ምስራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ በየት ከተማ ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በደብረ ታቦር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን የሥራ ኃላፊነታቸው ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ የእርግዝና ጊዜዋን አጠናቃ ልጅ በምትወልድበት ጊዜ የልጇ ቁመት ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሁለት ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ውስጥ የተገኘችው ረጅም እድሜ ያስቆጠረችው የሰው ቅሪተ አካል ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሉሲ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የመጀመሪያው ዳይሬክተር ማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ለአቼቤ 50 ወደሚሆኑ የአለም ቋንቋ የተተርጎመ እና 10,000,000 ቅጂዎች የተሸጡለት ድንቅ የስነፅሑፍ ስራው ምን በመባል ይታወቃል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ Things Fall Apart ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: የአንጎላ ሦስቱ የትግል ቡድኖች ከምን ስምምነት በኋላ ነበር ወደ ሽግግር መንግስት ምስረታ የገቡት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከአልቮር ስምምነት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: የባሕር ዳር ከተማን ስያሜ ያወጡት ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አፄ ሠርጸ ድንግል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: በጣና ሐይቅ ምን ያህል ደሴቶች አሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ35 በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሁዋዌ የተሰኘው ግዙፍ የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተሰምቷል። የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ሀገራቸው ከሁዋዌ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በቅንጅት ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ኩባንያው በቀጣይ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ነው የገለጹት። ሁዋዌ ቻይና ከአሜሪካ ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ መግባቷን ተከትሎ በዩናይትድ ስቴትስ አገልግሎት እንዳይሰጥ ክልከላ የተደረገበት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው አገልግሎት በሚሰጥባቸው ሀገራት በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጣልቃ ይገባል በሚል ካናዳ እና አውስትራሊያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት መሻከሩ ይታወቃል። ብሪታኒያ ከኩባንያው ጋር በቅንጀት ለመስራት እና አገልግሎቱን ለመጠቀም መፈለጓም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ሊያሻክረው እንደሚችል ተሰግቷል። ምንጭ፦ሲ ጂ ቲኤ ን \n \nጥያቄ: ሁዋዌ በአሜሪካ አገልግሎቱን ያቋረጠው ቻይና ከማን ጋር በገባችው የንግድ ጦርነት ምክንያት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከአሜሪካ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ በደቡብ በኩል ከማን ጋር ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ለኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል አንድ ሚሊዮን ብር ለመለገስ ቃል ገብቷል፡፡ በዛሬው ዕለት ማዕከሉን የጎበኘው አትሌት ኃይሌ በጉብኝቱ ወቅት የተለያዩ የሕክምና ክፍሎችን እና የሥራ ቦታዎችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል፡፡ አትሌት ኃይሌ ከጉብኝቱ በኋላ ማዕከሉን ለማጠናከር የሚውል የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግሯል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ለኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ስንት ብር ለመለገስ ቃል ገባ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አንድ ሚሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን የት ተከታተለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአራት ማዕዘን አራት ማዕዘን ማናቸውም አራት ቀጥተኛ መስመር የሆኑ \"ጎኖች\"ና አራት መገናኛወች ያላቸውን የሚወክል የሂሳብ ስያሜ ነው። እኒህ ጎኖች መነባበር ወይም አንዱ ባንዱ ላይ መንሳፈፈ የለባቸውም አለዚያ አራት ማዕዘን አይባሉም። የአራት ማዕዘን አራቱ ውስጣዊ ማዕዘኖች ሲደመሩ ምንጊዜም ውጤታቸው 360 ዲግሪ ነው። ፓራላሎግራም ሁለቱ ጎኑ ትይዩ የሆነ አራት ማዕዘን ፓርላሎግራም ይባላል። በፓራላሎግራም ስር የሚተድዳደሩ እንግዲህ ካሬ፣ ሬክታንግል፣ ሮምበስና ሮምባቶይድ ይባላሉ። ሮምበስ ማለት አራቱም ጎኑ እኩል የሆነ ፓራልላሎግራም ነው። በሌላ አነገጋገር ተጻራሪ ጎኖቹ ትይዩ ሲሆኑ ተጻራሪ ማዕዘኖቹ ደግሞ እኩል ናቸው፣ ወይም ደግሞ ዲያጎናሎቹ በ90 ደጊሪ እኩል ለኩል ይቋረጣሉ። ወይም በሌላ አባባል ወደጎን የተገፋ ካሬ ማለት ነው። ሮምባቶይድ ማለት ፓራሎግራም ሆኖ ተነካኪ ጎኖቹ እኩል ያልሆኑና ማዕዘኖቹ ኦብሊክ የሆኑ ማለት ነው። በሌላ አባባል የተገፋ ሬክታንግል ማለት ነው። ሬክታንግል ማለት አራቱም ማዕዘኖቹ 90ዲግሪ የሆነ አራት ማዕዘን ማለት ነው። በሌላ አባባል ዲያጎናሎቹ እኩል ሆነው እኩል የሚቋረጡ ማለት ነው። ካሬ አራቱም ጎኖቹ እኩል የሆኑ እንዲሁም አራቱም ማዕዘኖቹ 90 ዲግሪ የሆኑ ማለት ነው። በአንድ ጊዜ ሮምበስ እና ሬክታንግል የሆነ አራት ማዕዘን ምንጊዜም ካሬ ነው። \n \nጥያቄ: ፓራላሎግራም በውስጡ ምን ምን ይዟል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ካሬ፣ ሬክታንግል፣ ሮምበስና ሮምባቶይድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየሕገ መንግሥት ታሪክ የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና በ2093 ዓክልበ. ያሕል ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው። ሰነዱ እራሱ ገና አልተገኘም፤ ነገር ግን ለዜጎቹ አንዳንድ መብት እንደ ፈቀደላቸው ይታወቃል። ለምሳሌ ለመበለትና ለደሀ አደጎች ቀረጥ እንዳስቀረላቸው ድሆችንም ከሃብታሞች አራጣ እንደጠበቃቸው ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ብዙ መንግሥታት በተጻፈ ሕግ እንዲገዙ ልዩ ስርዓት ነበራቸው። ከተገኙት ሕግጋት ሁሉ ጥንታዊ የሆነው በ1983 ዓክልበ. የገዙ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው። በተለይ ዕውቅ የሆኑ የጥንት መንግሥት ሕጎች የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት (1832 ዓክልበ.) ፤ የኤሽኑና ሕግጋት (ምናልባት 1775 ዓክልበ. ግድም)፤ የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ.) እና፤ ሕገ ሙሴ ለእስራኤል (1661 ዓክልበ.) ናቸው። ሕገ ሙሴ በተለይ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 ያህዌ አስተካክሎ ከነዚህ ሁሉ የተሻሸሉት ብያኔዎች ይጠቅልላል። በኋላ ኬጢያውያን (1488 ዓክልበ. ግድም) እና አሦር (1080 ዓክልበ. ግድም) በበኩላቸው ለራሳቸው ሕግጋት አወጡ። \n \nጥያቄ: ኡሩካጊና የመጀመሪያውን እንደ ሕገ-መንግሥት የሚታየውን ሕገ ፍትሕ መቼ ነበር ያወጀው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ2093 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nብጫ ሱማራ ብጫ ሱማራ በ1960 ዓም ዘ ቢተልስ ሙዚቃ ቡድን የሠሩት ዝንኛና ተወዳጅነት ያገኘ የልጆች ካርቶን ፊልም ነበር። በርካታ ዘ ቢተልስ ዘፈኖች በካርቶኑ ሕልም ታሪክ ውስጥ ይሰማሉ። \n \nጥያቄ: ብጫ ሱማራ ፊልም መቼ ተሰራ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1960 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: የናዋትል ቋንቋ አሁን የሚጸፈው በምን ፊደላት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በላቲን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 ኖቤል ተሸላሚ የሆኑት በምን ዘርፍ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሥነ ጽሑፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጨኖ ጨኖ ግራጫ ቢጤ የሆነ፣ ፈርጠም ያለ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ አፍሪቃ፣ በተጨማሪም በኮንጎ ደኖች የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው ዓይነት ጨኖ የፀጉሩ ቀለም ግራጫና ጥቁር የሆነ፣ ፊቱ የጠቆረ ሰማያዊ የሆነ፣ አገጭና አንገቱ ነጭ ነው። የወንዶቹ ክብደት እስከ 12 ኪ.ግ. ሲሆን፤ አማካዩ 4.5 ኪ.ግ ይመዝናሉ። ጨኖ የደን ዝንጀሮ ነው። የደን ዝንጀሮች ብዙ ጊዜ ከዝናባማ ሥፍራዎች ደኖች ውጪ አይገኙም። ጨኖ ግን ከነዚህ ደኖች ውጪም በሚገኙ ደኖች ውስጥ ይኖራል። በኢትዮጵያ፣ በጎደሬ ደን ውስጥ፣ ቴፒ አጠገብ ሜጢ አካባቢ ይገኛሉ። በተራራማ ሥፍራዎች ደኖችም እስከ 3000 ሜትር ከፍታ ድረስ ይገኛሉ። እጅጉን በዛፍ ላይ የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። የሚገኘው በደን ዛፎች ግማሽ ላይ ነው። በተለያዩ ዓይነት ተግባሮች መገለጫ የሚሆኑ ሰባት ዓይነት ድምፆች አሏቸው። በቡድናቸው ውስጥ የሚታየው አብዛኛው ፀብ፣ በዋናው ወንድና ለአካለ መጠን ባልደረሱና ጎረምሳ ወንዶች መሃል የሚታየው ነው። በሴቶቹና ሕፃናትን በሚገድሉ ወንዶች መኻከል ከባድ ግጭት ያድጋል። በቡድኖች መኻከል የሚደረግ ግጭት የሚሆነው አልፎ አልፎ ነው። እንዲህ ያለ ግጭት የሚነሳው በድንበር አካባቢ በምግብ ሽኩቻ የተነሳ ነው። የእርግዝና ጊዜአቸውን 140 ቀን ነው። የልጆቻቸውን እድገትም ቀስ ያለ ነው። ከወለዱ ወዲያ ለሚቀጥለው እርግዝና 15 ወራት መቆየት አለባቸው። \n \nጥያቄ: ግራጫ ቢጤ የሆነ፣ ፈርጠም ያለ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ አፍሪቃ፣ በተጨማሪም በኮንጎ ደኖች የሚገኝ ዝንጀሮ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጨኖ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: በአፕል ኩባንያ ላይ ስንት አመት ምርመራ ከተደረገ በሁዋላ ነው የተቀጣው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለ10 ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: የሳውዲ የአገዛዝ ስርአት ምንድነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በዘውድ አገዛዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ የእርግዝና ጊዜ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ኢልግ በደሞዘኝነት ተቀጥሮ ሲሰራ የነበረው የስራ ዘርፍ ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በምሕንድስና ሥራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \n125ኛውን የአድዋ ድል በዓል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለማክበር የባሕልና ቱሪዝም ሚኒስትር ሂሩት ካሳው አሶሳ ከተማ ገቡ። በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሌ ሀሰን የተመራው የክልሉ ከፍተኛ አመራርም ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በዓሉም ከዛሬ ጀምሮ በፓናል ውይይት እና ታሪካዊ ቦታዎችን በመጎብኘት እንደሚካሄድ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: 125ኛው የአድዋ ድል የት ነው የሚከበረው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የዚህ ዓለም ጥንተ ፍጥረቱ ከአየር ነው ብሎ የሚያምን የነበረው ፈላስፋ ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አናክሲሜነስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንጉሥ ተፈሪ መኮንን የትውልድ ስፍራቸው የት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኤጀርሳ ጎሮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የመናገሻ አምባ ማርያምን ገዳም እያስተዳደሩ ሳሉ፤ ከዚህ ሥልጣናቸው በተጨማሪ የአዲስ አበባ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መምህርነት በየካቲት ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ/ም ተሰጣቸው። ከዚያም ቀጥሎ መጋቢት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፭ዓ/ም በኢየሩሳሌም ያሉ የኢትዮጵያን ገዳማት በመንፈሳዊ መሪነት አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመው ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ ወደአገራቸው ተመለሱ። የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፯ ዓ/ም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት መንበር፥ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ዘነበረ በመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተብለው፥ አምሣ-ዘጠነኛው ዕጨጌ ሆነውተሽሙ። በዚሁ በዕጨጌነታቸው ዘመን የፋሺስት ወረራ ኢትዮጵያን ባጠቃ ጊዜ፣ በጦርነቱ ግምባር ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ተሰልፈው አብያተ ክርስቲያናትንና መጻሕፍትን የሚያቃጥል የምእመናንን ዘር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና በሃይማኖት፤ በጸሎት፣ በምህላ በርታ እያሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲያጽናኑ ቆዩ። በጦርነቱም ጊዜ የተቀመጡበት በቅሎ በአረር ተመቶ እስኪወድቅና የለበሱትም ካባ አምስት ላይ በጥይት እስኪበሳሳ ድረስ ከንጉሠ ነገሥቱ ሳይለዩ የቆራጥነት ሥራ ሠርተዋል። ሠራዊቱም ድል ህኖ በተፈታ ጊዜ ክንጉሠ ነገሥቱ ጋር በስደት ወደኢየሩሳሌም አቅንተው እስከ ድል ጊዜ ድረስ በስደት ቆይተዋል። በዚሁ በስደት ዘመናቸውም ሳሉ በርካታ ሐዋሪያዊ መልእክቶችን ለአርበኞችም፤ ለሕዝቡም በመላክ የማጽናናትና የሃይማኖታዊ ጣምሮችን ያስተላልፉ ነበር። ንጉሠ ነገሥቱ በስደት ከነበሩበት ከ’ባዝ’ (ብሪታንያ) ፥ ጥር ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጊዜው በስደት ኢየሩሳሌም ለነበሩት ወደ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ አንድ ፅላትና ለአገልግሎት የሚበቁ አምስት መነኮሳትን ወደ እንግሊዝ አገር እንዲልኩላቸው በአባ ሐና ጅማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት፣ ዛሬ ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም የተባለውን የመድኀኔ ዓለምን ጽላት ወደንጉሠ ነገሥቱ ወዳሉበት ባዝ የላኩት እሳቸው ነበሩ፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፥ ጥር ፲፪ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በኢትዮጵያ ጠረፍ በኡም-ኢድላ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ-ዓላማ ሲተክሉ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስም አብረዋቸው ነበሩ። \n \nጥያቄ: አቡነ ባስልዮስ በመጀመርያ የምን ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኢየሩሳሌም ያሉ የኢትዮጵያን ገዳማት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ ከሱዳን ጋር የምትዋሰነው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በስሜን-ምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: በቤጂንግ እና ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር በከተሞቹ መካከል የነበረውን የስንት ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ ይቀንሰዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የ3 ሰዓት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሦስቱ የአንጎላ የትግል ቡድኖች መች ነበር የሽግግር መንግስት ለማቋቋም የወሰኑት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ የምትገኘው የት አህጉር ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበኢትዮጵያ የተለያዩ የቤተሰብ ሕግጋት ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ሕግጋት በሰው ፊት ዋጋ ያለው ግንኙነት የሚፈጠርበትን ጥምረት በተለያየ መንገድ ይደነግጋሉ፡፡ በቤተሰብ ሕግ ዕውቅና የተሰጣቸው የተቃራኒ ፆታዎች ጥምረት ሦስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያውና ዋናው ጋብቻ ሲሆን፣ አሥራ ስምንት ዓመት የሞላቸው ወንድና ሴት ጥንዶች ለዘለቄታው አብረው በትዳር ለመኖር በማሰብ የሚመሠርቱት ተቋም ነው፡፡ ይህ ተቋም በሕገ መንግሥቱ ዕውቅና የተሰጠው ሲሆን፣ ወጣቶች በሕጉ የተቀመጡትን የዕድሜ፣ የፈቃድና የዝምድና ሁኔታዎችን ካከበሩ ሊመሠርቱት የሚችሉት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ጥምረት በክብር በመዝገብ ሹም ፊት፣ በሃይማኖት ሥርዓት ወይም በባህል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ሁለተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው ጥምረት፣ ጋብቻ ሳይፈጸም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ነው፡፡ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድና አንዲት ሴት በሕግ በሚጸና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈጽሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ግንኙነት አለ የሚባለው ሰዎቹ እንደተጋቡ ዓይነት ሰዎች ዓይነት አኗኗር ማሳየታቸው እንደሆነ እንጂ በታወቀና በተደጋገመ ሁኔታ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸማቸው ብቻ አለመሆኑ በሕጉ በግልጽ ተመልክቷል፡፡ ሦስተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው መተጫጨትን ነው፡፡ መተጫጨት በተወሰኑ የክልል የቤተሰብ ሕግጋት ዕውቅና የተሰጠው እጮኛውና እጮኛይቱ ለወደፊት በመካከላቸው ጋብቻ ለመፈጸም የሚያደርጉት ስምምነት ነው፡፡ መተጫጨት ወደፊት በሚጋቡት ሰዎች ነፃ ፈቃድና ስምምነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚቆይ ጥምረት ነው፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ቤተሰብ ሕግ ተቀባይነት ያለው እጮኛና እጮኚት ወደፊት ለመጋባት የሚያደርጉት ስምምነት ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ መተጫጨት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን መች ነበር የአርካንሳው አስተዳዳሪነት ስልጣንን ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት ያሳደጉት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1984 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየጥንተ ንጥር ጥናት ኬሚስትሪ ወይም የጥንተ-ንጥር ጥናት የቁሶችን አሰራር እና ጸባይ ያጠናል። የ«ኬሚስትሪ» ስም የሚመጣ ከእንግሊዝኛ ሲሆን እሱ የተወለደ ከ1700 ዓ.ም. አካባቢ በፊት «አልኬሚ» ከተባለ ሌላ ጥናት ነበር። ይህም አልኬሚ ዋና ዒላማ ብረት ወደ ወርቅ ለመቀየር ነበር። የማይቻል ምኞት እንደ ነበር የዛኔ ተገነዘበ። አልኬሚ የሠራ ሰው 'አልኬሚስት' ተባለ ወይም በአጭሩ 'ኬሚስት'። በኋላ ትውልድ የኬሚስት ሥራ 'ኬሚስትሪ' ተባለ። የ«አልኬሚ» ስም ደግሞ የወጣ ከዓረብኛ «አል-ኪሚያ» (الكيمياء ወይም الخيمياء) ማለት «የመቀየር ጥበብ» ሲሆን የዚህ ቃል መነሻ በእርግጠኝነት አይታወቅም። ወይም ከግሪክ «ቄሜያ» (χημεία, ቀላጭ ብረታብረት) ወይም ከግብጽ ዱሮ ስም «ከመት» («የከመት ጥበብ» ለማለት) ሊሆን ይችላል። እንዲሁም በእንግሊዝኛ chemical ኬሚካል የሚለው ቃል ድምጽ ኃይል ከ«ኬሚስትሪ» ሲሆን፣ በዐማርኛ «ጥንተ ንጥር» መባሉ ከግዕዝ ነው። «ንጥር» ማለት የተነጠረ ወይም የተጠራ እንደ ንጥር ቅቤ ቢሆን ፅንሰ ሀሣቡ ከነጥሮን (ሶዲየም ከሰላ ወይም አምቦ አመድ) ጋር፣ በግሪክም /ኒትሮን/፣ ዓረብኛ /ናጥሩን/፣ ዕብራይስጥ /ኔቴር/፣ ግብጽኛ /ነቸሪት/ («የአምላክ») እንደ ተዛመደ ይታሥባል። ፔሪዮዳዊ ሢስተምክፍለ ጊዜአውዊ ስርአቱ ባምርኛ period የሚለውን´ ጴር ዮድ´ ተብሎ ማድመጽ ዪቻል ይሆን ? ግ እዝ የባህር ማዶን ቃል ውደራሱ ቛንቛ ማድመጽ ስፊ ልምምድ አለው፡ ሌሎች ቛንቋዎች ይህን ያደርጋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የቁሶችን አሰራር እና ጸባይ የሚያጠና ዘርፍ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኬሚስትሪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር በስንት ዓመተ ምሕረት ተመሰረተች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1915 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: አፕል ኩባንያ ከንግድ ውድድር ውጪ ተንቀሳቅሷል ተብሎ የተቀጣው በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ በምስራቅ በኩል በማን ትዋሰናለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሊቢያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: የአማራ ክልል በስንት ዞኖች የተከፈለ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጣልያን ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው ያነገሡት የማንን ልጅ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የልጅ ኢያሱን ልጅ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nትዊተር ተጠቃሚወች የሚለጥፏቸውን መረጃወች ተከትሎ የሚሰጡ ምላሾችን መቆጣጠር የሚያስችል አሰራር ሊሞክር መሆኑን አስታወቀ። ኩባንያው ሙከራው ደንበኞች በነጻነት እንዲሳተፉ ለማድረግ ያለመ ስለመሆኑም ገልጿል። ከዚህ አንጻርም ተጠቃሚዎች የሚለጥፏቸውን መረጃዎች መሰረት አድርገው የሚሰጡ ምላሾችን መቆጣጠርና መገደብ የሚያስችለውን ሙከራ አደርጋለሁ ብሏል። የአሁኑ እርምጃ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማህበራዊ ትስስር ገጾች በበይነ መረብ አማካኝነት የሚፈጸምን ዘለፋና ማንቋሸሽ መቆጣጠር አልቻሉም በሚል እየቀረበ ያለውን ወቀሳ ተከትሎ የሚወሰድ ነው ተብሏል። በቅርቡ ይሞከራል በተባለው አዲስ አሰራር ተጠቃሚዎች በአራት አማራጮች ለተለጠፉ መረጃዎች መልስ እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ነው ኩባንያው የገለጸው። በዚህም ዓለም አቀፍ በሆኑ ገጾች ላይ ማንኛውም ሰው ምላሽ መስጠት የሚችል ሲሆን፥ ቡድን አልያም የማህበረሰብ ገጾች ላይ ለተለጠፉ መረጃዎች ደግሞ የዛ ቡድን ተከታይና በመረጃው ውስጥ የተጠቀሱ ሰዎች ብቻ ምላሽ እንዲሰጡ ያስገድዳል። በተጨማሪም መወያያ አጀንዳዎችና ጉዳዮች ላይ ደግሞ በዛ መወያያ ሃሳብ ላይ የተጠቀሱ አካላት ብቻ ምላሽ ይሰጣሉ። የተለጠፉ መግለጫዎች ላይ ደግሞ ማንኛውም አካል ምላሽ እንዳይሰጥ ይደረጋል ብሏል ትዊተር ባወጣው መግለጫ። ኩባንያው ከዚህ ቀደም ተጠቃሚዎች ገጻቸው ላይ ለለጠፉት መረጃ የሚሰጡ ምላሾችን መደበቅ እንዲችሉ የሚያግዝ አሰራር ተግባራዊ ማድረጉ ይታወሳል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: ትዊተር ተጠቃሚወች የሚለጥፏቸን መረጃወች ተከትሎ የሚሰጡ ምላሾችን መቆጣጠር የሚያስችል አሰራር መተግበሩ ለደንበኞቹ ምን ጥቅም ያስገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ደንበኞች በነጻነት እንዲሳተፉ ለማድረግ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና ጽሁፎቿ በአብዛኛው የሚያተኩሩት ምን ላይ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ አነሳሽነት በ12ኛው ክፍለ ዘመን በአቡነ ዮሴፍ ተራራ ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ የተሰራ ቤተክርስቲያንና በዚያው ዋሻ ውስጥ ከቤተርክስቲያኑ ፊትለፊት ያለ ቤተ መንግስት ህንጻ በአንድነት የሚጠሩበት ስም ነው። ዋሻው ከላሊበላ የ6 ሰዓት የእግር ጉዞ ርቀት ላይ ይሚገኝ ሲሆን 45ሜትር ርዝመት በ6 ሜትር ቁመትና 50ሜትር ጉድጉደት አለው። በዋሻው ውስጥና ውጭ ለጸበል የሚያገለግሉ ምንጮች ይፈልቁበታል። ዓፄ ይምርሃነ ክርስቶስ ከሮሃ ሆኖ አገሩን ያስተዳድር እንጂ ይሄው ቤተክርስቲያንና ቤተመንግስት ሲታነጽ መኖሪያውን ወድዚህ ዋሻ እንዳዛወረ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ የህይወት ታሪኩ ይገልጻል። የቤተክርስቲያኑ ህንጻ 3 መግቢያዎች ሲኖሩት በሰሜን(ለወንዶች)፣ ደቡብ(ለሴቶች) እና ምሥራቅ (ለካህናት) ይገኛሉ። በግድግዳው ላይ የሚገኙ፣ ነገር ግን በአቧራ የተሸፉኑት ምስሎች ከዚሁ ዘመን የሚመነጩ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የግድግዳ ምስላት ቀደምት ናቸው። ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ይህን ቤተክርቲያን በ16ኛው ክፍለዘመን መግቢያ ላይ የጎበኘው ሲሆን፣ እንደርሱ ዘገባ በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኑ 200 ደብተራዎች የነበሩት ሲሆን አጠቃላይ ቤቱ በሊቀ ካህናት ይመራ እንደነበር ሲጠቅስ፤ በወቅቱ መነኮሳት እንደማይኖሩበትም ዘግቧል። ከይምርሃነ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ጀርባ 3 መቃብሮች ሲኖሩ፣ የራሳቸው የዓፄ ይምርሃነ፣ የሴት ልጃቸው እና ከእስክንድርያ ንጉሱን ሊጠይቁ የመጡ ፓትሪያርክ እንደሆኑ ይጠቀሳል። ወደዋሻው ውስጥ በጣም ርቆ ደግሞ የብዙ ምዕመናን አጽም የሚታይበት ሰፊና ጨለማ ክፍል አለ። \n \nጥያቄ: ይህን ቤተክርቲያን በ16ኛው ክፍለዘመን መግቢያ ላይ የጎበኘው ሰው ስሙ ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የዩኔስኮ አካል በይነ መንግስታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን መቼ አደረገ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበእንግሊዝ የተሰራውና የመንገድ ላይ ምልክት ማድረጊያው ሮቦት ሙከራውን አድርጓል። ሮቦቱ የተለያዩ የመንገድ ምልክቶችን በማስመር ወጪና ጊዜን ይቆጥባል ተብሏል። የሙከራ ስራውን ባደረገበት ወቅት ውጤታማነት ታይቶበታል የተባለውቅ ሮቦት፥ በአራት ሰዓት በ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር መንገድ ላይ ምልክቶችን ማድረጉ ተነግሯል። ይህ ቴክኖሎጂ ጊዜን በመቆጠብ ስራውን የሚሰሩ ሰራተኞች ያጋጥማቸው የነበረውን ድካም፣ የሚደርሰውን የወገብ ጉዳት እና ምልክት በሚያደርጉበት ወቅት የሚከሰተውን የመኪና አደጋ ይቀንሳል ነው የተባለው። ይህን ቴክኖሎጂ የተቀበሉት ዋይ ጂ የመንገድ ተቋራጭ ቡድን ሥራ አስኪያጅ ዌን ጆንስተን፥ ቴክኖሎጂው መጨናነቅን ለመቀነስ፣ ጊዜን እና ገንዘብን ለመቆጠብ እንዲሁም ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው ነው ያሉት። እንዲሁም ለተሻለ እና ጥራት ላለው የመንገድ ላይ ምልክት ያገለግላልም ብለዋል። ምንጭ፡- traffictechnologytoday.com ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመንገድ ላይ ምልክት ማድረጊያው ሮቦት ለመጀመሪያ ጊዜ በየት አገር ተሰራ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በእንግሊዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በመጽሐፍ ቅዱስ ለሚገኙት መጻሕፍት ርእስ የተሰጠው በማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሠለስቱ ምዕት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፍሬምናጦስ የተወለዱት ታይር በምትባል ቦታ በምሥራቃዊ የሮማ ነገሥት በ፬ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያዎቹ ሲሆን ማንም መርምሮ ሊደርስበት በማይችለው በእግዚአብሔር ሀሳብ ወደ ኢትዮጵያ መተው ክርስትናን ከመሠረቱት ዋነኛው አባት ሆኖ በመቆጠር ፣ አገራችንን ከሌሎች ክርስቲያን አገሮች ጋር ያስተዋወቁ ፣ ያስተካከሉ ፣ በአክሱም ዘመነ መንግሥትና መንግሥት የተወደዱና የተከበሩ ፣ በመላው ኢትዮጵያ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የተከበሩ ታላቅ አባት ናቸው ። አባታችን ፍሬምናጦስ የ፲፪ ዓመት ልጅ እያለ ሜሮጵዮስ የተባለ ነጋዴ ፈላስፋም የነበረ መርከበኛ ይዞት ወደ አገራችን መጣ ። ከእርሱም ጋር ወንድሙ ኤድስዮስ የተባለም አብሮት እንደነበረ ይታወቃል ። እነዚህን ሁለት ወጣቶች አስከትሎ የመጣው ሜሮጵዮስ በቀይ ባሕር አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች በጣሉለት አደጋ በዚሁ እንደ ሞተ ታሪክ ይነግረናል ። ይህም በንጉሥ ዒዛና ዘመነ መንግሥት ሆነ ። ፍሬምናጦስና ኤድስዮስ ግን በወቅቱ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ ታዜር ጋር አድገዋል ። ንጉሡ በአእምሮ መብሰላቸውን ተመልክቶ ፍሬምናጦስ በጅሮንድ ኤድስዮስም ጋሻ ጃግሬው አድርጎ ሾማቸው ። ከዚያ በኋላ ንጉሥ ታዜር ሲያርፍ ወደ ፈለጉበት እንድሄዱ ነፃ ስለተለቀቁ ኤድስዮስ ወደ አገሩ ተመልሶ ሄዷል ። አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ግን ወንድሙን ሸኝቶ \"በጨለማ የሚኖረውን ሕዝብ ትቼ ወደ አገሬ አልመለስም\" በማለት የኢትዮጵያን ሕዝብ በማፍቀር እንደቀረ ታሪክ ያስረዳናል ። የቅዱሳን ፍቅራቸው እውነትም ልብ ይነካል ። በዚያን ዘመን በአገራችን ኢትዮጵያ ክርስትና ነገሥታቱ የታወቀ ቢሆንምኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ስርዓተ ንስሐ ፣ ስርዓተ ጥምቀት ፣ ስርዓተ ቅዳሴ ፣ ስርዓተ ቅዱስ ቁርባን የሚያከናውን ጳጳስ ስላልነበረ ይህን የተመለከቱ ነገስታት ኢዛናና ሳይዛና ጵጵስና እንዲያመጣ አባታችን አቡነ ሰላማን ወደ ግብጽ ላኩት ። አባታችንም ወደ ግብጽ በመሄድ ስርዓቶቹን በመማር በቅዱስ አትናትዮስ አንብሮተ እድ \"ኤጲስ ቆጶስ ዘአክሱም ወዘኩላ ኢትዮጵያ\" ተብሎ ጵጵስና ተቀበለ። \n \nጥያቄ: አባ ፍሬምናጦስ ማን የተባለው ነጋዴ ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሜሮጵዮስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጅሩ ቆላ ውስጥ እምባጮ መግደላዊት በሚባል ሥፍራ መጋቢት ፲፯ ቀን በ፲፰፻፺፩ ዓ/ም ተወለዱ። በቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያ ትምህርታቸውን እስከ ዳዊት ድረስ ካጠናቀቁ በኋላ የዜማ ትምህርት ተከታትለው ጾመ ድጓ እና ድጓን ዘልቀዋል። ቀጥሎም የቅኔ ትምህርታችውን አጠናቀው በ ፲፱፻፭ ዓ/ም በአሥራ አራት ዓመት ዕድሜያቸው በወንበር ፀሐፊነት የመጀመሪያ ሥራቸውን ጀመሩ። የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ፤ የዮሐንስ አፈወርቅን ትርጓሜ፤ እንዲሁም የመቅድመ ወንጌልን ትርጓሜ ትምህርት ያጠናቀቁት እኝህ ታላቅ ሰው ብርሃንና ሰላም (ጋዜጣ) የተሰኘው ጋዜጣ ሲመሠረት የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ በመሆን፣ ቀጥለውም በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የግዕዝና የአማርኛ አስተማሪ በመሆን አገልግለዋል። ከፋሺስት ወረራ በኋላ ከ፲፱፻፴፫ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷፫ ዓ/ም ድረስ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ሥነ ጽሑፍንና ታሪክን በተመለከተ፣ አሥራ ሦስት መጻሕፍትን የደረሱ ሲሆን፣ ሰባት መጻሕፍት ደግሞ ተርጉመው አቅርበዋል። እንዲሁም የተለያዩ ጽሑፎችን አሰባስበው ከማዘጋጀታቸው ባሻገር፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ሥራዎችም ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በትብብር አዘጋጅተዋል። \n \nጥያቄ: ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ የት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጅሩ ቆላ ውስጥ እምባጮ መግደላዊት በሚባል ሥፍራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንክን እንዴት ነው የሞተው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nንጉሡ ላሊበላ የሚለውን ስም ያገኘው፣ ሲወለድ በንቦች ስለተከበበ ነው ይባላል። ላል ማለት ማር ማለት ሲሆን፤ ላሊበላ ማለትም -ላል ይበላል (ማር ይበላል) ማለት አንደሆነ ይነግራል። ውቅር ቤተክርስቲያናቱን ንጉሡ ጠርቦ የስራቸው ከመላእክት እገዛ ጋር እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ይነግራል። በ16ኛው ከፍለ ዘመን አውሮፓዊ ተጓዥ ላሊበላን ተመልክቶ «ያየሁትን ብናግር ማንም እንደኔ ካላየ በፍጹም አያምነኝም» ሲል ተናግሮ ነበር። በላሊበላ 11 ውቅር ዐብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ (ባለ መስቀል ቅርፁ) ሲታይ ውሃልኩን የጠበቀ ይመስላል። ቤተ መድሃኔ ዓለም የተባለው ደግሞ ከሁሉም ትልቁ ነው። ላሊበላ (ዳግማዊ ኢየሩሳሌም) የገና በዓል ታህሳስ 29 በልዩ ሁኔታ ና ድምቀት ይከበራል፣ \"ቤዛ ኩሉ\" ተብሎ የሚጠራው በነግህ የሚደረገው ዝማሬ በዚሁ በዓል የሚታይ ልዩ ና ታላቅ ትዕይንት ነው።የሚደረገውም ከቅዳሴ በኋላ በቤተ ማርያም ሲሆን ከታች ባለ ነጭ ካባ ካህናት ከላይ ደግሞ ባለጥቁር ካብ ካህናት በቅዱስ ያሬድ ዜማ ቤዛ ኩሉ እያሉ ይዘምራሉ። 11ዱ የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት ቤተ መድሃኔ ዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ደናግል፣ ቤተ መስቀል፣ ቤተ ደብረሲና፣ ቤተ ጎለጎታ፣ ቤተ አማኑኤል፣ ቤተ አባ ሊባኖስ፣ ቤተ መርቆሬዎስ፣ ቤተ ገብርኤል ወሩፋኤል፣ ቤተ ጊዮርጊስ ናቸው። \n \nጥያቄ: በላሊበላ የጌታ ልደት ቀን በቤተ ማርያም የሚቀርበው ልዩ ዝማሬ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ቤዛ ኩሉ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየፌስቡክ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን የሶስተኛ ወገን የትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም (Third-Party Fact-Checking Program) መጀመሩን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ፕሮግራሙን ካስጀመረባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛምቢያ፣ ሶማሊያ፣ ቡሪኪና ፋሶ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኮትዲቯር፣ ጊኔ ኮናክሪ እና ጋና ይገኙበታል፡፡ ሶስተኛ ወገን የመረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት የሚያስችል እንደሆነ ተነግሯል፡፡ በዚህም የፌስቡክ ተጠቃሚዎች በማህበራዊ ሚዲያው ጥራት ያለው መረጃ የሚያገኙበትን አሰራር የሚያሻሽል እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: ፌስቡክ ሶስተኛ ወገን የመረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም በስንት አፍሪካ ሀገሮች ለመተግበር ወሰነ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ10 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: የላይቤሪያ መንግስት በወታደራዊው ኃይል ከስልጣን የተፈናቀለው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1980 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: አማርኛና ትግሪኛ ቋንቋ በምን መደብ ይካተታሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሴማዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የቢልሃርዝያ በሽታ እንዴት ይሰራጫል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ዊልያም ጄፈርሰን «ቢል» ክሊንተን (William Jefferson Bill Clinton) (የትውልድ ስም፦ ዊልያም ጄፈርስን ብላይዝ ፬ኛ፣ እንግሊዘኛ፡ William Jefferson Blythe IV) በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) በሆፕ አርካንሳው የተወለዱ ሲሆን ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ድረስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕሬዝዳንት ከመሆናቸዉ በፊት አምስት ጊዜ የአርካንሳው ስቴት አስተዳዳሪ ነበሩ። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን መቼ ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: በፋሺስት ወረራ ዘመን በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጭ የበረራ መሥመር የነበረው ኩባንያ ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አላ ሊቶሪያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ዳግማዊ ሚኒሊክ በአድዋ ጦርነት በጣልያን ላይ የተጎናጸፉት ድል ለሌሎች ፋይዳው ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የመናገሻ አምባ ማርያምን ገዳም እያስተዳደሩ ሳሉ፤ ከዚህ ሥልጣናቸው በተጨማሪ የአዲስ አበባ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መምህርነት በየካቲት ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ/ም ተሰጣቸው። ከዚያም ቀጥሎ መጋቢት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፭ዓ/ም በኢየሩሳሌም ያሉ የኢትዮጵያን ገዳማት በመንፈሳዊ መሪነት አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመው ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ ወደአገራቸው ተመለሱ። የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፯ ዓ/ም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት መንበር፥ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ዘነበረ በመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተብለው፥ አምሣ-ዘጠነኛው ዕጨጌ ሆነውተሽሙ። በዚሁ በዕጨጌነታቸው ዘመን የፋሺስት ወረራ ኢትዮጵያን ባጠቃ ጊዜ፣ በጦርነቱ ግምባር ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ተሰልፈው አብያተ ክርስቲያናትንና መጻሕፍትን የሚያቃጥል የምእመናንን ዘር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና በሃይማኖት፤ በጸሎት፣ በምህላ በርታ እያሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲያጽናኑ ቆዩ። በጦርነቱም ጊዜ የተቀመጡበት በቅሎ በአረር ተመቶ እስኪወድቅና የለበሱትም ካባ አምስት ላይ በጥይት እስኪበሳሳ ድረስ ከንጉሠ ነገሥቱ ሳይለዩ የቆራጥነት ሥራ ሠርተዋል። ሠራዊቱም ድል ህኖ በተፈታ ጊዜ ክንጉሠ ነገሥቱ ጋር በስደት ወደኢየሩሳሌም አቅንተው እስከ ድል ጊዜ ድረስ በስደት ቆይተዋል። በዚሁ በስደት ዘመናቸውም ሳሉ በርካታ ሐዋሪያዊ መልእክቶችን ለአርበኞችም፤ ለሕዝቡም በመላክ የማጽናናትና የሃይማኖታዊ ጣምሮችን ያስተላልፉ ነበር። ንጉሠ ነገሥቱ በስደት ከነበሩበት ከ’ባዝ’ (ብሪታንያ) ፥ ጥር ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጊዜው በስደት ኢየሩሳሌም ለነበሩት ወደ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ አንድ ፅላትና ለአገልግሎት የሚበቁ አምስት መነኮሳትን ወደ እንግሊዝ አገር እንዲልኩላቸው በአባ ሐና ጅማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት፣ ዛሬ ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም የተባለውን የመድኀኔ ዓለምን ጽላት ወደንጉሠ ነገሥቱ ወዳሉበት ባዝ የላኩት እሳቸው ነበሩ፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፥ ጥር ፲፪ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በኢትዮጵያ ጠረፍ በኡም-ኢድላ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ-ዓላማ ሲተክሉ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስም አብረዋቸው ነበሩ። \n \nጥያቄ: ፋሺስት ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ አቡነ ባስልዮስ ምን ደረጃ ላይ ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አምሣ-ዘጠነኛው ዕጨጌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ የምን ቤተሰብ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከማዕከላዊ ኦማዊ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎግል በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በቻይና የሚገኘውን ቢሮውን በጊዜያዊነት መዝጋቱን አስታወቀ። የመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከቻይና በተጨማሪ በሆንኮንግ እና ታይዋን የሚገኙ አገልግሎት መስጫ ቢሮዎቹን መዝጋቱንም አስታውቋል። ከጎግል በተጨማሪ አማዞን እና ማይክሮሶፍትን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሰራተኞቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ በሚል ተመሳሳይ እርምጃ ውስጥ መግባታቸው ተገልጿል። ጎግል ሰራተኞቹ ወደ ቻይና እና ሆንግ ኮንግ ከሚያደርጉት ጉዞ እንዲታቀቡና በቻይና የሚገኙትም በተቻለ ፍጥነት እንዲወጡ መምከሩም ተነግሯል። ባለፈው ሳምንት ፌስቡክ ሰራተኞቹ ወደ ቻይና እንዳይጓዙ ያስጠነቀቀ ሲሆን፥ ተሽከርካሪ አምራቹ ጄኔራል ሞተርስም ፋብሪካዎቹን ዘግቷል። ከዚህ በተጨማሪም የጃፓኑ ቶዮታ እስከ ፈረንጆቹ የካቲት 9 ድረስ በቻይና አገልግሎት መስጠት ማቆሙን አስታውቋል። የፈረንሣዩ ፒ ኤስ ኤ እንዲሁም የጃፓኖቹ ሆንዳ እና ኒሳን ሰራተኞቻቸውን ከቻይና የማስወጣት እቅድ እንዳላቸው ተነግሯል። ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተገኘባት ውሃን ከተማ መቀመጫቸውን ያደረጉ ዓለም አቀፍ አምራቾችም ሰራኞቻቸውን ከቻይና ማስወጣት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ውሃን የቻይና ሰባተኛ ትልቋ ከተማ እና ዋነኛ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያዎች መቀመጫ ናት። ምንጭ፦ ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: የኮሮና ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በየትኛው የቻይና ከተማ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ውሃን ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ ከአፍሪካ ስንተኛ የኖቤል ሽልማት ያገኙ ግለሰብ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ስድስተኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የሮዴዢያን ግዛት ከኢያን ስሚዝ መንግሥት ነጻነቷን ያገኘችው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆነው የተሸሙት መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፱፻፹፱ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ፈረንሳያዊ ሱዳን በመባል የምትታወቀው አፍሪካዊ ሀገር ማናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ማሊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nናሚቢያ ናሚቢያ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ፣ በስሜን በአንጎላና በዛምቢያ፣ በምስራቅ በቦትስዋና፣ በደቡብም በደቡብ አፍሪቃ ትካለላለች። በ1982 አመተ ምኅረት ነጻነትዋን ከደቡብ አፍሪቃ ስላገኘች በጣም አዲስ አገር ነች። ዋና ከተማዋ ዊንድሁክ ነው። የናሚቢያ በረኅ አውራጃ ከጥንት ጀምሮ በሳን (ቡሽማን)፣ በዳማራና በናማቋ ሕዝቦች ተሰፈረ። በ14ኛው መቶ ዘመን፣ የባንቱ ወገኖች ባስፋፉ ጊዜ አገሩን ሠፈሩ። ክልሉ ግን ከ19ኛው መቶ ዘመን በፊት በአውሮጳውያን አልተዘለቀም። በዚያን ጊዜ ጀርመን ደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ተብላ አገሪቱ የጀርመን ቅኝ ግዛት ሆነች። ዳሩ ግን ዋልቪስ በይ የተባለው ትንሽ ወደብ ብቻ የእንግሊዝ ግዛት ነበር። \n \nጥያቄ: ናሚቢያ በአፍሪካ በየት አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በደቡብ-ምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ተርሚናል ዛሬ ተመረቀ። ተርሚናሉ በ12 ሂክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ 800 ከባድ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑ ተገልጿል። የዲቾቶ የከባድ ተሽከርካሪ ተርሚናል 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ወጭ ተደረጎበት መገንባቱ ተነግሯል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የጭነት ማቆያ ተርሚናል በስንት ሄክታር ላይ አረፈ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ12 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nንጉሡ «አፄ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ» የሚለውን ስም በተቀዳጁ በማግሥቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. ወይዘሮ ጣይቱ ብጡል እቴጌ ተብለው ተሰየሙ። እቴጌ ጣይቱም ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ የተቀበሉትን ዘውድ ደፉላቸው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በታወቁበት «እቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል የክብር ስም ማኅተም ተቀረፀላቸው። እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፏቸው የገነነውና በአገር አስተዳደርም ውስጥ ከፍተኛ ሚና መጫወት የጀመሩት ኢትዮጵያ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ/ም በውጫሌ ላይ ከኢጣሊያ ጋር በተፈራረመችው ውል ውስጥ በጣልያንኛው ትርጉም ሀገሪቷን ነፃነት እንደሌላት ጥገኛ በማስመሰል ዓላማ ላይ የተመረኮዘ ውንብድና መኖሩ ከታወቀ ወዲህ ነው። ይህ ለአድዋ ጦርነት መነሳት ምክንያትና ዋነኛ መንስዔ የሆነው ጉዳይ ሊታወቅ የቻለው እቴጌ ጣይቱ የውጫሌው ውል አንቀፅ ፲፯ ላይ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ የተባሉት ቋንቋ አዋቂ ዓፄ ምኒልክ በሰጧቸው ትዕዛዝ መሠረት የውሉን ሰነድ በመመርመር የውሉ አስራ ሰባተኛው አንቀፅ የያዘውን የትርጉም መዛባት በመግለፅ ጉዳዮ ኢትዮጵያ የምትጐዳበት ስለመለሆኑ ጭምር በማስረዳት በሰጡት ቃል ሲሆን እቴጌ በዚህ ወቅት ነገሮችን በጥንቃቄ የሚከታተሉ ስለነበር ዓፄ ምኒልክ በመጀመሪያ ሳይረዱ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ እንዲታሰሩ ቢያደርጉም እቴጌ ጣይቱ ግን እኒህ ሰው ትክክለኛ የኢትዮጵያ ወዳጅ መሆናቸውን ለዓፄ ምኒልክ በማስረዳት ከሦስት ዓመታት እስራት በኋላ ማስፈታቸው ይታወቃል። እቴጌ እንደተናገሩትም «ዓፅመ ጊዮርጊስ ቢታሰር ቢፈታም ለሀገሩ የሚገባውን ሠርቶ ነው። ኧረ ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ዮሴፍ፣ ጣሊያኖች በተንኮል ገብተው በማታለል ይህን የመሰለ ሥራ ሲሠሩ አነጋጋሪ ሆኖ ሳለ እንዴት ሳይስጠነቅቅዎ ቀረ?» በማለት የእቴጌ ጣይቱ የቁጣ መዓት ወደ ዮሴፍ ዞረ። \n \nጥያቄ: የውጫሌ ውል በስንት ዓ.ም የተደረገ ስምምነት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየቅርጫት ኳስ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬትቦል በዓለም ዙሪያ በቡድኖች የሚጫወት የኳስ እስፖርት ነው። ጨወታው በ1885 ዓም በካናዳዊው ዶ/ር ጄምስ ነይስሚስ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ። በመላው አለም ተወዳጅነትን ያተረፈ የቡድን ስፖርት አይነት ነው፡፡ ጨዋታው እኤአ በ1891 በካናዳዊው ዶ.ር ጀምስ ኒስሚዝ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ፡፡ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬት ቦል፡፡ ጨዋታው በእጅ የሚከናወን ሲሆን በመሰረታዊነት የ4 መአዘን ሬክታንግል ቅርፅ ያለው መጫወቻ ኮርት 5 ተጫዋቾ ያሉት ሁለት ቡድኖች እና በእጅ የሚወረወረው ድቡልቡል ኳስ ለጨዋታው አስፈላጊ የሆኑ ቁሶች ናቸው፡፡ 5ቱ ተጫዋቾ ሁልጊዜም የተጫዋቾችን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ከተጫዋቾቹ በቁመት ረጅም የሆነው ተጫዋች አብዛኛውን ጊዜ የመሀል ቦታ ይይዛል፡፡ እኤአ በ1891 በካናዳዊው የጂም መምህር ጀምስ ኒስሚዝ በስፕንግ ፊልድ ማሳቹስትስ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የተፈጠረው የቅርጫት ኳስ በአሁኑ ሰአት በአለማችን ላይ እጅግ ታዋቂና በመላው አለም በርካታ ተመልካቾች ያሉት የስፖርት አይነት ነው፡፡ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን ለአለም ፕፌሽናል ባስኬት ቦል በማሳደግና በማስተዋወቅ በክፍያ በተሰጥኦና በውድድር ብቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶለታል፡፡ ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ያሉ የብሄራዊ ሊግ መስፈርትን ያሟሉ ታላላቅ ክለቦች ለአህጉራዊ ቻምፒየን ሺፕ እንደ ኢሮሊግ እና FIBA አሜሪካ ሊግ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን አስተዋፅኦ ማሳያ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ የFIBA ባስኬት ቦል ወርልድ ካፕ እና men’s Olympic basketball ውድድር ዋና ዋና የአለማቀፍ ዝግጅቶችን እና የብሄራዊ ቡድኑ በርካታ ተጫዋቾችን መሳብ የቻሉ ውድድሮች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የቅርጫት ኳስ ጨዋታ መቼ ተፈጠረ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1885 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመስከረም 21/2012 ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚ) ህብረት ሲንፖዚየምን ልታስተናግድ ነው። ሲምፖዚየሙ ከመጪው ሳምንት ማክሰኞ መስከረም 27 ቀን 2012 ዓም ጀምሮ ለአራት ቀናት የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጰያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንሲቲትዩት ዛሬ ለኢዜአ ገልጿል። ከጥንታዊ ሳይንሶች አንዱ የሆነው ሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚ) ከመሬት ከባቢ አየር ውጪ የሚገኙ ክስተቶችን የሚያጠና የሳይንስ ክፍል ሲሆን ፀሐይ፣ የከዋክብትና የጨረቃዎች ስርዓት ማለት ነው። ሲንፖዚየሙ የኢትዮጰያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንሲቲትዩት፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ከምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባባሪያ ጽህፈት ቤት ጋር በጋራ በመሆን እንደሚካሄድ ተገልጿል። በምስራቅ አፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባ ውስጥ የሚካሄደው ሲንፖዚየም ከ30 አገራት የተውጣጡ ወደ 160 የሚደርሱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያውያን ተመራማሪዎችና ባለ ድርሻ አካላት ይሳተፉበታል። ሲንፖዚየሙ በአገሪቱ መካሄዱ በስፔስ ሳይንስ ዘርፍ ላይ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ልምድ ለማግኘት እድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል። አለም አቀፍ የሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚካል) ህብረት 100ኛ ዓመት እየተከበረ እንደሚገኝም ተገልፇል። ዓመቱ በኢትዮጵያም ስለየሥነ ፈለክ ሳይንስ ግንዛቤ በሚፈጥሩ ዝግጅቶች እየተከበረ መሆኑን ነው መግለጫው ያመለከተው። ሲንፖዚየሙ ከመካሄዱ በፊት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2ኛና 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች እና በአስር የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዙ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እንደሚሰጡም ተገልጿል። ከሲንፕዚየሙ ቀጥሎም ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን ስልጠና እንደሚሰጥም እንዲሁ። ከሲንፓዚየሙ ጎን ለጎን የሥነ ፈለክ ሳይንስ በአፍሪካ እንዲያድግ ስትራቴጂ ይቀረጽበታል ተብሎ የሚጠበቅ የአፍሪካ የሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚካል) ማህበር ውይይት እንደሚካሄድም ተገልጿል። ውይይቱ የሥነ ፈለክ ሳይንስ በአፍሪካ ያለውን ተደራሽነት ለማስፋት እንደሚያስችልም ነው የተጠቀሰው።   \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለምአቀፍ ሥነፈለግ (አስትሮኖመር) ህብረት ሲምፖዚየም የምታዘጋጀው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መስከረም 27 ቀን 2012 ዓም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ ከምን ያህል የመርርብ ጉዞ በኋላ እንግሊዝ ደረሰ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከሶስት ወራት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: በሳውዲ ከነዳጅ ምርቱዋ በተጨማሪ በምን ትታወቃለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአንድ ወጣት ተማሪ ከወዳደቁ ቁሳቁሶች በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ መስራቱ ተገለጸ፡፡ ጌታባለው መኩሪያው የተባለው ወጣት በባህርዳር ዩኒቨርስቲ 3ኛ ዓመት የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሲሆን ወጣቱ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች እንዲሁም አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የብስክሌት አካላትን ተጠቅሞ ነው የብስክሌት ጀልባ (Pedal-Boat) መስራት የቻለው፡፡ ጌታባለው መኩሪያው ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የሰራውን የብስክሌት ጀልባ በውሃ ላይ በመንዳት ሙከራ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: ፈጠራውን እንዴት አድርጎ ለማሳየት ሞከረ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በውሃ ላይ በመንዳት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nደስታ ተክለወልድ አለቃ ደስታ ተክለወልድ የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ነበሩ። ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ የተወለዱት አለቃ ደስታ፣ ያረፉት ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን ከአጥቢያቸው ጀምሮ እስከ ደብረ ሊባኖስ የቅኔና የዜማ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ቀለምን ፈጥኖ በመቀበልና በማስተዋል ችሎታቸው የተመሰከረላቸው አለቃ ደስታ የመጻሕፍት አንድምታ ትርጓሜን አደላድለዋል፡፡ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የሠሩ ሲሆን፣ በእርሳቸው አረጋጋጭነት በርካታ መጸሕፍት ለሕትመት በቅተዋል፡፡ በሀገረ ጀርመን በታተመው ኢንሳይክሎፔዲያ ኢትዮፒካ እንደተዘገበው፣ ወደ ድሬዳዋ በመሄድ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ሥራቸውን የቀጠሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው ከሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መተዋወቃቸው ነበር፡፡ ከ30 ዓመት በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምን እየሠሩ ዐምድ አጋጣሚውን እንዲህ ያስታውሰዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አለቃ ደስታ ተክለወልድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ የምትችል ተሸከርካሪ በኢትዮጵያዊ ወጣት መሰራቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ነዋሪ የሆነው ታዳጊ አጃዬ ማጆር ተሸከርካሪዋን ከወዳደቁ ብረቶች እንደሰራት ተነግሯል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባደረገለት ድጋፍ የተሰራችው የባለ ሁለት እግር ተሸከርካሪ ሞተርን በመጠቀም የተሰራች ሲሆን ወደ ኋላ መሄድ እንድትችል ተደርጋ ተሻሽላ ተሰርታለች፡፡ አራት ኩንታል ክብደት ያላት ተሽከርካሪዋ እስከ 4 ሰዎች የመጫን አቅም ያላት ሲሆን በአንድ ሊትር እስከ 40 ኪሎ ሜትር መጓዝ ትችላለች ተብሏል፡፡ ታዳጊው የ11ኛ ክፍል ተማሪ ሲሆን ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ መኪና መስራቱ ተገልጿል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለታዳጊው የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያዊው ወጣት የተሰራው ተሽከርካሪ ስንት ሰው መጫን ይችላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 4 ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒና በአትላንታ ኦሎምፒኮች የወርቅ ሜዳልያ ያገኘው በምን የሩጫ ዓይነት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: በጣና ሐይቅ ከሚገኙ ደሴቶች የቀደምት ኢትዮጵያውን መሪዎች መቃብር የሚገኘው በየትኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በዳጋ ደሴት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሶቪዬት ሕብረት ሶቭየት ሕብረት ሰብአዊ ሪፐብሊክ በ፲፱፻፲ ዓ.ም. የተከሰተውን የሩሲያ አብዮት ፍንዳታ፤ እንዲሁም ያንን ተከትሎ ለሦስት ዓመታት የተከናወነውን የሩሲያ «ውስጣዊ ሕዝባዊ የርስ በርስ ግጭት» ተከትሎ በኅብረተስብአዊ ሕገ መንግሥት (socialist constitution) በአራት ሪፑብሊኮች ቅንብርነት የተመሠረተ አገር ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ከቀድሞው የናዚ ጀርመን እጅ የተወሰዱ አገሮችን በማቀላቀል እንዲሁም በ፲፱፻፵፱ ዓ.ም በጉልበት ሌሎች የምሥራቅ አውሮፓ አገሮችን በመቀላቀል ኅብረቱ ዓሥራ ስድስት ሪፑብሊኮችን ያካተተ ነበር። በዘመን ቆይታና በጥንካሬም የጎለበተ ሕዝባዊ አብዮታዊ የኅብረት ሪፑብሊክ በመሆኑም በተለይ በ«ቀዝቃዛ ጦርነት» በሚባለው በ«ምዕራብና በምሥራቅ» ዓለም ተከስቶ በነበረው ፍጥጫ ጊዜ፣ በዓለም ላይ ለሚመሠረቱ ሕዝባዊ መንግሥታት ዋና የሽከታ አርአያ የነበረ መንግሥት ነበር። በ ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጀምሮ ይሄ ኅብረት እስከፈረሰበት እስከ ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ድረስ በተካሄደው የ«ቀዝቃዛ ጦርነት» ዘመን የሶቪየት ኅብረት በዓለም ከነበሩት ሁለቱ ተቃራኒ ኃያላን መንግሥታት አንዱ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ላይ በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም የተመሠረተውን የአብዮት ወታደራዊ የደርግ መንግሥት በጦር መሣሪያ፤ በአማካሪነት፤ በገንዘብ፤ ወዘተረፈ፤ ዋነኛ ደጋፊና ታላቅ ተዋናይ አገር ነበር። የቀድሞው የሶቪዬት ኅብረት መጨረሻ ላይ ታኅሣሥ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ተደምስሶ በዓለም መንግሥታት እውቀትና ስምምነት ሕጋዊ ወራሽነት የሩሲያ መንግሥት እንደሆነ ታወጀ። ሩሲያም በዚህ መሠረት የቀድሞውን የሶቪዬት ሕብረት የውጭ ዕዳዎች እንዲሁም የውጭ ንብረቶች በፈቃዱ ተቀበለ። በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ተፈርመው የነበሩም ዓለም አቀፍ ስምምነቶችንም ሩሲያ መቀበሏን አስታውቃለች። \n \nጥያቄ: የሶቪዬት ኅብረት መጨረሻ ላይ ታኅሣሥ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ፈርሶ በዓለም መንግሥታት እውቅናና ስምምነት ሕጋዊ ወራሽነት የማን እንዲሆን ታወጀ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሩሲያ መንግሥት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: የመለጋሲ ቋንቋ ከባንቱና ከአረብኛ ቋንቋዎች በመቶኛ ምን ያህል ቃላትን ተውሷል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 10% ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መስራች ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ በ1992 እ.ኤ.አ. የተደረገውን ዲሞክራሲያዊ ምርጫ በማሸነፍ ወደ ስልጣን የመጡት መሪ ማን ይባለሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አልፋ ዑመር ኮናሬ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ዘመነ ሰማዕታት የሚባለው ጊዜ ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ285 - 395 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር በሮማይስጥ ምን ማለት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በአዳማ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨረርሲቲ እየተገጣጠሙ ያሉት ሁለቱ ሊትል ስታር የተሰኙት ሳተላይቶች በየት ሀገር ባለሙያዎች ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \n‹‹አለቃ ኪዳነ ወልድ ብርሃንና ሰላምን ሲጎበኙ ደስታ ተክለ ወልድ የግእዙን መጽሐፍ ከፍ ባለ ድምፅ ሲያነብቡና ሲያናብቡ ሰምተው ‘ከኔ ጋር ሥራ’ ብለው ጠይቀዋቸው ነው ይባላል፡፡ ከዚህም የተነሣ በድሬዳዋ አልአዛር ማተሚያ ቤት 16 ዓመት ያህል ሠርተዋል፡፡ እንደገና ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በብርሃንና ሰላምና በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤቶች አገልግለዋል፡፡ ‹‹አስተማሪዬ መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ የጀመሩትን ግእዝ አማርኛ ግስ እንድጨርስ አዘውኝ ነበር፡፡ እነሆ እስከ ዛሬ ደክሜበታለሁ፤ አልተጠናቀቀልኝምና አንተ ተረክበኸኝ ሥራውን ቀጥል፡፡ ዘርሁን፤ ዘር ይውጣልህ›› ብለው አለቃ ኪዳነ ወልድ ለአለቃ ደስታ አደራ ሰጥተው ነበር፡፡ አለቃም አደራውን ጠብቀው በ1948 ዓ.ም. ከመደበኛ ሥራቸው ውጭ ሌት ከቀን በመሥራት ‹‹መጽሐፍ ሰዋሰው ወግስ፤ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ›› የተባለውን የመጀመሪያ ታላቅ መዝገበ ቃላት አሳትመዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር የነበሩት የታሪክ ምሁሩ ነፍስ ኄር ዶ/ር ብርሃኑ አበበ ስለ አለቃ ክፍሌና ስለ አለቃ ኪዳነ ወልድ ለ‹‹ምን እየሠሩ ነው?›› አዘጋጅ ሲገልጹ እንዲህ ብለዋል፤ ‹‹አለቃ ክፍሌ በወቅቱ የአገሪቱ የቀለም ሰዎች ከተባሉት አንዱ ነበሩ፡፡ ዘመኑም የአፄ ዮሐንስ ነበር፡፡ የሃይማኖት ክርክሩ ቦሩ ሜዳ ላይ ተነሥቶ አለቃ ክፍሌ በኋላቀር ካህናት ከሃዲ መስለው በመታየታቸውና በአፄ ዮሐንስ ዘንድ እጅግ ፊት በማጣታቸው የሸዋ ንጉሥ የነበሩት ምኒልክ አገር ጥለው እንዲሰደዱ ይመክሩዋቸዋል፡፡ ከዚያም በምድረ ሱዳን አድርገው ግብፅ ቀጥለውም ወደ ኢጣልያ ይሻገራሉ፡፡ እነ አግናጥዮስ ጒይዲንና ሌሎችንም ግእዝ ካማርኛ ያስተምራሉ፡፡ ቀጥሎም እርጅና ሲመጣባቸው ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ ያደርጋሉ፡፡ ከዚያም አለቃ ኪዳነ ወልድን ያገኛሉ፡፡ ያላቸውን ዕውቀት ከውድ መጻሕፍታቸው ጋር ለኪዳነ ወልድ ያስረክባሉ፡፡ በተለይም የግእዝና የአማርኛ መዝገበ ቃላት በውል ተሰናድቶ እንዲታተም ለኪዳነ ወልድ አደራ ይሰጣሉ፡፡ በአገሪቱ ዘመናዊ ማተሚያ ሲቋቋም አለቃ ኪዳነ ወልድ ለመጻሕፍት ትርጓሜ ሥራ ወደ አገራቸው ይጠራሉ፡፡ እሳቸው ከአለቃ ክፍሌ የተቀበሉትን አደራ ለአለቃ ደስታ ተክለ ወልድ ያስረክባሉ፡፡ የዚህ ዐቢይ መዝገበ ቃላት ሥራ መነሻው ይህ ነው፤›› በማለት ስለሦስቱም ሊቃውንት ያላቸው ግምት ከፍተኛ መሆኑን አንፀባርቀዋል፡፡ ዶ/ር ብርሃኑ የሦስቱንም የቀለም ሰዎች ታሪክ በፈረንሣይኛ ቋንቋ አዘጋጅተው ‹‹ሃይማኖተ አበው ቀደምት ወዘደኃርት›› ከተባለው የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፍ ጋር አዳብለው በ1978 ዓ.ም. በጀርመን ማሳተማቸው ይታወቃል፡፡ አለቃ ደስታ ለኢትዮጵያ ባህል፣ ቋንቋና ታሪክ ካበረከቷቸው ሥነ ጽሑፋዊ ትሩፋቶች መካከል የግእዝ መማርያ ‹‹ርባሐ ስም ወአንቀጽ›› (1946 ዓ.ም.) እና ‹‹ገበታ ሐዋርያት›› (1928 ዓ.ም.) ይገኙበታል፡፡ ‹‹አንባቢ ሆይ ያማርኛ ቋንቋ ይህ ብቻ እንዳይመስልህ ከዚህ የቀረውን የእንስሳትንና የአራዊትን የአዕዋፍን፣ የዓሣትን፣ የዕፅዋትን፣ ያገርንና የሰውን ስም አምልተን፣ አስፍተን፣ ከነትርጓሜው ለማሳየት ሐሳብ አለን፤ ለዚሁም ያምላካችን ፈቃዱ ይሁን፤›› ብለው በመዝገበ ቃላቱ ላይ ጽፈው ነበር፡፡ ያልታተሙትን ሥራዎቻቸውን ሁለተኛውን እትም ያሳተሙት ልጆቻቸውና ወራሾቻቸው ለንባብ እንደሚያበቁት ይጠበቃል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ ተክለወልድ በድሬዳዋ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ለምን ያህል አመት ሰሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 16 ዓመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለአገልግሎት ክፍት የምታደርግበት ምክንያት ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nብርቱካን ብርቱካን (ወይም ኦሬንጅ) ማለት የዛፍ አይነትም ሆነ በተለይ የዚሁ ዛፍ ፍሬ ማለት ነው። የሌሎች አትክልት ክልስ ሆኖ ከጥንት እንደ ለማ ይታሥባል። እርዝማኔው እስከ 10 ሜትር ድረስ ቢደርስም ዛፉ ትንሽ ይባላል፤ ቡቃያው እሾህ አለበትና ቅጠሎቹ ከ4 እስከ 10 ሳንቲሜትር ድረስ የሚዘረጉ እንደ ጥድም ወገን መቸም የማይረግፉ ናቸው። የፍሬው መጀመርያ ትውልድ በደቡብ-ምሥራቃዊ እስያ በህንደኬ፣ በቬትናም ወይም በደቡብ ቻይና ተገኘ። የብርቱካን እርሻ በብዙ አገሮች ምጣኔ ሀብት በጣም ታላቅ የንግድ ሥራ ነው። እዚህ ማለት በአሜሪካ፣ በሜዲቴራኔያን አገሮች፣ በሮማንያ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በቻይና፣ በአውስትራልያም ይከትታል። \n \nጥያቄ: የብርቱካን ዛፍ ቁመቱ ስንት ሜትር ይሆናል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 10 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየባሕል ጥናት የባህል ጥናት፣ ሥነ ኅብረተሠብ ወይን ሥነ ማኅበረሰብ ሌላ ስሙ ሶሲዮሎጂ የሰው ልጆች በቡድንና በተናጥል ያላቸውን ባሕል፣ ጠባይና አደረጃጀት የሚያጠና ክፍል ነው። በዚህም ውስጥ አንትሮፖሎጂ ወይም የሰው ልጅ ጥናት (ሥነ ሰብእ) አለ። ሶሲዮሎጂ የሚለው ቃል በፈረንሳያዊው ጸሐፊ ኤማኑወል-ዦሰፍ ሲዬ በ1772 ዓ.ም. ከሮማይስጥ ሶኪውስ (ባልንጀራ፣ ጓደኛ) እና ከግሪክ ሎጎስ (ቃል ወይም ጥናት) በማጋጠም ተፈጠረ። የፈረንሳይ ፈላስፋ ኦጉስት ኮምፕት ከ1830 ዓ.ም. ጀምሮ በሰፊ ጠቀመው። የኅብረተሰብ ጥናት ሲሆን የኅብረተሰብ ጽንሰ ሀሣብ በሮማይስጥ ትርጉም ሶኪየታስ ወይም የባልንጀሮች ግንኙነት ያመልከታል። \n \nጥያቄ: የሰው ልጆች በቡድንና በተናጥል ያላቸውን ባሕል፣ ጠባይና አደረጃጀት የሚያጠና የሳይንስ ክፍል ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሶሲዮሎጂ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍሪዩልያን ፍሪዩልያን (Furlan) በስሜን-ምሥራቅ እጣልያ በ600,000 ሰዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። ከነዚህ ተናጋሪውዎች አብዛኞቹ ደግሞ ጣልኛ የሚችሉ ናቸው። የቋንቋ ስም በጣልኛ ፍሪዩልያኖ ሲሆን በራሱ ግን ፉርላን ወይም ማሪለንጌ ይባላል። ላዲን ለሚባለው ቋንቋ ቅርብ ዝምድና ስላለው አንዳንዴ \"ምስራቅ ላዲን\" ይሰየማል። ከዚያ በላይ በስዊስ አገር ለሚናገረው ለሮማንሽ ቅርብ ዘመድ ነው። ዛሬ በጣልያ መንግሥት በኩል ፍሪዩልያን ይፋዊ ሁኔታ አለውና በብዙ ትምህርት ቤቶች ይማራል። ጥቂት ሥነ ጽሑፍ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም፣ ዘፈኖችና አንዳንድ የመንገድ ምልክት፣ ደግሞ የድረ-ገጽ ጋዜጣ በፍሪዩልያን አለ። ባለፈው አመት ውስጥ የቢራ ማስታወቂያ ቢሆንም በፍሪዩልያን በጣልያ ቴሌቪዥን ታይቷል። ስለዚህ ዱሮ ቋንቋው በጣም ትንሽ ከሆነ አሁን ግን በጉልበት እየተመለሠ ነው። \n \nጥያቄ: ፍሪዩልያን ቋንቋ በጣልያን በምን ያህል ሰዎች ይነገራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ600,000 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: በአንበሶች ዘንድ መንጋውን እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንበሶች ክብደታቸው ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: ዘጠኙ ቅዱሳን መቼ ወደ ኢትዮጵያ መጡ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ፬፻፶፩ ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፕሮፌሰር ሙሃመድ ዩኑስ ትውልድ በ28 ጁን 1940 እ.ኤ.አ. የባንግላዴሽ የባንክ ባለሞያና ኤኮኖሚስት ናችው። ማይክሮክሬዲት ተብሎ የሚታወቀውን የአነስተኛ የብድር አገልግሎት በችግር ለሚኖሩ ወገኖች የመስጠትን ስራ የጀመሩትና የስፋፉት ሰው ናችው። ፕሮፌሰሩ እንነኝህ ባንክ አላስተናግድ ብሎ የተዋቸውን ድሆች የሚያገለግለውን ግራሚን ባንክን አቋቁመዋል። በጥቅምት 1999 ፕሮፈሠሩና ባንኩ የሰላም የኖቤል ተሸላሚ ለመሆነ በቅተዋል ይህም ሽልማት የልማት እድገትና ማህበረሰባዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በማስመስከራቸውና ይህ ደግሞ ለሰላም ወሳኝነት ያለው መሆኑን ሽልማት ሰጭው ኮሚቴ ስላመነበት ነው። ፕሮፌሰር የበርካታ ሽልማቶች ባለቤት ሲሆኑ ከነዚህም የአለም የምግብ ሽልማት ይገኝበታል። የድሆች አበዳሪ በሚል ርዕስ አንድ የስራሳቸውንና የስራቸውን ታሪክ የሚያትት መጽሐፍ ደርሰዋል። \n \nጥያቄ: ማይክሮክሬዲት የተሰኘውን የአነስተኛ የብድር አገልግሎት ተቋም በችግር ለሚኖሩ ወገኖች የመስጠትን ስራ የጀመሩና ያስፋፉ ፕሮፌሰር ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፕሮፌሰር ሙሃመድ ዩኑስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ በስፋት ከሚነገሩ ቋንቋዎች በተናጋሪ ብዛት ሁለተኛ ደረጃ ያለው የቱ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ቆሣ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: ኮንግ-ፋጸ ፍልስፍና ውስጥ ልዩ ትኩረት ያገኙት የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ በሕንደኬ ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 45.5 ሚልዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ ፓርላሜንቱ የሚገኘው የት ከተማ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኬፕ ታውን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሳርፌ ቢዝነስ የብረት ማቅለጫ ማሽኑን ከየት ለመግዛት ነው የወሰነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከህንድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዩጋንዳ ከመቼ ጀምሮ ነበር በታላቁ ብሪታን ስትገዛ የነበረው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1894 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ ምድር ጸሓይን ትዞራለች እንጂ ፀሓይ መሬትን አትዞርም ብሎ ያስተማረው ማን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ መስከረም 15/2012 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሰራተኞቹ ጋር በሬድዬ ግንኙነት በመፍጠር አገልግሎቱን የሚያቀላጥፍበት የአስትሮ ሞቶሮላ የሬድዬ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት አስመረቀ። የፕሮጀክቱ ምረቃ ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር በተገኙበት በእንጦጦ ማሪያም የቴሌ ማይክሮዌቭ ማሰራጭያ ጣቢያ ተካሂዷል። በሁለት ምዕራፍ የተከፈለውን ፕሮጀክት ወደ ሥራ ለማስገባት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ሐምሌ 15 /2017 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና በሞቶሮላ ሶሉሽን ኩባንያ መካከል ስምምነት ተፈርሞ ነበር። የመጀመሪያው ምዕራፍ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአዲስ አበባና ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ኦሮሚያ ዞን ላይ ተግባራዊ ሆኗል። የኤሌክትሪክ የአገልግሎት አሰራሩን በማቀላጠፍ ለዜጎች የተሻለ አገልግሎት እንደሚሰጥ የታመነበት ይሄው ፕሮጀክት 6 ቡድኖችን በመያዝ በ 8 የግንኙነት ቻናሎች በጋራ እና በእኩል ሁኔታ እንዲጠቀሙ የሚያግዝ ነውም ተብሏል። የአስቸኳይ ጥገና ሥራን ማቀላጠፍ፣ ከሰብ ስቴሽን ጋር የሚኖረውን ግኝኑነት ማሳለጥ፣ በግንኙነት ክፍተት ሊፈጠሩ የሚችሉ የሰውና የንብረት አደጋን መቀነስ እንዲሁም የኃላፊዎችን መረጃ የመቀበልና መልዕክት የማስተላለፍ ሥራውን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገልጿል። በኤሌክትሪክ አገልግሎት የአውቶሜሽንና ኢነርጂ ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደመቀ ሮቢ አገልግሎቱ ስራውን የሚያከናውነው በስልክ እንደነበር አስታውሰው ይህም የሚሰጠው አገልግሎት ቅልጥፍና እንዳይኖረው አድርጎት ቆይቷል ይላሉ። ዛሬ የተመረቀው የሬድዮ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት መስክ የወጡ የጥገና ሰራተኞች ቢሮ ካሉ ሰራተኞች ጋር በፍጥነት እንዲገናኙ ከማድረጉም ባለፈ ከፍተኛና ዝቅተኛ ኃይል መስመር ላይ ካሉ ኦፕሬተሮች ጋርም በቀላሉ በመገናኘት ፍጥነት ያለው የጥገና አገልግሎቶች እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። በዚሁ የመጀመሪያው ምዕራፍም በአዲስ አበባና ዙሪያ በእጅ የሚያዙ 300 እንዲሁም 200 መኪና ላይ የሚገጠሙና 100 በጥሪ ማዕከልና በአስቸኳይ ጥገና ማዕከላት ላይ የሚገጠሙ ዲጂታል ሬዲዮኖች ጥቅም ላይ ውለዋል። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ ምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክቱንም ለማካሄድ ከአዲስ አበባ ውጪ 8 ከተሞች የተመረጡ ሲሆን ለዚህም ከ4 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት ተይዞለታል። \n \nጥያቄ: በምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክቱን ማካሄድና ከአዲስ አበባ ውጪ በስንት ከተሞች ሊሠራ ታስቧል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 8 ከተሞች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጎፋ ብሔረሰብ ለጋብቻ የሚሆን እድሜ ከስንት ጀምሮ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nብጉር ብጉር ማለት የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከቆዳ ስር በሚገኙ የወዝ እጢዎች በሚመነጭ ቅባት ወይም ወዝ እና በሞቱ የቆዳ ህዋሳት በብዛት መከማቸትና በቀዳዳው መደፈን የሚፈጠር እባጭ ነው። በርካታ ጥናቶች ጭንቀት ብጉርን ከማባባሱም በላይ የቆዳ ጤንነት ችግር ላይ እንዲወድቅ ያደርጋል ይላሉ። ብጉር በጣም ከተለመዱት የቆዳ ችግሮች ውስጥ አንዱ ነው። ዕድሜ ዘርና ጾታ ሳይገድበው ሁሉንም ያጠቃል። ቆዳችን ላይ ብዙ ጥቃቅን ቀዳዳዎች አሉ። በነዚህ ቀዳዳዎች ውስጥ ደግሞ ቅባታማ ፈሳሽ የሚያመነጩ ዕጢዎች አሉ። የቅባታማ ፈሳሽና የቀዳዳዎቹ ጥቅም የሞቱ የቆዳችን ህዋሳትን ለማስወገድ ነው፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች እነዚህ ቀዳዳዎች ሲዘጉ ቅባታማ ፈሳሹ በቆዳችን ውስጥ ስለሚጠራቀም ብጉር ይፈጠራል፡፡ የተጠራቀመው ቅባትም ለህዋሳት መራባት ዕድል ስለሚከፍት አንዳነዴ መግል ይይዛል፡፡ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከ'ስቤሸስ ግላንድ' ጋር የተያያዙ ናቸው፡ እነዚህ እጢዎች ሴበም የሚባል ንጥረነገር ሲያመነጩ ንጥረነገሩም በጸጉር መውጫ ቀዳዳ ወደላይ ወደቆዳ የሚወጣ እና ቆዳችን ላይ የሚያርፍ ነው። የብጉር መፈጠር የቆዳ ህዋሳትን ያበዛል። ይህ እባጭ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎችን ግርግዳ በመግፋት ነጫጭ የብጉር ሽፍታዎች ሲፈጥር የቀዳዳዎችን ግርግዳ በመጎተት ደግሞ ጥቋቁር የብጉር ሽፍታዎች (blackheads) ቆዳችን ላይ ሊፈጥር ይችላል። ብጉር በብዛት ሊወጣ የሚችልባቸው ቦታዎች፣ ፊት ላይ፣ በደረት፣ በኣንገት፣ በትከሻ ፣ እና በጀርባ ላይ ነው። \n \nጥያቄ: የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከቆዳ ስር በሚገኙ የወዝ እጢዎች በሚመነጭ ቅባት ወይም ወዝ እና በሞቱ የቆዳ ህዋሳት በብዛት መከማቸትና በቀዳዳው መደፈን የሚፈጠር እባጭ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ብጉር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: የሳውዲ አረብያ መሬት በምን የተከበበ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በረሃ የተከበበ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ የጣሉት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጥር 2፣ 1929 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: አፕል ኩባንያ በፈረንሳይ ስንት አመት አገልግሎት ሰጠ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የ40 ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: ኤዎስጣጤዎስ አጥብቀው የሚያስተምሩት ትምህርት ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ስለ ሰንበት መከበር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: ጋሊልዮ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ታህሳስ 15, 1564 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። \n \nጥያቄ: በ1937 የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለዓለም ያበሰረው የጀርመን ተወላጅ ማን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ቡክሀርት ባልደክኼር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሚያዝያ ፲፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፳፰ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፳፫ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፴፰ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፴፯ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ። ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ታሽኬንት በትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ክስተት ስትወድም ሰብ ስምንት ሺ መኖሪያ ቤቶች በመጥፋታቸው ከሦስት መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎቿ መኖሪያ ቢስ ሆነዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በሼክ ሞሀመድ ማህሙድ ኤል ሳዋ የተመራ የሳዑዲ አረቢያ\tልዑካን ቡድን ለአጭር ጉብኝት አዲስ አበባ ገባ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ከደርግ በተላለፈ ትእዛዝ መሠረት፣ የፖሊስ አለቆች፤ የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ታሠሩ። ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር። \n \nጥያቄ: በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር የመሠረቱት መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ መነሻ የሆነው ዘፋኝ ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አበበ ተሰማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ ላይ ምን ያህል አጫጭር ታሪኮችን ለዓለም አበርክቷል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: የአንባሳ ግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በምን ያህል ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሁለት ወር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ የምን ቋንቋ ቤተሰብ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የባንቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ የጋሊልዮ ጥናት ትክክለኛ እንደነበር በማመን ማንን ወክለው ነው ስለደረሰበት ግፍ ይቅርታ የጠየቁት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: የቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መቼ ተመረቀ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: የማሊ ሪፐብሊክ መሪ የነበረው ሞዲባ ኪየታ በመፈንለ-መንግሥት ከስልጣኑ የወረደው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1968 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአስዋን ግድብ የአስዋን ግድብ ደቡባዊ የግብፅ ከተማ በሆነችው አስዋን ውስጥ የሚገኝ የናይል ትልቅ ግድብ ነው። ከ1950ዎቹ እ.አ.አ. ጀምሮ ሥሙ የሚገልፀው ከፍተኛው ግድብ የሚለውን ሲሆን ይህም በ1902 እ.አ.አ. የተጠናቀቀውን የአስዋን ዝቅተኛ ግድብ አዲስ እና ታላቅ መሆኑን ለማሳየት ነው። ከ1960 እስከ 1970 እ.አ.አ. ነበር ከእንግሊዝ የሀገሪቱን ቅኝ ግዛት ነፃ መሆን ተከትሎ የዚህ ግድብ ግንባታ የተካሄደው። የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከማሳደግ አንጻር ከፍተኛ ሚና እንዲጫወት ተደርጎ የተገነባው ይኸው ግድብ ከአላስፈላጊ የጎርፍ አደጋዎች ለመጠበበቅ፣ ለግብርና የሚውል የውሃ ክምችት እንዲኖር በማድረግ በመጨረሻም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲኖር ለማድረግ አስችሏል። የዚህ ግድብ ቀዳሚ የግንባታ ሙከራ የተካሄደው በ11ኛው ክፍለ ዘመን ነበር። በዚህ ጊዜ የኢራቅ ተወላጅ የሆነው መሃንዲስ ኢብን አል ሃያትም በጊዜው በነበሩት የሃገሪቱ ከሊፎች ፋጢሚድ ከሊፍ እና አል ሃኪም ቢ-አምረላህ ተጠርቶ ነበር። ይህ የመጀመሪያው የግድቡ ግንባታ ሙከራ ሲሆን በመስክ ስራ ላይ አመርቂ ውጤት ባለማምጣቱ እና የጊዜውን ሀገረ ገዢዎች ቁጣ በመፍራቱ የአዕምሮ ጤና መታወክ ደርሶበት በቤት ውስጥ እስር ከ1011 እ.አ.አ. እስከ አልሃኪም ሞት 1021 እ.አ.አ. ድረስ እንዲቀጣ ተደርጎ ነበር። የ1882 እ.አ.አ. የእንግሊዝ ግብፆችን ወረራ ተከትሎ ነበር እንግሊዝ በ1898 እ.አ.አ. የግድቡን ስራ የጀመረችው። ግንባታው በ1902 እ.አ.አ. ተጠናቆ ክፍት የሆነው ዲሴምበር 10፣ 1902 ሲሆን ሙሉ ዲዛይን የተደረገው በዊሊያም ዊልኮክስ እና በጊዜው በነበሩ መለስተኛ መሃንዲሶች ነበር። በ1946 እ.አ.አ. የአስዋን ዝቅተኛ ግድብ በመሙላቱ እና የእንግሊዝ መንግስት ተጨማሪ ግድብ አስፈላጊ መሆኑን በማመኑ ይህን ግድብ ለሶስተኛ ጊዜ ከማራዘም ይልቅ በወንዙ 7 ኪሎ ሜትር አካባቢ ከፍ ብሎ አዲስ ግድብ ለመስራት ተወሰነ። ቀጥሎ በተከሰተው የፖለቲካ ለውጥ የነበረውን አሃዳዊ አገዛዝ በጋማል አብደል ናስር በሚመራው እንቅስቃሴ በማስወገድ እና የ1936ቱ የአንጎሎ ግብጾች ስምምነት በማድረግ ለዋናው ግድብ እ.አ.አ. በ1954 ፕላን ወጣ። \n \nጥያቄ: የአስዋን ግድብ ቀዳሚ የግንባታ ሙከራ የተካሄደው በየትኛው ክፍለ ዘመን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ11ኛው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በተማሩበት ከ1980-2006 ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረሱት የት ዩኒቨርሲቲ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎግል የሶስተኛ ወገን አጠቃቀምን የሚገድብ አዲስ የግላዊነት ማስጠበቂያ ፖሊሲ የሚተገበርበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ። ተቋማት በበይነ መረብ ላይ እየጨመረ የመጣውን ጥቃት ተከትሎ የግላዊነት ጥበቃ ደህንነታቸውን እንዲያጠናክሩ የሚያደርግ ግፊት እየጨመረ ነው። ለዚህ ደግሞ በሶስተኛ ወገን የተጠቃሚዎችን የበይነ መረብ እንቅስቃሴ መከታተል የሚያስችሉት መሳሪያዎች (ኩኪዎች) ጋር በተያያዘ ያለው አጠቃቀም አናሳ መሆኑ ይነገራል። ጎግልም በሶስተኛ ወገን አጠቃቀምን የሚገድብ አዲስ የግላዊነት ማስጠበቂያ ፖሊሲ የሚተገበርበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። አዲሱ ፖሊሲ ፕራይቬሲ ሳንድቦክስ የሚል መጠሪያ ያለው ሲሆን፥ የሶስተኛ ወገን ማስታወቂያ አሰራጮች የተጠቃሚዎችን መረጃ በፈለጉት ጊዜ ሳይሆን በጎግል አማካኝነት እንዲያገኙ የሚያደርጋቸው ነው። ይህ መሆኑ ደግሞ ጎግል በዲጂታል ማስታወቂያ ገበያው ያለውን ተደራሽነት የበለጠ ያሰፋለታል እየተባለ ነው። ኩኪዎች የዲጂታል ማስታወቂያ ባለሙያዎች የተጠቃሚዎችን እንቅስቃሴ ማዕከል ተንተርሰው ማስታወቂያ እንዲሰሩ ይረዷቸዋል። ኩባንያዎች በበይነ መረብ ላይ የግለሰቦችን እንቅስቃሴ ለማወቅ የመረጃ ማፈላለጊያዎች ላይ የተከማቹ መረጃዎችን ይጠቀማሉ። በዚህም የጎበኟቸውን ድረ ገጾች ጨምሮ በዲጅታል ማስታወቂያ የተደረጉ የግብይት እንቅስቃሴዎችን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን፥ ማስታወቂያ ሰሪዎችም ተጠቃሚወችን መሰረት ያደረገ መረጃ እንዲለቁ ያግዛቸዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: የሶስተኛ ወገን አጠቃቀምን የሚገድብ አዲስ የግላዊነት ማስጠበቂያ ፖሊሲ ያወጣው የቴክኖሎጂ ድርጅት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጎግል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ዳኞች ምን ዓይነት ቅጣት እንዲበይኑበት ሲጠየቅ የሶቅራጥስ መልስ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአክሱም አክሱም በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክ/ሃገር ከአድዋ ተራራዎች አጠገብ የምትገኝ ከተማ ነች። በክርስቶስ ልደት በፊት ተመስርቶ የነበረው የአክሱም ስርወ መንግስት ማእከል ነበረች የአክሱም ስርወ መንግስት በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ እየተዳከመ ሲመጣ የማእከላዊው መንግስት ወደ ደቡብ ተንቀሳቀሰ። ሰባ አምስት በመቶ የሚሆነው የከተማው ነዋሪ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ነው። የተቀሩት ነዋሪዎች የሱኒ እስልምና ተከታዮች ናቸው። ባላቸው ታሪካዊ ተፈላጊነት ከተማ ውስጥ የሚገኙት የአክሱም ስርወ መንግስት ቅሪቶች UNESCO በ1980 የአለም ቅርስ ቦታ ተብለው ተሰይመዋል ። አክሱም በኢትዮጵያ የ ትግራይ ክልል ከተማ ሲሆን በማዕከላዊ ዞንና በላዕላይ ማይጨው ወረዳ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የአክሱም ስርወ መንግስት መቀመጫ የነበረችው የኢትዮጵያ ከተማ ማናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አክሱም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየእብድ ውሻ በሽታ የእብድ ውሻ በሽታ የየቫይረስ በሽታ ሆኖ ከፍተኛ የየአንጎል መጉረብረብን በሰዎች እና በሌሎች ደመ-ሞቃት እንስሳት ላይ የሚያስከትል ነው። ቅድሚያ ምልክቶቹ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠልን ያካትታል። እነዚህ ምልክቶች ከሚከተሉት አንድ ወይም የበለጡ ምልክቶች አስከትለው ይመጣሉ- ሃይል የታከለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች፣ ከቁጥጥር ወጭ የሆ መሸበር፣ የውሀ ፍራቻ, የሰውነት ክፍለን ለማንቀሳቀስ አለመቻል፣ ግራ መጋባት፣ እና ህሊናን መሳት። ምልክቶቹ ከታዩ በኋላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ በአብላጫው ሁልጊዜ ሞትን ያስከትላል። በበሽታው በመያዘዎ እና ምልክቶቹ መታየት የሚጀምሩበት የጊዜ ገደብ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የጊዜ ገደብ ከሳምንት ባነሰ እና ከአመት በበለጠ ጊዜ ሊለያይ ይችላል። የጊዜ ገደቡ የሚወስነው የበሽታ አምጭው ረቂቅ ህዋስ ወደ የማዕከላዊ የነርብ ስርዓትለመድረስ በሚፈጅበት እርቀት ነው። የእብድ ውሻ በሽታ በአለም ዙሪያ በአመት ከ26,000 እሰከ 55,000 ሞቶች ምክንያት ነው። ከ95% በላይ እነዚህ ሞቶች የተከሰቱት በኢሲያ እና አፍሪቃነው። የእብድ ውሻ በሽታ ከ150 ሀገራት በላይ እና ከአንታርቲካ በቀር በሁሉም አሀጉራት ይገኛል። ከ3 ቢሊዮን ሰዎች በላይ የእብድ ወሻ በሽታ በሚከሰትበት የአለማችን ከፍሎች ውስጥ ይኖራሉ። እጅግ በአብዛኛው አውሮፓ እና አውስትራሊያ፣ የእብድ ወሻ በሽታ የሚገኘው በሌሊት ወፎች ላይ ነው። \n \nጥያቄ: እብድ ውሻ በሽታ የማይገኝበት አህጉር የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አንታርቲካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nታሊየም የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ መረጃ መዝባሪዎች ቡድን ሚስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር እንደተቆጣጠረው ማይክሮ ሶፍት አስታወቀ፡፡ መቀመጫው ሰሜን ኮሪያ እንደሆነ የታመነው ይህ መረጃ መዝባሪ ቡድን የመንግስት ሰራተኞችን ፣ የዩኒቨርሲቲ ሰራተኞችን ፣ የኒውክሌር ሙያተኞችን እና የጥናት ተቋማንን ኢላማ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የመረጃ መዝባሪ ቡድኑ በዋነኝነት ኢላማ ያደረገው በአሜሪካ የሚገኙ ተቋማትን ሲሆን በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚገኙ ተቋማንንም ኢላማ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡ ታሊየም በመጀመሪያ እይታ ትክክለኛ ሆነው የሚታዩ የኢሜል አድራሻዎችን በመጠቀም መረጃ ሲመዘብር ነበር ተብሏል፡፡ ማይክሮሶፍትም በአሁን ወቅት መረጃ መዝባሪ ቡድኑ የሚጠቀምባቸውን 50 የድር ጎራዎች መቆጣጠሩን የገለፀ ሲሆን በምሥራቃዊ ቨርጂኒያ አውራጃ በሚገኝ ፍርድ ቤት በጠለፋ ቡድን ላይ ክስ መመስረቱን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡-ሮይተርስ \n \nጥያቄ: ታሊየም የተባለው የሰሜን ኮሪያ ቡድን ምስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር የያዘው ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ማይክሮ ሶፍት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በግብጽ ሀገር አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ያዘጋጀው ፍትሐ ነገሥት መች ተጻፈ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1240 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጨረቃ ላይ መውጣት ጨረቃ ላይ መውጣት የምንለው ማናቸውም ሰው ሰራሽ መንኮራኩሮች ጨረቃ ገጽ ላይ ሲያርፉ ያለውን ክንውን ነው። ይህ እንግዲህ ሰውንም ሆነ ያለሰው የተደረጉ በጨረቃ የማረፍ ክንውኖችን ይጠቀላላል። ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰራሽ የሆነ ነገር ጨረቃ ላይ ያረፈው በመስከረም 13፣ 1959 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውም የሶቭዬት ህብረት ሉና 2 ሚሲዮን ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ልጅ እራሱ ጨረቃ ላይ የወጣው ሐምሌ 20፣ 1969 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውን በአሜሪካው የአፖሎ 11 ሚሲዮን መንኮራኩር ነበር። ባጠቃላይ 24 አሜሪካውያን ወደጨረቃ ተጉዘዋል፣ 12ቱ የጨረቃን ምድር በእግራቸው ረግጠዋል። በዚህ ወቅት ሶቪየት ህብረትም የራሷን ጠፈርተኞች ለመላክ ሞክራለች። ለዚህ እንዲረዳት ጨረቃ ላይ አራፊ LK የተሰኘ መንኮራኩር ሰራች፣ ሆኖም ግን ይህን መንኮራኩር ወደ ጨረቃ የሚወስድ ከባድ ሃይል ያለው ሮኬት ከአሜሪካ ቀድማ መስራት ስላልቻለች ተቀደመች። ዩጂን ከርናን የጨረቃን ምድር የረገጠው የመጨረሻው ሰው ነው። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ልጅ እራሱ ጨረቃ ላይ የወጣው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሐምሌ 20፣ 1969 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአንጎላ አንጎላ፣ በይፋ የአንጎላ ሪፑብሊክ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ስትሆን ከናሚቢያ ፣ ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ፣ እና ከዛምቢያ ጋር ድንበር ትጋራላች። በምዕራብ ጫፍ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር ትገናኛለች። የፖርቹጋል ቅኝ-ተገዥ ነበረች። ነዳጅ እና አልማዝ ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የሚመደቡ ናቸው። የአንጎላ የሕግ-አስፈጻሚ ፕሬዝዳንቱን ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና የሚኒስትሮች ካውንስሉን ያጠቃልላል። ሁሉም ሚኒስትሮችና ምክትል ሚኒስትሮች የሚኒስተሮች ካውንስሉን ሲሰሩ በየጊዜው እየተሰበሰቡ ስለተለያዩ የፖለቲካ ጉዳዮች ውሳኔ ይሰጣሉ። የአስራ ስምንቱ ክልሎች መሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚመረጡት። በ1992 እ.ኤ.ኣ. የወጣ ሕገ-መንግስት የመንግስቱን አወቃቀር እና የዜጎችን መብትና ግዴታ ይዘረዝራል። ፕሬዝዳንቱ መንግሥቱ በ2006 እ.ኤ.ኣ. ምርጫ ለማድረግ ዕቅድ እነዳለው ገልጸዋል። ይህ ምርጫ ከ1992 አ.ኤ.ኣ. በኋላ የመጀመሪያው ምርጫ ነው የሚሆነው። አንጎላ ውስጥ ሶስት ዋና ብሔረሰቦች ይገኛሉ። ኦቪምቡንዱ 37% ፣ ኪምቡንዱ 25% ፣ እና ባኮንጎ 13%። ሌሎች ብሔረሰቦች ቾክዌ (ሉንዳ)፣ ጋንጉዌላ፣ ንሀኔካ-ሁምቤ፣ አምቦ፣ ሄሬሮ፣ እና ዢንዱንጋን ያጠቃልላሉ። በተጨማሪም ክልሶች (አውሮፓና አፍሪካዊ) 2% ይሆናሉ። ፖርቱጋሎች አንጎላዊ ካልሆኑ ሰዎች ብዙዎቹ ናቸው። ታሪክ በአንጎላ መጀመሪያ የሠፈሩት የኮይሳን ሰዎች ነበሩ። በባንቱ ፍልሰቶች ጊዜ እነዚህ ሰዎች ወደ ደቡብ አንጎላ ሄዱ። በ1483 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋሎች በኮንጎ ወንዝ አጠገብ ሠፈሩ። በ1575 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋል ካቢንዳ ጋር በባሪያ ንግድ ላይ ያቶከረ ግዛት መሠረተች። በ16ኛው ክፍለ ዘመን፣ ፖርቱጋል የአንጎላ የባህር ጠረፍን ተቆጣጠረች። በተለያዩ ውሎችና ጦርነቶች የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት አንጎላ ተስፋፋ። የፖርቱጋል መመለሻ ጦርነትን ምክኒያት በማድረግ የደች ሪፐብሊክ ሏንዳን ከ1641 እስከ 1648 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ተቆጣጠረች። \n \nጥያቄ: አንጎላ በምዕራብ በኩል ከየትኛው ውቅያኖስ ጋር ነው የምትዋሰነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከአትላንቲክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ ምን ያህል መፃህፍትን ፅፈዋል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ 20 በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nከአፍሪካ ህዝብ ውስጥ 24 በመቶ ብቻ የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆናቸውን ዓለም ባንክ አስታወቀ፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት አለመስፋፋት በአህጉሪቱ አዳዲስ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ የስራ ዕድል ፈጠራዎችን ለማስፋፋት አዳጋች እንደሚሆን ነው ባንኩ የገለጸው፡፡ በአፍሪካ እኤአ ከ2015 እስከ 2035 ባለው ጊዜ ውስጥ 450 ሚሊዮን ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የዓለም ባንክና የአፍሪካ ልማት ባንክ በጥምረት ያወጡት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ እንደ ኢኮሜርስ እና ፋይናንስ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የስራ ዘርፎችን በአፍሪካ በማስፋፋት ከፍተኛ የስራ እድልን መፍጠር እንደሚቻል ተጠቅሷል፡፡ በዚህም፣ ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በቂ እውቀት እንዲኖራቸው በማድረግ ማሰማራት እንደሚገባ ተነግሯል፡፡ \n \nጥያቄ: በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ከ2015-2035 እ.ኤ.አ 450 ሚሊየን ያህል ስራ ፈላጊ ሰዎች ይኖራሉ ብሎ የገመተው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የዓለም ባንክና የአፍሪካ ልማት ባንክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ በአዲስ አበባ ሳለ በየት ቤተ ክርስቲያን ተቀጥሮ ሰራ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዞ አዞዎች ረዘም ብሎ ጠንካራ የሆነ የራስ ቅል አላቸው። በዛ ያሉ ጠንካራ ጥርስ አፋቸው ውስጥ ተደርድረው ይታያሉ። ውኃና ምግብ በአፋቸው በያዙበት ጊዜ እንኳን መተንፈስ የሚያስችላቸው ተፈጥሮ አላቸው። አዞዎች እንቁላል ጣዮች ናቸው። ከ20 እስከ 50 እንቁላሎች ብስባሽ ቅጠላ ቅጠሎች ውስጥ ጥለው እናቶቻቸው ይጠብቋቸዋል። ይህም እንቁላሉ ሊፈለፈል ሲቃረብ ከእንቁላሉ ውስጥ የሚሰሙት ድምፅ እንቁላሉን ሰብረው ጫጩቶቹ እንዲወጡ ለማድረግ ያስችላቸዋል። እንደ ኤሊዎችና አንዳንድ እንሽላሊቶች ሁሉ እንቁላሎቹ የተጣሉበት ሁኔታ (ጎጆ) የሙቀት መጠን የሚፈለፈሉትን ጫጩቶች ጾታ ይወስናል። ሆኖም ከኤሊዎች በተቃራኒ የእንቁላሉ ጎጆ የሙቀት መጠን መቀነስ ሴቶችን፣ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ደግሞ ወንዶችን እንዲፈለፈሉ ያደርጋል። ሁሉም አዞቻች አምፊቢየስ ይባላሉ። ምክንያቱም ታዳጊዎቹም ትልልቆቹም ከፊሉን ጊዜያቸውን ውኃ ውስጥ ከፊሉን መት ላይ ስለሚያሳልፉት ነው። ረጅምና ጠንካራ ጭራቸው እንደ መሣሪያ በማገልገል ሰውንም ሆነ ሌላ እንስሳ ፊቱ ላይ መትቶ በመጣል ለጥርሳቸው ያቀርብላቸዋል። በውኃ ውስጥም ባላቸው ፈጣን እንቅስቃሴ ከእነሱ ለማምለጥ ከባድ ይሆናል። ለረጅም ጊዜ ከውኃ ሥር ሆነው መቆየት ቢችሉም እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎች በሳምባ የሚተነፍሱ ናቸው። ስለዚህም አፍንጫቸውን ከውኃው በላይ በማውጣት አየር ይስባሉ። ሁሉም አዞዎች እንቁላል ይጥላሉ። እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎችም እንቁላሎቹን መሬት ውስጥ ይቀብራሉ። ሴቶቹ አዞዎች በሚሠሯቸው ጎጆዎች ይለያያሉ። አንዳንዶቹ አሸዋ ውስጥ ቀዳዳ በመቆፈር እንቁላሉን ይቀብሩትና ይሸፍኑታል። ሌሎቹ እንደ አሊጌተር ዓይነቶቹ ብዛት ያለው የበሰበሰ ቅጠላ ቅጠፀል በመሰብሰብ እዛ መሃል እንቁላሉን ይጥሉታል። ብዛት ያላቸው ደርዘን እንቁላሎች (እያንዳንዱ በመጠን ከዶሮ የበለጠ) በአንድ ቁጭታ ሊጥሉ ይችላሉ። ሲፈለፈሉ ታዳጊዎቹ አዞዎች ከ22-25 ሳንቲ ሜትር ቁመት ይኖራቸዋ”ል። አዞዎች ጥርሳቸውን በተደጋጋሚ ይተካሉ። የሚተካው (ያረጀው) ጥርስ ሥር ያለው አዲስ ጥርስ ሲሆን፤ አዲሱ ተኪ ጥርስ አድጎ ትልቅ ካልሆነ በስተቀር አሮጌው ቶሎ ብሎ ወልቆ አይወድቅም። የአዞ አይን 360 ዲግሪ ማየት ይችላል። እንዲሁም ሰው 180 ዲግሪ ዘውሮ ማየት ይችላል። \n \nጥያቄ: አዞዎች በምን መልክ ይራባሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አዞዎች እንቁላል ጣዮች ናቸው። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአራተኛ አልበሙ \"ፐርፐዝ\" በሁለት ሺ ሰባት ተለቀቀ እነዚህንም ቀጥር አንድ የሆኑ ሙዚቃዎች ያዝሉለታል፦ \"ዋት ዱ ዩ ሚን\"፣ \"ሶሪ\" እና \"ሎቭ ዩርሰልፍ\"። \"ዌር ኧር ዩ ናው\" ከአሜሪካው የኢዲኤም ቡድን ጃክ ዩጋ የሰራው ይህ ነጠላ ዘፈን በግራሚ ምርጥ ዳንስ ቅጅ በሚለው ፈርጅ ሊሸለም ችሏል። በቀጣይ ጊዜያት ጀስትን ቢበር አነዚህ ሙዚቃዎች ላይ ድምፁን አዋጣ ከተለያዩ አርቲስቶችጋ፣ ሙዚቃዎቹ፦ \"ኮልድ ዋተር\"፣ \"ለት ሚ ሎቭ ዩ\"፣ \"አይ አም ዘ ዋን\"፣ እና \"አይ ዶንት ኬር\" ፡ ሙዚቃዎቹም በአሜሪካ የደረጃ ሰንጠረዥ አምስት ውስጥ ሊገቡ ቻሉ። \"ደስፓሲቶ\" ለተሰኘው ሙዚቃም ድምፁን ሙዚቃው ከተለቀቀ በኋላ በማከል ዋና ዘፋኞቹን ደገፈ ፡ ሙዚቃውም ለብዙ ሳምንታት ከፍታ ላይ ቆየ በቢልቦርድ። \"ተን ታውዘንድ አወርስ\" ሙዚቃ ላይም በድምፅ ተሳትፏል ሙዚቃው ጥንድ/ቡድን በተሰኘ ፈርጅ ግራሚ ሊያሸንፍ ቻለ። አራተኛ አልበሙን ከለቀቀ አምስት አመት በኋላ ጀስትን በ፪፲፻፲፪ አምስተኛ አልበሙን በተለየ የሙዚቃ አቀራረብ ለቀቀ ከአልበሙም እነዚህ የአርኤንድቢ ሙዚቃዎች አምስት ውስጥ ሊገቡለት ቻሉ ፡ \"የሚ\" እና \"እንተንሽንስ\"። ከአለም ምርጥ ሻጭ አርቲስቶች አንዱ የሆነው ጀስትን ከአንድ መቶ ሀምሳ ሚልየን ቅጂዎች በላይ ሸጦ እናም የተለያዩ አያሌ ሽልማቶችን ሊያገኝ ችሏል ተካተው፦ ሀያ ሶስት የአለም ጊነስ ርኮርዶች፣ ሁለት ግራሚ፣ አንድ የርኮርድ ትወኒዋ ኤም ቲቪ ዩሮፕ ሚውዚክ፣ ሀያ የቢልቦርድ፣ አስራ ስምንት የሜሪከን ሚውዚክ አዋርድስ፣ ሁለት የብርት አዋርድስ፣ አራት የኤም ቲቪ ሚውዚክ ቪድዮ ሽልማቶችና አንድ ደግሞ የላቲን ግራሚ ሽልማ። \"ታይም\" የተባለ ታዋቂ የመረጃ ተቋም የአለማችን መቶ ከፍተኛ ተፅእኖ ፈጣሪ ሰዎች ብሎ ካወጣቸው ውስጥ ጀስትን ቢበር አንዱ ነበር በሁለት ሺ ሶስት። \n \nጥያቄ: ጀስቲን ቢበር ምን ያህል ቅጅዋችን ሸጧል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከአንድ መቶ ሀምሳ ሚልየን ቅጂዎች በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት አዳነ ግርማ በግንባሩ ገጭቶ ጎል ያስቆጠረው ስንተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ላይ ነበር ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 29ኛው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ የቀብር ስነ ስርዓት የት ተፈፀመ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአል ረሽዳን መስጊድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና ብሔራዊ ቋንቋ ባይሆንም በስፋት የሚነገረው ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ትዊኛ (አካንኛ) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: በ1989 የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ እንዲያስተላልፉበት ያደረገው ስራው ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 15/2012 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሰራተኞቹ ጋር በሬድዬ ግንኙነት በመፍጠር አገልግሎቱን የሚያቀላጥፍበት የአስትሮ ሞቶሮላ የሬድዬ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት አስመረቀ። የፕሮጀክቱ ምረቃ ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር በተገኙበት በእንጦጦ ማሪያም የቴሌ ማይክሮዌቭ ማሰራጭያ ጣቢያ ተካሂዷል። በሁለት ምዕራፍ የተከፈለውን ፕሮጀክት ወደ ሥራ ለማስገባት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ሐምሌ 15 /2017 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና በሞቶሮላ ሶሉሽን ኩባንያ መካከል ስምምነት ተፈርሞ ነበር። የመጀመሪያው ምዕራፍ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአዲስ አበባና ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ኦሮሚያ ዞን ላይ ተግባራዊ ሆኗል። የኤሌክትሪክ የአገልግሎት አሰራሩን በማቀላጠፍ ለዜጎች የተሻለ አገልግሎት እንደሚሰጥ የታመነበት ይሄው ፕሮጀክት 6 ቡድኖችን በመያዝ በ 8 የግንኙነት ቻናሎች በጋራ እና በእኩል ሁኔታ እንዲጠቀሙ የሚያግዝ ነውም ተብሏል። የአስቸኳይ ጥገና ሥራን ማቀላጠፍ፣ ከሰብ ስቴሽን ጋር የሚኖረውን ግኝኑነት ማሳለጥ፣ በግንኙነት ክፍተት ሊፈጠሩ የሚችሉ የሰውና የንብረት አደጋን መቀነስ እንዲሁም የኃላፊዎችን መረጃ የመቀበልና መልዕክት የማስተላለፍ ሥራውን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገልጿል። በኤሌክትሪክ አገልግሎት የአውቶሜሽንና ኢነርጂ ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደመቀ ሮቢ አገልግሎቱ ስራውን የሚያከናውነው በስልክ እንደነበር አስታውሰው ይህም የሚሰጠው አገልግሎት ቅልጥፍና እንዳይኖረው አድርጎት ቆይቷል ይላሉ። ዛሬ የተመረቀው የሬድዮ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት መስክ የወጡ የጥገና ሰራተኞች ቢሮ ካሉ ሰራተኞች ጋር በፍጥነት እንዲገናኙ ከማድረጉም ባለፈ ከፍተኛና ዝቅተኛ ኃይል መስመር ላይ ካሉ ኦፕሬተሮች ጋርም በቀላሉ በመገናኘት ፍጥነት ያለው የጥገና አገልግሎቶች እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። በዚሁ የመጀመሪያው ምዕራፍም በአዲስ አበባና ዙሪያ በእጅ የሚያዙ 300 እንዲሁም 200 መኪና ላይ የሚገጠሙና 100 በጥሪ ማዕከልና በአስቸኳይ ጥገና ማዕከላት ላይ የሚገጠሙ ዲጂታል ሬዲዮኖች ጥቅም ላይ ውለዋል። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ ምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክቱንም ለማካሄድ ከአዲስ አበባ ውጪ 8 ከተሞች የተመረጡ ሲሆን ለዚህም ከ4 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት ተይዞለታል። \n \nጥያቄ: በኤሌክትሪክ አገልግሎት የአውቶሜሽንና ኢነርጂ ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደመቀ ሮቢ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል አጎታቸው ማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ንጉሥ ኃይለ መለኮት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአስትራዜኔካ የኮቪድ-19 ክትባት ላይ በአሜሪካ፣ በቺሊና በፔሩ በተደረገ ሙከራ የጎንዮሽ ጉዳት የሌለውና አስተማማኝ መሆኑን የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በሶስቱ አገሮች በሁሉም የእድሜ ክልል በሚገኙ 32 ሺህ በጎ ፈቃደኛ ሰዎች ላይ ባደረገው ምርምር ክትባቱ ውጤታማና ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መሆኑን ማረጋገጡን የሮይተርስን ዋቢ አድርጓ ኢዜአ ዘገቧል ፡፡ \n \nጥያቄ: በአስትራዜኔካ ላይ የተደረገው ጥናት ውጤት ስለክትባቱ ምንን አመላከተ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ክትባቱ ውጤታማና ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መሆኑን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በአፍሪካ ውስጥ ስንት ሀገሮች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 54 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: የፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የክትባት ግኝት በዓለም ላይ ያሉ ከብቶችን በምን በሽታ እንዳይጠቁ ማድረግ ችሏል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በደስታ በሽታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nከአድዋ ሽንፈት በኋላ ጣሊያኖች ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራርመው አዲስ ገዢ፣ ፈርዲናንዶ ማርቲኒ፣ 1897 ላይ በመሾም ግዛታቸውን ማጽናት ጀመሩ። በዚህ ወቅት የቀደመው ወታደራዊ ስርዓት እንዲቋረጥ ተደርጎ አገሪቱ የብሔር ልዩነትን \"በሚያከበር\" አስተዳደር ተከፍሎ እንዲቋቋም ተደረገ። ዳህላክ፣ አፋር እና ሰምሃር አንድ ላይ \"ምስራቃዊ ክፍል\" ተብለው ከምጽዋ እንዲተዳደሩ ተደረገ። \"ምዕራባዊ ክፍል\" ከአቆርዳት እንዲተዳደር ሲደረግ ቤኒ አሚርን፣ ናራንና ኩናማ ምድርን ያጠቃልል ነበር። ከከረን ሆኖ የሚተዳደረው ደግሞ ሰሜናዊ ሐማሴን (የእስልምና ተከታይ የሆነ)፣ ቤት አሰገደና ዓድ ሼኽ ነበሩ። ቀሪው ሐማሴን ከአስመራ፣ ሰራየ ከመንደፈራ(አዲ ወግሪ) እንዲተዳደር ሲደረግ አካለ ጉዛይ ከሳሆ ጋር ተዋህዶ ከአዲ ቀይሕ ይገዛ ጀመር። ከላይ ወደታች በተዘርጋ መዋቅር የጣሊያን ባለስልጣኖች እያንዳንዱን ክፍል ያስተዳድሩ ጀመር። የአገሪቱ ዋና ከተማ ከምጽዋ ወደ አስመራ የተዛወረው በዚህ ወቅት፣ በ1898 ነበር። ከ1898 እስከ 1908 በተደረጉ ውሎች (ከኢትዮጵያ፣ ከአንግሎ-ግብጻዊ ሱዳንና ከጅቡቲ ጋር) መሰረት የቅኝ ግዛቱ ድንበር ታወቀ። ኢትዮጵያን ስለ ድንበሩ ለማሳመን 3 አመትና 5ሚሊዮን ሊሬ ፈጅቶባቸው ግንቦት 1900 ላይ ያሰቡት ሊሳካላቸው ቻለ። ድንበሩ ከሞላ ጎደል የመረብ፣ በለሳና ሙና ወንዞችን የታከከ ነበር። \n \nጥያቄ: ጣልያኖች በአድዋ ጦርነት በኢትዮጰያ ከተሸነፉ በኋላ በኤርትራ ፈርዲናንዶ ማርቲኒ የሾሙት መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1897 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት የነበሩት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ዎሌ ሾይንካ የሥነ ጽሑፍ ኖቤል ተሸላሚ የነበሩት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1986 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የሴቶች የስራ ፈጠራ ፕሮጀክትን ለማገዝ የሚውል የ100 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ። ከባንኩ ትዊተር ገጽ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ድጋፉ ሴት ስራ ፈጣሪዎችን ስራዎቻቸውን ለማሳደግ የሚችሉበት ገንዘብ፣ ክህሎትና አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሴቶች የሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት የሚውል ምን ያህል ገንዘብ ለመስጠት ወሰነ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የ100 ሚሊየን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት ያስተዋቀቀው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መንግሥቱ ለማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ ስንት ክልሎች አሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አራት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየመደመር መንገድ መጽሐፍ ሁለት ዓላማ ያነገበ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡ ይህም በአንድ በኩል ሐሳብ ማስተላለፍ በሌላ በኩል በገቢው ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል፡፡ የመጽሐፉ የነጠላ መሸጫ ዋጋ 350 ብር ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አንባቢዎች ሊዳረስ የሚችል በቂ ቅጅ ስላለ ከዚህ በላይ ከሚሸጡት እንዳይገዙም አሳስበዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የመደመር መንገድ መጽሐፍ ስንት ዓላማዎች አሉት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን የባርነት ተቋዋሚዋች ሪፐብሊካን ፓርቲን መቼ መሰረቱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የተመዘገበበት የፋየል እና የውሳኔ ቁጥር ስንት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የት ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አድዋ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ከሱዳን ተገንጥላ ራሷን የቻለችው ሀገር ማን ትባባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ደቡብ ሱዳን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በኦምዱርማን ውግያ የእንግሊዝ ሠራዊት ሱዳንን ድል በማድረግ ቅኝ አገር ያደረጉት በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1890 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nንጉሡ ላሊበላ የሚለውን ስም ያገኘው፣ ሲወለድ በንቦች ስለተከበበ ነው ይባላል። ላል ማለት ማር ማለት ሲሆን፤ ላሊበላ ማለትም -ላል ይበላል (ማር ይበላል) ማለት አንደሆነ ይነግራል። ውቅር ቤተክርስቲያናቱን ንጉሡ ጠርቦ የስራቸው ከመላእክት እገዛ ጋር እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ይነግራል። በ16ኛው ከፍለ ዘመን አውሮፓዊ ተጓዥ ላሊበላን ተመልክቶ «ያየሁትን ብናግር ማንም እንደኔ ካላየ በፍጹም አያምነኝም» ሲል ተናግሮ ነበር። በላሊበላ 11 ውቅር ዐብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ (ባለ መስቀል ቅርፁ) ሲታይ ውሃልኩን የጠበቀ ይመስላል። ቤተ መድሃኔ ዓለም የተባለው ደግሞ ከሁሉም ትልቁ ነው። ላሊበላ (ዳግማዊ ኢየሩሳሌም) የገና በዓል ታህሳስ 29 በልዩ ሁኔታ ና ድምቀት ይከበራል፣ \"ቤዛ ኩሉ\" ተብሎ የሚጠራው በነግህ የሚደረገው ዝማሬ በዚሁ በዓል የሚታይ ልዩ ና ታላቅ ትዕይንት ነው።የሚደረገውም ከቅዳሴ በኋላ በቤተ ማርያም ሲሆን ከታች ባለ ነጭ ካባ ካህናት ከላይ ደግሞ ባለጥቁር ካብ ካህናት በቅዱስ ያሬድ ዜማ ቤዛ ኩሉ እያሉ ይዘምራሉ። 11ዱ የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት ቤተ መድሃኔ ዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ደናግል፣ ቤተ መስቀል፣ ቤተ ደብረሲና፣ ቤተ ጎለጎታ፣ ቤተ አማኑኤል፣ ቤተ አባ ሊባኖስ፣ ቤተ መርቆሬዎስ፣ ቤተ ገብርኤል ወሩፋኤል፣ ቤተ ጊዮርጊስ ናቸው። \n \nጥያቄ: ከላሊበላ አስራ አንዱ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ግዙፉ የትኛው ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቤተ መድሃኔ ዓለም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዞ አዞዎች ረዘም ብሎ ጠንካራ የሆነ የራስ ቅል አላቸው። በዛ ያሉ ጠንካራ ጥርስ አፋቸው ውስጥ ተደርድረው ይታያሉ። ውኃና ምግብ በአፋቸው በያዙበት ጊዜ እንኳን መተንፈስ የሚያስችላቸው ተፈጥሮ አላቸው። አዞዎች እንቁላል ጣዮች ናቸው። ከ20 እስከ 50 እንቁላሎች ብስባሽ ቅጠላ ቅጠሎች ውስጥ ጥለው እናቶቻቸው ይጠብቋቸዋል። ይህም እንቁላሉ ሊፈለፈል ሲቃረብ ከእንቁላሉ ውስጥ የሚሰሙት ድምፅ እንቁላሉን ሰብረው ጫጩቶቹ እንዲወጡ ለማድረግ ያስችላቸዋል። እንደ ኤሊዎችና አንዳንድ እንሽላሊቶች ሁሉ እንቁላሎቹ የተጣሉበት ሁኔታ (ጎጆ) የሙቀት መጠን የሚፈለፈሉትን ጫጩቶች ጾታ ይወስናል። ሆኖም ከኤሊዎች በተቃራኒ የእንቁላሉ ጎጆ የሙቀት መጠን መቀነስ ሴቶችን፣ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ደግሞ ወንዶችን እንዲፈለፈሉ ያደርጋል። ሁሉም አዞቻች አምፊቢየስ ይባላሉ። ምክንያቱም ታዳጊዎቹም ትልልቆቹም ከፊሉን ጊዜያቸውን ውኃ ውስጥ ከፊሉን መት ላይ ስለሚያሳልፉት ነው። ረጅምና ጠንካራ ጭራቸው እንደ መሣሪያ በማገልገል ሰውንም ሆነ ሌላ እንስሳ ፊቱ ላይ መትቶ በመጣል ለጥርሳቸው ያቀርብላቸዋል። በውኃ ውስጥም ባላቸው ፈጣን እንቅስቃሴ ከእነሱ ለማምለጥ ከባድ ይሆናል። ለረጅም ጊዜ ከውኃ ሥር ሆነው መቆየት ቢችሉም እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎች በሳምባ የሚተነፍሱ ናቸው። ስለዚህም አፍንጫቸውን ከውኃው በላይ በማውጣት አየር ይስባሉ። ሁሉም አዞዎች እንቁላል ይጥላሉ። እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎችም እንቁላሎቹን መሬት ውስጥ ይቀብራሉ። ሴቶቹ አዞዎች በሚሠሯቸው ጎጆዎች ይለያያሉ። አንዳንዶቹ አሸዋ ውስጥ ቀዳዳ በመቆፈር እንቁላሉን ይቀብሩትና ይሸፍኑታል። ሌሎቹ እንደ አሊጌተር ዓይነቶቹ ብዛት ያለው የበሰበሰ ቅጠላ ቅጠፀል በመሰብሰብ እዛ መሃል እንቁላሉን ይጥሉታል። ብዛት ያላቸው ደርዘን እንቁላሎች (እያንዳንዱ በመጠን ከዶሮ የበለጠ) በአንድ ቁጭታ ሊጥሉ ይችላሉ። ሲፈለፈሉ ታዳጊዎቹ አዞዎች ከ22-25 ሳንቲ ሜትር ቁመት ይኖራቸዋ”ል። አዞዎች ጥርሳቸውን በተደጋጋሚ ይተካሉ። የሚተካው (ያረጀው) ጥርስ ሥር ያለው አዲስ ጥርስ ሲሆን፤ አዲሱ ተኪ ጥርስ አድጎ ትልቅ ካልሆነ በስተቀር አሮጌው ቶሎ ብሎ ወልቆ አይወድቅም። የአዞ አይን 360 ዲግሪ ማየት ይችላል። እንዲሁም ሰው 180 ዲግሪ ዘውሮ ማየት ይችላል። \n \nጥያቄ: አዞዎች በምን ይተነፍሳሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሳምባ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. መሠረቱ። ከምዕራቡ ሮማ መንግሥት ውድቀት ደግሞ ወደ ተረፈው ሕዋእ ውስጥ ከፈለሱት ጀርመናውያን ወገኖች አብዛኛው የራሳቸውን ሕጎች ዝርዝር በጽሑፍ አወጡ። በተለይ የሚታወቁም የቪዚጎቶች አለቃ ዩሪክ ሕግ (463 ዓ.ም.)፣ የቡርጎንዳውያን ሕግጋት (እኚህ ለጀርመናውያንና ለሮማውያን የተለያየ ፍትሕ ነበራቸው)፣ የአላማናውያን ሕግጋትና፣ የፍራንኮች ሕግጋት ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ የተጻፉት ከ492 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በ498 ዓ.ም. የቪዚጎቶች አለቃ 2ኛ አላሪክ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስና አንዳንድ የተለያዩ የቀድሞ ሮማ ሐገጋት አከማችተው አዋጁአቸው። ከዚህም በኋላ የታዩ ሕጎች የሎምባርዶች ሕግጋት (635 ዓ.ም.)፣ የቪዚጎቶች አዳዲስ ሕግጋት (646 ዓ.ም.)፣ የአላማናውያን አዳዲስ ሕግጋት (722 ዓ.ም.) እና የፍሪዝያውያን ሕግጋት (777 ዓ.ም.) አሉ። በአውሮፓ አኅጉር ላይ የተጻፉት እነኚህ ፍትሖች ሁሉ በሮማይስጥ ቢጻፉም፣ በእንግሊዝ አገር ግን የተጠቀሙት ሕጎች ከኬንት ንጉሥ ኤጠልቤርት ሕጎች (594 ዓ.ም.) ጀምሮ በጥንታዊ እንግሊዝኛ የተቀነባበሩ ነበሩ። በ885 ዓ.ም. ታላቁ አልፍሬድ ይህንንና ሁለት የድሮ ፍትሖች ከሕገ ሙሴና ከሕገ ወንጌል ጋራ አጋጥመው የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ዶም ቦክ ሠርተዋል። \n \nጥያቄ: የሎምባርዶች ሕግጋት መች ነበር የታወጀው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 635 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የሙዚቃ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የት ተማሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቶክ ፒሲን ቶክ ፒሲን (Tok Pisin) በስሜን ፓፑዋ ኒው ግኒ የሚናገር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ዲቃላ ነው። ከእንግሊዝኛ ስዋሰው በጣም ተለውጧልና ዛሬ እንደ ራሱ ቋንቋ ይቆጠራል። የፓፑዋ ኒው ግኒ መደበኛ ቋንቋ ሆኖ በ120,000 ያሕል ተናጋሪዎችና በ4 ሚሊዮን እንደ 2ኛ ቋንቋ ይነገራል። የቶክ ፒሲን አጀማመር በፓሲፊክ ውቅያኖስ ደሴቶች ላይ የሚኖሩ የተላያዩም ልሣናት የሚችሉ ሰራተኞች አንድላይ ለአትክልት ስፍራዎች ሲሰሩ ነበር። ብዙ ጊዜ የእነዚህ ሰራተኞች የጋራ ቋንቋ ጥቂት ቀላል እንግሊዝኛ ቃሎች ብቻ ነበር። ስለዚህ አዲስ \"የቋንቋ ዲቃላ\" ተወለደ። ከእንግሊዝኛ ብቻ ሳይሆን ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከደሴተኞቹ ቋንቋዎች፣ ከጀርመንኛ፣ ወይም ከፖርቱጊዝ ነበር። ይህ ቋንቋ \"ፕጅን\" ተብሎ አሁን ሶስት ተወላጆች አሉት፣ እነሱም ቢስላማ (በቫኑዋቱ) ፒጂን (በሰሎሞን ደሴቶች) እና ቶክ ፒሲን ይባላሉ። ቶክ ፒሲን በአንዳንድ ትምህርት ቤት የትምህርት ቋንቋ ነው። \n \nጥያቄ: በስሜን ፓፑዋ ኒው ግኒ የሚነገረው የቶክ ፒሲን ቋንቋ የምን ቋንቋ ድቅል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የእንግሊዝኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: በአሪዞና ሕግ አውጪ አካል 30ዎቹ አባላት ምንድን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሴኔት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ የተለያዩ የቤተሰብ ሕግጋት ያሉ ሲሆን፣ እነዚህ ሕግጋት በሰው ፊት ዋጋ ያለው ግንኙነት የሚፈጠርበትን ጥምረት በተለያየ መንገድ ይደነግጋሉ፡፡ በቤተሰብ ሕግ ዕውቅና የተሰጣቸው የተቃራኒ ፆታዎች ጥምረት ሦስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያውና ዋናው ጋብቻ ሲሆን፣ አሥራ ስምንት ዓመት የሞላቸው ወንድና ሴት ጥንዶች ለዘለቄታው አብረው በትዳር ለመኖር በማሰብ የሚመሠርቱት ተቋም ነው፡፡ ይህ ተቋም በሕገ መንግሥቱ ዕውቅና የተሰጠው ሲሆን፣ ወጣቶች በሕጉ የተቀመጡትን የዕድሜ፣ የፈቃድና የዝምድና ሁኔታዎችን ካከበሩ ሊመሠርቱት የሚችሉት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ጥምረት በክብር በመዝገብ ሹም ፊት፣ በሃይማኖት ሥርዓት ወይም በባህል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ሁለተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው ጥምረት፣ ጋብቻ ሳይፈጸም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ነው፡፡ ጋብቻ ሳይፈጽሙ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድና አንዲት ሴት በሕግ በሚጸና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈጽሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ግንኙነት አለ የሚባለው ሰዎቹ እንደተጋቡ ዓይነት ሰዎች ዓይነት አኗኗር ማሳየታቸው እንደሆነ እንጂ በታወቀና በተደጋገመ ሁኔታ የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት መፈጸማቸው ብቻ አለመሆኑ በሕጉ በግልጽ ተመልክቷል፡፡ ሦስተኛው ሕጉ ዕውቅና የሚሰጠው መተጫጨትን ነው፡፡ መተጫጨት በተወሰኑ የክልል የቤተሰብ ሕግጋት ዕውቅና የተሰጠው እጮኛውና እጮኛይቱ ለወደፊት በመካከላቸው ጋብቻ ለመፈጸም የሚያደርጉት ስምምነት ነው፡፡ መተጫጨት ወደፊት በሚጋቡት ሰዎች ነፃ ፈቃድና ስምምነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፣ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚቆይ ጥምረት ነው፡፡ \n \nጥያቄ: እድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በላይ የሆኑ ሴትና ወንድ የሚመሰርቱት ተቋም ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጋብቻ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nረጅሙ የቦይንግ አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን በስኬት አጠናቋል። ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው ይህ አውሮፕላን ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ርዝመት እንዳለው ተገልጿል። አዲሱ አውሮፕላን በኩባንያው ምርቶች ላይ በሚፈጠሩ እክሎች ምክንያት የሚደርሱ አደጋዎችን ለመቀነስ ያስችላል ነው የተባለው። የአውሮፕላኑ የተሳካ የበረራ ሙከራ ሲያትል ከተማ አካባቢ የተከናወነ ሲሆን፥ ይህ ሙከራ ከመካሄዱ በፊት በአየር ፀባይ ችግር ምክንያት ሊካሄዱ የነበሩ ሁለት የሙከራ በረራዎች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ኩባንያው እስካሁን 309 የሚሆኑ 777 ኤክስ አውሮፕላኖችን የሸጠ ሲሆን፥ የአንዱ ዋጋም 442 ሚሊየን ዶላር ነው ተብሏል። ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዢያ የሆኑ ሁለት አውሮፕላኖች ተከስክሰው የ346 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሚያመርታቸው አውሮፕላኖች ደህንነት አስተማማኝ አይደለም በሚል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና በባለሙያዎች ከፍተኛ ወቀሳ ሲቀርብበት ቆይቷል። ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን   \n \nጥያቄ: ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው አውሮፕላን ምን ያህል ርዝመት እና ስንት ሞተር አለው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: የአሦር መንግስትን ድል አድርጎት ዙሪያው ደ ባቢሎን መንግሥት እንዲተላለፍ ያደረገው የባቢሎን ንጉስ ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ንጉስ ሃሙራቢ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሶቪዬት ሕብረት ሶቭየት ሕብረት ሰብአዊ ሪፐብሊክ በ፲፱፻፲ ዓ.ም. የተከሰተውን የሩሲያ አብዮት ፍንዳታ፤ እንዲሁም ያንን ተከትሎ ለሦስት ዓመታት የተከናወነውን የሩሲያ «ውስጣዊ ሕዝባዊ የርስ በርስ ግጭት» ተከትሎ በኅብረተስብአዊ ሕገ መንግሥት (socialist constitution) በአራት ሪፑብሊኮች ቅንብርነት የተመሠረተ አገር ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ከቀድሞው የናዚ ጀርመን እጅ የተወሰዱ አገሮችን በማቀላቀል እንዲሁም በ፲፱፻፵፱ ዓ.ም በጉልበት ሌሎች የምሥራቅ አውሮፓ አገሮችን በመቀላቀል ኅብረቱ ዓሥራ ስድስት ሪፑብሊኮችን ያካተተ ነበር። በዘመን ቆይታና በጥንካሬም የጎለበተ ሕዝባዊ አብዮታዊ የኅብረት ሪፑብሊክ በመሆኑም በተለይ በ«ቀዝቃዛ ጦርነት» በሚባለው በ«ምዕራብና በምሥራቅ» ዓለም ተከስቶ በነበረው ፍጥጫ ጊዜ፣ በዓለም ላይ ለሚመሠረቱ ሕዝባዊ መንግሥታት ዋና የሽከታ አርአያ የነበረ መንግሥት ነበር። በ ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጀምሮ ይሄ ኅብረት እስከፈረሰበት እስከ ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ድረስ በተካሄደው የ«ቀዝቃዛ ጦርነት» ዘመን የሶቪየት ኅብረት በዓለም ከነበሩት ሁለቱ ተቃራኒ ኃያላን መንግሥታት አንዱ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ላይ በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም የተመሠረተውን የአብዮት ወታደራዊ የደርግ መንግሥት በጦር መሣሪያ፤ በአማካሪነት፤ በገንዘብ፤ ወዘተረፈ፤ ዋነኛ ደጋፊና ታላቅ ተዋናይ አገር ነበር። የቀድሞው የሶቪዬት ኅብረት መጨረሻ ላይ ታኅሣሥ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ተደምስሶ በዓለም መንግሥታት እውቀትና ስምምነት ሕጋዊ ወራሽነት የሩሲያ መንግሥት እንደሆነ ታወጀ። ሩሲያም በዚህ መሠረት የቀድሞውን የሶቪዬት ሕብረት የውጭ ዕዳዎች እንዲሁም የውጭ ንብረቶች በፈቃዱ ተቀበለ። በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ተፈርመው የነበሩም ዓለም አቀፍ ስምምነቶችንም ሩሲያ መቀበሏን አስታውቃለች። \n \nጥያቄ: በ፲፱፻፵፱ የሶቭየት ሕብረት ስንት ሪፐብሊካንን ያካተተ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዓሥራ ስድስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በአረማያ እርሻ ኮሌጅ ለስንት ዓመት ተማሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ለሁለት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአል የተባለ ሰው ሰራሽ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ከሐኪሞች በተሻለ ትክክለኛ መሆኑን አንድ ጥናት አመለከተ። ሰው ሰራሹ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ሁለት ሐኪሞች በጋራ ከሚሰሩት በተሻለ መልኩ ትክክለኛ መሆኑን ባለሙያዎቹ አረጋግጠናል ብለዋል። ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጣው ቡድን አል የተባለው ሰው ሰራሽ መሳሪያን ይዘው በ29 ሺህ ሴቶች ላይ ሙከራ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በዚህም መሳሪያው የጡት ካንሰርን በመለየት ረገድ የስድስት ራዲዮሎጂ ባለሙያዎችን ያክል ውጤታማ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህም ሁለት የዘርፉ ሐኪሞች (ዶክተሮች) ከሚሰሩት ስራ ጋር እኩል ውጤት ያለው ስለመሆኑም በጥናት ውጤታችን አረጋግጠናል ነው ያሉት። ከዚህ ባለፈም መሳሪያው እንደ ሐኪሞቹና ራዲዮሎጂስቶቹ የግለሰቧን የቀደመ የጤና ሁኔታ የሚገልጽ መረጃ ሳይኖረው የጡት ካንሰሩን መለየት መቻሉም የተሻለ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለው አሰራር ሁለት የራዲዮሎጂ ባለሙያዎች ችግሩን ለመለየት የጡት ካንሰር መለያ መሳሪያውን የሚያነቡ ሲሆን፥ ባልተስማሙባቸው ጉዳዮች ላይ ሦስተኛ ሐኪም ተጨምሮ ምስሎቹን እንዲገመግም ይደረጋል። አዲሱ መሳሪያ ራሱን ችሎ ከማንበቡም በላይ ችግሩን ለይቶ በመረዳት በኩል ውጤታማ ስለመሆኑ በባለሙያዎቹ ተመስክሮለታል። መሳሪያው የጡት ካንሰር ምርመራ ውጤት ላይ ከባለሙያዎቹ የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡም ተገልጿል፤ በዚህም ለታካሚዋ የጡት ካንሰር አለብሽ በሚል በባለሙያ የሚነገራትን ሃሰተኛ የምርመራ ውጤት በ1 ነጥብ 2 በመቶ ቀንሷል። ከዚህ ባለፈም በምርመራ ወቅት የጡት ካንሰር የለም በሚል የሚነገር የተሳሳተ ውጤት ደግሞ ከባለሙያ አንጻር መሳሪያው በ2 ነጥብ 7 በመቶ መቀነሱን ባለሙያዎቹ ገልጸዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አል የተባለው የጡት ካንሰር መመርመሪያ ከባለሙያ አንጻር ያለውን ስህተት በምን ያህል ቀነሰ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ2 ነጥብ 7 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nከአፍሪካ ህዝብ ውስጥ 24 በመቶ ብቻ የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆናቸውን ዓለም ባንክ አስታወቀ፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት አለመስፋፋት በአህጉሪቱ አዳዲስ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ የስራ ዕድል ፈጠራዎችን ለማስፋፋት አዳጋች እንደሚሆን ነው ባንኩ የገለጸው፡፡ በአፍሪካ እኤአ ከ2015 እስከ 2035 ባለው ጊዜ ውስጥ 450 ሚሊዮን ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የዓለም ባንክና የአፍሪካ ልማት ባንክ በጥምረት ያወጡት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ እንደ ኢኮሜርስ እና ፋይናንስ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የስራ ዘርፎችን በአፍሪካ በማስፋፋት ከፍተኛ የስራ እድልን መፍጠር እንደሚቻል ተጠቅሷል፡፡ በዚህም፣ ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በቂ እውቀት እንዲኖራቸው በማድረግ ማሰማራት እንደሚገባ ተነግሯል፡፡ \n \nጥያቄ: በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ስንት በመቶ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች አሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 24 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ የቬንዳ ቋንቋ በተናጋሪ ብዛት ስንተኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 10ኛው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ በ1942 ዓ/ም የት ተቀጠሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንጉሠ ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ በስንት ዓመት ምሕረት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ ምን ያህል ጊዜ በእስር ቆይተዋል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 20 አመታት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: የአሪዞና ሕግ አስፈጻሚ ዘርፍ አስተዳዳሪነት ከስንት ጊዜ በላይ በተከታታይ መመረጥን ይከለከላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከሁለት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ወላጅ አባቱ ሚካኤል ሲባልየ እናቱ ስሟ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዩጂኒያ ብሪን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: ወንዱ ቀጭኔ ርዝማኔው ምን ያህል ይሆናል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበቶኪዮ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ በመሳተፍ በ58 ኪ.ግ ምድብ 7ኛ በመያዝ ዲፕሎማ አግኝታለች፡፡ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ የወከለው አትሌት ሰለሞን ቱፋ እየተካሄደ ባለው የቶኪዮ ኦሎምፒክ በ58 ኪ .ግ ምድብ ባደረገው ውድድር 7ኛ ደረጃ በመያዝ ዲፕሎማ መገኘቱን ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በቶኪዮ ኦሎምፒክ በወርልድ ቴኳንዶ በ58 ኪ.ግ ኢትዮጵያን ወክሎ የተሳተፈው አትሌት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አትሌት ሰለሞን ቱፋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: የአብርሃም ሊንከን አባት ስራቸውስ ምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ገበሬ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት የተጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1956 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ የትኞቱ የግሩፕ አባላት ሀገር ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኒሺ ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ (ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900) ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ሲሆን አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። እርግጥ ኒሺ፣ በነበረበትም ሆነ በኋላ ዘመኑ ብዙ ተቃዋሚወች ቢነሱበትም በዚያው ልክ ብዙ ሰወች ስራወቹን እንደ ታላቅ የፍልስፍና እና ስነ ጽሁፍ ስራ ይወስዷቸዋል። ኒትሸ አብዛኛው ጽሁፉ የሚያተኩረው ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ምክንያት እሱ ይኖርበት የነበረውን ዘመን የጀርመን ሥነ ምግባር (ኤቲክስ) በመንቀፍ ብዙ ጽፎአል። ሠናይ እና እኩይ (ጥሩና መጥፎ) ተብለው ተለይተው ይሰራባቸው የነበሩትን የጊዜውን ሥነ ምግባር ዋጋወች በመተቸት ሰወች አዲስ ሥነ ምግባር ፈጥረው ለሁሉም ምግባር አዲስ የሠናይነትና እኩይነት (ጥሩ እና መጥፎ) ዋጋ እንዲሰጡ በጽሑፎቹ ብዙ ሞክሯል።በዚህ መሰረት፣ ለምሳሌ፣ በክርስቲያኖች ዘንድ የሚሰራበትን ለደካሞች ማዘንን ሠናይነት ተቃውሟል። በሱ አስተያየት ደካሞች ሲታዘንላቸው የበለጠ ይዳከማሉ የሚል ነው ምክንያቱም በሱ አስተያየት ደካሞቹ በጠንካሮቹ ላይ የበለጠ ጥገኛ በመሆን መላው ህብረተሰብ ይዳከማል የሚል ነው። በተጨማሪም፣ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ተጨባጩን አለም መገንዘብ እና ክሁሉ በላይ ስለዚሁ ዓለም ማተኮር አለበት ብሏል። ሰማይና ሌሎች አለማትን በማጣጣል፣ የሰው ልጅ እነዚህን አይነት አለሞች የሚፈጥረው አሁን ያለበትን ተጨባጩ የውኑ አለም ችግሮች መፍታት ሲያቅተው ለመፈርጠጥ ነው በማለት የሰው ልጅ ስለዚህ ምድር ብቻ እንዲያስብ ይወተውታል። ኒሽ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል አጥብቆ ያምናል። በኒሺ ፍልስፍና፣ አንድ እራሱን ያሽነፈ ሰው በጣም የተለወጠ እና የተሻለ ስለሚሆን \"ሱፐር ማን\" ወይም \"የበላይ ሰው\" እንዲባል ሰይሟል። የበላይ ሰው እንግዴህ ጠንካራና በሌሎች ሰወች \"ሠናይ\" እና \"እኩይ\" ወይም ደግሞ \"ጥሩ\" ና \"መጥፎ\" ዋጋወች የማይመራ፣ ይልቁኑ የራሱን ሥነ ምግባር የሚፈጥር ነው። \n \nጥያቄ: የኒትሽ ጹሁፎች በምን ዙርያ ያተኩራሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና የትውልድ ቦታዋ ት ሀገር ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጋና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአል የተባለ ሰው ሰራሽ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ከሐኪሞች በተሻለ ትክክለኛ መሆኑን አንድ ጥናት አመለከተ። ሰው ሰራሹ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ሁለት ሐኪሞች በጋራ ከሚሰሩት በተሻለ መልኩ ትክክለኛ መሆኑን ባለሙያዎቹ አረጋግጠናል ብለዋል። ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጣው ቡድን አል የተባለው ሰው ሰራሽ መሳሪያን ይዘው በ29 ሺህ ሴቶች ላይ ሙከራ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በዚህም መሳሪያው የጡት ካንሰርን በመለየት ረገድ የስድስት ራዲዮሎጂ ባለሙያዎችን ያክል ውጤታማ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህም ሁለት የዘርፉ ሐኪሞች (ዶክተሮች) ከሚሰሩት ስራ ጋር እኩል ውጤት ያለው ስለመሆኑም በጥናት ውጤታችን አረጋግጠናል ነው ያሉት። ከዚህ ባለፈም መሳሪያው እንደ ሐኪሞቹና ራዲዮሎጂስቶቹ የግለሰቧን የቀደመ የጤና ሁኔታ የሚገልጽ መረጃ ሳይኖረው የጡት ካንሰሩን መለየት መቻሉም የተሻለ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለው አሰራር ሁለት የራዲዮሎጂ ባለሙያዎች ችግሩን ለመለየት የጡት ካንሰር መለያ መሳሪያውን የሚያነቡ ሲሆን፥ ባልተስማሙባቸው ጉዳዮች ላይ ሦስተኛ ሐኪም ተጨምሮ ምስሎቹን እንዲገመግም ይደረጋል። አዲሱ መሳሪያ ራሱን ችሎ ከማንበቡም በላይ ችግሩን ለይቶ በመረዳት በኩል ውጤታማ ስለመሆኑ በባለሙያዎቹ ተመስክሮለታል። መሳሪያው የጡት ካንሰር ምርመራ ውጤት ላይ ከባለሙያዎቹ የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡም ተገልጿል፤ በዚህም ለታካሚዋ የጡት ካንሰር አለብሽ በሚል በባለሙያ የሚነገራትን ሃሰተኛ የምርመራ ውጤት በ1 ነጥብ 2 በመቶ ቀንሷል። ከዚህ ባለፈም በምርመራ ወቅት የጡት ካንሰር የለም በሚል የሚነገር የተሳሳተ ውጤት ደግሞ ከባለሙያ አንጻር መሳሪያው በ2 ነጥብ 7 በመቶ መቀነሱን ባለሙያዎቹ ገልጸዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አል የተባለው የጡት ካንሰር መመርመሪያ ከምርመራ ውጤት አንጻር ያለውን ስህተት በምን ያህል ቀነሰ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1 ነጥብ 2 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የተገነባው በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሩሲያኖች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: ጋና በየት አህጉር የሚገኝ ሀገር ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበዚህ በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. ላይ የቱርክ፣ የመስኮብ፤ የጀርመን፤ የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይና የኤስፓኝ መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት መቆጠራቸው አልቀረም። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ የፖርቱጋል መንግሥት በሌላው እንኳን ባይሆን በመርከብና አገር በመያዝ ከቀሩት ይበልጥ ነበር። የቀሩት የኤውሮፓ መንግሥታት እዚያው ወሰናቸው ላይ ገዥነታቸውን ለማጽደቅ እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ የፖርቱጋል መንግሥት ግን ደኅና ደኅና መርከቦችን አዘጋጅቶ እየላከ ከመንግሥቱና ከኤውሮፓ ርቆ የሚገኘውን የአሜሪካን፤ የእስያን፤ የአፍሪካን አገሮች ያስመረምር ነበር። መርማሪዎቹም እነቫስኮ ደጋማ፤ እነፔሬዝ፤ እነአንድራድ፤ እነካብራል በመርከብ እየሄዱ ለመከላከል ጉልበት የሌለውንና በጠባዩ ሀብት ያለበትን አገር መርምረው ሲመለሱ መንግሥቱ ወታደር በመርከብ እየላከ ብዙ አገር ያዘ። በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ. ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል የተባለው የፖርቱጋል መኮንን በትልቅ መርከብ ሄዶ ይን ጊዜ ለቀረው ዓለም ያልታወቀውን የብራዚልን አገር አስገበረና በፖርቱጋል መንግሥት ስም ቅኝ አገር አደረገው። ከዚያም አገር በተገኘው ወርቅ መንግሥቱ ሀብታም ሆነ። እንደዚሁም የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ ወደ ህንድ አገር ሄዶ አገሩን ያዘ። ከተማውንም በጎአ አድርጎ ህንድንም የፖርቱጋል የቄሣር ግዛት አደረገና አገር ገዥውም የንጉሥ እንደራሴ ይባል ጀመር። ከዚያም በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን የሚባለውን አገር በየጊዜው በጦር ኃይል አስገበራቸው። በዚሁ አኳኋን ወደ ኢትዮጵያም እነኮቪልሐኦ ቀደም ብለው በዓፄ እስክንድር ዘመን መጥተው እንደመረመሩትና የኢትዮጵያ መንግሥት በዚያ ጊዜ በነሱ አጠራር የቄሱ የዮሐንስ መንግሥት አለ ብለው አውርተው እንደነበረ ሌላ የፖርቱጋል የጦር መርከብ በአፍሪካ ድንበር በቀይ ባሕር ላይም እየተመላለሰ አስቀድሞ ከያዙት ከቱርኮችና ከግብጾች እየተዋጋ አንድ ጊዜም እየተሸነፈ አንድ ጊዜም እያሸነፈ ብዙ ጊዜ ተመላለሰ። በዚህ ሁሉ ምክንያት የፖርቱጋል መንግሥት ታላቅነት በሌላው ዓለም እንደ ታወቀ እንደዚሁም ፩ኛ ትልቅ መንግሥት መሆኑ ፪ኛ ክርስቲያን መሆኑ ኢትዮጵያ ባሉት የውጭ አገር ሰዎች አፍ እየተነገረ ዝናው በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ዘንድ መሰማት ቻለ። \n \nጥያቄ: በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ሁሉም የዚምባቡዌ ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን የተፈራረሙት መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1979 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nስታምፎርድ ብሪጅ (የእግር ኳስ ሜዳ) ስታምፎርድ ብሪጅ በፉልሃም ለንደን የሚገኝ የቼልሲ እግር ኳስ ቡድን የእግር ኳስ ሜዳ ነው። የእግር ኳስ ሜዳው የሚገኘው በሙር ፓርክ ኢስቴት (በሌላ አጠራር በዋልሃም ግሪን) ወይም በተለምዶ ዘ ብሪጅ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ነው። ይህ የእግር ኳስ ሜዳ 41,798 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ ከፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ትልቅ የእግር ኳስ ሜዳ ያደርገዋል። የተከፈተው እ.ኤ.አ በ1877 ሲሆን እስከ 1905 ድረስ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ይጠቀምበት ነበር። ሜዳው ብዙ ለውጦችን አካሂዷል። በቅርቡ ደግሞ (እ.ኤ.አ 1990ዎቹ) ወደ ዘመናዊና ለሁሉም ተመልካቾች መቀመጫ ያለው ሆኖ ተሠርቷል። ስታምፎርድ ብሪጅ የተለያዩ የእንግሊዝ ዓለም አቀፋዊ ጨዋታዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ግማሽ ፍጻሜዎችን እና የቻሪቲ ፊልድ ጨዋታዎችን አስተናግዷል። ለተለያዩ ስፖርቶችም እንደ ክሪኬት ፣ ራግቢ ዩኒየን ፣ ስፒድዌይ ፣ ግሬይሃውንድ ሬሲንግ ፣ ቤዝቦል እና የአሜሪካን ፉትቦል ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ጥቅም ላይ ውሏል። የስታዲየሙ ትልቁ ኦፊሲዬላዊ የታዳሚዎች ቁጥር 82,905 ሲሆን ፤ ይህ የሆነው ቼልሲ ከአርሰናል እ.ኤ.አ በኦክቶበር 12 1935 ባካሄዱት የሊግ ጨዋታ ነበር። ስታምፎርድ ብሪጅ ፤ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ስታዲየም ሆኖ እ.ኤ.አ በ1877 ተከፈተ። በዚያ ሜዳ ላይ ታላላቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት የፈለጉ ገስ እና ጆሴፍ ሚየርስ የተባሉ ወንድማማቾች ኮንትራቱን እስካገኙበት ጊዜ ድረስ ለለንደን አትሌቲክስ ክለብ እስከ እ.ኤ.አ 1904 ድረስ አገልግሏል። \n \nጥያቄ: ስታምፎርድ ብሪጅ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ስታድየም ሆኖ መች ተመሰረተ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እ.ኤ.አ በ1877 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከ39 ዓመታት በኋላ ስንተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ተሳተፈ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 29ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን በማንሳት ላይ ያሉት ድርጅቶች ማን እና ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኢንስታግራም እና ፌስቡክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፀሐይ ፀሓይ በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። \n \nጥያቄ: በስርዓተ-ፈለክ ውሥጥ ያሉ አካላት የብርሃን ምንጫቸው ማናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፀሓይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል በየትኛው አህጉር ውስጥ የምትገኘው ሀገር ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም መቼ ገባች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1971 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nድረ ገጽ መረብ የድረ ገጽ መረብ (ወይም ኢንተርኔት) በጣም ብዙ የኮምፒዩተር አውታሮችን የያዘ የመገናኛ መረብ ነው። በመረቡ ውስጥ ብዙ ድረ ገጽ ይገኛሉ። ከዚያ በላይ በርካታ የመነጋገርና መገናኘት መንገዶች አሉ። ከሁሉ አስቀድሞ የተፈጠረ ክፍለ-ኢንተርኔት «USENET» የሚባለው አገልግሎት ነው። ይህ በ1973 ዓ.ም. (1980 እ.ኤ.አ.) አካባቢ ሲጀመር በተለይ ለዩኒቨርሲቴዎችና ኮሌጆች ብቻ የታወቀ መገናኛ ሆኖ ቆየ። ይህ ጽሑፍ በተገናኙት ኮምፒውተሮች ላይ መልጠፍ የሚፈቅድ ሥርዓት ብቻ እንጂ ስዕል ወይም ሌላ ነገር አልነበረም። መጀመርያው e-mail አድራሳዎች የተሰጡት ከዚያ ዘመን ነው። ዛሬም ብዙዎች ተጠቃሚዎቹ ግን ስንኳ ስለ USENET መኖሩን አያውቁም። መጀመርያው ድረ ገጽ የተፈጠረው በ1983 ዓ.ም. (1990 እ.ኤ.አ.) ሆነ። \n \nጥያቄ: ክፍለ ኢንተርኔት መቼ ነው የተጀመረው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1973 ዓ.ም. (1980 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአልፍሬድ ኢልግ ከሠራቸው አንዱ አዋሽ ወንዝ ላይ ያቆመው ድልድይ ነው። ስለዚህ ድልድይ ሥራ ኢልግ ሲጽፍ፤ የመጀመሪያው የድልድይ ሥራ እንደነበረና የድልድዩ ቋሚዎች በሰው ሸክም አሥራ አምስት ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንደመጡ ይተርክና ሥራውን በሐሩር እና በዶፍ እንዲሁም በማታ የዱር አራዊትን በመቋቋም እራሱ ድንጋይ እየጠረበ፣ ምስማር፣ ችንካር እና ብሎን እያቀለጠ እየቀጠቀጠ እንደሠራው ይነግረናል። ምኒልክ በሸዋ ንጉሥ ከሆኑ በኋላ ሐዲድ አዘርግተው ባቡር ለማስገባት አሰቡ። ይህም ሀሳባቸው እንዲፈቀድላቸው የበላያቸውን ንጉሠ ነገሥቱን አጤ ዮሐንስን ፈቃድ ጠየቁ። በአጤ ዮሐንስ አካባቢ የነበሩ መኳንንቶች መክረው ምኒልክ ከግዛታቸው ከሸዋ ውጭ ሐዲድ ለመዘርጋት እንደማይችሉ ተነገራቸው። በሳቸው መቸኮልና መጓጓት ምክንያት አልፍሬድ ኢልግ በሥራና በሀሳብ ተጠምዶ እንደነበር ወዲያውም ለጃንሆይ ምኒልክ የሞዴል ባቡር ተጎታች ጋሪዎችን እየጎተተ በሐዲድ ላይ ሲሄድ የሚያሳይ ሠርቶ ሲያሳያቸው በጣም እንደተደሰቱ ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፋቸው ዘግበዋል። ከዓፄ ዮሐንስ ሞት በኋላ ምኒልክ የንጉሠ ነግሥትነትን ዘውድ በጥቅምት ወር ጭነው ወዲያው በኅዳር ወር ላይ የምድር ባቡርን ሥራ አንቀሳቅሰዋል። ለዚህም ኢልግ ከማንኛውም ኩባንያ ጋር ተዋውሎ ሐዲዱን ለማሠራት የሚችልበትን ፈቃድና የሚዋዋልበትን የውል ዓይነት መጋቢት ፩ ቀን ፲፰፻፹፮ ዓ/ም አስጽፈው በማህተማቸው አትመው ሰጡት። ኢልግም ፓሪስ ከተማ ላይ ቢሮ ከፍቶ ለሥራው የሚያስፈልገውን መዋእለ ነዋይ፤ ሥራውን የሚኮናተሩ ድርጅቶችን እና ሌላም ጥናቶችን ማቀናበር ጀመረ። የዚህ የምድር ባቡር መሥመር ከጂቡቲ ወደብ ተነስቶ አዲስ አበባ ድረስ ፯፻፹፬ ኪሎ ሜትር ሲሆን ሥራው በ፲፰፻፺ ዓ/ም ተጀምሮ ከሀያ ዓመታት በኋላ በ ፲፱፱፻፲ ዓ/ም ተገባደደ። መቸም የኃሳቡ ጸንሳሽ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክም ሆኑ ሕልማቸውን ዕውን በማድረግ ብዙ አስተዋጽዖ ያስመዘገበው ኢልግም ፍጻሜውን ባያዩትም በኢትዮጵያ የምድር ባቡርን ስናስብ የነዚህ የሁለቱ ሰዎች ትዝታ በታሪክ ተመዝግቦ ይኖራል። \n \nጥያቄ: የምድር ባቡር መስመር ዝርጋት መቸተ ተጠናቀቀ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ ፲፱፱፻፲ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ተንኮል በገቡ ከብቶች ምክንያት ተዛምቶ በሀገራችን ብዙ ከብቶችን የፈጀው በሽታ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የደስታ በሽታ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: የላይቤሪያ ዋና ከተማ ስያሜዋን ያገኘችወ በየትኛው የአሜሪካን ፕሬዝደንት ስም ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጄምስ ሞንሮው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: በአራቱም ወንጌላውያን ዘመን ኅዳር 15 የሚጀምረው ጾም ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጾመ ነቢያት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሃሙራቢ ሃሙራቢ (አካድኛ፤ ከአሞርኛ አሙራፒ) ከ1705 እስከ 1662 ዓክልበ. ድረስ ('ኡልትራ አጭር አቆጣጠር') የባቢሎን ንጉሥ ነበረ። አባቱ ሲን-ሙባሊት ማዕረጉን ከተወ በኋላ ወራሹ ሃሙራቢ የባቢሎንን መንግሥት ግዛት በሜስፖጦምያ በጦርነት አስፋፋ። ሃሙራቢ በተለይ የሃሙራቢ ሕገ ፍትሕ ስለሚባለው የ1704 ዓክልበ. ሕገ ፍትሕ ይታወቃል። ሕግጋቱ የተቀረጹ ቁመቱ 2.4 ሜትር በሆነ ድንጋይ ሲሆን በ1893 ዓ.ም. ለሥነ ቅርስ ተገኝቷል። ሃሙራቢ እንደ ሕግ-ሰጪ ንጉሥ ዝነኛ ስለሚሆን፣ ምስሉ በአሜሪካ መንግስት ቤቶች ዛሬው ሊታይ ይችላል። ዋሺንግተን ዲሲ በአሜሪካ ምክር ቤት ውስጥ በእብነ በረድ ተቀርጸው ከ23 ታሪካዊ ሕግ-ሰጪዎች ምስሎች መካከል የሃሙራቢ ምስል አንዱ ነው። በአሜሪካ ላይኛ ችሎት ቤት ውስጥ በደቡብ ግድግዳ ላይ ሃሙራቢ ከታሪካዊ ሕግ-ሰጪዎች ጋራ የሚያሳይ ትርዒት አለ። \n \nጥያቄ: የሃሙራቢ አባት ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሲን-ሙባሊት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ አየር መንገድ መቼ ተመሰረተ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nከ2009 ዓ.ም ህዳር ወር ጀምሮ ሲዘጋጅ የነበረው አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡ ዝርዝር እቅዱን ለመተግበር ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡ ገንዘቡ በኢትዮጵያ መንግስትና በአጋር ድርጅቶች እንደሚሸፈንም ተነግሯል፡፡ አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ የሚቆይ ነው ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: የአገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ እቅዱ ከመቼ ጀምሮ ተዘጋጀ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ2009 ዓ.ም ህዳር ወር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር። ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች ኮሞዲቲ ገንዘብ መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ ከብትና እህል (ገብስ) መደበኛ ነበሩ። በተለይ ዛጎል በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። መዳብ፣ ብረት፣ ብርና ወርቅ በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረታብረት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ። በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ የፈተና ደንጊያ ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሳንቲም እና የብር ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ልድያውያን ነበር።. በኢትዮጵያም በአክሱም ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል። ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው ተወካይ ገንዘብ የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። ሆኖም ስዊድን የወረቀት ብር ያወጣው ምክንያት ጦርነት ለማድረግ ፈልጎ በቂ ወርቅ ወይም ሌላ ገንዘብ በአገሩ ስላልነበረው ነው። አሁን ወዲያው የስዊድን መንግሥት ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ሥራተኖች መክፈል ቻለ። በጥቂት ዓመት ውስት የስዎድን ወረቀት ገንዘብ ወደቀ። ነገር ግን ከትንሽ በኋላ የእንግላንድ መንግሥት በፈረንሣይ ላይ በጦርነት ተይዞ ለጦርነትም ያህል በቂ ሀብት ባለመኖሩ እንዲህ አይነት መፍትሄ መረጡ፤ የኢንግላንድ ፓውንድ ድፍን ጀመሩ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አገራት ፈቃዳቸውን ለመፈጽም አዲስ የወርቅ ወይም የብር ማዕድን ማግነት አስፈላጊ አልነበረም። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ይህ በወርቅ የተደገፈ የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በይፋ በመላው ዓለም ተንሰራፋ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብሬቶን ውድስ ስብሰባ፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች ፊያት ገንዘብን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር። በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታት እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ የብር እና የወርቅ ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ልድያውያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል የት አካባቢ ነው የእብነ በረድ ክምችት እንዳለ በጥናት የተለየው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በዓባይ ሸለቆ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1923 ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደጃፓን የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ የላከች መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር በኢትዮያ በየትኛው አቅጣጫ የምትገኝ ከተማ ናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሰሜን-ምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: አሌክሳንድርያ ከተማ በነዋሪ ቁጥር ከግብጽ ከተሞች ስንተኛዋ ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሁለተኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔዎች በቀን ምን ያህል ኪሎ ግራም ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እስከ 34 ኪሎ ግራም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ ሁለተኛ ቋንቋቸው የሆኑ ምን ያህል ሕዝቦች አሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት በብቸኛነት የሚያጠቃት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አንበሳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መቼ ተመረቀች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1974 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: ሜሪላንድ በየትኛው ውቅያኖስ ትዋሰናለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በአትላንቲክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ መቼ ዘውዳቸውን ጫኑ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1436 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በአይቮሪኮሰስት ከ2018 በኋላ ባሉት ተከታታይ ሁለት ዓመታት በተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች ምን ያህል ክፍሎች ለመስራት ታቅዷል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 528 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: አሌክሳንድርያ ከግብጽ ከተሞች በዋናነት የምትታወቅበት ነገር ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የአገሪቱ ዋና ወደብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም ወቅት አሜሪካን ይመሩ የነበሩት የአሜሪካ መሪ ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቅዱስ ላሊበላ ቅዱስ ላሊበላ በ 1101 አ.ም ትህሳስ 29 ቀን ከ እናቱ ከኬርዮርና ከአባቱ ዛንስዮም ላሰታ ቡግና ወረዳ ሮሃ ከተባለች ቦታ ከፍልፍል ቤተ መቅደስ ውስጥ ተወለደ በዚህ ፍልፍል ቤተ-መቅደስ ውስጥ እድገቱን አደረገ ስድስት አመት ሲሞላው ቤተ-መንግስት አባ ዳንእል የተባሉ መምህር ተቀጥረውለት ከ ፊደል እስከ ዳዊት አጠናቆ ከዚያም የተማረውን የዕሁፍ ጥበብ በቤተ ጎሎጎታ ደብረ ሲና በሚገኘው ከ ኪዳነ ምህረት መንበር ታቦት ዙሪያ ላይ እራሱ የተዓፋቸው የሚዐለይበት ዕሁፎቸች ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ 12 አመት ሲሞላው አባቱ ዘንሳዮም 40 አመት ነግሶ በተወለደ በ 76 አመቱ ከዚህ አለም በ ሞት ተለየ ወድያው ብዙም ሳይቖይ እናቱ ኬርዮርና በሞት ተለየች፡፡ ቅዱስ ላሊበላ በ እናቱ ና አባቱ ህልፈተ ህይወተ በደረሰበት ሀዘን የተነሳ ሁሉን ነገር ለመርሳት ና የትምህርት ፍላጎት ለሞሞላት ጉዞውን ወደ ጎጃም በማድረገ አለም ስላሴ ከተባለው ደብር ከመምህር ኬፋ ሃዲሳቱን አጠናቖ በመመረቅ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በወቅቱም በኤትዮጵያ ላይ ነግሶ የነበረው ታላቅ ወንድሙ ቅዱሰ ገብረ ማሪያም ነበር ይህ እንዲህ እያለ በእህቱ ላይ እሱ ሊነግስ መሆኑ ቅናት አሳደረባት ቅዱስ ላሊበላ ሁሌም እሚጠጣው ባህላዊ መድሃኒት ውስጥ መርዝ በመጨመር ታስቀምጥለታለች አትሙት ያላት ነፍስ ግን የሃገሬውን በሃል ምክንያት አድርጎ ሳይቀመስ አይሰጥምና አብሮት የነበረው ዲያቖን የተቀመጠውን መድሃኒት ቀምሶ ወደ ነበረበት ጠረቤዛ ላይ አንዳሰቀመጠው ወድያውኑ ህይወቱ ታልፋለች ቅዱስ ላሊበላ ይህን ባየ ጊዚ እኔን ለማጥፋት የመጣው መድሃኒት የሌላውን ነፍስ አጠፋች በማለት የቀረውን መድሃኒት በመጠጣት ለሶሰት ለሊት እንደ ወደቀ ቀረ ከዚያም ነዋሪው ገንዞ ለመቅበር ሲዘጋጁ የሰውነቱ ሙቀት አልተለየውም ነበር ይሄን ጊዜ ወድያው ቅዱስ ላሊበላ ነቃ የተመለከቱት ሰዎች ተደናገጡ ከዚያም ይህ ሁሉ ነገር በእህቱ መደረጉ ያሳዘነው ቅዱስ ላሊበላ በመነሳት ጉዞውን ወደ ጫካ አደረገ ኑሮውንም ለረጅም አመት እዚያው አደረገ ይህ እንዲ እንዳለ ሚስት እምትሆነውን ሴት አገኝ ቤተሰቧን በማስጠየቅ በቤተክርስትያን ስርአት ተጋብተው ጥቂት አመት እንደቆዩ ጉዞውን እየሩሳሌም አደረገ ለተከታታይ 13 አመታትም ቆይታ በኋላ ወደ ባለቤቱ ተመልሶ ከወንድሙ ከ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ጋር እርቅ በማውረድ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ንግስናውን ለቅዱስ ላሊበላ በተወለደ በ57 አመቱ በማስረከብ ኑሮውን በገዳም አደረገ፡፡ \n \nጥያቄ: ቅዱስ ላሊበላ መቼ ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ 1101 አ.ም ትህሳስ 29 ቀን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየቅርጫት ኳስ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬትቦል በዓለም ዙሪያ በቡድኖች የሚጫወት የኳስ እስፖርት ነው። ጨወታው በ1885 ዓም በካናዳዊው ዶ/ር ጄምስ ነይስሚስ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ። በመላው አለም ተወዳጅነትን ያተረፈ የቡድን ስፖርት አይነት ነው፡፡ ጨዋታው እኤአ በ1891 በካናዳዊው ዶ.ር ጀምስ ኒስሚዝ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ፡፡ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬት ቦል፡፡ ጨዋታው በእጅ የሚከናወን ሲሆን በመሰረታዊነት የ4 መአዘን ሬክታንግል ቅርፅ ያለው መጫወቻ ኮርት 5 ተጫዋቾ ያሉት ሁለት ቡድኖች እና በእጅ የሚወረወረው ድቡልቡል ኳስ ለጨዋታው አስፈላጊ የሆኑ ቁሶች ናቸው፡፡ 5ቱ ተጫዋቾ ሁልጊዜም የተጫዋቾችን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ከተጫዋቾቹ በቁመት ረጅም የሆነው ተጫዋች አብዛኛውን ጊዜ የመሀል ቦታ ይይዛል፡፡ እኤአ በ1891 በካናዳዊው የጂም መምህር ጀምስ ኒስሚዝ በስፕንግ ፊልድ ማሳቹስትስ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የተፈጠረው የቅርጫት ኳስ በአሁኑ ሰአት በአለማችን ላይ እጅግ ታዋቂና በመላው አለም በርካታ ተመልካቾች ያሉት የስፖርት አይነት ነው፡፡ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን ለአለም ፕፌሽናል ባስኬት ቦል በማሳደግና በማስተዋወቅ በክፍያ በተሰጥኦና በውድድር ብቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶለታል፡፡ ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ያሉ የብሄራዊ ሊግ መስፈርትን ያሟሉ ታላላቅ ክለቦች ለአህጉራዊ ቻምፒየን ሺፕ እንደ ኢሮሊግ እና FIBA አሜሪካ ሊግ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን አስተዋፅኦ ማሳያ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ የFIBA ባስኬት ቦል ወርልድ ካፕ እና men’s Olympic basketball ውድድር ዋና ዋና የአለማቀፍ ዝግጅቶችን እና የብሄራዊ ቡድኑ በርካታ ተጫዋቾችን መሳብ የቻሉ ውድድሮች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የቅርጫት ኳስ ጨዋታ ማን ፈጠረው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዶ/ር ጄምስ ነይስሚስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየዲጂታል ኢኮኖሚውን የሚያጠናክር ሬድፎክስ የተሰኘ የመረጃ ቋት ማዕከል ይፋ ሆነ፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ መረጃ አዲሱ ነዳጅ መሆኑን ገልጸው፣ የዲጂታል መሰረተ ልማቱ መጠናከር በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና በሌሎች መስኮች ላይ አስተዋጽኦን ያሳርፋል ብለዋል፡፡ ሬድፎክስ ለረጅም ዓመታት በቴሌኮም ዘርፍና በመረጃ ቴክኖሎጂ ልምድ ባካበቱ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች የተቋቋመ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ሚኒስትር ዲኤታው ዳያስፖራዎቸ በዘርፉ ላይ በመሰማራታቸው ያላቸውን አድናቆት መግለጻቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታው ማን ይባላሉ ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዶክተር እዮብ ተካልኝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: ሀምሌ 16/1961 አፓሎ 11 ከመሬት ሲመነጠቅ በውስጡ የያዛቸው ጠፈርተኞችን እነማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቅዱስ ላሊበላ ቅዱስ ላሊበላ በ 1101 አ.ም ትህሳስ 29 ቀን ከ እናቱ ከኬርዮርና ከአባቱ ዛንስዮም ላሰታ ቡግና ወረዳ ሮሃ ከተባለች ቦታ ከፍልፍል ቤተ መቅደስ ውስጥ ተወለደ በዚህ ፍልፍል ቤተ-መቅደስ ውስጥ እድገቱን አደረገ ስድስት አመት ሲሞላው ቤተ-መንግስት አባ ዳንእል የተባሉ መምህር ተቀጥረውለት ከ ፊደል እስከ ዳዊት አጠናቆ ከዚያም የተማረውን የዕሁፍ ጥበብ በቤተ ጎሎጎታ ደብረ ሲና በሚገኘው ከ ኪዳነ ምህረት መንበር ታቦት ዙሪያ ላይ እራሱ የተዓፋቸው የሚዐለይበት ዕሁፎቸች ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ 12 አመት ሲሞላው አባቱ ዘንሳዮም 40 አመት ነግሶ በተወለደ በ 76 አመቱ ከዚህ አለም በ ሞት ተለየ ወድያው ብዙም ሳይቖይ እናቱ ኬርዮርና በሞት ተለየች፡፡ ቅዱስ ላሊበላ በ እናቱ ና አባቱ ህልፈተ ህይወተ በደረሰበት ሀዘን የተነሳ ሁሉን ነገር ለመርሳት ና የትምህርት ፍላጎት ለሞሞላት ጉዞውን ወደ ጎጃም በማድረገ አለም ስላሴ ከተባለው ደብር ከመምህር ኬፋ ሃዲሳቱን አጠናቖ በመመረቅ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በወቅቱም በኤትዮጵያ ላይ ነግሶ የነበረው ታላቅ ወንድሙ ቅዱሰ ገብረ ማሪያም ነበር ይህ እንዲህ እያለ በእህቱ ላይ እሱ ሊነግስ መሆኑ ቅናት አሳደረባት ቅዱስ ላሊበላ ሁሌም እሚጠጣው ባህላዊ መድሃኒት ውስጥ መርዝ በመጨመር ታስቀምጥለታለች አትሙት ያላት ነፍስ ግን የሃገሬውን በሃል ምክንያት አድርጎ ሳይቀመስ አይሰጥምና አብሮት የነበረው ዲያቖን የተቀመጠውን መድሃኒት ቀምሶ ወደ ነበረበት ጠረቤዛ ላይ አንዳሰቀመጠው ወድያውኑ ህይወቱ ታልፋለች ቅዱስ ላሊበላ ይህን ባየ ጊዚ እኔን ለማጥፋት የመጣው መድሃኒት የሌላውን ነፍስ አጠፋች በማለት የቀረውን መድሃኒት በመጠጣት ለሶሰት ለሊት እንደ ወደቀ ቀረ ከዚያም ነዋሪው ገንዞ ለመቅበር ሲዘጋጁ የሰውነቱ ሙቀት አልተለየውም ነበር ይሄን ጊዜ ወድያው ቅዱስ ላሊበላ ነቃ የተመለከቱት ሰዎች ተደናገጡ ከዚያም ይህ ሁሉ ነገር በእህቱ መደረጉ ያሳዘነው ቅዱስ ላሊበላ በመነሳት ጉዞውን ወደ ጫካ አደረገ ኑሮውንም ለረጅም አመት እዚያው አደረገ ይህ እንዲ እንዳለ ሚስት እምትሆነውን ሴት አገኝ ቤተሰቧን በማስጠየቅ በቤተክርስትያን ስርአት ተጋብተው ጥቂት አመት እንደቆዩ ጉዞውን እየሩሳሌም አደረገ ለተከታታይ 13 አመታትም ቆይታ በኋላ ወደ ባለቤቱ ተመልሶ ከወንድሙ ከ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ጋር እርቅ በማውረድ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ንግስናውን ለቅዱስ ላሊበላ በተወለደ በ57 አመቱ በማስረከብ ኑሮውን በገዳም አደረገ፡፡ \n \nጥያቄ: ቅዱስ ገብረ ማርያም ንግስናውን ለቅዱስ ላሊበላ በስንት ዓመቱ አስረከበው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ57 አመቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ ላይ ምን ያህል ተውኔቶችን ለዓለም አበርክቷል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አምስት ተውኔቶችን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: በመለጋሲኛ ቋንቋ የሚናገሩ የማዳጋስካር ነዋሪዎች ከእንዶኔዚያ የመጡት ከስንት ዓመት በፊት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1500-2000 አመታት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል በአፍሪካ በየትኛው አቅጣጫ የምትገኘው ሀገር ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ ለዓለም ከምታቀርባቸው ምርቶች ዋነኞቹ የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ካካውና ጎማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቻይና በማርስ ላይ የምታካሂደውን የመጀመሪያ ሳይንሳዊ ጥናት የፊታችን ሃምሌ ወር እንደምትጀምር ይፋ አድርጋለች። ጥናቱን የምታከናውነው ሳተላይት ሎንግ ማርች 5-ዋይ 4 በተሰኘ ሮኬት ወደ ህዋ እንደምትላክም የቻይና የጠፈር ምርምር ተቋም አስታውቋል። ሮኬቱ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቅ የሚያሰችል አቅም እንዳለው በሙከራ ተረጋግጧልም ነው የተባለው። ከሃይድሮጅን እና ኦክስጅን ጋዞች የተሰራ ሞተር ያለው ሮኬት በተያዘው ዓመት በርካታ ሳተላይቶችን ወደ ህዋ ያደርሳል ተብሎ ታምኖበታል። ወደ ህዋ የምትላከው ሳተላይትም በማርስ ፕላኔት ዙሪያ በርካታ አዳዲስ ግኝቶች እና መረጃዎችን ለምርምር ተቋሙ ታደርሳለች ተብሎ ይጠበቃል። \n \nጥያቄ: ቻይና በማርስ ላይ የምታካሂደው የመጀመሪያ ሳይንሳዊ ጥናት በምን ወር ትጀምራለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሃምሌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: በሀይቲ ደሴት ላይ የነበረው የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ያከተመው በስንት ዓመተ ምህተት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፲፯፻፺፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ከትዳር አጋሩ ጋር ኑሮውን ለ17 ዓመታት ያሳለፈባት ግዛት ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኮኔቲከት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየሆሊውዱ የፊልም ኩባንያ ዋርነር ብሮስ የቦክስ ኦፊስን የደረጃ ሰንጠረዥ በሰው ሰራሽ መሳሪያ (አርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ) መገመት ሊጀምር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ሰው ሰራሽ መሳሪያው ዋርነር ብሮስ የሚያዘጋጃቸው ፊልሞች ምን ያህል ስኬታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ ግምቱን ያስቀምጣል ተብሏል፡፡ ይህ አሰራር የተዋናይ አመራረጥን፣ የማከፋፈሉን ሂደት እና የሚለቀቅበትን ጊዜ መነሻ በማድረግ ትርፋማነቱን ይገመግማል ነው የተባለው፡፡ በሆሊውድ መንደር ከስድስት ትልልቅ የፊልም ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ዋርነር ብሮስ ይህን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ከኤልኤ ስታርት አፕ ሲኔለይቲክ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ የመገመቻ መሳሪያው ባለፈው ዓመት ይፋ የሆነ ሲሆን ለዘርፉ አዲስ ይዘት እና አሰራርን ይዞ መምጣቱ ሲኔለይቲክ በድረ ገፁ አስነብቧል፡፡ መሳሪያው የተለያዩ መረጃዎችን በመጠቀም የቦክስ ኦፊስ የደረጃ ሰንጠረዥን በትክክል እንደሚገምት ተጠቁሟል፡፡ አንዱ የዚህ መሳሪያ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ተዋንያን የሚመርጡበት ሂደት እንዴት በፊልሙ ትርፋማነት ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር መመልከት እንዲችሉ ያደርጋል ነው የተባለው፡፡ ምንጭ፡-ስካይ ኒውስ \n \nጥያቄ: የትኛው የሆሊውዱ የፊልም ኩባንያ ነው የቦክስ ኦፊስን የደረጃ ሰንጠረዥ በሰው ሰራሽ ሊያስገምት የፈለገው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዋርነር ብሮስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ1913 በፕሬዝዳንት ዋረን ሃርዲንግ ዘመን ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ሆኑ። በሃርዲንግ ተከታይ በፕሬዝዳንት ካልቪን ኩሊጅ ዘመን ደግሞ እንዲህ ያለን ማዕረግ ይዘው አገለገሉ። የንግድ ሚኒስትር እየሆኑ ሃይለኛ ሰው ነበሩ። የንግድ ዘርፍና መንግሥት አንድላይ ይሠሩ የሚለውን ተስፋ በመያዛቸው በዚህ አንጻር ብዙ አደረጉ። በማዶ ባሕርና በውጭ አገር ለባለጉዳዮች ምክርና እርዳታ የሚሰጡ መሥርያ ቤቶች በማስከፈቱ የአለም አቀፍ ንግድ በጉልበት አስለሙ። በተለይም የሆሊዉድ ፊልም ማዶ ባሕር ለመግፋፋት ጉጉ ነበሩ። ዜጎችም ቤት እንዲያገነቡና የራሳቸው መሬት ባለአባት እንዲሆኑ አበረታቷቸው። ስለ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የክላርክ ሰነድ በ1920 ተጽፎ ሁቨር ፕሬዝዳንት እየሆኑ በ1922 ግልጽ ሆኖ ወጣ። በዚህ ሰነድ ዘንድ፥ አውሮጳ በላቲን አሜሪካ ላይ ዛቻ ካልጣለች በተቀር አሜሪካ በውጭ አገር ጥልቅ ለማለት ሕጋዊ መብት አልነበራትም የሚል ማስታወሻ ነበር። በዚያን ጊዜ አሜሪካ ሠራዊት በኒካራጓና በሃይቲ ነበራት። ስለዚህ ሁቨር ከነዚህ አገራት የሠራዊቱን ቁጥር ቀነሱ። በላቲን አሜሪካ ውስጥ የጦርነት መሣርያ እንዳይደርስ ማዕቀብ ለመጣል አሠቡ። በ1924 ጃፓን ማንቹርያን በወረረ ጊዜ አዲስ ፖሊሲ አወጡ። እሱም በግፍና በወረራ የሚገኝ የመሬት ለውጥ ሁሉ አናከብርም የሚል ነበር። ከታላቁ ጭፍግግ የተነሣ ብዙ ባንክ ቤቶች ስለወደቁ አንዳችም ብድር ለማግኘት ከባድ ሆነ። ብዙ ሰዎች ሥራ ፈት ሆኑ። በአውሮፓም ምጣኔ ሃብቱ ችግር ውስጥ ስለ ገባ ሁቨር ጀርመን ስለመጀመርያው ጦርነት ለፈረንሳይ ከምትከፍል ካሣ ለአንድ አመት ይቅር ትበል የሚል ዕቅድ አዋጁ። በሚከተለውም አመት የጀርመን ዕዳ በሙሉ ተሰረዘ። በ1925 ምርጫ ተቃራኒው ፍራንክሊን ሮዘቨልት በሰፊ መጠን አሸነፉና በሳቸው ፈንታ ፕሬዚዳንት ሆኑ። ሁቨር ፕሬዚዳንት ከሆኑ በኋላ ረጀም ዕድሜ ነበራቸው። እስከ 1957 ዓ.ም. ድረስ ኖሩ። ከ2ኛ አለማዊ ጦርነት ቀጥሎ በ1939 ስለ ቀድሞው ልምዳቸው ፕሬዚዳንት ሃሪ ትሩማን የአውሮፓ ምግብ ፍላጎት ለመወሰን ወደ አውሮፓ ላኳቸው። \n \nጥያቄ: በ1913 የሄርበርት ሁቨር የስራ መስካቸው ምን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። \n \nጥያቄ: ቡክሀርት ባልደክኼር የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለዓለም ያበሰረው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1937 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመርያው ሦስት ወራት፣ ከ12.2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ቢሮው እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ የሚዘልቅ ግብር የማሳወቅና የመሰብሰብ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጾ፣ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጨረሻ ሳምንት ባለው ጊዜ ከግብር አሰባሰቡ የተገኘው ገቢ ከታቀደው በላይ እንደሆነ አስታወቋል፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊነትን አዲስ በተመረጠው የከተማ አስተዳደር እንዲመሩ በድጋሚ የተመረጡት አቶ ሙሉጌታ ተፈራ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ ገቢዎች ቢሮው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የተጀመሩትን የከተማዋን ገቢ በተጠናከረ ሁኔታ የመሰብሰብ ሥራ ዘመናዊ በሆነ ሥርዓትና ቅንጅታዊ አተገባበር እየተከናወነ ነው፡፡ በተያዘው በሩብ ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ የታቀደው የግብር ገቢ 11.5 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ያስታወቁት ኃላፊው፣ ከሦስት ያላነሱ ቀናት የገቢ አሰባሰብ መረጃ ሳይካተት እስከ መስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ 12.26 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አቶ ሙሉጌታ ተፈራ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ኃላፊነታቸው ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሥነ ቁጥር ሥነ ቁጥር ወይንም በእንግሊዝኛ \"አርቲሜቲክስ\" ከሁሉ የሒሳብ ዘርፎች አንጋፋውና በሁሉም ሰው ጥቅም ላይ የሚውል ክፍል ነው። ሥነ ቁጥር የቁጥሮችን ቅልቅል ውጤት የሚያጠና ሲሆን ብዙ ጊዜ ቁጥሮች ሲደመሩ፣ ሲቀነሱ፣ ሲባዙና ሲካፈሉ የሚያሳዩትን ባህርይ ይመረምራል። ሒሳብ ተማሪዎች የቁጥር ኅልዮት ውጤቶችን ከፍተኛ ሥነ ቁጥር በማለት ከለተ ተለት መደመርና መቀነስ ጥናቶች ይለዩዋቸዋል። የሰው ልጆች ከጥንት ጀምሮ ሥነ ቁጥርን ተጠቅመዋል። ለምሳሌ አፍሪቃ ውስጥ የተገኘ 22፣000 ዓመት እንዳለው የሚቆጠር የአጥንቶች ቁርጥራጭ ለመቁጠርና ለመደመር ያገለግል እንደነበር ይጠቀሳል። በኋላም የግብጽ እና ባቢሎን ሰወች ቁጥርን መጻፍ እንደጀመሩና ይህን ፈጠራቸውን ለመደመርና ለመቀነስ እንደተገለገሉበት አሁን የተገኙ ቅርሶች ያስገነዝባሉ። የግብጽን የአጻጻፍ ስልት የተከተሉ ግሪኮችም በዩክሊድ እና ሌሎች የግሪክ ተማሪዎች አማካይነት ጥናቱን ለማሳደግ ችለዋል። ሆኖም እስከዚህ ዘመን የነበረው የቁጥር አጻጻፍ ስልት አቀማመጣዊ አልነበረም። ስለሆነም ለመደመርና ለመቀነስ፣ በተለይ ደግሞ ለማባዛትና ለማካፈል እጅግ የተወሳሰበና አሰልቺ ነበር። የሒሳብና የሥነ ቁጥር እድገት ከፍተኛ እመርታ ያሳየው ሕንዳውያን ተማሪዎች ዜሮና አቀማመጣዊ አጻጻፍ ስልትን በ4ኛው ክፍለዘመን ሲፈለስፉ ነበር። ይህም አሁን በመላው አለም የሚሰራበት ህንዲ-አረብ ቁጥር (ማለቱ፡ 0 1 2 3 4 5 6 7 8 9 ) እንዲፈጠር አደረገ። ፊቦናቺ የተሰኘው የጣሊያን ነጋዴ የዚህን ድንቅ ቁጥር ቀመርና ጥቅም በመጽሐፉ በ1202 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) በመጻፍና በአውሮጳ አገራት ሁሉ በማሰራጨት ታዋቂነቱ እንዲገን ሆነ። የህንዲ-አረብ ቁጥር ስርዓት በጣም ቀላል ከመሆኑ የተነሳ የሒሳብ ትምህርት በአውሮጳ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አደረገ። ይሄው አዲሱ ስልት ለሒሳብ ጥናት መሰረት በመሆን የጥንቶቹን ሒሳብ ተማሪዎች ድንቅ ውጤቶች ከአዲሱ ስርዓት ጋር ሲነጻጻሩ እምብዛም ሆነው እንዲታዩ አደረጉ። የሂንዲ አረብ ቁጥር ስርዓት ለዘመናዊው የሒሳብ ትምህርት መነሳት ምክንያት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። \n \nጥያቄ: አሁን በመላው አለም የሚሰራበት ቁጥር ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የህንዲ-አረብ ቁጥር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኒቅያ ጉባኤ የተደረገው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በኒቂያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየሻይ ቅጠል ልማት ለማካሄድ ፈቃድ ወስዶ፣ ነገር ግን በሕገወጥ መንገድ ጣውላ ሲያመርት የተገኘው የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሐርቨስት፣ አሁን ደግሞ በሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ተጠያቂ ሆነ፡፡ ቬርዳንታ ሐርቨስት ቀጥሮ ጉልበታቸውን ሲበዘብዝ ነበር የተባሉት አብዛኞቹ ሕፃናት ከሰባት ዓመት በታች እንደሆኑ፣ የተወሰኑት ደግሞ እስከ 15 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 250 ሕፃናትን በመቅጠር ሲያሠራ መገኘቱን፣ ከጋምቤላ ክልል የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ የጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ጉደሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮናስ ከፑምሳ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቬርዳንታ ሐርቨስት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የሕፃናቱን ጉልበት ሲበዘብዝ ቆይቷል፡፡ ‹‹ሕፃናቱን ሲያሠራ ቢቆይም ቃል የገባውን ክፍያ በመቀነስ ሕፃናቱ ቅሬታቸውን ይዘው ወደኛ መጥተዋል፤›› በማለት አቶ ዮናስ ገልጸው፣ ‹‹ጉዳዩ በዞን ደረጃ እየታየ ነው፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ ‹‹የሕፃናቱ መብት መጠበቅ አለበት፡፡ እኛ ሕፃናት እንዲህ ያለ ሥራ መሥራት የለባቸውም የሚል አቋም ነው ያለን፤›› ብለው የህንዱ ኩባንያ የፈጸመውን ተግባር ኮንነዋል፡፡ ይህንን ሕገወጥ ተግባር የፈጸመውን ይህ ኩባንያ የሚወስድበት ዕርምጃ በቀጣይ እንደሚታወቅም አቶ ዮናስ አክለው ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የሕንዱ ኩኩንያ ቬርዳንት ኸርቨስት ፈቃድ ያወጣው በየት አካባቢ ለመስራት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጋምቤላ ክልል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nብሪታኒያ የቻይናው ሁዋዌ 5ኛ ትውልድ (5G) ኔትወርክ በተወሰነ ገደብ በሀገሯ ስራውን እንዲቀጥል ውሳኔ አሳለፈች፡፡ ውሳኔው የተላለፈው ብሪታኒያ ኩባንያውን እንድታግደው አሜሪካ ጫና እየፈጠረች ባለችበት ወቅት፡፡ ብሪታኒያ ውሣኔውን ያሳለፈችው በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ገደብ በመጣል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ኩባንያው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልገው ወሳኝ ክፍል (ኮር) ተብሎ የሚጠራውን አካል እንዳያቀርብ እገዳ ተጥሎበታል፡፡ ሁዋዌ ኩባንያ በብሪታኒያ 35 በመቶ በሚሆነው 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ ዝርጋት እንዲሰማራ እንደተፈቀደለት ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከወታደራዊ ማዕከላት እና ከኒውክሌር ጣቢያዎች አቅራቢያ እቀባ እንደተጣለበት ነው የተገለጸው፡፡ ቤጂንግ ኩባንያው ከታገደ በብሪታኒያ ሌሎች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ከፍተኛ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቃ ነበር፡ ኩባንያው በበኩሉ ይህ መፈቀዱ ብሪታኒያ የዓለም-መሪ ቴክኖሎጂን ማግኘት እንድትችል እና ተወዳዳሪ የሆነ ገበያ እንዲኖራት ያደርጋል ብለዋል፡፡ አያይዘውም የ5G ልቀትን ለማስቀጠል ከደንበኞቻችን ጋር አብረን መሥራታችን እንደምንቀጥል ለብሪታኒያ መንግስት እናረጋግጣለን ማለታቸው ነው የተነገረው፡፡ ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: በብሪታንያ ሁዋዌ በመቶኛ ምን ያህል 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ እንዲዘረጋ ተፈቀደለት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 35 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ አብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል በምን በረሃ ውስጥ ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሰሐራ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በስንት አፍሪካ ሀገራት የነዳጅ ማደያዎች ከፍቷል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ18 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቢል ክሊንተን ዊልያም ጄፈርሰን «ቢል» ክሊንተን (William Jefferson Bill Clinton) (የትውልድ ስም፦ ዊልያም ጄፈርስን ብላይዝ ፬ኛ፣ እንግሊዘኛ፡ William Jefferson Blythe IV) በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) በሆፕ አርካንሳው የተወለዱ ሲሆን ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ድረስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕሬዝዳንት ከመሆናቸዉ በፊት አምስት ጊዜ የአርካንሳው ስቴት አስተዳዳሪ ነበሩ። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን የት ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሆፕ አርካንሳው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየሻይ ቅጠል ልማት ለማካሄድ ፈቃድ ወስዶ፣ ነገር ግን በሕገወጥ መንገድ ጣውላ ሲያመርት የተገኘው የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሐርቨስት፣ አሁን ደግሞ በሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ተጠያቂ ሆነ፡፡ ቬርዳንታ ሐርቨስት ቀጥሮ ጉልበታቸውን ሲበዘብዝ ነበር የተባሉት አብዛኞቹ ሕፃናት ከሰባት ዓመት በታች እንደሆኑ፣ የተወሰኑት ደግሞ እስከ 15 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 250 ሕፃናትን በመቅጠር ሲያሠራ መገኘቱን፣ ከጋምቤላ ክልል የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ የጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ጉደሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮናስ ከፑምሳ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቬርዳንታ ሐርቨስት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የሕፃናቱን ጉልበት ሲበዘብዝ ቆይቷል፡፡ ‹‹ሕፃናቱን ሲያሠራ ቢቆይም ቃል የገባውን ክፍያ በመቀነስ ሕፃናቱ ቅሬታቸውን ይዘው ወደኛ መጥተዋል፤›› በማለት አቶ ዮናስ ገልጸው፣ ‹‹ጉዳዩ በዞን ደረጃ እየታየ ነው፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ ‹‹የሕፃናቱ መብት መጠበቅ አለበት፡፡ እኛ ሕፃናት እንዲህ ያለ ሥራ መሥራት የለባቸውም የሚል አቋም ነው ያለን፤›› ብለው የህንዱ ኩባንያ የፈጸመውን ተግባር ኮንነዋል፡፡ ይህንን ሕገወጥ ተግባር የፈጸመውን ይህ ኩባንያ የሚወስድበት ዕርምጃ በቀጣይ እንደሚታወቅም አቶ ዮናስ አክለው ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ቬርዳንት ኸርቨስት ከሕግ ውጪ ምን ያህል እድሜያቸው ለሥራ ያልደረሰ ሕጻናትን አሰርቷል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 250 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራን በደቡብ-ምሥራቅ የምትጎራበታት ሀገር ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጅቡቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር። ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች ኮሞዲቲ ገንዘብ መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ ከብትና እህል (ገብስ) መደበኛ ነበሩ። በተለይ ዛጎል በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። መዳብ፣ ብረት፣ ብርና ወርቅ በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረታብረት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ። በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ የፈተና ደንጊያ ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሳንቲም እና የብር ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ልድያውያን ነበር።. በኢትዮጵያም በአክሱም ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል። ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው ተወካይ ገንዘብ የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። ሆኖም ስዊድን የወረቀት ብር ያወጣው ምክንያት ጦርነት ለማድረግ ፈልጎ በቂ ወርቅ ወይም ሌላ ገንዘብ በአገሩ ስላልነበረው ነው። አሁን ወዲያው የስዊድን መንግሥት ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ሥራተኖች መክፈል ቻለ። በጥቂት ዓመት ውስት የስዎድን ወረቀት ገንዘብ ወደቀ። ነገር ግን ከትንሽ በኋላ የእንግላንድ መንግሥት በፈረንሣይ ላይ በጦርነት ተይዞ ለጦርነትም ያህል በቂ ሀብት ባለመኖሩ እንዲህ አይነት መፍትሄ መረጡ፤ የኢንግላንድ ፓውንድ ድፍን ጀመሩ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አገራት ፈቃዳቸውን ለመፈጽም አዲስ የወርቅ ወይም የብር ማዕድን ማግነት አስፈላጊ አልነበረም። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ይህ በወርቅ የተደገፈ የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በይፋ በመላው ዓለም ተንሰራፋ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብሬቶን ውድስ ስብሰባ፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች ፊያት ገንዘብን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር። በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታት እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው። \n \nጥያቄ: በቻይና የሶንግ ስርወ መንግስት ዘመን የሚባለው ከመቼ እስከ መቼ ነው ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ ኢትዮጵያዊው ሊቅና ጻድቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ የተወለዱት በ፲፫፻፶፯ ዓ.ም. በወሎ ክፍለ ሀገር በቦረና ወረዳ ሸግላ/ሰግላ በተሰኘች ቦታ ነው። አባታቸው ሕዝበ ጽዮን ከተከበሩ መምህራን ወገን የሆኑ የቤተ መንግሥት ባለሟል ፤ መጽሐፍትን የሚያውቁ ጥበብ የተሞሉ ሲሆን የሰግላ አገረ ገዢም ነበሩ ። እናታቸው እምነጽዮንም ከወለቃ ሹማምንት ወገን የሆኑ ደግ ሰው ነበሩ። ሲጀመር እናታቸው ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማሩ በጥበብና በዕውቀት አሳደጓቸው ። አባ ጊዮርጊስ የተመረጠ የሆነ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በመማፀን የተወለዱ ልጃቸው ስለሆኑ እንደሰማዕቱ የእውነት ምስክር እንዲሆኑላቸው በመመኘት ስማቸውን ጊዮርጊስ ብለው ጠርተዋቸዋል ። ከተወለዱበትም ሀገር በመነሳት ጊዮርጊስ ሰግላዊ ተብለው ሲጠሩ በጊዮርጊስ ዘጋስጭና በጊዮርጊስ ሰግላዊ መካከል ምንም ልዩነት የለም። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ እንደ ሰማዕት ግርፋትንና እሥራትን የተቀበሉ ፣ እንደ ሊቃውንት የመናፍቃንና የከሀድያንን ክርክር የረቱ ፣ እንደ መሐንዲስ ሐናጺ ፣ የሕግና የሥርዐት የሚስጥራትና የትርጉዋሜያት መምህር ፣ የጸሎትና የትምህርት መጻሐፍት ደራሲ ፣ የሥርዓተ ገዳምና ማኅበረ መነኰሳት አባት እንዲሁም ቢያንስ የአንድ ትምህርት መሥራች ሲሆኑ በግዞት በሄዱባቸውና በታሰሩባቸው ቦታዎችም ሆነ በተሾሙባቸው እንደ ደብረዳሞ ገዳም በመሰሉ ቦታዎች ሁሉ ሲያስተምሩና ሲገስጹ ኖረዋል ። በድርሰቱም እስካሁን በሃገራችን ተወዳዳሪ የላቸውም ። እጃቸው ከብዕር ተጨማሪ ከጠንካራ ሥራ ሳይቦዝኑ ዋሻ ሲፈለፍሉ የውሃ ጉድጉዋድ ሲቆፍሩ ድልድይ ሲሠሩ ኖረዋል ። አንደበታቸውና ሕሊናቸው ከምስጋና ሳያቁዋርጡ ለቤተክርስቲያን ጸሎትና ምስጋና ሥርዓት ሲተጉ ኖረው በፅድቅና በቅድስና ሕይወት እንዳጌጡ ለተዋህዶ ኮከብ ሆነው በተወለዱ በ፷ ዓመታቸው በ፲፬፻፲፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፯ ቀን አርፈዋል ። ተማሪዎቻቸውም በመረረ ሐዘን ሆነው አፅማቸውን በጋስጫ ራሳቸው ፈልፍለው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በሠሩት ገዳም ውስጥ አስቀምጠውታል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ በስንት ዓመታቸው አረፉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፷ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመንግሥት እና ፖለቲካ ናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ሲሆን መንግሥቷ በአሜሪካ መንግሥት ላይ ነው የተመረኮዘው። የህግ አውጪው አካል አወቃቀር የዌስትሚኒስትር ሥርዓትን ይከተላል። በአሁኑ ጊዜ ጉድላክ ጆናታን ፕሬዝዳንት ናቸው። ፕሬዝዳንቱ ለሁለት የአራት ዓመት ጊዜ ሲያገለግል በሕዝቡ ነው የሚመረጠው። የናይጄሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ሁለት አካሎች አሉት። እነዚህም ሴኔት እና የተወካዮች ምክር ቤት ናቸው። ሴኔቱ 109 መቀመጫዎች ሲኖሩት እያንዳንዱ ክልል በሶስት አባሎች ይወከላል። የአቡጃ ርዕሰ አካባቢም አንድ ተወካይ አለው። የሴኔት አባላት በሕዝብ ይመረጣሉ። የተወካዮች ምክር ቤት 360 መቀመጫዎች ሲኖሩት የእያንዳንዱ ክልል ወካዮች በሕዝብ ብዛት ነው የሚወሰነው። የውጭ ግንኙነቶች ነፃነቷን በ1960 እ.ኤ.አ. ካገኘች በኋላ ናይጄሪያ ለአፍሪካ ነፃነትና ክብር መታገል ዋና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አድርጋለች። የደቡብ አፍሪካን አፓርታይድ ሥራዓት በመቃወም ትልቅ ሚና ተጫውታለች። በ1960ዎቹ እ.ኤ.አ. ናይጄሪያ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት የነበራት ሲሆን እስራኤል የናይጄሪያ ፓርላማ ህንጻዎችን አሰርታለች። ናይጄሪያ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መስራች አገር ናት። በምዕራብ አፍሪካም ሆነ በአፍሪካ በጠቅላላ ትልቅ ተጽዕኖ አላት። በተጨማሪም እንደ ኤኮዋስ ያሉ የምዕራብ አፍሪካ የትብብር ድርጅቶች መሥራች ናች። ከ1970ዎቹ እ.ኤ.አ. ጀምሮ ናይጄሪያ ዋና የነዳች አምራች ስትሆን የኦፔክ አባል ሀገር ናት። በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ናይጄሪያውያን በኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተሰድደዋል። ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ናይጄሪያውያን በአሜሪካን እንደ ሚኖሩ ይገመታል። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ ነጻነቷን ያገኘችው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1960 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: ከፀሀይ የመጠነ ቁስ ጥንቅር ነገሮች መካከል የሃይድሮጂን መጠን ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 74% ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 15/2012 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሰራተኞቹ ጋር በሬድዬ ግንኙነት በመፍጠር አገልግሎቱን የሚያቀላጥፍበት የአስትሮ ሞቶሮላ የሬድዬ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት አስመረቀ። የፕሮጀክቱ ምረቃ ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር በተገኙበት በእንጦጦ ማሪያም የቴሌ ማይክሮዌቭ ማሰራጭያ ጣቢያ ተካሂዷል። በሁለት ምዕራፍ የተከፈለውን ፕሮጀክት ወደ ሥራ ለማስገባት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር ሐምሌ 15 /2017 በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትና በሞቶሮላ ሶሉሽን ኩባንያ መካከል ስምምነት ተፈርሞ ነበር። የመጀመሪያው ምዕራፍ 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአዲስ አበባና ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ኦሮሚያ ዞን ላይ ተግባራዊ ሆኗል። የኤሌክትሪክ የአገልግሎት አሰራሩን በማቀላጠፍ ለዜጎች የተሻለ አገልግሎት እንደሚሰጥ የታመነበት ይሄው ፕሮጀክት 6 ቡድኖችን በመያዝ በ 8 የግንኙነት ቻናሎች በጋራ እና በእኩል ሁኔታ እንዲጠቀሙ የሚያግዝ ነውም ተብሏል። የአስቸኳይ ጥገና ሥራን ማቀላጠፍ፣ ከሰብ ስቴሽን ጋር የሚኖረውን ግኝኑነት ማሳለጥ፣ በግንኙነት ክፍተት ሊፈጠሩ የሚችሉ የሰውና የንብረት አደጋን መቀነስ እንዲሁም የኃላፊዎችን መረጃ የመቀበልና መልዕክት የማስተላለፍ ሥራውን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ተገልጿል። በኤሌክትሪክ አገልግሎት የአውቶሜሽንና ኢነርጂ ማኔጅመንት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ደመቀ ሮቢ አገልግሎቱ ስራውን የሚያከናውነው በስልክ እንደነበር አስታውሰው ይህም የሚሰጠው አገልግሎት ቅልጥፍና እንዳይኖረው አድርጎት ቆይቷል ይላሉ። ዛሬ የተመረቀው የሬድዮ ኮሙኒኬሽን ፕሮጀክት መስክ የወጡ የጥገና ሰራተኞች ቢሮ ካሉ ሰራተኞች ጋር በፍጥነት እንዲገናኙ ከማድረጉም ባለፈ ከፍተኛና ዝቅተኛ ኃይል መስመር ላይ ካሉ ኦፕሬተሮች ጋርም በቀላሉ በመገናኘት ፍጥነት ያለው የጥገና አገልግሎቶች እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል። በዚሁ የመጀመሪያው ምዕራፍም በአዲስ አበባና ዙሪያ በእጅ የሚያዙ 300 እንዲሁም 200 መኪና ላይ የሚገጠሙና 100 በጥሪ ማዕከልና በአስቸኳይ ጥገና ማዕከላት ላይ የሚገጠሙ ዲጂታል ሬዲዮኖች ጥቅም ላይ ውለዋል። እንደ አቶ ደመቀ ገለጻ ምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክቱንም ለማካሄድ ከአዲስ አበባ ውጪ 8 ከተሞች የተመረጡ ሲሆን ለዚህም ከ4 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት ተይዞለታል። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሠራተኞቹ ጋር የሚገናኝበት ሬዲዮ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአስትሮ ሞቶሮላ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኤንመርካር ኤንመርካር በሱመር (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የኡሩክ (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የኡቱ ልጅ መስኪያጝካሸር ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከኤአና ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል። የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። «ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ» በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የጸሓይ አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በኤሪዱም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ አራታ እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል። በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት ሹቡር፣ ሐማዚ፣ ሱመር፣ ኡሪ-ኪ (የአካድ ዙርያ) እና የማርቱ አገር ናቸው። ከዚህ በላይ የኤንመርካርን መንግሥት የሚገልጹ ሦስት ተጨማሪ ጽሑፎች አሉ። «ኤንመርካርና ኤንሱሕጊርዓና» የሚባል ተረት የኤንመርካርና የአራታ መቀያየም ሲገልጽ፣ ሐማዚ ተሸንፎ እንደ ነበር ይጠቅሳል። በ«ሉጋልባንዳ በተራራ ዋሻ»፣ ኤንመርካር በአራታ ላይ ዘመቻ ሲመራ ይታያል። አራተኛውና መጨረሻውም ጽላት፣ «ሉጋልባንዳና የአንዙድ ወፍ» ኤንመርካርና ሠራዊቱ በአራታ ዙሪያ ለ1 አመት እንደ ከበቡት ይላል። ለመሆኑ ኤንመርካር 50 አመት ከነገሰ በኋላ፣ የማርቱ ሕዝብ (አሞራውያን) በሱመርና በአካድ ሁሉ ተነሥተው ኡሩክን ለመጠብቅ ግድግዳ በበረሃ መስራት እንደ ነበረበት ይጠቅሳል። በነዚህ መጨረሻ 2 ጽላቶች፣ ከኤንመርካር ጦር አለቆች አንድ የሚሆን ሉጋልባንዳ የሚባል ሰው ይተረታል። በሱመር ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ፣ ይህ ሉጋልባንዳ «እረኛው» ኤንመርካርን ወደ ኡሩክ ዙፋን ተከተለው። ይህ ሉጋልባንዳ ደግሞ በጊልጋመሽ ትውፊት በተባለው ግጥም ዘንድ የኋለኛው ኡሩክ ንጉሥ የጊልጋመሽ አባት ነበረ። ዴቪድ ሮኅል የሚባል አንድ የታሪክ ሊቅ የኤንመርካርና የናምሩድ ተመሳሳይነት አመልክቷል። «-ካር» የሚለው ክፍለ-ቃል በሱመር ቋንቋ ማለት «አዳኝ» ነው። ኡሩክ ከተማ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ነበር ሲባል፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በሌላ ትውፊቶች ዘንድ ይህ ናምሩድ የባቢሎን ግንብ መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪም አቶ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም «ባቤል» እንደ ነበር ያምናል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ። «ባቢሎን» ማለት የኤሪዱ መጠሪያ እንደ ነበር የሚል ማስረጃ በሌሎችም ጥናቶች አለ። ሮማዊው ጸሐፊ ክላውዲዩስ አይሊያኑስ በጻፈ አንድ ትውፊት ዘንድ (200 ዓ.ም. ግድም)፣ የባቢሎን ንጉስ «ኤወኮሮስ» የተከታዩን «ጊልጋሞስ» አያት ይባላል። ይህ «ጊልጋሞስ» ማለት የኡሩክ ንጉስ ጊልጋመሽ መሆኑን የአሁኑ ሊቃውንት ስለ ገነዘቡ፣ እንዲሁም «ኤወኮሮስ» ማለት ኤንመርካር ሳይሆን አይቀርም የሚል አስተሳሰብ ያቀርባሉ። ከዚህ በላይ የከላውዴዎን ታሪክ ጸሐፊ ቤሮሶስ በጻፈው ዝርዝር መሰረት፣ ከማየ አይህ ቀጥሎ የከላውዴዎንና የአሦር መጀመርያው ንጉስ «ኤወኮዮስ» ይባላል፤ ስለዚህ የዚሁ «ኤወኮዮስ»ና የናምሩድ መታወቂያ አንድ ናቸው የሚለው አሳብ ለረጅም ዘመን የቆየ ነው። \n \nጥያቄ: ከሱመር ነገስታት መካከል ኤንመርካር የመሰረታት ከተማ ማናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የኡሩክ (ኦሬክ) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኮረማሽ ኮረማሽ በአማራ ክልል ውስጥ፤ በሰሜን ሸዋ የምትገኝ ወረዳ ናት። ከአዲስ አበባ በምሥራቅ በኩል ሰማንያ አምሥት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ሥፍራ ስትሆን፣ በስምጥ ሸለቆ ምሥራቃዊ ፍንጭ አናት ላይ ያላት ገዥ ይዞታ ከአፋር (የቀድሞው አዳል) እና ከሶማሌ በኩል በታሪክ ዘገባ ይመነጩ የነበረቱን እስላማዊ አጥቂዎች ለመከላከል የተመቸች ቦታ በመሆኗ የተመሠረተች ጥንታዊ ምሽግ ናት። ከፊት ለፊትዋ የመገዘዝ ተራራ፤ እንኮይ፤ ሰንበሌጥ፤ ቡልጋ እና ወደ ምሥራቅ የደረቂት እና አማሪት ወንዞች ከከሰም ወንዝ ጋር ሲቀላቀሉ እንዲሁም የመስኖ ዘንባባ ተራራ እና የመስኖ ማርያም ቤተ ክርስቲያን፤ ሜዳማው የሾላ ገበያ ወደደቡብ ምሥራቅ ደግሞ ከማዶ የክርስቶስ ሰምራ ትውልድ አገር እና ምንጃር ቁልጭ ብለው ይታያሉ። የአካባቢው ቃለ ታሪክ ሥፍራዋ በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አያት ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እንደተመሠረተች ሲያረጋግጥ፤ የልጅ ልጃቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ደግሞ የሸዋ ንጉሥ በነበሩ ጊዜ እስካሁን ድረስ ያለውን ታላቅ የመሣሪያ ምሽግ እና በግቢው ውስጥ ያሉትን አሥራ አንድ ቤቶች እንዳሠሩ ብዙ የጽሑፍና የቃል ታሪኮች እንዲሁም ሕንጻዎቹ እራሳቸው ምስክር ናቸው። ከነኚህ አሥራ አንድ ሕንጻዎች ሁለቱ በ ፲፱፻፸፯ ዓ/ም በሉተራን ኃይማኖታዊ ተልዕኮ ልገሣ ታድሰው የ ጥራ ጥሬ እና የ እህል ምርት ማከማቻ ጎተራ ሆነዋል። ሌሎቹ ቤቶች የወረዳው ፍርድ ቤት፤ የቤተ ክህነት ጽ/ቤት ፤ የወረዳው የፖሊስ ጽ/ቤት እና የመሳሰሰሉ መንግሥታዊ ቢሮዎችን ይዘዋል። በጥቅምት ወር ፲፱፻፱ ዓ/ም አዲስ በተመሠረተው የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እና የራስ ተፈሪ መኮንን መንግሥት ላይ ጦርነት አውጀው ከወሎ የዘመቱትን የልጅ እያሱ አባት ንጉሥ ሚካኤልን ሊከላከል የተሰለፈው የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠራዊት ጥቃቱን ያደራጀው እዚሁ ኮረማሽ ላይ ሲሆን፡ ኋላም ዓርብ ጥቅምት ፲፯ ቀን ራስ ተፈሪና ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሰገሌ ሜዳ ላይ ንጉሥ ሚካኤልን ድል ያደረጉት ከዚሁ ደጀን ቦታ ነው። በ፳፻፩ ዓ/ም ከ ዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የኤሌክትሪክ መሥመር ተዘርግቶ ለዚች መንደርና ለአካባቢው የቡልጋ ሕዝብ የልማት መስፋፊያ ጮራ ተገልጾለታል። በዘመናዊ መልክ የተገነባው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በተመረቀበት ዋዜማ፣ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ባለው የአሥራ ሦስት ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ ላይ በሳምንት ሁለት ጊዜ፤ ማለትም ሐሙስ እና ቅዳሜ ለገበያ የሚያመች የሕዝብ መመላለሻ የአውቶቡስ መሥመር አገልግሎቱን ጀምሮ፣ በተለይም ቆለኞቹ ምርታቸውን ወደ ገበያ በማቅረብ ላይ የነበረባቸውን የእግር ጉዞ እንግልት ቀንሶላቸዋል። ወደፊትም ገብያቸውን ሐሙስ ገበያ ድረስ ከመሄድ እዚችው ኰረማሽ ላይ ለመመሥረት ተስፋ ሰጥቷቸዋል። ለ የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምረቃ ሥነ ስርዐት የተጓዙ እንግዶች በዚሁ የአውቶቡስ አገልግሎት ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ቢያንስ የሦስት ሰዐት የእግር ጉዞ ቀርቶላቸዋል። \n \nጥያቄ: የኮረማሽ ወረዳ የት ክልል ትገኛለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በአማራ ክልል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nከ1936 ጀምሮ ኤርትራ የኢኮኖሚ እድገት ማሳየት ችሏል። በ30ዎቹ መጨረሻ 2፣198 የኢንደስትሪ ተቋሞች በአገሪቱ ተመስርተዋል። ይሁንና ጣሊያኖች አገሪቱ እራሷን እንድትችል ሳይሆን የነርሱ ጥገኛ እንድትሆን ነበር ያደረጉት፣ ለዚህ ሲሉ አብዛኛው ምርት ከውጭ ያስመጡ ነበር። ከ10-15% የሚሆነው የአገሬው ወንድ ሃይል በኢንደስትሪ፣ በእርሻና በጥቃቅን የተላላኪ ስራወች ተቀጥርው ይሰሩ ነበር። ከ1936-41 ድረስ አብዛኛውን የአግሬውን ወንድ ቀጥሮ ያሰራ የነበረው የቅኝ ገዥው ውትድርና ተቋም ነበር (40% ወይም 60፣000 ለአቅመ አዳም የደርሱ ወንዶችን)። እኒህ ወታደሮች ኢትዮጵያን ለመውረር ያገለገሉ ሲሆን ለዚህ ታማኝነታቸው ምክንያቱ ቅኝ ገዥወች በኤርትራ ላይ ያሰፈኑት ፖለቲካዊ መረጋጋት እንደምክንያት ይጠቀሳል። የጤና፣ የገበያ ኢኮኖሚ እንዲሁም ቁሳዊ ፍጆታ መስፋፋት በ1905ዓ.ም. 250 ሺህ ብቻ የነበረው የኤርትራ ህዝብ ወደ 614 ሺሕ በ1935 ዓ.ም. እንዲያድግ አድርጓል። ትግርኛ ተናጋሪው ክፍል በዚህ ጊዜ 54% የአገሪቱ ክፍል ነበር። እኒህ ለውጦች በአገሬው ላይ የስነ ልቦና ለውጥን አስከተሉ፣ ስለሆነም ከኢትዮጵያውያን ጐረቤቶቻቸው የተለዩ ህዝቦች የመሆን ማንነትን ፈጠረ። ሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ እንግሊዞች ከአንግሎ ግብጻዊ ሱዳን በመነሳት ጥር 1941 በኤርትራ ላይ ጥቃት አደረሱ። ከሶስት ወር በኋላ የከረን ጦርነትን በማሸነፍ ሚያዝያ 1941 ሙሉ ኤርትራን ተቆጣጠሩ። የእንግሊዝ ወታደራዊ አገዛዝ(BMA) በጣሊያኖች ምትክ አገሪቱን ማስተዳደር ጀመረ። 1947 ጣሊያን በፈረመችው የሰላም ውል መሰረት ኤርትራ ለአራቱ ሃይላት ተሰጠች። ከዚህ በኋላ ኤርትራ የጣሊያን ቅኝ መሆኗ አበቃላት። \n \nጥያቄ: የእንግሊዝ ጦር በኤርትራ ያለውን የጣልያን ጦር አሸንፎ ሀገርቷን የተቆጣጠረው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1941 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ትዳር የመሰረቱት ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከወይዘሮ የሺ እመቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: ዋዝንቢት ድምጽ የሚወያወጣው እንዴት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ክንፎቹን በማፋተግ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: በናይጄሪያ ትልቁ ተራራ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቻፓል ዋዲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሚገኝበት ልሳነ ምድር ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በካፕ-ቨርት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በ84ኛው የየካቲት 12 ሰማዕታት መታሰቢያ ቀን ላይ በመገኘት የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል። በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የአባት አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ተገኝተዋል። በሰመዕታት መታሰቢያ ቀን የካቲት 12 ቀን በየአመቱ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፤አባት አርበኞች፤ እና የህብረተሰብ ክፍሉ በስድስት ኪሎ ታስቦ ይውላል፡፡ \n \nጥያቄ: ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን አባት አርበኞች ማህበር ውስጥ በምን ኃላፊነት ላይ ይገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፕሬዚዳንት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፍሬምናጦስ የተወለዱት ታይር በምትባል ቦታ በምሥራቃዊ የሮማ ነገሥት በ፬ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያዎቹ ሲሆን ማንም መርምሮ ሊደርስበት በማይችለው በእግዚአብሔር ሀሳብ ወደ ኢትዮጵያ መተው ክርስትናን ከመሠረቱት ዋነኛው አባት ሆኖ በመቆጠር ፣ አገራችንን ከሌሎች ክርስቲያን አገሮች ጋር ያስተዋወቁ ፣ ያስተካከሉ ፣ በአክሱም ዘመነ መንግሥትና መንግሥት የተወደዱና የተከበሩ ፣ በመላው ኢትዮጵያ የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የተከበሩ ታላቅ አባት ናቸው ። አባታችን ፍሬምናጦስ የ፲፪ ዓመት ልጅ እያለ ሜሮጵዮስ የተባለ ነጋዴ ፈላስፋም የነበረ መርከበኛ ይዞት ወደ አገራችን መጣ ። ከእርሱም ጋር ወንድሙ ኤድስዮስ የተባለም አብሮት እንደነበረ ይታወቃል ። እነዚህን ሁለት ወጣቶች አስከትሎ የመጣው ሜሮጵዮስ በቀይ ባሕር አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች በጣሉለት አደጋ በዚሁ እንደ ሞተ ታሪክ ይነግረናል ። ይህም በንጉሥ ዒዛና ዘመነ መንግሥት ሆነ ። ፍሬምናጦስና ኤድስዮስ ግን በወቅቱ የአክሱም ንጉሥ የነበረው ንጉሥ ታዜር ጋር አድገዋል ። ንጉሡ በአእምሮ መብሰላቸውን ተመልክቶ ፍሬምናጦስ በጅሮንድ ኤድስዮስም ጋሻ ጃግሬው አድርጎ ሾማቸው ። ከዚያ በኋላ ንጉሥ ታዜር ሲያርፍ ወደ ፈለጉበት እንድሄዱ ነፃ ስለተለቀቁ ኤድስዮስ ወደ አገሩ ተመልሶ ሄዷል ። አባታችን አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ግን ወንድሙን ሸኝቶ \"በጨለማ የሚኖረውን ሕዝብ ትቼ ወደ አገሬ አልመለስም\" በማለት የኢትዮጵያን ሕዝብ በማፍቀር እንደቀረ ታሪክ ያስረዳናል ። የቅዱሳን ፍቅራቸው እውነትም ልብ ይነካል ። በዚያን ዘመን በአገራችን ኢትዮጵያ ክርስትና ነገሥታቱ የታወቀ ቢሆንምኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ስርዓተ ንስሐ ፣ ስርዓተ ጥምቀት ፣ ስርዓተ ቅዳሴ ፣ ስርዓተ ቅዱስ ቁርባን የሚያከናውን ጳጳስ ስላልነበረ ይህን የተመለከቱ ነገስታት ኢዛናና ሳይዛና ጵጵስና እንዲያመጣ አባታችን አቡነ ሰላማን ወደ ግብጽ ላኩት ። አባታችንም ወደ ግብጽ በመሄድ ስርዓቶቹን በመማር በቅዱስ አትናትዮስ አንብሮተ እድ \"ኤጲስ ቆጶስ ዘአክሱም ወዘኩላ ኢትዮጵያ\" ተብሎ ጵጵስና ተቀበለ። \n \nጥያቄ: አባ ፍሬምናጦስ የስንት ዓመት እድሜ እያሉ ወደ ኢትዮጵያ መጡ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የ፲፪ ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቅልልቦሽ ቅልልቦሽ የኢትዮጵያ ህጻናት በጠጠር የሚጫወቱት ሲሆን አጨዋወቱም አንዱዋን ጠጠር ወደአየር በማጉናት እሱዋ ባየር ላይ እያለች የተቻለን ያክል ጠጠር ከመሬት ማፈስ ነው። ባየር ላይ ያለችው ጠጠር ስትመለስ በተጫዋቹ እጅ \"መቀለብ\" ወይም \"መያዝ\" ይኖርባታል። ሳትያዝ መሬት ላይ ከወደቀች፣ ጨዋታው አለቀ ማለት ነው። ጨዋታው \"ጠጠር\" በመባልም ይጠራል። ብዙ አይነት የቅልልብልቦሽ ጨዋታዎች ሲኖሩ፡ በጣም የታወቀው \"ዓይጥ አለብሽ\" በመባባል የሚጫወቱት ነው። ልጆቹ ሁለት ወይም ሶስት ይሆኑና፡ አምስት ቆንጆ ድብልብል ጠጠሮች፡ ስፋትና ርዝመታቸው ከግማሽ ኢንች የማይበልጡ፡ ይለቅሙና መሬት ይቀመጣሉ። ቀድሞ \"ብጀ\" ያለ መጀመርያ ይጀምራል። ብጀ ማለት ብጀምር ማለት ነው። ያንን ለማለት እሽቅድምድም ነው።\"ብቀ\" ያለ ከርሱ የሚከተል ነው ማለት ነው፡፡ ብቀ ማለት ብቀጥል ማለት ነው። ሁለት ልጆች እኩል \"ብቀ\" ካሉ በድምጽም ቢሆን ቀድሞ \"ብ!\" ከአፉ የወጣው ሰው ሁለተኛነቱን ያገኛል። \"ብቀጣጥል!\" ያለ ሶስተኛ ነው። \"እንጀራ ብጋግር!\" ያለ አራተኛ ነው። አምስተኛ ካለ \"ወጥ ብሰራ!\" ብሎ ተራውን ያሳውቃል። በዚህ ተራ ተስማምተው ጀማሪው ይጀምራል። \n \nጥያቄ: በቅልብልቦሽ ጨዋታ ብቀ ማለት ምን ማለት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ብቀጥል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየሆሊውዱ የፊልም ኩባንያ ዋርነር ብሮስ የቦክስ ኦፊስን የደረጃ ሰንጠረዥ በሰው ሰራሽ መሳሪያ (አርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ) መገመት ሊጀምር መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ሰው ሰራሽ መሳሪያው ዋርነር ብሮስ የሚያዘጋጃቸው ፊልሞች ምን ያህል ስኬታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ ግምቱን ያስቀምጣል ተብሏል፡፡ ይህ አሰራር የተዋናይ አመራረጥን፣ የማከፋፈሉን ሂደት እና የሚለቀቅበትን ጊዜ መነሻ በማድረግ ትርፋማነቱን ይገመግማል ነው የተባለው፡፡ በሆሊውድ መንደር ከስድስት ትልልቅ የፊልም ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ዋርነር ብሮስ ይህን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ከኤልኤ ስታርት አፕ ሲኔለይቲክ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ የመገመቻ መሳሪያው ባለፈው ዓመት ይፋ የሆነ ሲሆን ለዘርፉ አዲስ ይዘት እና አሰራርን ይዞ መምጣቱ ሲኔለይቲክ በድረ ገፁ አስነብቧል፡፡ መሳሪያው የተለያዩ መረጃዎችን በመጠቀም የቦክስ ኦፊስ የደረጃ ሰንጠረዥን በትክክል እንደሚገምት ተጠቁሟል፡፡ አንዱ የዚህ መሳሪያ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ተዋንያን የሚመርጡበት ሂደት እንዴት በፊልሙ ትርፋማነት ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳድር መመልከት እንዲችሉ ያደርጋል ነው የተባለው፡፡ ምንጭ፡-ስካይ ኒውስ \n \nጥያቄ: የሆሊውዱ የፊልም ኩባንያ ዋርነር ብሮስ በሰው ሰራሽ መሳሪያ (አርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ) ለማስገመት ያሰበው ምንን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የቦክስ ኦፊስን የደረጃ ሰንጠረዥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: በግራኝ መሃመድ ወረራ ወቅት ኢትዮጵያ ከማን ጋር ግንኙነት ፈጠረች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከፖርቱጋሎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: ለበዛብህ የወላጆቹን ሞት ማን ነገረው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: የፍቅር እስከ መቃብር የታሪኩ ይዘት ምን አይነት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: ዝናሽ ማሞ ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nንጉሡ ላሊበላ የሚለውን ስም ያገኘው፣ ሲወለድ በንቦች ስለተከበበ ነው ይባላል። ላል ማለት ማር ማለት ሲሆን፤ ላሊበላ ማለትም -ላል ይበላል (ማር ይበላል) ማለት አንደሆነ ይነግራል። ውቅር ቤተክርስቲያናቱን ንጉሡ ጠርቦ የስራቸው ከመላእክት እገዛ ጋር እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ይነግራል። በ16ኛው ከፍለ ዘመን አውሮፓዊ ተጓዥ ላሊበላን ተመልክቶ «ያየሁትን ብናግር ማንም እንደኔ ካላየ በፍጹም አያምነኝም» ሲል ተናግሮ ነበር። በላሊበላ 11 ውቅር ዐብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ (ባለ መስቀል ቅርፁ) ሲታይ ውሃልኩን የጠበቀ ይመስላል። ቤተ መድሃኔ ዓለም የተባለው ደግሞ ከሁሉም ትልቁ ነው። ላሊበላ (ዳግማዊ ኢየሩሳሌም) የገና በዓል ታህሳስ 29 በልዩ ሁኔታ ና ድምቀት ይከበራል፣ \"ቤዛ ኩሉ\" ተብሎ የሚጠራው በነግህ የሚደረገው ዝማሬ በዚሁ በዓል የሚታይ ልዩ ና ታላቅ ትዕይንት ነው።የሚደረገውም ከቅዳሴ በኋላ በቤተ ማርያም ሲሆን ከታች ባለ ነጭ ካባ ካህናት ከላይ ደግሞ ባለጥቁር ካብ ካህናት በቅዱስ ያሬድ ዜማ ቤዛ ኩሉ እያሉ ይዘምራሉ። 11ዱ የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት ቤተ መድሃኔ ዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ደናግል፣ ቤተ መስቀል፣ ቤተ ደብረሲና፣ ቤተ ጎለጎታ፣ ቤተ አማኑኤል፣ ቤተ አባ ሊባኖስ፣ ቤተ መርቆሬዎስ፣ ቤተ ገብርኤል ወሩፋኤል፣ ቤተ ጊዮርጊስ ናቸው። \n \nጥያቄ: በላሊበላ ስንት ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 11 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: ጾመ ነብያት መቼ ይጀምራል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኅዳር ዐሥራ አምስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ የንዴቤሌም ቋንቋ በተናጋሪ ብዛት ስንተኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 11ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና የክርስቲያኖች ብዛት በመቶኛ ምን ያህል ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 70% ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: የአዲስ ዘመን ጋዜ በሳምንት አንድ ቀን ከመታተም ወደ ስድስት ቀን እንዲያድግ የተደረገው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: አባይ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ግዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዩጋንዳ የምትገኘው የት አህጉር ውስጥ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nግሪክ ግሪክ ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋ አንድ ትንሽ አገር ነው። ከምሥራቅ ወደ ትንሽ እስያ፤ ከምዕራብ ወደ ኢጣሊያ አገር ከሁለቱም ወገን ርቀቱ ትክክል ነው። ግሪክ በሰሜን ወገን ከመቄዶንያ ይዋሰናል። ግሪክ ኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው። በደቡብና በምሥራቅ ወገን አያሌ ደሴቶች አሉ። ከእነርሱም በአያሌዎቹ መንደሮችና ከተሞች ተሠርተውባቸዋል። አንዱ አንቲፖሮስ ይባላል። በእዚህም ስፍራ ያለው ታላቅ ያጌጠ ዋሻ የታወቀ ስመ ጥሩ ነው። እኩሌቶቹም የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እየተወረወሩ የወጡ ይመስላሉ። እኩሌቶቹም ከጥንት ጀምረው ይታዩ የነበሩት ያሉበት አይታወቅም ጠፍተዋል። ይህ እንግዳ ነገር እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ከባሕር በታች የተነሳው እሳተ ገሞራ ነው። በደቡብ ግሪክ ወገን ባሉት ደሴቶች አየሩ በአሜሪካ እንዳለው እንደ ቨርጂኒያ ግዛት አየር ቀላል ነው። በዚህ አገር ብዙ አይነት ፍሬ ሁሉ ሞልቶዋል። በሰሜን በኩል ደግሞ አየሩ ቅዝቃዜ ያለበት ነው። በየጠረፉ የመርከብ መቋሚያዎች ወደቦች ይገኛሉ። ብዙዎቹ የአገሩ ሰዎችም መርከበኞች ናቸው። በደኑም ፓይን (ጥድ) የተባለው ጠንካራ ዛፍ ይገኛል። በላይኛው አውራጃ ኦክ የተባለው ዛፍ ይገኛል። ወደታች ባለው ክፍልም ቸስትነትና ዋልነት የሚባሉት ዕንጨቶች ይገኛሉ። በዚህ ስፍራ የሚገኘው ዋናው ነገር ደረቅ ፍራፍሬ፣ ዘቢብ፣ ጥጥ፣ ሐር ጠጉር፣ ሩዝ፣ ትንባሆና በቆሎ ነው። የእጅ ሥራ ጥቂት ነው። በቤት የተለመደ ሥራ እንደ ጥጥ እንደ ጠጉር እንደ ሐር የመሰለ ነገር ነው። ቀለም ማግባት ወይም መቀባት በጣም የተለመደ ከሆነ ብዙ ጊዜው ሆነው። ከዛፎች ፍሬ ዋነኛው ወይራ ሲሆን በብዛት ይተከላል። ወይን፣ በኽረ? ሎሚ፣ በለስ፣ አልሞንድ (ለውዝ)፣ ተምር፣ ሴትሮን፣ ፓሜግራኔት (ሮማን)፣ ኩሬንትም ይበቅላሉ። \n \nጥያቄ: ግሪክ በግዘቷ ውስጥ አያሌ ደሴቶቿ በየትኛው ወገን ይገኛሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በደቡብና በምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት ላይ በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስቱ ፍላጻዎች ምንን ይወክላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nክሻትሪያ ክሻትሪያ የህንዳውያን ኅብረተሠብ በተለያዩ 4 መደባት የሚከፋፈልበት አንዱ የህብረተሰባዊ ክፍል (ካስት) ነው። በዚህ አከፋፈል ዘዴ የወታደሮችና የገዢዎች ክፍል እሱ ነው። ክሻትሪያ ከብራህሚን (ቄሳውንትና አስተማሮች) በታችና ከቫይስያ (ነጋዴዎች) እንዲሁም ከሹድራ (ሠራተኞች፣ አገልጋዮች) በላይ ሆኖ ይቆጠራል። በመጀመርያ በጥንት ይህ ደረጃ በሰው ችሎታ፣ ተግባርና ጸባይ ምክንያት ሊገኝ የቻላ ሲሆን፣ በዘመናት ላይ ግን የተወረሰ ማዕረግ (በዘር የሚዛወር) ብቻ ሆነ። በአንዳንድ ወቅት ደግሞ የክሻትሪያ (መኳንንት) ክፍል ከብራህሚኖች (ቄሳውንት) ክፍል ይልቅ ላየኛነቱን ይይዝ ነበር። ብራህሚኖችም በኋላ የበለጡት ከትግል በኋላ እንደ ሆነ ይታመናል። የቃሉ ሥር በሕንዳዊ-ኢራናዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ «*ክሺ» 'መግዛት' ሲሆን ለዚሁ ብዙ የተዛመዱ ቃሎች (እንደ ሳንስክሪት «ክሻትራ» 'ግዛት') ይኖራሉ። በጥንታዊ ፋርስኛ በኩል «ሕሻጥራ» ማለት 'ሃይል፣ መንግሥት' ነበረ፤ የ«ሕሻያጢያ» ትርጉም የፋርስ ንጉሠ ነገስት ሆኖ ከዚህ በዘመናዊ ፋርስኛ ንጉሥ ሻህ ይባላል። በአማርኛ፣ ቼዝ (ሰንጠረዥ) የሚባል ጨዋታ ስም ከዚህ የመጣ ነው። በተጨማሪ በፋርስ ታሪክ የጠቅላይ ግዛት ወይም አገረ ገዥ ማዕረግ «ሕሻጥራ-ፓዋ» (የግዛት ጠባቂ) በኋላ «ሳትራፕ» ሆነ። ሌሎች ቃላት በታይላንድኛ «ካሳት» 'ንጉስ' በመላይኛም «ሳትሪያ» 'ጀግና' ከ«ክሻትሪያ» የተነሡ ናቸው። \n \nጥያቄ: የህንዳውያን የወታደሮችና የገዢዎች ክፍል ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ክሻትሪያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. መሠረቱ። ከምዕራቡ ሮማ መንግሥት ውድቀት ደግሞ ወደ ተረፈው ሕዋእ ውስጥ ከፈለሱት ጀርመናውያን ወገኖች አብዛኛው የራሳቸውን ሕጎች ዝርዝር በጽሑፍ አወጡ። በተለይ የሚታወቁም የቪዚጎቶች አለቃ ዩሪክ ሕግ (463 ዓ.ም.)፣ የቡርጎንዳውያን ሕግጋት (እኚህ ለጀርመናውያንና ለሮማውያን የተለያየ ፍትሕ ነበራቸው)፣ የአላማናውያን ሕግጋትና፣ የፍራንኮች ሕግጋት ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ የተጻፉት ከ492 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በ498 ዓ.ም. የቪዚጎቶች አለቃ 2ኛ አላሪክ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስና አንዳንድ የተለያዩ የቀድሞ ሮማ ሐገጋት አከማችተው አዋጁአቸው። ከዚህም በኋላ የታዩ ሕጎች የሎምባርዶች ሕግጋት (635 ዓ.ም.)፣ የቪዚጎቶች አዳዲስ ሕግጋት (646 ዓ.ም.)፣ የአላማናውያን አዳዲስ ሕግጋት (722 ዓ.ም.) እና የፍሪዝያውያን ሕግጋት (777 ዓ.ም.) አሉ። በአውሮፓ አኅጉር ላይ የተጻፉት እነኚህ ፍትሖች ሁሉ በሮማይስጥ ቢጻፉም፣ በእንግሊዝ አገር ግን የተጠቀሙት ሕጎች ከኬንት ንጉሥ ኤጠልቤርት ሕጎች (594 ዓ.ም.) ጀምሮ በጥንታዊ እንግሊዝኛ የተቀነባበሩ ነበሩ። በ885 ዓ.ም. ታላቁ አልፍሬድ ይህንንና ሁለት የድሮ ፍትሖች ከሕገ ሙሴና ከሕገ ወንጌል ጋራ አጋጥመው የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ዶም ቦክ ሠርተዋል። \n \nጥያቄ: በሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት በ264 አክልበ. የታወጀው ሕግ ምን በመባል ይታወቅ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የአሾካ አዋጆች ሕግጋት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሥነ ቁጥር ሥነ ቁጥር ወይንም በእንግሊዝኛ \"አርቲሜቲክስ\" ከሁሉ የሒሳብ ዘርፎች አንጋፋውና በሁሉም ሰው ጥቅም ላይ የሚውል ክፍል ነው። ሥነ ቁጥር የቁጥሮችን ቅልቅል ውጤት የሚያጠና ሲሆን ብዙ ጊዜ ቁጥሮች ሲደመሩ፣ ሲቀነሱ፣ ሲባዙና ሲካፈሉ የሚያሳዩትን ባህርይ ይመረምራል። ሒሳብ ተማሪዎች የቁጥር ኅልዮት ውጤቶችን ከፍተኛ ሥነ ቁጥር በማለት ከለተ ተለት መደመርና መቀነስ ጥናቶች ይለዩዋቸዋል። የሰው ልጆች ከጥንት ጀምሮ ሥነ ቁጥርን ተጠቅመዋል። ለምሳሌ አፍሪቃ ውስጥ የተገኘ 22፣000 ዓመት እንዳለው የሚቆጠር የአጥንቶች ቁርጥራጭ ለመቁጠርና ለመደመር ያገለግል እንደነበር ይጠቀሳል። በኋላም የግብጽ እና ባቢሎን ሰወች ቁጥርን መጻፍ እንደጀመሩና ይህን ፈጠራቸውን ለመደመርና ለመቀነስ እንደተገለገሉበት አሁን የተገኙ ቅርሶች ያስገነዝባሉ። የግብጽን የአጻጻፍ ስልት የተከተሉ ግሪኮችም በዩክሊድ እና ሌሎች የግሪክ ተማሪዎች አማካይነት ጥናቱን ለማሳደግ ችለዋል። ሆኖም እስከዚህ ዘመን የነበረው የቁጥር አጻጻፍ ስልት አቀማመጣዊ አልነበረም። ስለሆነም ለመደመርና ለመቀነስ፣ በተለይ ደግሞ ለማባዛትና ለማካፈል እጅግ የተወሳሰበና አሰልቺ ነበር። የሒሳብና የሥነ ቁጥር እድገት ከፍተኛ እመርታ ያሳየው ሕንዳውያን ተማሪዎች ዜሮና አቀማመጣዊ አጻጻፍ ስልትን በ4ኛው ክፍለዘመን ሲፈለስፉ ነበር። ይህም አሁን በመላው አለም የሚሰራበት ህንዲ-አረብ ቁጥር (ማለቱ፡ 0 1 2 3 4 5 6 7 8 9 ) እንዲፈጠር አደረገ። ፊቦናቺ የተሰኘው የጣሊያን ነጋዴ የዚህን ድንቅ ቁጥር ቀመርና ጥቅም በመጽሐፉ በ1202 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) በመጻፍና በአውሮጳ አገራት ሁሉ በማሰራጨት ታዋቂነቱ እንዲገን ሆነ። የህንዲ-አረብ ቁጥር ስርዓት በጣም ቀላል ከመሆኑ የተነሳ የሒሳብ ትምህርት በአውሮጳ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አደረገ። ይሄው አዲሱ ስልት ለሒሳብ ጥናት መሰረት በመሆን የጥንቶቹን ሒሳብ ተማሪዎች ድንቅ ውጤቶች ከአዲሱ ስርዓት ጋር ሲነጻጻሩ እምብዛም ሆነው እንዲታዩ አደረጉ። የሂንዲ አረብ ቁጥር ስርዓት ለዘመናዊው የሒሳብ ትምህርት መነሳት ምክንያት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። \n \nጥያቄ: የሒሳብና የሥነ ቁጥር እድገት በስንተኛው ክፍለ ዘመን በጣም አደገ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ4ኛው ክፍለዘመን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሊቢያ ኦይል ሊሚትድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ ሥራ ለማስፋፋት መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ዱባይ ከሚገኘው የሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ ዋና መሥሪያ ቤት ወደ አዲስ አበባ የመጣው ኮርፖሬት ማኔጅመንት፣ ከሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል የአንድ ሳምንት ጉባዔ አካሂዷል፡፡ ከ18 የአፍሪካ አገሮች የሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ የሽያጭና ማርኬቲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካሪያስ ወሊቃ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ማኔጅመንቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ዕድገት በመገምገም ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ እንቅስቃሴ ለማስፋፋት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ካፀደቁት ኢትዮጵያ ውስጥ የ150 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ለማካሄድ አቅዷል፡፡ \n \nጥያቄ: የ18 የአፍሪካ ሀገራት ሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች የተሳተፉበት ውይይት በየት ተካሄደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: የላይቤሪያ ዋና ከተማ ስም ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሞንሮቪያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና በአፍሪካ በየትኛው ክፍል ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በደቡባዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና ከዚምባብዌ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሰሜን ምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመስከረም 21/2012 ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚ) ህብረት ሲንፖዚየምን ልታስተናግድ ነው። ሲምፖዚየሙ ከመጪው ሳምንት ማክሰኞ መስከረም 27 ቀን 2012 ዓም ጀምሮ ለአራት ቀናት የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጰያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንሲቲትዩት ዛሬ ለኢዜአ ገልጿል። ከጥንታዊ ሳይንሶች አንዱ የሆነው ሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚ) ከመሬት ከባቢ አየር ውጪ የሚገኙ ክስተቶችን የሚያጠና የሳይንስ ክፍል ሲሆን ፀሐይ፣ የከዋክብትና የጨረቃዎች ስርዓት ማለት ነው። ሲንፖዚየሙ የኢትዮጰያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንሲቲትዩት፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ከምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባባሪያ ጽህፈት ቤት ጋር በጋራ በመሆን እንደሚካሄድ ተገልጿል። በምስራቅ አፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ አበባ ውስጥ የሚካሄደው ሲንፖዚየም ከ30 አገራት የተውጣጡ ወደ 160 የሚደርሱ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያውያን ተመራማሪዎችና ባለ ድርሻ አካላት ይሳተፉበታል። ሲንፖዚየሙ በአገሪቱ መካሄዱ በስፔስ ሳይንስ ዘርፍ ላይ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ልምድ ለማግኘት እድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል። አለም አቀፍ የሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚካል) ህብረት 100ኛ ዓመት እየተከበረ እንደሚገኝም ተገልፇል። ዓመቱ በኢትዮጵያም ስለየሥነ ፈለክ ሳይንስ ግንዛቤ በሚፈጥሩ ዝግጅቶች እየተከበረ መሆኑን ነው መግለጫው ያመለከተው። ሲንፖዚየሙ ከመካሄዱ በፊት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2ኛና 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች እና በአስር የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዙ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች እንደሚሰጡም ተገልጿል። ከሲንፕዚየሙ ቀጥሎም ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን ስልጠና እንደሚሰጥም እንዲሁ። ከሲንፓዚየሙ ጎን ለጎን የሥነ ፈለክ ሳይንስ በአፍሪካ እንዲያድግ ስትራቴጂ ይቀረጽበታል ተብሎ የሚጠበቅ የአፍሪካ የሥነ ፈለክ (አስትሮኖሚካል) ማህበር ውይይት እንደሚካሄድም ተገልጿል። ውይይቱ የሥነ ፈለክ ሳይንስ በአፍሪካ ያለውን ተደራሽነት ለማስፋት እንደሚያስችልም ነው የተጠቀሰው።   \n \nጥያቄ: የሥነ ፈለክ አለምአቀፍ ህብረት ስንተኛ ዓመቱን እያከበረ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 100ኛ ዓመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የመጀመሪያ ትምህርት በየት ትምህርት ቤት ተማሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በዳግማዊ ምኒልክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: ፍቅር እስከ መቃብር በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ መቼ ቀረበ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና ከናሚቢያ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በምዕራብና ሰሜን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየአመራር ክፍሎች ናይጄሪያ በሠላሳ ስድስት ክፍላገራት እና አንድ የፌዴራል ግዛት ተከፍላለች። እነዚህ ክፍላገራት ወደ ፯፻፸፬ የአካባቢ ግዛቶች ተከፍለዋል። ስድስት የናይጄሪያ ከተሞች ከአንድ ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች አሉባቸው። እነዚህም ሌጎስ፣ ካኖ፣ ኢባዳን፣ ካዱና፣ ፖርት ሀርኮርት እና ቤኒን ከተማ ናቸው። ሌጎስ ከ፰ ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሲኖሩባት ከሣህራ በታች በአፍሪካ ትልቁ ከተማ ናት። ብሔረሰቦች በናይጄሪያ ውስጥ ከ፪፻፶ በላይ ብሔሮች ይገኛሉ። ትልቆቹ ብሔሮች ፉላኒ ወይም ሀውዛ፣ ዮሩባ እና ኢግቦ ናቸው። ከእነሱ ቀጥሎ ደግሞ ኤዶ፣ ኢጃው፣ ካኑሪ፣ ኢቢብዮ፣ ኑፔ እና ቲቭ ይገኛሉ። በናይጄሪያ ውስጥ የተቆጠሩት ቋንቋዎች ፭፻፳፩ ይሆናሉ። ከእነዚህም ውስጥ ፭፻፲ቹ መደበኛ ተናጋሪዎች አሏቸው። ሁለት ቋንቋዎች እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ብቻ ነው የሚነገሩት። ዘጠኙ ደግሞ ተናጋሪ የሌላቸው የጠፉ ቋንቋዎች ናቸው። ከእንግሊዝኛ በኋላ ዋናዎቹ ልሳናት ዮሩብኛ፣ ሐውዝኛና ኢግቦኛ ናቸው። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ ምን ያህል ብሔሮች አሏት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ፪፻፶ በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \n67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ አንጋፎቹ ገጣሚያን ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ዶ/ር ሙሉአለም ተገኝወርቅ፣ መርድ ተስፋዬና ቤዛ ትዕዛዙ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ዲስኩር እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ \n \nጥያቄ: በ67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት ላይ ዲስኩር የሚያቀርቡት ማናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አቶ አበባው አያሌው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በኒው ዮርክ የመጀመሪያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ መች ተከፈተ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በጥር 1928 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኮምፒዩተር ኮምፕዩተር ማለት ማንኛውንም ኢንፎርሜሽን ፕሮሰስ የሚያደርግ ማሽን ነው። ይህንም የሚያደርገው በተርታ የተቀመጡ ትዕዛዞች በመፈጸም ነው። ለብዙ ሰዎች ኮምፒዩተር ሲባል ዐዕምሯቸው ላይ የሚመጣው የግል (ፐርሰናል) ኮምፒዩተር ነው። ነገር ግን ኮምፒዩተር ሲባል በጣም ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። ላፕቶፕ ፣ ዴስክቶፕ ፣ ማይክሮ-ኮምፒዩተር ፣ ሱፐር-ኮምፒዩተር ፣ ካልኩሌተር ፣ዲጂታል ካሜራ እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ቀድሞ አስሊ ማለት አንድ በሒሳባዊ ትዕዛዝ የተለያዩ የጥንት መሣሪያዎችን እየተጠቀመ ቁጥሮችን የሚያሰላ ሰው ነበር። እስከ 20ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የተለያዩ ጠቃሚ መሣሪያዎች ተሰርተዋል። ከዛ በኋላ ትልልቅ ማሸኖች መሠራት ጀመሩ። እነዚህ ማሽኖች ከዛሬው ኮምፒዩተሮች(አስሊዎች) ጋር ሲወዳደሩ በጣም ትልቅና ቀርፋፋ ናቸው። የኮምፕዩተር የውስጥ ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1.ሞኒተር - የምንሰራውን ነገር እንዲያሳየን፤ምስል፣ጽሑፍ፣ ቪዲዮ ወይም ማንኛውም ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ሞኒተር 14 ኢንች፣ 15 ኢንች፣ ወዘተ. እየተባለ ይገላጻል፡፡ 2.ማዘርቦርድ - እናት ሰሌዳ ሁሉም የኮምፕዩተር ክፍሎች(ዕቃዎች)የሚቀዳጁበት 3.ሲፒዩ - የኮምፕዩተሩ አእማሮ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሲፒዩን ከሰው አእምሮ ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ 4.ሜሞሪ - የምንሰራውን ስራ ወይም ፋይል በጊዚያዊነት አስቀምጠንበት የምንሰራበት፡፡ ሜሞሪበባይት (Bytes) ይለካል፡፡ ከ Bytes ፊት Kilo፣ ማለትም ኪሎባይት (kilobytes)([1,024 ባይቶች ወይም Bytes ማለት ነው፡፡ ] ፣ Mega[1,048,576 ባይቶች ወይም Bytes ] ፣ Giga [1,073,741,824 ባይቶች ወይም Bytes]፣ ወዘተ የሚሉትን ቃላት በመጠቀም ኪሎባይት(kilobyte)፣ ሜጋባይት (megabyte)፣ ጊጋባይት (gigabyte) እያልን የኮምፒዩተር ሜሞሪ መግለፅ እንገልጻለን፡፡ ለምሳሌ 10 MegaBytes ወይም ባጭሩ ሲጸፍ 10MB ይህ ማለት 10,485,760 Bytes ይሆናል ማለት ነው፡፡ 5.ኤክስፓንሽ ስሎት 6.የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረቢያ (power supply) 7.የሲዲ ማሰሪያ (cd drive) 8.ሀርድ ዲስክ (የምንሰራውን ወይም የምንጠቀምበትን ፋይል በቋሚነት ለማስቀመጥ) 9. መሎጊያ (ማውስ) 10.የፊደል ገበታ (ኪቦርድ) የመጀመሪያቹ ኮምፕዩተሮች የሚሠሩት በእንግሊዝኛ ፊደል ብቻ ነበር። ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ኣገሮች ሊቃውንት በየራሳቸው ፊደላት እንዲሠሩ ኣደረጉ። ኮምፕዩተር በእያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኣበራ ሞላ ነው። በቅርቡም አያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት ዩኒኮድ የሚባል የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ መግባት ቀጥሏል። \n \nጥያቄ: በኮምፒዩተር ውስጥ መረጃን በቋሚነት ለማጠራቀም የሚጠቅም የኮምፒዩተሩ ክፍል ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሀርድ ዲስክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ በዩጋንዳ ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 150,000 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የከተማዋ የአየር ንብረት ምን አይነት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል። ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ። \n \nጥያቄ: ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ የትኞቹን የእምነት ተከታዮት ወደ ክርስትና መለሱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሶቪዬት ሕብረት ሶቭየት ሕብረት ሰብአዊ ሪፐብሊክ በ፲፱፻፲ ዓ.ም. የተከሰተውን የሩሲያ አብዮት ፍንዳታ፤ እንዲሁም ያንን ተከትሎ ለሦስት ዓመታት የተከናወነውን የሩሲያ «ውስጣዊ ሕዝባዊ የርስ በርስ ግጭት» ተከትሎ በኅብረተስብአዊ ሕገ መንግሥት (socialist constitution) በአራት ሪፑብሊኮች ቅንብርነት የተመሠረተ አገር ነበር። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ከቀድሞው የናዚ ጀርመን እጅ የተወሰዱ አገሮችን በማቀላቀል እንዲሁም በ፲፱፻፵፱ ዓ.ም በጉልበት ሌሎች የምሥራቅ አውሮፓ አገሮችን በመቀላቀል ኅብረቱ ዓሥራ ስድስት ሪፑብሊኮችን ያካተተ ነበር። በዘመን ቆይታና በጥንካሬም የጎለበተ ሕዝባዊ አብዮታዊ የኅብረት ሪፑብሊክ በመሆኑም በተለይ በ«ቀዝቃዛ ጦርነት» በሚባለው በ«ምዕራብና በምሥራቅ» ዓለም ተከስቶ በነበረው ፍጥጫ ጊዜ፣ በዓለም ላይ ለሚመሠረቱ ሕዝባዊ መንግሥታት ዋና የሽከታ አርአያ የነበረ መንግሥት ነበር። በ ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጀምሮ ይሄ ኅብረት እስከፈረሰበት እስከ ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ድረስ በተካሄደው የ«ቀዝቃዛ ጦርነት» ዘመን የሶቪየት ኅብረት በዓለም ከነበሩት ሁለቱ ተቃራኒ ኃያላን መንግሥታት አንዱ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም ላይ በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም የተመሠረተውን የአብዮት ወታደራዊ የደርግ መንግሥት በጦር መሣሪያ፤ በአማካሪነት፤ በገንዘብ፤ ወዘተረፈ፤ ዋነኛ ደጋፊና ታላቅ ተዋናይ አገር ነበር። የቀድሞው የሶቪዬት ኅብረት መጨረሻ ላይ ታኅሣሥ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም ተደምስሶ በዓለም መንግሥታት እውቀትና ስምምነት ሕጋዊ ወራሽነት የሩሲያ መንግሥት እንደሆነ ታወጀ። ሩሲያም በዚህ መሠረት የቀድሞውን የሶቪዬት ሕብረት የውጭ ዕዳዎች እንዲሁም የውጭ ንብረቶች በፈቃዱ ተቀበለ። በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ተፈርመው የነበሩም ዓለም አቀፍ ስምምነቶችንም ሩሲያ መቀበሏን አስታውቃለች። \n \nጥያቄ: የሶቪየት ሕብረት ሰብአዊ ሪፐብሊክ መቼ ተመሰረተ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ፲፱፻፲ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: ሮማውያን 12ቱ ሰንጠረዦች የተሰኘውን ሕጋቸውን መች ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጡት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ457 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: የዛሬዋ ቱርክ ይህን ስሟ ከማግኘቷ በፊት ትጠራበት የነበረው መጠሪያ ስሟ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ካሩም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየባሕል ጥናት የባህል ጥናት፣ ሥነ ኅብረተሠብ ወይን ሥነ ማኅበረሰብ ሌላ ስሙ ሶሲዮሎጂ የሰው ልጆች በቡድንና በተናጥል ያላቸውን ባሕል፣ ጠባይና አደረጃጀት የሚያጠና ክፍል ነው። በዚህም ውስጥ አንትሮፖሎጂ ወይም የሰው ልጅ ጥናት (ሥነ ሰብእ) አለ። ሶሲዮሎጂ የሚለው ቃል በፈረንሳያዊው ጸሐፊ ኤማኑወል-ዦሰፍ ሲዬ በ1772 ዓ.ም. ከሮማይስጥ ሶኪውስ (ባልንጀራ፣ ጓደኛ) እና ከግሪክ ሎጎስ (ቃል ወይም ጥናት) በማጋጠም ተፈጠረ። የፈረንሳይ ፈላስፋ ኦጉስት ኮምፕት ከ1830 ዓ.ም. ጀምሮ በሰፊ ጠቀመው። የኅብረተሰብ ጥናት ሲሆን የኅብረተሰብ ጽንሰ ሀሣብ በሮማይስጥ ትርጉም ሶኪየታስ ወይም የባልንጀሮች ግንኙነት ያመልከታል። \n \nጥያቄ: የባህል ጥናት፣ ሥነ ኅብረተሠብ ወይን ሥነ ማኅበረሰብ ሌላ ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሶሲዮሎጂ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: ዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ መቼ መስራት ጀመረች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 1979 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የደአማት መንግሥት ከስልጣን የወደቀበት ዘመን መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በኢትዮጵያ ለአውሮፕላን ነዳጅ ማከማቻ ማስፋፊያና ለኢታኖል መደባለቂያ ግንባታ ምን ያህል ገንዘብ አውጥቷል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 50 ሚሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፋሲለደስ ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው አፄ ሱሰኒዮስ እና እናታቸው ልዕልት ስልጣነ ምገሴ በመገዛዝ፣ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው። አፄ ፋሲል አዘዞ ተብላ በምትታወቀው ከጎንደር ከተማ 5 ማይል ርቃ በምትገኘው ከተማ ጥቅምት18፣1667 እ.ኤ.አ. (ጥቅምት 10፣ 1660) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አስከሬናቸውም የአገሪቱ መላ ህዝብ ባዘነበት ሁኔታ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ተብላ በምትታወቀው ደሴት የዘላለም እረፍት አገኘ። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲል ለምን ያህል ጊዜ በንግስና ቆዩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በሜሪላንድ ስቴት ትልቁ የከፍታ ቦታ የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የባክቦን ተራራ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። \n \nጥያቄ: የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለዓለም ያበሰረው ቡክሀርት ባልደክኼር የምን ሀገር ተወላጅ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የጀርመን ተወላጅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየሕገ መንግሥት ታሪክ የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና በ2093 ዓክልበ. ያሕል ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው። ሰነዱ እራሱ ገና አልተገኘም፤ ነገር ግን ለዜጎቹ አንዳንድ መብት እንደ ፈቀደላቸው ይታወቃል። ለምሳሌ ለመበለትና ለደሀ አደጎች ቀረጥ እንዳስቀረላቸው ድሆችንም ከሃብታሞች አራጣ እንደጠበቃቸው ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ብዙ መንግሥታት በተጻፈ ሕግ እንዲገዙ ልዩ ስርዓት ነበራቸው። ከተገኙት ሕግጋት ሁሉ ጥንታዊ የሆነው በ1983 ዓክልበ. የገዙ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው። በተለይ ዕውቅ የሆኑ የጥንት መንግሥት ሕጎች የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት (1832 ዓክልበ.) ፤ የኤሽኑና ሕግጋት (ምናልባት 1775 ዓክልበ. ግድም)፤ የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ.) እና፤ ሕገ ሙሴ ለእስራኤል (1661 ዓክልበ.) ናቸው። ሕገ ሙሴ በተለይ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 ያህዌ አስተካክሎ ከነዚህ ሁሉ የተሻሸሉት ብያኔዎች ይጠቅልላል። በኋላ ኬጢያውያን (1488 ዓክልበ. ግድም) እና አሦር (1080 ዓክልበ. ግድም) በበኩላቸው ለራሳቸው ሕግጋት አወጡ። \n \nጥያቄ: በጽኹፍ ከተገኙ ሕግጋት ጥንታዊ የሆነው ሕግ የማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኮንግ-ፉጸ ኮንግ-ፉጸ ወይም ኮንፉክዩስ 558-487 ዓክልበ. የኖረ ቻይናዊ ፋላስፋ ነበረ። ፍልስፍናውና ትምህርቱ «የኮንግፉጸ ትምህርት» በተለይ በቻይና፣ በኮርያ፣ በጃፓንና በቬትናም አገር ባህሎች ላይ ጥልቅ ያለ ተጽእኖ አሳድሮዋል። በእርሱ ፍልስፍና፣ የግለሰብና የመንግሥት ግብረገብ፣ የኅብረተሠባዊ ግንኙነቶች ትክከለኛነት፣ የወላጆች ክብር፣ ፍርድና ቅንነት ልዩ ትኩረት አገኙ። ኮንግ-ፉጸ በሉ ክፍላገር የተወለደ ሲሆን፣ በክፍላገሩ ውስጥ የፖለቲካ ሰው ነበር። በ509 ዓክልበ. የአንድ ከተማ ከንቲባ ከመሆኑ በኋላ፤ የክፍላገሩ ወንጀል ሚኒስትር ሆነ። ነገር ግን በፖለቲካ ረገድ በሙሉ ስኬታማ አልነበረም። ከክፍላገሩ ሦስት ታላላቅ ኃይለኛ ቤተሠቦች ወገኖች፣ ሁለቱ አምባዎቻቸው እንዲፈርሱ በመጨረሻ ተስማሙ፣ እንጂ ሦስተኛው እምቢ ብሎ ለኮንግ-ፉጸ እቅድ አልተከናወነለትም። ስለዚህ በ505 ዓክልበ. ኮንግ-ፉጸ ከሉ ክፍላገር ሸሽቶ ለጊዜው በስደት ኖረ። ከዚያ እስከ 491 ዓክልበ. ድረስ ወደየክፍላገሩ ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ የፖለቲካ ፍልስፍናውን ያስተምር ነበር፤ ሆኖም ሁላቸው ምክሩን ስላላስገቡ ይህ ደግሞ በጣም ስኬታም አልነበረም። በ491 ዓክልበ. ወደ ሉ በክብር ተመልሶ ከዚያ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ወይም ለ4 ዓመታት ዕውቀቱን ለ77 ደቃ መዛሙርት (ተማሪዎች) ያስተምር ነበር። ከኮንግፉጸ ሕይወት በኋላ ትምህርቶቹ ተከታይነት አገኙ፤ በ148 ዓክልበ. የሃን ሥርወ መንግሥት የኮንግ-ፉጸ ትምህርት ይፋዊ አደረጉት። ወደ ማዕረግ ለመሾም ዕጩዎቹ በዚህ እምነት መጻሕፍት ይፈተኑ ነበር። ከ212 እስከ 1360 ዓም ድረስ ግን ልዩ ልዩ የቻይና ግዛቶች ዳዊስም ወይም ቡዲስም የመንግሥት ሃይማኖት አድርገው ነበር። እንደገና 1360-1903 ዓም ዘመናዊው የኮንግፉጸ ትምሕርት በቻይና ይፋዊ ሆነ። በዳዊስም ሃይማኖት ዘንድ፣ የእምነቱ መሥራች ላው ድዙ በ539 ዓክልበ. ያሕል ዳው ዴ ቺንግ እንደ ጻፈ፣ እንዲሁም አንዴ ከኮንግ-ፉጸ ጋራ እንደ ተገናኙ ይታመናል። በዘመናዊ ዳዊስም በኩል፣ ላው ድዙና ኮንግ-ፉጸ ሁለቱ እንደ አማልክት ይከብራሉ። በተለይ በፓኪስታን የሚታወቅ ከእስልምና የወጣ ክፍልፋይ አሕማዲያ እስልምና እንዳለው፣ ኮንግ-ፉጸ እና ላው ድዙ ሁለቱ የአላህ ነቢዮች ነበሩ። \n \nጥያቄ: ኮንግ-ፋጸ ለስንት ደቀ መዛሙርቱ የፍልስፍና ትምህርቱን አስተማረ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ለ77 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአስትራዜኔካ የኮቪድ-19 ክትባት ላይ በአሜሪካ፣ በቺሊና በፔሩ በተደረገ ሙከራ የጎንዮሽ ጉዳት የሌለውና አስተማማኝ መሆኑን የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በሶስቱ አገሮች በሁሉም የእድሜ ክልል በሚገኙ 32 ሺህ በጎ ፈቃደኛ ሰዎች ላይ ባደረገው ምርምር ክትባቱ ውጤታማና ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መሆኑን ማረጋገጡን የሮይተርስን ዋቢ አድርጓ ኢዜአ ዘገቧል ፡፡ \n \nጥያቄ: የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በአስትራዜኔካ የኮቪድ-19 ክትባት ዙሪያ ጥናት ያደረገው በየትኛው እድሜ ክልል በሚገኙ ሰዎች ላይ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሁሉም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. በፊሎ ፍራንስዎርዝ ተሰርቶ ተግባር ላይ የዋለው የመጀመሪያውን የተሟላ የቴሌቭዥን ስርዓት የሚሰራው እንዴት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዓረብኛ ዓረብኛ የሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ አባል ሆኖ የዕብራይስጥ የአረማያ እንዲሁም የአማርኛ ቅርብ ዘመድ ነው። ፪፻፶ (250) ሚሊዮን የሚያሕሉ ሰዎች እንደ እናት ቋንቋ ይናገሩታል። ከዚህም በላይ በጣም ብዙ ሰዎች እንደ ፪ኛ ቋንቋ ተምረውታል። የሚጻፈው በዓረብኛ ፊደል ነው። በዓረብ አለም ውስጥ አያሌ ቀበሌኞች ይገኛሉ። ቋንቋው በእስልምና ታላቅ ሚና አጫውቷል። እስላሞች አላህ ለሙሐማድ ቁርዓንን ሲገልጽ በዓረብኛ እንደ ሆነ ስለሚያምኑ እንደ ቅዱስ ቋንቋ ይቆጥሩታል። አብዛኛው ዓረብኛ ተናጋሪዎች ሙስሊሞች ናቸው። ዛሬ በምዕራብ ዓለም ደግሞ ብዙ ሰዎች አረብኛ እያጠኑ ነው። በታሪክ ከፍተኛ ሚና በማጫወቱ መጠን ፤ ብዙ የዓረብኛ ቃላት ወደ ሌሎች ቋንቋዎች ገብተዋል። \n \nጥያቄ: እስላሞች በብዛት የሚናገሩት የዓረብኛን ለምን እንደ ቅዱስ ቋንቋ ይቆጥሩታል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አላህ ለሙሐማድ ቁርዓንን ሲገልጽ በዓረብኛ እንደ ሆነ ስለሚያምኑ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: የበፊቱ አራቱ ሳውዲ አረብያ ግዛቶች የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: ከጣና ሐይቅ በዓመት ምን ያል የዓሳ ምርት ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 1,454 ቶን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ የእስክንድርያ ትምህርት ተቋምን ከመቼ እስከ መቼ መራ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ182-194 ዓም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: የፍቅር እስከ መቃብር ድርሰት ከሌሎቹ ከዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ድርሰቶች በምን ይለያል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nንጉሡ «አፄ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ» የሚለውን ስም በተቀዳጁ በማግሥቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. ወይዘሮ ጣይቱ ብጡል እቴጌ ተብለው ተሰየሙ። እቴጌ ጣይቱም ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ ከንጉሠ ነገሥቱ እጅ የተቀበሉትን ዘውድ ደፉላቸው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በታወቁበት «እቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል የክብር ስም ማኅተም ተቀረፀላቸው። እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳትፏቸው የገነነውና በአገር አስተዳደርም ውስጥ ከፍተኛ ሚና መጫወት የጀመሩት ኢትዮጵያ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ/ም በውጫሌ ላይ ከኢጣሊያ ጋር በተፈራረመችው ውል ውስጥ በጣልያንኛው ትርጉም ሀገሪቷን ነፃነት እንደሌላት ጥገኛ በማስመሰል ዓላማ ላይ የተመረኮዘ ውንብድና መኖሩ ከታወቀ ወዲህ ነው። ይህ ለአድዋ ጦርነት መነሳት ምክንያትና ዋነኛ መንስዔ የሆነው ጉዳይ ሊታወቅ የቻለው እቴጌ ጣይቱ የውጫሌው ውል አንቀፅ ፲፯ ላይ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ የተባሉት ቋንቋ አዋቂ ዓፄ ምኒልክ በሰጧቸው ትዕዛዝ መሠረት የውሉን ሰነድ በመመርመር የውሉ አስራ ሰባተኛው አንቀፅ የያዘውን የትርጉም መዛባት በመግለፅ ጉዳዮ ኢትዮጵያ የምትጐዳበት ስለመለሆኑ ጭምር በማስረዳት በሰጡት ቃል ሲሆን እቴጌ በዚህ ወቅት ነገሮችን በጥንቃቄ የሚከታተሉ ስለነበር ዓፄ ምኒልክ በመጀመሪያ ሳይረዱ ዓለቃ ዓፅመ ጊዮርጊስ እንዲታሰሩ ቢያደርጉም እቴጌ ጣይቱ ግን እኒህ ሰው ትክክለኛ የኢትዮጵያ ወዳጅ መሆናቸውን ለዓፄ ምኒልክ በማስረዳት ከሦስት ዓመታት እስራት በኋላ ማስፈታቸው ይታወቃል። እቴጌ እንደተናገሩትም «ዓፅመ ጊዮርጊስ ቢታሰር ቢፈታም ለሀገሩ የሚገባውን ሠርቶ ነው። ኧረ ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ዮሴፍ፣ ጣሊያኖች በተንኮል ገብተው በማታለል ይህን የመሰለ ሥራ ሲሠሩ አነጋጋሪ ሆኖ ሳለ እንዴት ሳይስጠነቅቅዎ ቀረ?» በማለት የእቴጌ ጣይቱ የቁጣ መዓት ወደ ዮሴፍ ዞረ። \n \nጥያቄ: ወይዘሮ ጣይቱ ብጡል በስንት ዓ.ም እቴጌ ተብለው ተሰየሙ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ማሊን ከሴኔጋል ጋር በማድረግ የተፈጠረው ፌደሬሽን ምን ይባል ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የማሊ ፌደሬሽን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው የኖቤልን ሽልማት ተሸላሚ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ናጊብ ማህፉዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: በዓለም ላይ እስካሁን ምን ያክል የአስትሮኖሚካል ሲምፖዚየም ተከናውነዋል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 355 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ የት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሳር አምባ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የቪስቶሶቶሚሲስ በሽታ ሲቆይ በልጆች ላይ ምን ሊያስከትል ይችላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: የበዛብህ ወላጆች እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የሳርፌ ቢዝነስ ለብረታ ብረት ማምረቻ ፋብሪካው መስሪያ ቦታ ከማን ነው የተሰጠው??", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከዱከም ከተማ አስተዳደር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: የፀሀይ የመጠነ ቁስ ጥንቅር ነገሮች መካከል 1% ያህሉ ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየቻይና ተመራማሪዎች እጅግ በጣም ከፍተኛ በሆነ የሙቀት ወቅት የአውሮፕላኖችን ሁኔታ መከታተል የሚያስችል ዘዴ ይፋ አደረጉ። አዲሱ ቴክኖሎጂ አውሮፕላኖች ከ800 እስከ 1 ሺህ 300 ዲግሪ ሴሊሺየስ ባለው የሙቀት መጠን ውስጥ ሲሰሩ በአውሮፕላኖቹ ውስጥ የሚከሰተውን መዋቅራዊ ብልሽት መለየት የሚያስችል መሆኑን ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል። ይህም እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሙቀትና ቅዝቃዜ ባለበት የአየር ንብረት ውስጥ የሚንቀሳቀሱ አውሮፕላኖችን አጠቃላይ ሁኔታ ለመከታተል የሚያግዝ ነው ተብሏል። ከዚህ ባለፈም አውሮፕላኑ በከፍተኛ ፍጥነት በሚበርበት ወቅት የሚያጋጥመውን ከፍተኛ ሙቀት ተቋቁሞ በረራውን መቀጠል ስለመቻል አለመቻሉም ለመወሰን እንደሚያግዝም ከተመራማሪዎቹ አንዱ የሆኑት ዋንግ ዚዮንግ ተናግረዋል። የአውሮፕላኖች አሰራር እጅግ ከፍተኛ በሆነ የሙቀት መጠን ውስጥ የሚደረግን በረራ መቋቋም ስለመቻል አለመቻሉ በመወሰን አዲስ ለሚሰራ የአውሮፕላን ንድፍ እንደ ማጣቀሻ ሆኖ ያገለግላልም ነው የተባለው። ከዚህ አንጻርም የአውሮፕላን አካላትን ንድፍ ለማሻሻል እንዲሁም ቀላል እና ብዙ ጭነቶችን መሸከም የሚችሉ አውሮፕላኖችን ለመስራት በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ሊኖረው እንደሚችልም ተገልጿል። ምንጭ፦ ሲ ጂ ቲ ኤን \n \nጥያቄ: እጅግ በጣም ከፍተኛ በሆነ የሙቀት ወቅት የአውሮፕላኖችን ሁኔታ መከታተል የሚያስችል ዘዴ ይፋ ያደረጉት የምን ሀገር ተመራማሪዎች ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የቻይና ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት የወጣችው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ ለአንባብያን ስንት መጻሕፍት አበርክተዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የ10 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ ላይ የፈረደበት በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፺ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት ርዕስ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ስሙር መሬት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: የተከበሩ አቶ አፈወርቅ ተክሌ እናታቸው ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: አንጎላ ከቅኝ ግዛት የተላቀቀቸው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በኅዳር ፲፱፻፷፰ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ወላጅ እናት እና አባት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት ቀረቡ። በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ኢትዮጵያን በመወከል ለአፍሪካ ህብረት የትምህርት፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚሽነርነት በእጩነት መቅረባቸው ነው የተነገረው። የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት ፕሮፌሰር ሂሩት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋና የቋንቋ ጥናት ክፍል ለረጅም ዓመታት በመምህርነት አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም የምን ሚንስቲር ሆነው ሰርተዋል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሦር አሦር (አሹር) ማለት በጥንታዊ ዘመን በላይኛ ጤግሮስ ወንዝ አጠገብ የተገኘ ከተማና አካባቢው ነበረ። በኋለኛ ጊዜ የአሦር መንግሥት ሃይለኛ ሆኖ መላ መሬት እስከ ግብጽ ድረስ ገዛ። በጥንታዊ አሦር ከተማና በጤግሮስ አጠገብ ያሉትም ተራሮች እስከ ዛሬው አርሜንያ ድረስ 'የአሦር ተራሮች' ይሰየሙ ነበር። በኦሪት ዘፍጥረት መሠረት አሦር (አሹር) ከኖኅ ልጅ ሴም ልጆች አንዱ ሲሆን፥ ከሰናዖር ወጥቶ አንዳንድ ከተማ ሠራ። በአሦራውያንም እምነት ዘንድ 'አሹር' ከተማውን የመሠረተው አምላክ ስም ነበረ። ከቅድመኛው ዘመን አውራጃው ሹቡር ተብሎ ከሰናዖር (ሹመር)፣ ማሪ ወይም ከአካድ ይገዛ ነበር። ሹቡር በታላቁ ሳርጎን መንግሥት ውስጥ ክፍል ሆኖ ጉታውያን እስከ አጠፉት ድረስ ቆየ። በኋላ እስከ 1879 ዓክልበ. ግ. ከኡር 3ኛ ሥርወ መንግሥት ይቆጣጠር ነበር። የዑር መንግሥት ሲወድቅ የአሦር ከተማ ነገሥታት ሊሙ ስሞች ይመዘገባሉ። በዚህ ወቅት አሦር ከተማ-አገር ብቻ ነበረ። ሆኖም አሦራውያን የብረታብረት ንግዳቸውን ለማስፋፋት በማሰብ አንዳንድ ቅኝ-ከተማ (ካሩም) በሐቲ (ዛሬው ቱርክ) ውስጥ መሠረቱ። ከነዚህም ዋነኛው ካነሽ የተባለው ከተማ ነበር። በ1720 ዓክልበ. ግ. አሞራዊው ንጉሥ 1 ሻምሺ-አዳድ አገሩን ከነአሦር ከተማ አቀና። ልጁን 1 እሽመ-ዳጋን (1688-1678 ዓክልበ.) በአሦር ላይ ሾመው። ነገር ግን የባቢሎን ንጉስ ሃሙራቢ ድል አድርጎት ዙሪያው ወደ ባቢሎን መንግሥት ተሳለፈ። ከትንሹ እስያ ይካሄድ የነበረው የብረታብረት ንግድ በዚያን ጊዜ ተቋረጠ። ለሚከተለው መቶ አመት አሦር ለባቢሎን ተገዥ ነበር። በ1507 ዓክልበ. ግ. ባቢሎን ለካሣውያን ከወደቀ በኋላ፥ አሦር በሚታኒ መንግሥት (ሑራውያን) በ1441 ዓክልበ.ግ. ይሸነፍ ነበር። ሚታኒ በኬጢያውያን ግፊት ሲወድቅ ግን የአሦር ንጉስ አሹር-ኡባሊት ነጻነቱን አዋጀ (1366 ዓክልበ. ያህል)። ከዚህ በላይ ይህ አሹር-ኡባሊት የራሱን ልጅ ኩሪጋልዙን በባቢሎን ዙፋን ላይ አሾመው። በ1290 ዓክልበ. የአሦር ንጉስ 1 አዳድ-ኒራሪ የሚታኒን መንግሥት አሸነፈ። የአዳድ-ኒራሪ ተከታይ 1 ስልምናሶር መንግሥቱን በከጢያውያን አግጣጫ እስከ ከርከሚሽ ድረስ አስፋፋ። የስልምናሶርም ልጅ 1 ቱኩልቲ-ኒኑርታ እንኳን በባቢሎን ላይ ገዛ። ሆኖም በቅርብ ጊዜ ባቢሎን በአሦር ላይ አመጽ ታደርግ ነበር። በ1200 ዓክልበ.. አካባቢ የኬጢያውያን መንግሥት በሙሽኪ (ፍሩጋውያን) ግፊት ስለ ወደቀ፥ ባቢሎንና አሦር ለአሞራውያን መሬት ተወዳዳሪዎች ሆኑ። የአሦር ንጉስ 1 አሹር-ረሽ-ኢሺ በዚህ አቅራቢያ በ1140 ዓክልበ. በባቢሎንን ንጉሥ 1 ናቡከደነጾር ላይ አሸነፈ። የአሹር-ረሽ-ኢሺ ልጅ 1 ቴልጌልቴልፌልሶር የመንግሥቱን ጠረፍ በጣም አስፋፋ። ከርከሚሽን ከመማረኩ በላይ በሙሽኪ ላይ እስከ ጥቁር ባሕር ድረስ ዘመቻ አደረገ። ደግሞ እስከ ሜድትራኒያን ባሕር ድረስ ሲዘረጋ ፊንቄን (ሊባኖስ) ያዘ። ከ1 ቴልጌልቴልፌልሶር በኋላ ከጎረቤቶቹ ከአራማውያንና ከኡራርቱ የተነሣ የአሦር ኅይል ደክሞ ነበር። በ920 ዓክልበ. ግን 2 አዳድ ኒራሪ ንጉሥ ሆሞ የአሦር ሃይል ታደሰ። ደግሞ ወደ ስሜን የኖሩትን ሕዝቦች በሙሉ በሰፈራ አፈለሳቸው። ይሁንና መንግሥቱ ከአቦር ወንዝ ወደ ምዕራብ አልዘረጋም። ንጉስ አሹር-ናሲር-ፓል ከ890 ዓክልበ. ጀምሮ ነግሦ ያለ ምኅረት ጠረፎቹም አስፋፋ። ከአቦርና ከኤፍራጥስ መካከል ያሉትን አራማውያን ድል አድርጎ በሜድትራኒያን ሲደርስ ፊንቄን ቀረጠ። ካልሁንም ዋና ከተማው እንዲሆን አደረገው። በልጁ 3 ስልምናሶር 34 አመት ዘመን (865-831 ዓክልበ.) አሦር በየአመቱ ለጦርነት ሠለፈ። ባቢሎን ተወርሮ ተቀረጠ። የሶርያ (አራም-ደማስቆ) ንጉስ ወልደ አዴር (አድርአዛር) ከእስራኤል ንጉስ አክዓብ ጋራ በቃርቃር ፍልሚያ ስልምናሶርን አጋጠመው። ስልምናሶርም ፊንቄንና የእስራኤል ንጉስ ኢዩን አስቀረጠ። በዋና ከተማው በካልሁ የተገኘው ጥቁር ሐውልት ስለ 3 ስልምናሶር ዘመን ድርጊቶች ይመሰክራል። \n \nጥያቄ: አሹር-ኡባሊት በባቢሎን ዙፋን ላይ የሾመው የልጁ ስም ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኩሪጋልዙን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: ጆን ሎጂ ቤርድ በ1926 እ.ኤ.አ. በቴሌቪዥን ምን ዓይነት ምስሎችን ነበር ማስተላለፍ የቻለው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጥቁርና ነጭ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበዚህ በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. ላይ የቱርክ፣ የመስኮብ፤ የጀርመን፤ የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይና የኤስፓኝ መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት መቆጠራቸው አልቀረም። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ የፖርቱጋል መንግሥት በሌላው እንኳን ባይሆን በመርከብና አገር በመያዝ ከቀሩት ይበልጥ ነበር። የቀሩት የኤውሮፓ መንግሥታት እዚያው ወሰናቸው ላይ ገዥነታቸውን ለማጽደቅ እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ የፖርቱጋል መንግሥት ግን ደኅና ደኅና መርከቦችን አዘጋጅቶ እየላከ ከመንግሥቱና ከኤውሮፓ ርቆ የሚገኘውን የአሜሪካን፤ የእስያን፤ የአፍሪካን አገሮች ያስመረምር ነበር። መርማሪዎቹም እነቫስኮ ደጋማ፤ እነፔሬዝ፤ እነአንድራድ፤ እነካብራል በመርከብ እየሄዱ ለመከላከል ጉልበት የሌለውንና በጠባዩ ሀብት ያለበትን አገር መርምረው ሲመለሱ መንግሥቱ ወታደር በመርከብ እየላከ ብዙ አገር ያዘ። በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ. ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል የተባለው የፖርቱጋል መኮንን በትልቅ መርከብ ሄዶ ይን ጊዜ ለቀረው ዓለም ያልታወቀውን የብራዚልን አገር አስገበረና በፖርቱጋል መንግሥት ስም ቅኝ አገር አደረገው። ከዚያም አገር በተገኘው ወርቅ መንግሥቱ ሀብታም ሆነ። እንደዚሁም የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ ወደ ህንድ አገር ሄዶ አገሩን ያዘ። ከተማውንም በጎአ አድርጎ ህንድንም የፖርቱጋል የቄሣር ግዛት አደረገና አገር ገዥውም የንጉሥ እንደራሴ ይባል ጀመር። ከዚያም በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን የሚባለውን አገር በየጊዜው በጦር ኃይል አስገበራቸው። በዚሁ አኳኋን ወደ ኢትዮጵያም እነኮቪልሐኦ ቀደም ብለው በዓፄ እስክንድር ዘመን መጥተው እንደመረመሩትና የኢትዮጵያ መንግሥት በዚያ ጊዜ በነሱ አጠራር የቄሱ የዮሐንስ መንግሥት አለ ብለው አውርተው እንደነበረ ሌላ የፖርቱጋል የጦር መርከብ በአፍሪካ ድንበር በቀይ ባሕር ላይም እየተመላለሰ አስቀድሞ ከያዙት ከቱርኮችና ከግብጾች እየተዋጋ አንድ ጊዜም እየተሸነፈ አንድ ጊዜም እያሸነፈ ብዙ ጊዜ ተመላለሰ። በዚህ ሁሉ ምክንያት የፖርቱጋል መንግሥት ታላቅነት በሌላው ዓለም እንደ ታወቀ እንደዚሁም ፩ኛ ትልቅ መንግሥት መሆኑ ፪ኛ ክርስቲያን መሆኑ ኢትዮጵያ ባሉት የውጭ አገር ሰዎች አፍ እየተነገረ ዝናው በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ዘንድ መሰማት ቻለ። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ የያዛት ሀገር ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ህንድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በአይቬሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት በመኖሩ ምክንያት ምን ያህል ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አይሄዱም?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት ያወጣው ማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ክሊስቴኔስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: ዋዝንቢት የጥሪ ዘፈን ድምጽ ለምን ተግባር ሊያወጣ ይችላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየቻይናው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ በፈረንጆቹ 2019 240 ሚሊየን ስልኮችን ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡ ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሽያጭ ገቢው 850 ቢሊየን ዩዋን ወይም 122 ቢሊየን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል ፡፡ ሽያጩ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ 18 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፥ የተጠበቀውን ያክል ገቢ አለመገኘቱም ተመላክቷል ፡፡ የኩባንያው መሳሪያዎቹን በመጠቀም ስለላ ሊያካሂድ ይችላል በሚል በአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ባለሥልጣናት ላይ ስጋትን በመጫሩ ከአሜሪካ የግንኙነት መረቦች በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዛዝ መታገዱ ይታወሳል ፡፡ ይህም ለሁዋዌ አስቸጋሪ ሁኔታን ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ ኩባንያው በ2020ም የተፈጠረውን ችግር በመቋቋም ገበያው ላይ መቆየት ተቀዳሚ አላማው መሆኑን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ተናግረዋል። ምንጭ፡-www.cnet.com/ \n \nጥያቄ: የቻይናው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ በፈረንጆቹ 2019 ምን ያህል ስልኮችን ለገበያ አቀረበ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 240 ሚሊየን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የኢያን ስሚዝ አመራር የሮዴዢያን ሪፕብሊክ መሆኑን ያስታወቀው መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1970 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ በማን አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ሬድዮ ልትገባ ቻለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አቶ ታደሰ ሙሉነህ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን አባት የሆነው ሚካኤል ስራው ምንድነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር ከተማ ከጣና ሐይቅ በየትኛው አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደቡባዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ ሹል የሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ የምትጠቀምበት አካሏ የቱን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ምላሷ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማሊ በአፍሪካ በየትኛው አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በሰቆጣ የነበረዉ ትልቁ ግብይት ምንድን ነዉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ለሳርፌ ብረታ ብረት ፋብሪካ የተሰጠው መሬት ስፋቱ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 30,000 ካሬ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ ታላቅ ወንድማቸው ወደ ግዞት እንዲሄዱ ያደረጉት ወዴት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወደ አምባ ግሽን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nግርማዊ ጃንሆይ በአልጋ ወራሽነታቸው በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. አውሮፓን ጎብኝተው ሲመለሱ አርባ የአርመን ተወላጆች በበጎ አድራጎት ለመርዳት ካስመጧቸው የመንፈስ ማነቃቂያና የሞራል መጠበቂያ እንዲሁም ለሀገሪቱ የሥልጣኔ እርምጃ ይጠቅማል በማለት የሙዚቃ ትምህርት ቤት አቋቋሙ። ከዚህ በኋላ በዚሁ ዓመተ ምሕረት ከወለጋ ጠቅላይ ግዛት ከሾጎሌ ፻፳ የሚሆኑ ወጣቶች መጥተው በሙዚቃ ትምህርት እንዲሰለጥኑ ተደርጎ በ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. የግርማዊ ጃንሆይ ንግሥ በዓል በነዚሁ ሙዚቀኞች ተከብሮ ውሏል። እነዚህ የመጀመሪያው ኢትዮጵያውያን ሙዚቀኞች በጣሊያን ወረራ ጊዜ ግማሾቹ ሲገደሉ የቀሩትም ተበታትነዋል። የኢትዮጵያ ነፃነት እንደተመለሰ ይኸው የሙዚቃ ክፍል ድርጅት አስፈላጊ በመሆኑ ከመስከረም ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፬ ዓ.ም. ጀምሮ እንደገና እንዲቋቋም በግርማዊ ጃንሆይ ትዕዛዝ ተሰጥቶ ከጣሊያን ወረራ በፊት በቦይስካውትና በየትምህርት ቤቱ የሙዚቃ ትምህርት የጀመሩ ስለነበሩ ተመርጠው በካፒቴን ኬቮርክ ናልባንዲያን አስተማሪነት ሥራው በክቡር ዘበኛ ድርጅት ውስጥ ተጀመረ። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ሥልጣኔ የተስፋፋውና የተጀመረው ከውጭ ሀገር የሙዚቃ መምህራንን በማስመጣት በክቡር ዘበኛ ሙዚቃ ክፍል ሲሆን ለዚሁ ክፍል ከሰለጠኑት ብዙዎቹ በልዩ ልዩ ድርጅቶች ውስጥ በመሰማራት የሀገራቸውን ወጣቶች በሙዚቃ ጥበብ በማሰልጠን ላይ ይገኛሉ። ከዚህም በተረፈ ድርጅቱ ያሰለጠናቸውን የሙዚቃ አዋቂዎች በ፲፱፻፴፭ ዓ.ም. ወደ ምድር ጦር ሙዚቃ ክፍል እየላከ እንዲያስተምሩ አድርጓል። በ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት አሁን የቀ.ኃ.ሥ. ቲያትር ክፍል የተባለው ተቋቁሞ ቲያትር በሚታይበት ጊዜ የክብር ዘበኛ ሙዚቃ ክፍል ረድቷል። የክብር ዘበኛ ሙዚቀኛ ክፍል በግርማዊ ቀ.ኃ.ሥ. መልካም አሳቢነት ከ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. ሥራውን ከወጠነበት ቀን ጀምሮ የተጣለበትን አደራ በሚገባ ያከናወነ ለመሆኑ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ክፍሎች የረዳ ከመሆኑም በላይ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የአማርኛ ሙዚቃን አራቆ በመቀመር ለሌሎች ሁሉ መልካም አርአያ ሆኖ የኢትዮጵያ ዜማ ከሀገሩ አልፎ በሌላው ዓለም እንዲታወቅ አድርጓል። በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. በቀ.ኃ.ሥ. ቲያትር ቤት በተደረገው የሙዚቃ ውድድር የክ/ዘ ሙዚቃና ቲያትር ክፍል ፩ኛ ሆኖ የተሸለመ ከመሆኑም በላይ እስከ ዛሬ ድረስ ሌላ ውድድር ስላልተደረገ የከፍተኛነቱን ደረጃ አሁንም እንደያዘ ነው። \n \nጥያቄ: የሙዚቃ ትምህርት ቤት የተቋቋመው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሁዋዌ የተሰኘው ግዙፍ የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተሰምቷል። የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ሀገራቸው ከሁዋዌ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በቅንጅት ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ኩባንያው በቀጣይ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ነው የገለጹት። ሁዋዌ ቻይና ከአሜሪካ ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ መግባቷን ተከትሎ በዩናይትድ ስቴትስ አገልግሎት እንዳይሰጥ ክልከላ የተደረገበት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው አገልግሎት በሚሰጥባቸው ሀገራት በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጣልቃ ይገባል በሚል ካናዳ እና አውስትራሊያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት መሻከሩ ይታወቃል። ብሪታኒያ ከኩባንያው ጋር በቅንጀት ለመስራት እና አገልግሎቱን ለመጠቀም መፈለጓም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ሊያሻክረው እንደሚችል ተሰግቷል። ምንጭ፦ሲ ጂ ቲኤ ን \n \nጥያቄ: ብሪታንያ ከሁዋዌ ጋር ለመስራት ፈቃደኛ በመሆኗ ከማን ጋር ያላት ግንኙነት ሊሻክር ይችላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከአሜሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ስንት ክብረ ወሰኖችን ሰበረ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፳፮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ young men’s Cristian association tinning school በአሁኑ መጠሪያው spring filed college ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ YMCA ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን FYBA አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ Czechoslovakia ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ lasiva፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡ \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድር መቼ ተጀመረ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1892 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nብሪታኒያ የቻይናው ሁዋዌ 5ኛ ትውልድ (5G) ኔትወርክ በተወሰነ ገደብ በሀገሯ ስራውን እንዲቀጥል ውሳኔ አሳለፈች፡፡ ውሳኔው የተላለፈው ብሪታኒያ ኩባንያውን እንድታግደው አሜሪካ ጫና እየፈጠረች ባለችበት ወቅት፡፡ ብሪታኒያ ውሣኔውን ያሳለፈችው በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ገደብ በመጣል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ኩባንያው ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልገው ወሳኝ ክፍል (ኮር) ተብሎ የሚጠራውን አካል እንዳያቀርብ እገዳ ተጥሎበታል፡፡ ሁዋዌ ኩባንያ በብሪታኒያ 35 በመቶ በሚሆነው 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ ዝርጋት እንዲሰማራ እንደተፈቀደለት ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከወታደራዊ ማዕከላት እና ከኒውክሌር ጣቢያዎች አቅራቢያ እቀባ እንደተጣለበት ነው የተገለጸው፡፡ ቤጂንግ ኩባንያው ከታገደ በብሪታኒያ ሌሎች የንግድ እና የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ከፍተኛ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቃ ነበር፡ ኩባንያው በበኩሉ ይህ መፈቀዱ ብሪታኒያ የዓለም-መሪ ቴክኖሎጂን ማግኘት እንድትችል እና ተወዳዳሪ የሆነ ገበያ እንዲኖራት ያደርጋል ብለዋል፡፡ አያይዘውም የ5G ልቀትን ለማስቀጠል ከደንበኞቻችን ጋር አብረን መሥራታችን እንደምንቀጥል ለብሪታኒያ መንግስት እናረጋግጣለን ማለታቸው ነው የተነገረው፡፡ ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: ብሪታንያ ሁዋዌ ስንተኛ ትውልድ ኔትወርክ በሀገሯ እንዲሰራ ፈቀደች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 5ኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የስንት ዓመት ሰው ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የ73 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: የተከበሩ አቶ አፈወርቅ ተክሌ የት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አንኮበር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: የጣና ሐይቅ ስፋት ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 66 ኪ.ሜ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ትምህርታቸውን በየት ተከታተሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፀሐይ ፀሓይ በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። \n \nጥያቄ: እጽዋት ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች የሚያስተጻምሩት በምን አማካኝነት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በፀሓይ ብርሃን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዋትስ አፕ የተሰኘው የፅሁፍ እና የምስል መልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያ በሚሊየን በሚቆጠሩ ዘመናዊ ስልኮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት ሊያቋርጥ መሆኑን አስታወቀ። ዕቅዱ በተለይም ኦፕሬቲንግ ሲስተማቸውን ማዘመን ባልቻሉ የአንድሮይድ እና አይፎን ስልኮች ላይ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ ነው የተገለጸው። እርምጃው የደንበኞችን የመረጃ ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንም ኩባንያው ገልጿል። በዚህ መሰረት መተግበሪያው አይፎን ኦፕሬቲንግ ሲስተም አይ ኦ ኤስ 8ን ጨምሮ ከዚያ በፊት በተመረቱ ተመሳሳይ መለያ ባላቸው ስልኮች ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት እንደሚያቆም ተገልጿል። እንዲሁም አንድሮይድ 2፣3፣7 እና ከዚያ በፊት ያሉትን ያልዘመኑ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮች ላይ የሚሠጠውን እንደሚያቋርጥም ተነግሯል። በመተግበሪያው ላይ ማሻሻያ እያደረገ መሆኑን የገለጸው ኩባንያው፥ ይህም የመረጃ ደህንነትን ከማስጠበቅ ባለፈ ደንበኞች ሀሰተኛ ገጽ በመክፈት የተዛቡ መረጃዎችን እና የጥላቻ ንግግሮችን እንዳያሰራጩ የሚያግዝ ነው መሆኑን አስታውቋል።   ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision   \n \nጥያቄ: ዋትስ አፕ የተሰኘው የፅሁፍ እና የምስል መልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያ በምን ምክንያት ነው አገልግሎቱን የሚያቋርጠው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የደንበኞችን የመረጃ ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኤስፔራንቶ ኤስፔራንቶ (Esperanto) ከሁሉም አለማቀፋዊ ሠው ሰራሽ ቋንቋዎች እጅጉን የተስፋፋ ቋንቋ ነው። በ1859 እ.ኤ.አ. በዛሬይቷ ፖሎኝ የተወለደውና በሞያው የአይን ሀኪም የሆነው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ በ1887 እ.ኤ.አ. ቋንቋውን ለህዝብ አሳወቀ። አላማው ኤስፔራንቶን በቀላሉ ሊማሩት የሚቻል፣ የጋራ የሆነና ለአለማቀፋዊ መግባባት የሚረዳ ግን ያሉትን ቋንቋዎች የማይተካ ቋንቋ ማድረግ ነበር። ኤስፔራንቶ ከ1,600,000 በላይ ተናጋሪዎች ቢኖሩትም የቋንቋው ደጋፊ ያልሆኑ እንግሊዝኛን ከመስፋፋቱ አንፃር ለአለማቀፋዊ ቋንቋነት በተሻለ ይመርጡታል። \n \nጥያቄ: ኤስፔራንቶ የተሰኘውን ዓለም አቀፋዊ ቋንቋ በዓለም ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ1,600,000 በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nእንቁላሎቿን ሆዷ ውስጥ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ የእንቁራሪት ዝርያ (ጋስትሪክ ብሩዲንግ ፍሮግ) ያልተለመደ ዓይነት የመራቢያ ሥርዓት አላት፤ የዚህች እንቁራሪት ዝርያ ከ2002 ጀምሮ እንደጠፋ ይታሰባል የሚለው ጄደብሊው ዶት ኦርግ ድረ ገጽ ነው። \n \nጥያቄ: እንቁላሏን በሆዷ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ እንቁራሪት ዝርያ የጠፋችው ከመቼ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ2002 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ወይዘሮ ሔለን ደበበ በደቡብ ክልል ያላቸው ኃላፊነት ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: ድራኮ የአቴና ሕግጋትን መች ጻፈ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ628 ዓክልበ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: የሜሪላንድን ስቴት መሀል ለመሀል የሚከፍለው ወሽመጥ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቼሳፒክ ወሽመጥ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዶናልድ ትራምፕ ከኒው ዮርክ ከአምስቱ ቀጠናዎች አንዱ በሆነው በክዊንስ በእ.ኤ.አ. ጁን 14 1946 ተወለደ። ለእናቱ ሜሪ አን እና ለአባቱ ፍሬድ ትራምፕ ከአምስት ልጆች መሃል አራተኛው ልጃቸው ነበር። እናቱ የተወለደችው በስኮትላንድ ሉዊስ ኤንድ ሃሪስ ደሴት ላይ ቶንግ በተባለው ስፍራ ነው። በእ.ኤ.አ. 1930 በ18 ዓመቷ ዩናይትድ ስቴትስን ጎበኘች እናም ከፍሬድ ትራምፕ ጋር ተገናኘች። በእ.ኤ.አ. 1936 ትዳር ይዘው በጃማይካ ኢስቴትስ ክዊንስ መኖር ጀመሩ። በዚህም ስፍራ ፍሬድ ትራምፕ ታላቅ የሪል ኢስቴት ገንቢ ሆኖ ነበር። ዶናልድ ትራምፕ፥ ሮበርት የተባለ አንድ ወንድም፣ ሜሪአን እና ኤሊዛቤት የተባሉ ሁለት እህቶች አሉት። ፍሬድ ጁኒየር የተባለ ወንድሙ ደግሞ ከአልኮል ሱስ ጋር በተያያዘ ምክንያት ሕይወቱ አልፏል ፤ ይህም ከአልኮሆል መጠጥ እና ከትምባሆ እንዲታቀብ እንዳደረገውም ዶናልድ ትራምፕ ይናገራል። የዶናልድ ትራምፕ አባት ከካልሽታት ጀርመን በስደት ከመጡት ከፍሬድሪክ እና ከኤሊዛቤት ትራምፕ በዉድሄቨን ክዊንስ ተወለደ። ዶናልድ ትራምፕ በእ.ኤ.አ. 1976ቱ የኒው ዮርክ ታይምስ የሕይወት ታሪክ መዛግብት ላይ እንዲሁም በእ.ኤ.አ. 1987 በታተመው ዘ አርት ኦፍ ዲል በተሠኘው መጽሐፉ ውስጥ በተሳሳተ መልኩ ፍሬድሪክ የስዊድን ዝርያ እንዳለው ገልጿል። ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ የቤተሰብ ታሪክ ጸሐፊ ነው ብሎ የጠራው የወንድም ልጅ እንዳለው ከሆነ ፍሬድሪክ ትራምፕ ይህንን አቋም ለረጅም ጊዜያት የያዘው \"ብዙ አይሁዳዊያን ጓደኛሞች ስለነበሩት እና ጀርመናዊ መሆን ጥሩ ስላልሆነ ነበር\" ነው ብሏል። ኋላ ግን ዶናልድ ትራምፕ በቅድመ አያቶቹ ጀርመን መሆኑን አምኖ በእ.ኤ.አ. 1999 በኒው ዮርክ ከተማ በተካሄደው በጀርመን - አሜሪካን ስቱበን ሰልፍ ላይ በግራንድ ማርሻልነት አገልግሏል። \n \nጥያቄ: ትራምፕ ለቤቱ ስንተኛ ልጅ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አራተኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ከሰቆጣ ምን ያህል ርቆ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤተክርስቲያን ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 6 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nባቢሌ የዝሆን መጠለያ ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከአዲስ አበባ ወደ ጅጅጋ መስመር፣ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ይህ መጠለያ በቆዳ ስፋት ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር የሚመዘን ሲሆን፣ ከጠቅላላ ስፋቱም ውስጥ ፸፯ ከመቶ ያህሉ በአሁኑ አጠራር ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ይገኛል። የአካባቢው የኦሮሚያ ብሔር ተወላጆች ‹‹ወረ-ሃርባ›› (ባለዝሆኖቹ) በማለት የሚጠሩትና በፌዴራል የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሥር የሚተዳደረው የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት፣ በ፲፱፻፷፪ ነው የተመሠረተው። የምሥረታውም ዋነኛ ዓላማ፥ በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ ሲሆን ባሁን ጊዜ መጠለያው በተጨማሪም ከ፴ በላይ ጡት አጥቢ የዱር እንስሳት፣ ከ፪መቶ ፶ በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች፣ ፫መቶ ያህል የዕፅዋት ዝርያዎች የሚገኙበት ነው። ከሌሎች አዕዋፍ እና የዱር አራዊት ዝርያዎች ደግሞ ከገጸ ምድር የመጥፋት አደጋ ላይ ያለው የሳልቫዶሪ ዘረ-በል ወፍ እና ባለጥቁር ጎፈር አንበሳ በዚህ መጠለያ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: የባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ጠቅላላ ስፋት ስንት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኒኑስ ኒኑስ በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ የነነዌ መስራችና የአሦር ንጉስ ነበረ። ለዘመናዊ ሥነ ቅርስ የታወቀ አንድ ግለሰብ አይመስልም፤ ዳሩ ግን የአያሌ ታሪካዊ ወይም አፈ ታሪካዊ ግለሰቦች ትዝታ በአንድ ስም በግሪኮች በኋለኛ ዘመን እንደ ተዘከረ አሁን ይታስባል። የንጉሥ ኒኑስና ሚስቱ ንግሥት ሴሚራሚስ ስሞች በጽሁፍ መጀመርያ የተገኘው ክቴስያስ ዘክኒዱስ (400 ዓክልበ. ገዳማ) በጻፈው በፋርስ አገር ታሪክ ነው። ክቴስያስ ለ2 አርጤክስስ (2 አርታሕሻጽታ) የመንግሥት ሀኪም ሆኖ የፋርስ ነገሥታት ታሪካዊ መዝገቦች አንብቤያለሁ ብሎ አሳመነ። ከዚህ በኋላ የግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ የክቴስያስን ወሬ አስፋፋ። የአለም ታሪክ ሊቃውንት እስከ 1880ዎቹ ድረስ የኒኑስ ታሪክ ዕውነት መሆኑን ይቈጠሩት ነበር። በዚያን ጊዜ የኩኔይፎርም ጽሕፈት ፍች ስለ ተፈታ፣ በሜስፖጦምያና በነነዌ ብዙ ቅርሶችም በመገኘታቸው፣ የአሦር ትክክለኛ ታሪክ ዕውቀት ተጨመረልን። ኒኑስ የቤሉስ ወይም ቤል ልጅ ተባለ፤ ይህም ምናልባት በሴማዊ ቋንቋ ሥር «ባል» (ጌታ) የመሰለ ማዕረግ ሊሆን ይችላል። በካስቶር ዘሮድስ ዘንድ ኒኑስ ለ52 ዓመታት ነገሰ፤ ክቴስያስም እንዳለው መጀመርያው ዓመተ መንግሥቱ 2198 ዓክልበ. ነበረ። በ17 አመታት ውስጥ ኒኑስ በአረቢያ ንጉስ አርያዎስ እርዳታ ምዕራብ እስያን በሙሉ እንዳሸነፈ ተብሏል። ከዚህ ቀጥሎ የአርመን ንጉስ ባርዛኔስን (ይቅርታ የሰጠውን) እና የሜዶን ንጉስ ፋርኖስን (በስቅለት ይሙት በቃ የሰጠውን) ድል በማድረግ የአለም መጀመርያ ንጉሠ ነገስት እንደ ሆነ ተብሏል። \n \nጥያቄ: ኑኒስ በእነማን እርዳታ ነው ምዕራብ እስያን ማሸነፍ የቻለው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአረቢያ ንጉስ አርያዎስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ 150,000 ያህል ተናጋሪዎች ያሉት በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በዩጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ የትውል ቦታው የት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታውጆ እስከ 1948 አ.ም. ሲያገለግል የነበረው ሕገ መንግሥት መች ነበር የታወጀው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 1923 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ያስገነባው የኢታኖል መደባለቂያ የሚገኘው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nባህር ዛፍ ባህር ዛፍ በተፈጥሮው ከአውስትራሊያ የሚገኝ አበባ ሚያብብ የዛፍ ወገን ነው። በአለም ላይ 700 አይነት የባህር ዛፍ ዝርያዎች አሉ፣ ከነዚህ ውስጥ 15ቱ ከአዉስትራሊያ ውጭ በተፈጥሮ ሲገኙ ከ700ው 9ኙ ዘር ብቻ አውስትራሊያ ውስጥ በተፈጥሮ አይገኝም። በኢትዮጵያ በተለይ የታወቁት፦ ነጭ ባሕር ዛፍ ቀይ ባሕር ዛፍ ናቸው። በአዲስ አበባ ከተማ ዳግማዊ ምኒልክ የባህር ዛፍ ፍሬ አስመጥተው ካስተከሉ በኋላ ይሄ አዲስ ዕጽ ዓየሩ ተስማምቶት ለከተማዋ የአረንጓዴ መቀነት ይመስል በጥቂት ዓመታት አሸበረቃት። በ፲፱፻፵ ዎቹ ይሄ መቀነት እስከ አርባ ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት በመያዙ ከተማዋን በሰፊው የባህር ዛፍ ከተማ የተባለ ቅጽል ስምን አትርፎላት ነበር። በአሁኑ ወቅት ባህር ዛፍ አለም አቀፍ ተፈላጊነት አግኝቷል። ይህም የሆነበት ምክንያት ቶሎ በማደግ አስፈላጊ እንጨት ይሰጣል የዛፉ ዘይት ለጽዳት እና እንዲሁም በራሪ ትንኞችን ለማባረር እንዲሁም ለመግደል ይረዳል:: አልፎ አልፎ ለወባ ትንኝ ማደግ ምቹ የሆኑ አረንቋወችን ለማድረቅ ይረዳል። ሆኖም ግን ባህር ዛፍ ከላይ ለተጠቀሱት አላማወች ቢያገለግልም ትልቁ ችግሩ ውሃ በጣም ይወዳል። ስለሆንም እርሱ በተተከለበት ሌሎች አትክልቶች የማደግ እድላቸው ዝቅተኛ ነው። ኢትዮጵያም ውስጥ በአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ምንጮችን እንዳደረቀ መረጃ አለ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዛፍ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጣ ያደረጉት ንጉስ ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዳግማዊ ምኒልክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: የማሊ ፌደሬሽን ማሊን ከሴኔጋል ጋር በማድረግ የተፈጠረው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ መቼ ታሠሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: የእቴጌ ጣይቱ አባት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ የተሠራው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ ውስጥ ስንት ማደያዎች አሉት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 143 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየብረት ማዕድኖች የብረት ማዕድናት በሁለት ይከፈላሉ። እነሱም ፕሪሽየስ ሜታል መደብ እና ቤዝ ሜታል መደብ ናቸው። ወርቅ እንደ ሌሎቹ የብረታ ብረት ማዕድኖች የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በትሮይ አውንስ መጠን ነው። አንድ ትሮይ አውንስ ፤ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው። ትሮይ የሚባለውን ስም ያገኘው ከግሪክ አገር ሳይሆን ፤ በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ነው። የወርቅ ጌጥ ማድረግ ለሚወዱ ሰዎች ደግሞ ፤ የንፁህ ወርቅ መጠን በካራት ይለካል። በጣም ንፁህ የሆነው ሃያ አራት ካራት ሲሆን ከዚያ ዝቅ ያለ መጠን ያለው ደግሞ ከሌላ ብረት ማዕድን ጋር የተደባለቀው ነው። የዋጋውም ዓይነት በዚሁ መጠን በወርቅ ሰሪ ቤቶች ሱቅ ውስጥ ይለያያል። ብር የተባለው ማዕድን ደግሞ ተፈላጊነቱ በድሮ ጊዜ ለመገበያያነት ቀጥሎም ለተለያዩ የንብረት እቃዎችና የፋብሪካ ውጤቶች አገልግሎቱን የሚሰጥ የማዕድን ብረት ነው። ንፁህ ብር የሚባለው ብዙውን ጊዜ ዘጠና ሁለት ነጥብ አምስት ያክሉን ሲልቨር የሚይዘው ነው። የተቀረው ሰባት ነጥብ አምስት ከመዳብ (ኮፕር) - ወይንም ከሌላ የብረት ማዕድን ጋር የሚደባለቀው ነው። የአጠቃላይ ስሙም እስተርሊንግ ሲልቨር ይባላል። መደባለቁ የሚጠቅመው የብር ይዘቱን ለማጠንከር ወይንም በቀላሉ ከውስጡ ያሉትን ንጥረ ማዕድኖች በሙቀት ጊዜ ወይንም በቅዝቃዜ መጠናቸው እንዳይለወጥ ነው። \n \nጥያቄ: በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ምን የሚለው ስያሜ ተገኘ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ትሮይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ ከተወለደች በኋላ እየተውተረተረች ትነሳና የእናቷን ጡት ለመጥባት ምን ያህል ጊዜ ይፈጅባታል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ15 ደቂቃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በአዲስ መልክ የተዘጋጀው የመረጃ አያያዝ ምን ምን መረጃዎችን አካቶ ይዟል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሳ አራዊት ከሚባሉት አውሬ በቁመቱና ክብደቱ ስንተኛ ደረጃ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለተኛ ደረጃ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመስከረም 22/2012 በአገሪቷ ወጥ የምርምር ስርአት ለመዘርጋት ብሄራዊ የሳይንስና ምርምር ካውንስል ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ አስታወቀ። በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ የሳይንስና ምርምር አውደ ጥናት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከከፍተኛ ትምህርት ፣ ከምርምር ተቋማትና ከሞያ ማህበራት የተውጣጡ ተመራማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል። የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረ ማርያም እንደተናገሩት በአገሪቷ በሳይንስ ዘርፉ ብቃትና አቅም ያላቸው ተማራማሪዎች ቢኖሩም ምርምሮች ወጥ ባልሆነና ቅንጅት በጎደለው መልኩ እየተከናወኑ ይገኛል። በመሆኑም በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናወንና ምርምሮች ላይ ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ ብሄራዊ የሳይንስና ምርምር ካውንስል ማቋቋም ያስፈልጋል ብለዋል። የካውንስሉ መቋቋም በአገሪቷ ወጥ የሆነ የምርምር አሰራር ስርአት ለመዘርጋት፣ በዘርፉ ያለውን የሰው ኃይል፣ በጀትና የምርምር መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ ለመጠቀም እንደሚያስችል ጠቁመዋል። በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር የሳይንስና የምርምር ዘርፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ቢኖር በበኩላቸው ካውንስል ቢቋቋም የሳይንስ ዘርፍ ለአገሪቷ ዕድገትና ልማት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በሳይንስ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ አገራት ተሞክሮም የካውንስሉን መቋቋም ጠቀሜታ ያረጋግጣል ብለዋል። የሚንስቴሩን አደረጃጀት የመፈተሽና በተገቢው መልኩ የማዋቀር ምርምሮችን ለመከታተል የሚያስችል የመረጃ ስርዓት የመዘርጋት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። በአገር ወስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎችን ጥራት ለማሳደግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት የመዘርጋት እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የዩንቨርስቲ ኢንደሰትሪ ትስስር ያለመጎልበት፣ የምርምር ተቋማት ቅንጅት ክፍተት፣ በሳይንስ ፖሊሲና አገራዊ ልማት አጀንዳ ላይ የምሁራን ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆን በዘርፉ ከሚጠቀሱ ችግሮች መሆናቸውንም ዶክተር ሰለሞን አብራርተዋለ። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም እንዳሉትም የሳይንስና ምርምር አውደ ጥናቱ ዋነኛ ትኩረት በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ምርምሮች ጥራት፣ በጀት፣ ስርጭትና ውጤቶችን ለመዳሰስ ነው። በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን መለየትና በተለያዩ ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮች ተግባራዊነትን መዳሰስም የአውደ ጥናቱ ትኩረት መሆኑን አንስተዋል። ከአውደ ጥናቱ በሳይንስ ዘርፉ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ዘርፉን ለማሳደግ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዚዳንት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረ ማርያም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ከሠራቸው አንዱ አዋሽ ወንዝ ላይ ያቆመው ድልድይ ነው። ስለዚህ ድልድይ ሥራ ኢልግ ሲጽፍ፤ የመጀመሪያው የድልድይ ሥራ እንደነበረና የድልድዩ ቋሚዎች በሰው ሸክም አሥራ አምስት ኪሎ ሜትር ተጉዘው እንደመጡ ይተርክና ሥራውን በሐሩር እና በዶፍ እንዲሁም በማታ የዱር አራዊትን በመቋቋም እራሱ ድንጋይ እየጠረበ፣ ምስማር፣ ችንካር እና ብሎን እያቀለጠ እየቀጠቀጠ እንደሠራው ይነግረናል። ምኒልክ በሸዋ ንጉሥ ከሆኑ በኋላ ሐዲድ አዘርግተው ባቡር ለማስገባት አሰቡ። ይህም ሀሳባቸው እንዲፈቀድላቸው የበላያቸውን ንጉሠ ነገሥቱን አጤ ዮሐንስን ፈቃድ ጠየቁ። በአጤ ዮሐንስ አካባቢ የነበሩ መኳንንቶች መክረው ምኒልክ ከግዛታቸው ከሸዋ ውጭ ሐዲድ ለመዘርጋት እንደማይችሉ ተነገራቸው። በሳቸው መቸኮልና መጓጓት ምክንያት አልፍሬድ ኢልግ በሥራና በሀሳብ ተጠምዶ እንደነበር ወዲያውም ለጃንሆይ ምኒልክ የሞዴል ባቡር ተጎታች ጋሪዎችን እየጎተተ በሐዲድ ላይ ሲሄድ የሚያሳይ ሠርቶ ሲያሳያቸው በጣም እንደተደሰቱ ጳውሎስ ኞኞ “አጤ ምኒልክ” በተባለው መጽሐፋቸው ዘግበዋል። ከዓፄ ዮሐንስ ሞት በኋላ ምኒልክ የንጉሠ ነግሥትነትን ዘውድ በጥቅምት ወር ጭነው ወዲያው በኅዳር ወር ላይ የምድር ባቡርን ሥራ አንቀሳቅሰዋል። ለዚህም ኢልግ ከማንኛውም ኩባንያ ጋር ተዋውሎ ሐዲዱን ለማሠራት የሚችልበትን ፈቃድና የሚዋዋልበትን የውል ዓይነት መጋቢት ፩ ቀን ፲፰፻፹፮ ዓ/ም አስጽፈው በማህተማቸው አትመው ሰጡት። ኢልግም ፓሪስ ከተማ ላይ ቢሮ ከፍቶ ለሥራው የሚያስፈልገውን መዋእለ ነዋይ፤ ሥራውን የሚኮናተሩ ድርጅቶችን እና ሌላም ጥናቶችን ማቀናበር ጀመረ። የዚህ የምድር ባቡር መሥመር ከጂቡቲ ወደብ ተነስቶ አዲስ አበባ ድረስ ፯፻፹፬ ኪሎ ሜትር ሲሆን ሥራው በ፲፰፻፺ ዓ/ም ተጀምሮ ከሀያ ዓመታት በኋላ በ ፲፱፱፻፲ ዓ/ም ተገባደደ። መቸም የኃሳቡ ጸንሳሽ ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክም ሆኑ ሕልማቸውን ዕውን በማድረግ ብዙ አስተዋጽዖ ያስመዘገበው ኢልግም ፍጻሜውን ባያዩትም በኢትዮጵያ የምድር ባቡርን ስናስብ የነዚህ የሁለቱ ሰዎች ትዝታ በታሪክ ተመዝግቦ ይኖራል። \n \nጥያቄ: የምድር ባቡር መሰራት ዝርጋት ከስንት ዓመታት በኋላ ተጠናቀቀ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከሀያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ በ2004 እ.ኤ.አ. ከቻይናው ኤክሲም ባንክ ምን ያህል ብር ተበድራለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፪ ቢሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: ሀምሌ 16/1961 አፓሎ 11 ከመሬት ሲመነጠቅ በውስጡ ስንት ጠፈርተኞችን ይዞ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 3 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nደስታ ተክለወልድ አለቃ ደስታ ተክለወልድ የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ነበሩ። ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ የተወለዱት አለቃ ደስታ፣ ያረፉት ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን ከአጥቢያቸው ጀምሮ እስከ ደብረ ሊባኖስ የቅኔና የዜማ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ቀለምን ፈጥኖ በመቀበልና በማስተዋል ችሎታቸው የተመሰከረላቸው አለቃ ደስታ የመጻሕፍት አንድምታ ትርጓሜን አደላድለዋል፡፡ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የሠሩ ሲሆን፣ በእርሳቸው አረጋጋጭነት በርካታ መጸሕፍት ለሕትመት በቅተዋል፡፡ በሀገረ ጀርመን በታተመው ኢንሳይክሎፔዲያ ኢትዮፒካ እንደተዘገበው፣ ወደ ድሬዳዋ በመሄድ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ሥራቸውን የቀጠሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው ከሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መተዋወቃቸው ነበር፡፡ ከ30 ዓመት በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምን እየሠሩ ዐምድ አጋጣሚውን እንዲህ ያስታውሰዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ ተክለወልድ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት በምን ስራ አገልግለዋል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቅልልቦሽ ቅልልቦሽ የኢትዮጵያ ህጻናት በጠጠር የሚጫወቱት ሲሆን አጨዋወቱም አንዱዋን ጠጠር ወደአየር በማጉናት እሱዋ ባየር ላይ እያለች የተቻለን ያክል ጠጠር ከመሬት ማፈስ ነው። ባየር ላይ ያለችው ጠጠር ስትመለስ በተጫዋቹ እጅ \"መቀለብ\" ወይም \"መያዝ\" ይኖርባታል። ሳትያዝ መሬት ላይ ከወደቀች፣ ጨዋታው አለቀ ማለት ነው። ጨዋታው \"ጠጠር\" በመባልም ይጠራል። ብዙ አይነት የቅልልብልቦሽ ጨዋታዎች ሲኖሩ፡ በጣም የታወቀው \"ዓይጥ አለብሽ\" በመባባል የሚጫወቱት ነው። ልጆቹ ሁለት ወይም ሶስት ይሆኑና፡ አምስት ቆንጆ ድብልብል ጠጠሮች፡ ስፋትና ርዝመታቸው ከግማሽ ኢንች የማይበልጡ፡ ይለቅሙና መሬት ይቀመጣሉ። ቀድሞ \"ብጀ\" ያለ መጀመርያ ይጀምራል። ብጀ ማለት ብጀምር ማለት ነው። ያንን ለማለት እሽቅድምድም ነው።\"ብቀ\" ያለ ከርሱ የሚከተል ነው ማለት ነው፡፡ ብቀ ማለት ብቀጥል ማለት ነው። ሁለት ልጆች እኩል \"ብቀ\" ካሉ በድምጽም ቢሆን ቀድሞ \"ብ!\" ከአፉ የወጣው ሰው ሁለተኛነቱን ያገኛል። \"ብቀጣጥል!\" ያለ ሶስተኛ ነው። \"እንጀራ ብጋግር!\" ያለ አራተኛ ነው። አምስተኛ ካለ \"ወጥ ብሰራ!\" ብሎ ተራውን ያሳውቃል። በዚህ ተራ ተስማምተው ጀማሪው ይጀምራል። \n \nጥያቄ: የቅልልብልቦሽ ጨዋታ ለስንት ነው የሚጫወቱት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ወይም ሶስት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ1936 ጀምሮ ኤርትራ የኢኮኖሚ እድገት ማሳየት ችሏል። በ30ዎቹ መጨረሻ 2፣198 የኢንደስትሪ ተቋሞች በአገሪቱ ተመስርተዋል። ይሁንና ጣሊያኖች አገሪቱ እራሷን እንድትችል ሳይሆን የነርሱ ጥገኛ እንድትሆን ነበር ያደረጉት፣ ለዚህ ሲሉ አብዛኛው ምርት ከውጭ ያስመጡ ነበር። ከ10-15% የሚሆነው የአገሬው ወንድ ሃይል በኢንደስትሪ፣ በእርሻና በጥቃቅን የተላላኪ ስራወች ተቀጥርው ይሰሩ ነበር። ከ1936-41 ድረስ አብዛኛውን የአግሬውን ወንድ ቀጥሮ ያሰራ የነበረው የቅኝ ገዥው ውትድርና ተቋም ነበር (40% ወይም 60፣000 ለአቅመ አዳም የደርሱ ወንዶችን)። እኒህ ወታደሮች ኢትዮጵያን ለመውረር ያገለገሉ ሲሆን ለዚህ ታማኝነታቸው ምክንያቱ ቅኝ ገዥወች በኤርትራ ላይ ያሰፈኑት ፖለቲካዊ መረጋጋት እንደምክንያት ይጠቀሳል። የጤና፣ የገበያ ኢኮኖሚ እንዲሁም ቁሳዊ ፍጆታ መስፋፋት በ1905ዓ.ም. 250 ሺህ ብቻ የነበረው የኤርትራ ህዝብ ወደ 614 ሺሕ በ1935 ዓ.ም. እንዲያድግ አድርጓል። ትግርኛ ተናጋሪው ክፍል በዚህ ጊዜ 54% የአገሪቱ ክፍል ነበር። እኒህ ለውጦች በአገሬው ላይ የስነ ልቦና ለውጥን አስከተሉ፣ ስለሆነም ከኢትዮጵያውያን ጐረቤቶቻቸው የተለዩ ህዝቦች የመሆን ማንነትን ፈጠረ። ሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ እንግሊዞች ከአንግሎ ግብጻዊ ሱዳን በመነሳት ጥር 1941 በኤርትራ ላይ ጥቃት አደረሱ። ከሶስት ወር በኋላ የከረን ጦርነትን በማሸነፍ ሚያዝያ 1941 ሙሉ ኤርትራን ተቆጣጠሩ። የእንግሊዝ ወታደራዊ አገዛዝ(BMA) በጣሊያኖች ምትክ አገሪቱን ማስተዳደር ጀመረ። 1947 ጣሊያን በፈረመችው የሰላም ውል መሰረት ኤርትራ ለአራቱ ሃይላት ተሰጠች። ከዚህ በኋላ ኤርትራ የጣሊያን ቅኝ መሆኗ አበቃላት። \n \nጥያቄ: በ1905 የኤርትራ ሕዝብ ብዛት ስንት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 250 ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ የበታተናቸው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየብረት ማዕድኖች የብረት ማዕድናት በሁለት ይከፈላሉ። እነሱም ፕሪሽየስ ሜታል መደብ እና ቤዝ ሜታል መደብ ናቸው። ወርቅ እንደ ሌሎቹ የብረታ ብረት ማዕድኖች የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በትሮይ አውንስ መጠን ነው። አንድ ትሮይ አውንስ ፤ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው። ትሮይ የሚባለውን ስም ያገኘው ከግሪክ አገር ሳይሆን ፤ በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ነው። የወርቅ ጌጥ ማድረግ ለሚወዱ ሰዎች ደግሞ ፤ የንፁህ ወርቅ መጠን በካራት ይለካል። በጣም ንፁህ የሆነው ሃያ አራት ካራት ሲሆን ከዚያ ዝቅ ያለ መጠን ያለው ደግሞ ከሌላ ብረት ማዕድን ጋር የተደባለቀው ነው። የዋጋውም ዓይነት በዚሁ መጠን በወርቅ ሰሪ ቤቶች ሱቅ ውስጥ ይለያያል። ብር የተባለው ማዕድን ደግሞ ተፈላጊነቱ በድሮ ጊዜ ለመገበያያነት ቀጥሎም ለተለያዩ የንብረት እቃዎችና የፋብሪካ ውጤቶች አገልግሎቱን የሚሰጥ የማዕድን ብረት ነው። ንፁህ ብር የሚባለው ብዙውን ጊዜ ዘጠና ሁለት ነጥብ አምስት ያክሉን ሲልቨር የሚይዘው ነው። የተቀረው ሰባት ነጥብ አምስት ከመዳብ (ኮፕር) - ወይንም ከሌላ የብረት ማዕድን ጋር የሚደባለቀው ነው። የአጠቃላይ ስሙም እስተርሊንግ ሲልቨር ይባላል። መደባለቁ የሚጠቅመው የብር ይዘቱን ለማጠንከር ወይንም በቀላሉ ከውስጡ ያሉትን ንጥረ ማዕድኖች በሙቀት ጊዜ ወይንም በቅዝቃዜ መጠናቸው እንዳይለወጥ ነው። \n \nጥያቄ: በጣም ንፁህ የሆነ ወርቅ መጠን ምን ያህል ይሆናል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሃያ አራት ካራት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምን ማዕድን ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የኦፓል ማዕድን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በኢዲአሚን ሥልጣን ዘመን ስንት ሰው አለቀ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 300,000 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ10ኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ዚምባቡዌያውያን ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በየት ነበር ንግድ የጀመሩት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በኢንዲያን ባህር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: አዳነ ግርማ ኢትዮጵያ ስንተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ከዛምቢያ ጋር ስትጫወት ግብ አስቆጠረ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 29ኛው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ወደ ቀጭኔ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው የደም ቧንቧ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ካሮቲድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nግሪክ ግሪክ ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋ አንድ ትንሽ አገር ነው። ከምሥራቅ ወደ ትንሽ እስያ፤ ከምዕራብ ወደ ኢጣሊያ አገር ከሁለቱም ወገን ርቀቱ ትክክል ነው። ግሪክ በሰሜን ወገን ከመቄዶንያ ይዋሰናል። ግሪክ ኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው። በደቡብና በምሥራቅ ወገን አያሌ ደሴቶች አሉ። ከእነርሱም በአያሌዎቹ መንደሮችና ከተሞች ተሠርተውባቸዋል። አንዱ አንቲፖሮስ ይባላል። በእዚህም ስፍራ ያለው ታላቅ ያጌጠ ዋሻ የታወቀ ስመ ጥሩ ነው። እኩሌቶቹም የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እየተወረወሩ የወጡ ይመስላሉ። እኩሌቶቹም ከጥንት ጀምረው ይታዩ የነበሩት ያሉበት አይታወቅም ጠፍተዋል። ይህ እንግዳ ነገር እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ከባሕር በታች የተነሳው እሳተ ገሞራ ነው። በደቡብ ግሪክ ወገን ባሉት ደሴቶች አየሩ በአሜሪካ እንዳለው እንደ ቨርጂኒያ ግዛት አየር ቀላል ነው። በዚህ አገር ብዙ አይነት ፍሬ ሁሉ ሞልቶዋል። በሰሜን በኩል ደግሞ አየሩ ቅዝቃዜ ያለበት ነው። በየጠረፉ የመርከብ መቋሚያዎች ወደቦች ይገኛሉ። ብዙዎቹ የአገሩ ሰዎችም መርከበኞች ናቸው። በደኑም ፓይን (ጥድ) የተባለው ጠንካራ ዛፍ ይገኛል። በላይኛው አውራጃ ኦክ የተባለው ዛፍ ይገኛል። ወደታች ባለው ክፍልም ቸስትነትና ዋልነት የሚባሉት ዕንጨቶች ይገኛሉ። በዚህ ስፍራ የሚገኘው ዋናው ነገር ደረቅ ፍራፍሬ፣ ዘቢብ፣ ጥጥ፣ ሐር ጠጉር፣ ሩዝ፣ ትንባሆና በቆሎ ነው። የእጅ ሥራ ጥቂት ነው። በቤት የተለመደ ሥራ እንደ ጥጥ እንደ ጠጉር እንደ ሐር የመሰለ ነገር ነው። ቀለም ማግባት ወይም መቀባት በጣም የተለመደ ከሆነ ብዙ ጊዜው ሆነው። ከዛፎች ፍሬ ዋነኛው ወይራ ሲሆን በብዛት ይተከላል። ወይን፣ በኽረ? ሎሚ፣ በለስ፣ አልሞንድ (ለውዝ)፣ ተምር፣ ሴትሮን፣ ፓሜግራኔት (ሮማን)፣ ኩሬንትም ይበቅላሉ። \n \nጥያቄ: የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እዲወረወሩ እና እንዳይታዩ ያደረጋቸው ኃይል ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ እሳተ ገሞራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፕሮፌሰር ሙሃመድ ዩኑስ ትውልድ በ28 ጁን 1940 እ.ኤ.አ. የባንግላዴሽ የባንክ ባለሞያና ኤኮኖሚስት ናችው። ማይክሮክሬዲት ተብሎ የሚታወቀውን የአነስተኛ የብድር አገልግሎት በችግር ለሚኖሩ ወገኖች የመስጠትን ስራ የጀመሩትና የስፋፉት ሰው ናችው። ፕሮፌሰሩ እንነኝህ ባንክ አላስተናግድ ብሎ የተዋቸውን ድሆች የሚያገለግለውን ግራሚን ባንክን አቋቁመዋል። በጥቅምት 1999 ፕሮፈሠሩና ባንኩ የሰላም የኖቤል ተሸላሚ ለመሆነ በቅተዋል ይህም ሽልማት የልማት እድገትና ማህበረሰባዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በማስመስከራቸውና ይህ ደግሞ ለሰላም ወሳኝነት ያለው መሆኑን ሽልማት ሰጭው ኮሚቴ ስላመነበት ነው። ፕሮፌሰር የበርካታ ሽልማቶች ባለቤት ሲሆኑ ከነዚህም የአለም የምግብ ሽልማት ይገኝበታል። የድሆች አበዳሪ በሚል ርዕስ አንድ የስራሳቸውንና የስራቸውን ታሪክ የሚያትት መጽሐፍ ደርሰዋል። \n \nጥያቄ: በፕሮፌሰር ሙሃመድ ዩኑስ የስራሳቸውንና የስራቸውን ታሪክ የሚያትት የተጻፈው የመፅሐፍ ርዕስ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የድሆች አበዳሪ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ሯጭ ኃይሌ በሩጫ ሕይወቱ ዙሪያ የሚያጠነጥነው ፊልም መቼ ተሰራ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ዶ/ር ውለታ ለማ ያሸነፉበት አዲስ የሥራ ፈጠራቸው ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አባይ ሲ ኤች አር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ ርዕሱ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ The Dilemma of a Ghost ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዶናልድ ትራምፕ ከኒው ዮርክ ከአምስቱ ቀጠናዎች አንዱ በሆነው በክዊንስ በእ.ኤ.አ. ጁን 14 1946 ተወለደ። ለእናቱ ሜሪ አን እና ለአባቱ ፍሬድ ትራምፕ ከአምስት ልጆች መሃል አራተኛው ልጃቸው ነበር። እናቱ የተወለደችው በስኮትላንድ ሉዊስ ኤንድ ሃሪስ ደሴት ላይ ቶንግ በተባለው ስፍራ ነው። በእ.ኤ.አ. 1930 በ18 ዓመቷ ዩናይትድ ስቴትስን ጎበኘች እናም ከፍሬድ ትራምፕ ጋር ተገናኘች። በእ.ኤ.አ. 1936 ትዳር ይዘው በጃማይካ ኢስቴትስ ክዊንስ መኖር ጀመሩ። በዚህም ስፍራ ፍሬድ ትራምፕ ታላቅ የሪል ኢስቴት ገንቢ ሆኖ ነበር። ዶናልድ ትራምፕ፥ ሮበርት የተባለ አንድ ወንድም፣ ሜሪአን እና ኤሊዛቤት የተባሉ ሁለት እህቶች አሉት። ፍሬድ ጁኒየር የተባለ ወንድሙ ደግሞ ከአልኮል ሱስ ጋር በተያያዘ ምክንያት ሕይወቱ አልፏል ፤ ይህም ከአልኮሆል መጠጥ እና ከትምባሆ እንዲታቀብ እንዳደረገውም ዶናልድ ትራምፕ ይናገራል። የዶናልድ ትራምፕ አባት ከካልሽታት ጀርመን በስደት ከመጡት ከፍሬድሪክ እና ከኤሊዛቤት ትራምፕ በዉድሄቨን ክዊንስ ተወለደ። ዶናልድ ትራምፕ በእ.ኤ.አ. 1976ቱ የኒው ዮርክ ታይምስ የሕይወት ታሪክ መዛግብት ላይ እንዲሁም በእ.ኤ.አ. 1987 በታተመው ዘ አርት ኦፍ ዲል በተሠኘው መጽሐፉ ውስጥ በተሳሳተ መልኩ ፍሬድሪክ የስዊድን ዝርያ እንዳለው ገልጿል። ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ የቤተሰብ ታሪክ ጸሐፊ ነው ብሎ የጠራው የወንድም ልጅ እንዳለው ከሆነ ፍሬድሪክ ትራምፕ ይህንን አቋም ለረጅም ጊዜያት የያዘው \"ብዙ አይሁዳዊያን ጓደኛሞች ስለነበሩት እና ጀርመናዊ መሆን ጥሩ ስላልሆነ ነበር\" ነው ብሏል። ኋላ ግን ዶናልድ ትራምፕ በቅድመ አያቶቹ ጀርመን መሆኑን አምኖ በእ.ኤ.አ. 1999 በኒው ዮርክ ከተማ በተካሄደው በጀርመን - አሜሪካን ስቱበን ሰልፍ ላይ በግራንድ ማርሻልነት አገልግሏል። \n \nጥያቄ: የዶናልድ ትራምፕ አያቶች ከየት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጀርመናዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር ምን ያህል አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞች ከአውሮፓ ወደ አገራቸው መልሰዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 120,000 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ young men’s Cristian association tinning school በአሁኑ መጠሪያው spring filed college ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ YMCA ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን FYBA አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ Czechoslovakia ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ lasiva፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡ \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድር መቼ ተጀመረ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መጋቢት 21 1893 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ መጠሪያ ስሙን ያገኘው ከየት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: አናክሳጎራስ ስለፀሀይ በሰጠው ሳይንሳዊ መግለጫ ምክንያት ከተፈረደበት የሞት ፍርድ በማን ዳነ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በፔሪክልስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: አብዱላይ ዋዲ ለመጀመሪያ ጊዜ የሴኔጋል ፕሬዝዳንት የሆነው መቼ በተደረገው ምርጫ አሸንፎ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ2000 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ በታንዛንያ ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 250,000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሃይማኖት ሃይማኖት አንድ ሕብረተሠብ የሚያምንባቸው ጽኑ እምነቶች መሠረት ነው። በዓለም ውስጥ በርካታ ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች አሉ። ዋና ዓለማዊ ሃይማናቶች ክርስትና፣ እስልምና፣ አይሁድና፣ የሕንዱ ሃይማኖት እና ቡዲስም ናቸው። እነዚህ ሃይማኖቶች በአንዳንድ አገር በይፋ የመንግሥት ሃይማኖት ሁኔታ አላቸው። ከነዚህ መጀመርያ ሦስቱ. ክርስትና፣ እስልምናና አይሁድና፣ ሁላቸው ከአብርሐም ስለ ተነሡ፣ «አብርሃማዊ ሃይማኖቶች» ተብለዋል። ሒንዱኢዝምና ቡዲስም ግን ከሕንድ ተነሡና «ሕንዳዊ» ወይም «ዳርማዊ ሃይማኖቶች» ተብለዋል። ሌሎች ሃይማኖቶች በአሁኑ ሰዓት በየትም አገር የመንግሥት ሃይማኖት ባይሆኑም፣ ባለፉት ዘመናት በታሪክ መንግሥታት ይኖራቸው ነበር፦ በተለይ ዛርጡሽና፣ ጃይኒስም፣ ሲኪስም፣ ዳዊስም፣ የኮንግ-ፉጸ ትምህርት፣ ሺንቶና የተለያዩ ኗሪ ወይም አረመኔ ሃይማኖቶች የቀድሞ መንግሥታት ነበሯቸው፤ የጠፉት ሃይማኖቶች ማኒኪስም እና አሪያኒስም ደግሞ የቀድሞ መንግስታት ነበሯቸው። በተጨማሪ መቸም መንግስት ያልነበረላቸው በርካታ ሌሎች አነስተኛ ሃይማኖቶች ወይም እምነቶች አሉ ወይም በታሪክ ተገኝተዋል። \n \nጥያቄ: ከሕንድ የተነሱ ሃይማኖት ምን በመባል ይታወቃሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሒንዱኢዝም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና የመጀመሪያ ድርሰቷ በ1965 ያሳተመላት ድርጅት ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: የደቡብ አፍሪካ ትልቁ ከተማ ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጆሃንስበርግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: በ17ኛ ምእት በቴሌስኮፕ የታገዘ የፀሓይ ምርምር ጀማሪ ማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጋሊሌዮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: አፋር ክልል በኢትዮጵያ ክልል ስንት ተብሎ ይታወቃል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ክልል 2 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: በግራኝ መሃመድ ወረራ ምክንያት ኢትዮጵያ ከየትኛው የአውሮፓ ሀገር ጋር ግንኙነት ፈጠረች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከፖርቱጋሎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: ከሰባቱ አጽዋማት ስንቱ መባጃ ሐመር ያስፈልጋቸዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አራቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማርኮ ፖሎ ማርኮ ፖሎ (1254 - ጥር 8፣ 1324) ጥንታዊው የጣሊያን ተጓዥ እና ነጋዴ ነበር። ታዋቂነትም ያተረፈው በተለይ ወደቻይና እና ሞንጎሊያ ከተጓዙት አውሮጳውያን ቀደምትነት ስለነበረው ነው። በዚህ ምክንያት ከሱ በኋላ ዘግይተው የተነሱት እነ ክርስቶፎር ኮሎምበስ ሳይቀር ለሱ ከፍተኛ ግምት እና አድንቆት እንደነበራቸው ታሪክ ይዘክራል። 17 አመት ሲሞላው ከጣሊያን ቬኒስ ከተማ በመነሳት፣ መጀመሪያ በጀልባ ከዚያም በእግሩና በግመል ተራሮችን በርሃን አቆራርጦ ቤይቺንግ ቻይና (በድሮ ስሟ ካቴ) ለመድረስ ችሏል። በጊዜው ቻይና ትመራ የነበረው በሞንጎሉ መሪ ኩብላ ካህን የሚባለው የጌንጊዝ ካህን ልጅ ነበር። ስርዓቱም የዩዋን ሥርወ መንግስት ይባል ነበር። ለሚቀጥሉት 17 ዓመታት በኩብላ ካህን ቤተመንግስት አስተዳደር ተሰጥቶት መንግስቱን አገልግሏል። ከዚያም ወደ ጣሊያን በውቅያኖሶች አቋርጦ ተመልሷል። ወደ 600 የሚሆኑ አብሮ ተጓዦች ግን በበሽታና በጥቃት ሞተዋል። ይህ ተጓዥ ኑድል የተባለውን የቻይኖች የምግብ አይነት ወደ አገሩ ጣልያን በማምጣት የፓስታ ስራ አሰራርን ለጣሊያኖች ለመጀመሪያ ጊዜ አስተዋውቋል። በጣሊያኖች እርስ በርስ ጦርነት ተማርኮ እስር ቤት ከገባ በኋላ ለእስር ጓደኛው ርስቲቸሎ የነገረውን ታሪክ ረስቲቸሎ ጽፎ በማሳተም ለማርኮ ፖሎ በአውሮጳ ዙርያ ታላቅ መታወቅን አስገኝቶለታል። \n \nጥያቄ: ማርኮ ፖሎ የምን ሀገር ዜጋ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የጣሊያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: በስዊድኑ አካዴሚ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ የሆኑት ጸሐፊ ዜግነታቸው ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ታንዛኒያዊው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በምን ያህል ዶላር የምርምርና ልህቀት ማእከላትን እያደራጀ ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ86 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ በዓለም ዉስጥ ክሚገኙ ጥንታዊ አገሮች ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ አስቆጥራለች፡፡ በግእዝ/ዓማርኛ እና በመጽሀፍ ቅዱስ ከተመዘገቡት ተጨባጭ መረጃዎች በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን (ድንቅነሽን) አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡ ግብጽን ሲገዛ የነበረው ሄሮደስ የሚባለው ንጉስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታሪክ ፀሀፊ የጥንቷን ኢትዮጵያ በጽሁፎቹ ላይ ይገልፃታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይም ብዙ ግዜ የምትወሳ ስትሖን በተለይም ብሉይ ኪዳን ላይም የንግስት ሳባ (መከዳ) ኢየሩሳሌም መሄድና ለንጉስ ሰለሞን ከባድ የሆኑ ጥያቄዎች ማንሳቷ ተጽፏል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ያላትን መልክ እንድትይዝ ያደረጋት ንጉስ ሚኒሊክ የንግስት ሳባና የንጉስ ሰለሞን ዘር ናቸው፡፡ የንግስት ሳባ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም አካባቢ ይገኛል፡፡ ክርስትናን ኢትዮጵያዉያን ከመቀበላቸዉ በፊት (ኣስቅድመዉ) የኦሪትን ህግ ሰለሚያዉቁ ኣመተ ዓለምን ወደታች እየቆጠሩ የጌታን መወለድ ይጠብቁ ሰለነበረ ክርስትናን ለመቀበል ኣላስቸገራቸዉም፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትያን ርቃ ቆይታለች፡፡ \n \nጥያቄ: በዓለም ጥንታዊ ከሚባሉት ሀገሮች አንዷ የሆነችው ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: አፈወርቅ ተክሌ ፲፱፻፵ ዓ.ም ለከፍተኛ ት/ት ተመርጠው የተላኩት ወዴት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እንግሊዝ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ መቼ ሥልጣን ያዙ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1908 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት በገጠሙት ውጊያ የተማረከው ንጉስ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: ፊት አውራሪ መሸሻ እንዴት ሞቱ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጎፋ ብሔረሰብ ዋና የሃብት መሰረቱ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጥምር ግብርና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ስም ማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአንኮበር በ፲፯፻፳ ዓ/ም በሸዋው ነጋሲ በመርድ አዝማች አብዬ የተመሠረተችና በአልጋ ወሪሹ መርድ አዝማች አምኀ ኢየሱስ የተስፋፋች የሸዋ ከተማ ስትሆን ከደብረ ብርሃን ምስራቃዊ አቅጣጫ ፵፫ ኪሎ ሜትር ርቀት የስምጥ ሸለቆው አፋፍ ላይ ትገኛለች። አንኮበር ከዓፄ ይኵኖ አምላክ (፲፪፻፸-፲፪፻፹፭ ዓ/ም) ዘመን ጀምሮ ለኢትዮጰያ ነገሥታት በማረፊያነት አገልግላለች። ዓፄ አምደ ጽዮን ፲፫፻፲፬-፲፫፻፵፬ ዓ/ም የድንኳን ከተማቸውን እንደተከሉባት ይነገራል። አስቲት ኪዳነ ምሕረት የርሳቸው ትክል ናት። ጦረኛዉ ዓፄ አምደ ጽዮን በ፲፫፻፴፭ ዓ/ም አዳልን ለማስገበር የዐማራን፣ የዳሞትን፣ የጐዣምን ሠራዊት ይዘው አንኮበር ሠፈሩ።ለ፬ ወራት ያህል እስከ ዘይላና በርበራ ድረስ በመዝለቅ ድል አድርገው አስገብረውታል። ዓፄ ልብነ ድንግል (፲፭፻፰-፲፭፻፵ ዓ/ም) ደግሞ በተሻለ ሁኔታ በቦለድ የባለወልድን ቤተ ክርስቲያን ለማነጽ ጀምረው እንደነበር የሚጠቁሙ መረጃዎች አሉ። የከተማነት ታሪኳ የጐላው ግን ከግራኝ ወረራ በኋላ ተበታትኖ የቆየውን የጥንታዊ ሸዋን ግዛት አንድ ለማድረግ የሸዋ ስርወ-መንግሥት በአቤቶ ነጋሲ በመንዝ አጋንቻ ላይ በ፲፮፻፷፭ ዓ/ም ተጀምሮ በተከታታይ እስከ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም የጥንት ኢትዮጶያ ግዛትን ለማስመለስ በተደረገው እንቅስቃሴ ነው። የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ወደ ፲፫ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሥር መሠረቱ የረር | እንጦጦ እስከዞረበትና በኋላም አዲስ አበባ እስከተቆረቆረችበት ጊዜ ድረስ በቀዝቃዛ አየሯ የምትታወቀው አንኮበር ለአምስት የሸዋ ነገሥታት በማእከልነት አገልግላለች። \n \nጥያቄ: አንኮበር ከተማ በማን ተቆረቆረች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሸዋው ነጋሲ በመርድ አዝማች አብዬ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመርያው ሦስት ወራት፣ ከ12.2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ቢሮው እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ የሚዘልቅ ግብር የማሳወቅና የመሰብሰብ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጾ፣ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጨረሻ ሳምንት ባለው ጊዜ ከግብር አሰባሰቡ የተገኘው ገቢ ከታቀደው በላይ እንደሆነ አስታወቋል፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊነትን አዲስ በተመረጠው የከተማ አስተዳደር እንዲመሩ በድጋሚ የተመረጡት አቶ ሙሉጌታ ተፈራ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ ገቢዎች ቢሮው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የተጀመሩትን የከተማዋን ገቢ በተጠናከረ ሁኔታ የመሰብሰብ ሥራ ዘመናዊ በሆነ ሥርዓትና ቅንጅታዊ አተገባበር እየተከናወነ ነው፡፡ በተያዘው በሩብ ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ የታቀደው የግብር ገቢ 11.5 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ያስታወቁት ኃላፊው፣ ከሦስት ያላነሱ ቀናት የገቢ አሰባሰብ መረጃ ሳይካተት እስከ መስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ 12.26 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በ2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ምን ያህል ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 11.5 ቢሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: የተከበሩ አቶ አፈወርቅ ተክሌ አባታቸው ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አቶ ተክሌ ማሞ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: እበ ለገሰ የስንት ዓመት ወጣት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የ35 ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ የኖቤል የሥነ ጽሑፍ ተሸላሚ የሆኑት በመቼ ዓመተ ምሕረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የ2021 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር አይሁድ ያልሆኑ ስንት የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን አስገደለ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 5 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎጉል እና አፕል ለስለላ ጥቅም ላይ ይውላል በማለት የጠረጠሩትን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን መተግበሪያ ቶቶክን ማስወገዳቸው ተገለፀ፡፡ ቶቶክ የተሰኘው ይህ መተግበሪያ ሰዎች በቀላሉ በተንቀሳቃሽ ምስል እና በፅሁፍ እንዲያወሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ ኔውዮር ታይምስ አንደዘገበው ከዋትስ አፕ ጋር ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጠው ቶቶክ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ለስለላ መሳሪያት ጥቅም ላይ ይውላል ተብሏል፡፡ ኔውዮርክ ታይምስ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ በዘገባው እንዳሰፈረው ቶቶክ የተሰኘው መተግበሪያ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሰላዮች የተጠቃሚዎችን ውይይት ፣ እንቅስቃሴ እና ፎቶ መሰል የግል መረጃዎች አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ጎግል ይህን መተግበሪያ ባለፈው ሀሙስ ማጥፋቱ የተገለፀ ሲሆን አፕልም ጎግልን በመከተል በቀጣዩ ቀን ከመተግበሪያ ዝርዝሮቹ ውስጥ ማጥፋቱ ተጠቁሟል፡፡ ቶቶክ መተግበሪያ ለተጠቃሚዎቹ በቅርቡ በአፕ ስቶር እንደሚመለስ አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ባስተላለፈው መልዕክት በጎግል ስቶር እና በአፕል ስቶር በጊዜያዊነት እንደማይገኝ የገለፀ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ የቴክኒክ ጉዳይ መሆኑን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡- ቢቢሲ በፌቨን ቢሻው   \n \nጥያቄ: ጎጉል እና አፕል የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን መተግበሪያ ቶቶክን ማስወገዳቸው በምን ምክንያት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለስለላ ጥቅም ላይ ይውላል በማለት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን የማን አባት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአስትራዜኔካ የኮቪድ-19 ክትባት ላይ በአሜሪካ፣ በቺሊና በፔሩ በተደረገ ሙከራ የጎንዮሽ ጉዳት የሌለውና አስተማማኝ መሆኑን የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በሶስቱ አገሮች በሁሉም የእድሜ ክልል በሚገኙ 32 ሺህ በጎ ፈቃደኛ ሰዎች ላይ ባደረገው ምርምር ክትባቱ ውጤታማና ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መሆኑን ማረጋገጡን የሮይተርስን ዋቢ አድርጓ ኢዜአ ዘገቧል ፡፡ \n \nጥያቄ: የአስትራዜኔካ ክትባት በስንት ሰዎች ላይ ሙከራ ተደረገበት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 32 ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፯ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፴፯ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፪ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፱ ቀናት፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፰ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፭፻ ዓ/ም - በስመ መንግሥት አንበሳ በፀር ይባሉ የነበሩት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አርፈው የ፲፪ ዓመት ልጃቸው ዓፄ ልብነ ድንግል ወናግሰገድ ተብለው ነገሡ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በኩባ ደሴት በእስፓኝ እና በአሜሪካ መኻል የነበረው የማስተዳደር ፍልሚያ ትግል አከተመ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ከፈረንሳይ ቅኝ ተገዢነት ነፃነቷን አወጀች። ዴቪድ ዳኮ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፭፻ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: ዐፄ ኖኦድን ተክተው የነገሱት ልጃቸው ስማቸው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዓፄ ልብነ ድንግል ወናግሰገድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: አብዱልራዛቅ ፕሮፌሰርነታቸው በምን ዘርፍ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አቶ ክብርይስፋ ተክሌ በሳርፌ ቢዝነስ ውስጥ ኃላፊነታቸው ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዋና ሥራ አስኪያጅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመዓዛ ብሩ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ታቀርባቸው የነበሩት ሥራዎች ይዘት ማህበራዊ ሕይወት እንዲሠምር በመጣር ላይ ያተኮሩ ሆነው ግልጽ፣ ቀላልና ለዛ ያልተለያቸው ስለነበሩ ከሶስት አሥርት ዓመታት በኋላም ትውስታቸው ከአድማጭ ህሊና አልጠፉም፡፡ በዚሁ ፕሮግራም ላይ መዓዛ ካበረከተቻቸው የፈጠራ ሥራዎቿ ውስጥ ጎልቶ የሚታወሰው “የአዲሱ ቤተሰብ” የተሰኘ ባለ ሰማንያ ስድስት ክፍል ድራማ ሲሆን በዘመኑ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም የሚያደምጠው ተወዳጅ የቤተሰብ ድራማ ነበር፡፡ መዓዛ በ “መርሀ ስፖርት” እና በሬዲዮ መካከል ሆና ከአራት ዓመት በላይ ከቆየች በኋላ በ1979 ዓ.ም የባህል ሚኒስቴርን ለቃ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀጠረች፡፡ አዲሱን መስሪያ ቤቷን ከተቀላቀለችበት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከሬዲዮ እየራቀች መጣች፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየችው ለሶስት ዓመታት ያህል ሲሆን ከዚያ በኋላ የግሏን የማስታወቂያ ሥራ ድርጅት መሥርታ የራስዋ ተቀጣሪ ሆናለች፡፡ ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1992 ዓ.ም ባሉት የአስራ ሶስት ዓመታት ጊዜ ግን መዓዛና ሬዲዮ ተራራቁ፡፡ መዓዛና ሬዲዮ ዳግም የተዋደዱት ከላይ እንደተገለጸው በ1992 ዓ.ም ሳምንታዊውን የ “ጨዋታ” ፕሮግራም በኤፍ ኤም 97.1 ከተፈሪ ዓለሙ ጋር በጋራ ማቅረብ ሲጀምሩ ነበር፡፡ የ “ጨዋታ” ፕሮግራም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ በአድማጮቹ እንደተወደደ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ላይ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የኤፍ ኤም ሬዲዮ ፈቃዶችን ለግሉ ዘርፍ ለመስጠት ሲዘጋጅ፣ ዝርዝር የሥራ እቅድ አቅርባ ባመለከተችው መሠረት፤ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ ከአስር አመልካቾች መካከል አንዷ ሆና የመጀመሪያ የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ባለቤት ያደረጋትን ፈቃድ ተቀበለች፡፡ መዓዛ የሬዲዮ ማሰራጫ መሳሪያዎችን ውድነት፣ የማሰራጫ ቦታ እና የባለሙያ እጦትን ተቋቁማ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮን በታህሳስ 1999 ዓ.ም አበረከተችልን፡፡ ባለትዳርና የሶስት ልጆች እናት የሆነችው መዓዛ እንደ ባለቤት፣ ሥራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ በመሆን በኢትዮጵያ ተወዳጁንና የመጀመሪያውን የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ትመራለች፡ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!”እያለች:: \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ራድዮ ጣብያን መቼ አቋቋመች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በታህሳስ 1999 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1925 እ.ኤ.አ. 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በቴሌቪዥን ለመላክ የቻለው የስኮትላንድ ተመራማሪ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጆን ሎጂ ቤርድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ ከጎረቤቷ ሞሮኮ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዓረብኛ ዓረብኛ የሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ አባል ሆኖ የዕብራይስጥ የአረማያ እንዲሁም የአማርኛ ቅርብ ዘመድ ነው። ፪፻፶ (250) ሚሊዮን የሚያሕሉ ሰዎች እንደ እናት ቋንቋ ይናገሩታል። ከዚህም በላይ በጣም ብዙ ሰዎች እንደ ፪ኛ ቋንቋ ተምረውታል። የሚጻፈው በዓረብኛ ፊደል ነው። በዓረብ አለም ውስጥ አያሌ ቀበሌኞች ይገኛሉ። ቋንቋው በእስልምና ታላቅ ሚና አጫውቷል። እስላሞች አላህ ለሙሐማድ ቁርዓንን ሲገልጽ በዓረብኛ እንደ ሆነ ስለሚያምኑ እንደ ቅዱስ ቋንቋ ይቆጥሩታል። አብዛኛው ዓረብኛ ተናጋሪዎች ሙስሊሞች ናቸው። ዛሬ በምዕራብ ዓለም ደግሞ ብዙ ሰዎች አረብኛ እያጠኑ ነው። በታሪክ ከፍተኛ ሚና በማጫወቱ መጠን ፤ ብዙ የዓረብኛ ቃላት ወደ ሌሎች ቋንቋዎች ገብተዋል። \n \nጥያቄ: ዓረብኛ ቋንቋ የሚጻፈው በምን ፊደል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በዓረብኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ለቀጭኔ ወደ ላይ በመንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ከባዱ ነገር ምንድነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከ መምራት የደረሰው የስዊትዘርላንድ ዜጋ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አልፍሬድ ኢልግ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: ስለአስተሮኖሚ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም ስንት የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ለማድረግ ታቅዷል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 10 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: የ2014 እ.ኤ.አ ፊፋ የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገር ማን ነበረች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ብራዚል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: በላይቤሪያ የእርስ በእርስ ጦርነት የነበረው ከመቼ እስከ መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ትዳር መቼ ያዙ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1975 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጎጉል እና አፕል ለስለላ ጥቅም ላይ ይውላል በማለት የጠረጠሩትን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን መተግበሪያ ቶቶክን ማስወገዳቸው ተገለፀ፡፡ ቶቶክ የተሰኘው ይህ መተግበሪያ ሰዎች በቀላሉ በተንቀሳቃሽ ምስል እና በፅሁፍ እንዲያወሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ ኔውዮር ታይምስ አንደዘገበው ከዋትስ አፕ ጋር ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጠው ቶቶክ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ለስለላ መሳሪያት ጥቅም ላይ ይውላል ተብሏል፡፡ ኔውዮርክ ታይምስ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ በዘገባው እንዳሰፈረው ቶቶክ የተሰኘው መተግበሪያ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሰላዮች የተጠቃሚዎችን ውይይት ፣ እንቅስቃሴ እና ፎቶ መሰል የግል መረጃዎች አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ጎግል ይህን መተግበሪያ ባለፈው ሀሙስ ማጥፋቱ የተገለፀ ሲሆን አፕልም ጎግልን በመከተል በቀጣዩ ቀን ከመተግበሪያ ዝርዝሮቹ ውስጥ ማጥፋቱ ተጠቁሟል፡፡ ቶቶክ መተግበሪያ ለተጠቃሚዎቹ በቅርቡ በአፕ ስቶር እንደሚመለስ አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ባስተላለፈው መልዕክት በጎግል ስቶር እና በአፕል ስቶር በጊዜያዊነት እንደማይገኝ የገለፀ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ የቴክኒክ ጉዳይ መሆኑን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡- ቢቢሲ በፌቨን ቢሻው   \n \nጥያቄ: ጎጉል እና አፕል ለስለላ ጥቅም ላይ ይውላል በማለት የጠረጠሩትን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን መተግበሪያ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ቶቶክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ መጽሐፍ መቼ ታተመ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1931 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ማዕከል መሥራች ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮሮና ቫይረስ ፅኑ ህክምና ማዕከል ውስጥ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዘሚ የኑስ በአሁኑ ሰአት ከ200 በላይ ለሚሆኑ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: በጆይ ኦቲዝም ማዕከል ከ200 በላይ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ልጆችን ሲንከባከቡ የነበሩት ግለሰብ ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዘሚ የኑስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ሬይን ሜከርስ በኢትዮጵያ ያለውን ችግር ለመቅረፍ አንዱ መፍትሔ ምንድን ነው ይላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየቻይናው ግዙፉ የቴሌኮም ኩባንያ ሁዋዌ በፈረንጆቹ 2019 240 ሚሊየን ስልኮችን ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡ ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሽያጭ ገቢው 850 ቢሊየን ዩዋን ወይም 122 ቢሊየን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል ፡፡ ሽያጩ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ 18 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፥ የተጠበቀውን ያክል ገቢ አለመገኘቱም ተመላክቷል ፡፡ የኩባንያው መሳሪያዎቹን በመጠቀም ስለላ ሊያካሂድ ይችላል በሚል በአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ባለሥልጣናት ላይ ስጋትን በመጫሩ ከአሜሪካ የግንኙነት መረቦች በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዛዝ መታገዱ ይታወሳል ፡፡ ይህም ለሁዋዌ አስቸጋሪ ሁኔታን ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ ኩባንያው በ2020ም የተፈጠረውን ችግር በመቋቋም ገበያው ላይ መቆየት ተቀዳሚ አላማው መሆኑን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ተናግረዋል። ምንጭ፡-www.cnet.com/ \n \nጥያቄ: የሁዋዌ የ2019 ዓ.ም. ዓመታዊ ሽያጭ ከ2018 ዓ.ም. አንጻር በመቶኛ ምን ያህል ይልቃል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 18 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ያለው ከፍተኛ የውሃ ሀብት ክምችት የምን ዘርፍ ልማት ለማድረግ ምቹ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መስኖ ልማት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nንጉሡ ላሊበላ የሚለውን ስም ያገኘው፣ ሲወለድ በንቦች ስለተከበበ ነው ይባላል። ላል ማለት ማር ማለት ሲሆን፤ ላሊበላ ማለትም -ላል ይበላል (ማር ይበላል) ማለት አንደሆነ ይነግራል። ውቅር ቤተክርስቲያናቱን ንጉሡ ጠርቦ የስራቸው ከመላእክት እገዛ ጋር እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ይነግራል። በ16ኛው ከፍለ ዘመን አውሮፓዊ ተጓዥ ላሊበላን ተመልክቶ «ያየሁትን ብናግር ማንም እንደኔ ካላየ በፍጹም አያምነኝም» ሲል ተናግሮ ነበር። በላሊበላ 11 ውቅር ዐብያተ ክርስቲያናት ያሉ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ (ባለ መስቀል ቅርፁ) ሲታይ ውሃልኩን የጠበቀ ይመስላል። ቤተ መድሃኔ ዓለም የተባለው ደግሞ ከሁሉም ትልቁ ነው። ላሊበላ (ዳግማዊ ኢየሩሳሌም) የገና በዓል ታህሳስ 29 በልዩ ሁኔታ ና ድምቀት ይከበራል፣ \"ቤዛ ኩሉ\" ተብሎ የሚጠራው በነግህ የሚደረገው ዝማሬ በዚሁ በዓል የሚታይ ልዩ ና ታላቅ ትዕይንት ነው።የሚደረገውም ከቅዳሴ በኋላ በቤተ ማርያም ሲሆን ከታች ባለ ነጭ ካባ ካህናት ከላይ ደግሞ ባለጥቁር ካብ ካህናት በቅዱስ ያሬድ ዜማ ቤዛ ኩሉ እያሉ ይዘምራሉ። 11ዱ የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት ቤተ መድሃኔ ዓለም፣ ቤተ ማርያም፣ ቤተ ደናግል፣ ቤተ መስቀል፣ ቤተ ደብረሲና፣ ቤተ ጎለጎታ፣ ቤተ አማኑኤል፣ ቤተ አባ ሊባኖስ፣ ቤተ መርቆሬዎስ፣ ቤተ ገብርኤል ወሩፋኤል፣ ቤተ ጊዮርጊስ ናቸው። \n \nጥያቄ: በላሊበላ የጌታ ልደት ቀን በልዩ ሁኔታ የሚዘመረው ቤዛ ኵሉ የተሰኘው ዝማሬ የሚቀርበው በየትኛው ቤተ መቅደስ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በቤተ ማርያም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሠለስቱ ምእት በኒቅያ ጉባኤ ማንን አወገዙ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አርዮስን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nታሊየም የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ መረጃ መዝባሪዎች ቡድን ሚስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር እንደተቆጣጠረው ማይክሮ ሶፍት አስታወቀ፡፡ መቀመጫው ሰሜን ኮሪያ እንደሆነ የታመነው ይህ መረጃ መዝባሪ ቡድን የመንግስት ሰራተኞችን ፣ የዩኒቨርሲቲ ሰራተኞችን ፣ የኒውክሌር ሙያተኞችን እና የጥናት ተቋማንን ኢላማ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የመረጃ መዝባሪ ቡድኑ በዋነኝነት ኢላማ ያደረገው በአሜሪካ የሚገኙ ተቋማትን ሲሆን በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚገኙ ተቋማንንም ኢላማ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡ ታሊየም በመጀመሪያ እይታ ትክክለኛ ሆነው የሚታዩ የኢሜል አድራሻዎችን በመጠቀም መረጃ ሲመዘብር ነበር ተብሏል፡፡ ማይክሮሶፍትም በአሁን ወቅት መረጃ መዝባሪ ቡድኑ የሚጠቀምባቸውን 50 የድር ጎራዎች መቆጣጠሩን የገለፀ ሲሆን በምሥራቃዊ ቨርጂኒያ አውራጃ በሚገኝ ፍርድ ቤት በጠለፋ ቡድን ላይ ክስ መመስረቱን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡-ሮይተርስ \n \nጥያቄ: ታሊየም የተባለው የሰሜን ኮሪያ ቡድን ምስጢራዊ መረጃዎችን በመመዝበሩ በየት ተከሰሰ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በምሥራቃዊ ቨርጂኒያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: ቮልታ ሐይቅ ምን ዓይነት ሐይቅ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሠው ሰራሽ ሐይቅ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በአይቮሪኮሰስት በ2018 በተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች ምን ያህል ክፍሎች ተሰሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 26 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nብርቱካን ብርቱካን (ወይም ኦሬንጅ) ማለት የዛፍ አይነትም ሆነ በተለይ የዚሁ ዛፍ ፍሬ ማለት ነው። የሌሎች አትክልት ክልስ ሆኖ ከጥንት እንደ ለማ ይታሥባል። እርዝማኔው እስከ 10 ሜትር ድረስ ቢደርስም ዛፉ ትንሽ ይባላል፤ ቡቃያው እሾህ አለበትና ቅጠሎቹ ከ4 እስከ 10 ሳንቲሜትር ድረስ የሚዘረጉ እንደ ጥድም ወገን መቸም የማይረግፉ ናቸው። የፍሬው መጀመርያ ትውልድ በደቡብ-ምሥራቃዊ እስያ በህንደኬ፣ በቬትናም ወይም በደቡብ ቻይና ተገኘ። የብርቱካን እርሻ በብዙ አገሮች ምጣኔ ሀብት በጣም ታላቅ የንግድ ሥራ ነው። እዚህ ማለት በአሜሪካ፣ በሜዲቴራኔያን አገሮች፣ በሮማንያ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በቻይና፣ በአውስትራልያም ይከትታል። \n \nጥያቄ: የብርቱካን ፍሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው የት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በደቡብ-ምሥራቃዊ እስያ በህንደኬ፣ በቬትናም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ማራባውት የሚባሉት የእስልምና ሃይማኖት መሪዎች ምን ዓይነት ተጽዕኖ አላቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የፖለቲካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያዊቷ ዶ/ር ውለታ ለማ ያሸነፉበት የውድድር በየስንት ጊዜው ይካሄዳል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በየዓመቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: በሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ግምት የፀሀይ እድሜ ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: የኡቶ-አዝቴካዊ ቋንቋ ቤተሠብ የሆነና በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚነገር ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ናዋትል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nግሥላ ግሥላ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኝ አጥቢ አውሬ ነው። በእስያ የተገኘው ነብር የግስላ ቅርብ ዘመድ ሆኖ፣ በአነጋገር «ግስላ»ና «ነብር» የሚሉ ስሞች ሊለዋወጡ ይችላሉ። የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደት ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ሲደርስ በርዝመት ከ90 ሴ.ሜ እስከ 1,60 ሜ.ና በአፍሪካ የሚገኘው ዘር እስከ 1,90 ሜ ይደርሳል ። ከመሬት እስከ ሆዱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖረው ጭራው ደግሞ እስከ 100 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያሳያል ። ሴቲቱ ከወንዱ አነስ ትላለች ። በዱር ሲኖር እስከ 10 አመት እንደሚኖር ሲታወቅ በሰው ተይዘው ሲኖሩ እስከ 20 አመት እድሜ ያስመዘገቡ ግሥሎች አሉ። \n \nጥያቄ: የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደ ምን ያህል ድረስ ሊመዝን ይችላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ማን ነች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: አፈወርቅ ተክሌ ለከፍተኛ ትምህርት በስንት አመታቸው ተመረጡ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በአሥራ አምስት ዓመታቸው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ግብይት የሚያስፈጽመው ግዥና ሻጭን መድረክ ላይ በማገናኘት በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው፡፡ ይህ የተለመደው አሠራር የበለጠ ውጤታማ የሚሆነው ግን በድረ ገጽ ግብይት ሲደረግ በመሆኑ ይህንን የድረ ገጽ ግብይት ለማስጀመር ከሦስት ዓመት በፊት ሥራው የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ችሏል፡፡ በተለመደው የመድረክ የግብይት አሠራር በቀን የሚፈጸመው የግብይት መጠን ከ200 እስከ 300 የሚደርስ ነው፡፡ ይህም የግብይት መጠኑ ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የድረ ገጽ ግብይት መጀመሩ ግን ይህንን በመለወጥ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል፡፡ ይህም አሠራሩን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው ተቋም ጭምር ዕውቅና አግኝቶበታል፡፡ እንደ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያሉ ተቋማትም ይህንን አገልግሎት ፈትሸው ማረጋገጫ ተሰጥቶት እየተሠራበት ስለመሆኑም የምርት ገበያው የሥራ ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህንን ዘመናዊ አገልግሎት ሥራ ለማስጀመር ከመጀመሪያው ጀምሮ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) የተባለው ተቋም ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮጀክት 2.2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ይህ ግብይት በቡና የተጀመረ ሲሆን፣ ሁሉም በዚህ የግብይት ሥርዓት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ የግብይት ሥርዓቱ አዲስ በመሆኑ በዚህ ለመጠቀም ተገበያዮች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም 380 ተገበያዮች በድረ ገጽ ለመገበያየት ሥልጠና ወስደው ብቁ መሆናቸው ተረጋግጦ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የድረ ገጽ የግብይት ሥርዓትን የተጀመረው በምን ምርት ግብይት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በቡና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዞ አዞዎች ረዘም ብሎ ጠንካራ የሆነ የራስ ቅል አላቸው። በዛ ያሉ ጠንካራ ጥርስ አፋቸው ውስጥ ተደርድረው ይታያሉ። ውኃና ምግብ በአፋቸው በያዙበት ጊዜ እንኳን መተንፈስ የሚያስችላቸው ተፈጥሮ አላቸው። አዞዎች እንቁላል ጣዮች ናቸው። ከ20 እስከ 50 እንቁላሎች ብስባሽ ቅጠላ ቅጠሎች ውስጥ ጥለው እናቶቻቸው ይጠብቋቸዋል። ይህም እንቁላሉ ሊፈለፈል ሲቃረብ ከእንቁላሉ ውስጥ የሚሰሙት ድምፅ እንቁላሉን ሰብረው ጫጩቶቹ እንዲወጡ ለማድረግ ያስችላቸዋል። እንደ ኤሊዎችና አንዳንድ እንሽላሊቶች ሁሉ እንቁላሎቹ የተጣሉበት ሁኔታ (ጎጆ) የሙቀት መጠን የሚፈለፈሉትን ጫጩቶች ጾታ ይወስናል። ሆኖም ከኤሊዎች በተቃራኒ የእንቁላሉ ጎጆ የሙቀት መጠን መቀነስ ሴቶችን፣ ከፍተኛ የሙቀት መጠን ደግሞ ወንዶችን እንዲፈለፈሉ ያደርጋል። ሁሉም አዞቻች አምፊቢየስ ይባላሉ። ምክንያቱም ታዳጊዎቹም ትልልቆቹም ከፊሉን ጊዜያቸውን ውኃ ውስጥ ከፊሉን መት ላይ ስለሚያሳልፉት ነው። ረጅምና ጠንካራ ጭራቸው እንደ መሣሪያ በማገልገል ሰውንም ሆነ ሌላ እንስሳ ፊቱ ላይ መትቶ በመጣል ለጥርሳቸው ያቀርብላቸዋል። በውኃ ውስጥም ባላቸው ፈጣን እንቅስቃሴ ከእነሱ ለማምለጥ ከባድ ይሆናል። ለረጅም ጊዜ ከውኃ ሥር ሆነው መቆየት ቢችሉም እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎች በሳምባ የሚተነፍሱ ናቸው። ስለዚህም አፍንጫቸውን ከውኃው በላይ በማውጣት አየር ይስባሉ። ሁሉም አዞዎች እንቁላል ይጥላሉ። እንደሌሎቹ ገበሎ አስተኔዎችም እንቁላሎቹን መሬት ውስጥ ይቀብራሉ። ሴቶቹ አዞዎች በሚሠሯቸው ጎጆዎች ይለያያሉ። አንዳንዶቹ አሸዋ ውስጥ ቀዳዳ በመቆፈር እንቁላሉን ይቀብሩትና ይሸፍኑታል። ሌሎቹ እንደ አሊጌተር ዓይነቶቹ ብዛት ያለው የበሰበሰ ቅጠላ ቅጠፀል በመሰብሰብ እዛ መሃል እንቁላሉን ይጥሉታል። ብዛት ያላቸው ደርዘን እንቁላሎች (እያንዳንዱ በመጠን ከዶሮ የበለጠ) በአንድ ቁጭታ ሊጥሉ ይችላሉ። ሲፈለፈሉ ታዳጊዎቹ አዞዎች ከ22-25 ሳንቲ ሜትር ቁመት ይኖራቸዋ”ል። አዞዎች ጥርሳቸውን በተደጋጋሚ ይተካሉ። የሚተካው (ያረጀው) ጥርስ ሥር ያለው አዲስ ጥርስ ሲሆን፤ አዲሱ ተኪ ጥርስ አድጎ ትልቅ ካልሆነ በስተቀር አሮጌው ቶሎ ብሎ ወልቆ አይወድቅም። የአዞ አይን 360 ዲግሪ ማየት ይችላል። እንዲሁም ሰው 180 ዲግሪ ዘውሮ ማየት ይችላል። \n \nጥያቄ: አዞዎች ለምን አምፌቢያን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከፊሉን ጊዜያቸውን ውኃ ውስጥ ከፊሉን መት ላይ ስለሚያሳልፉት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: ኤዎስጣጤዎስ ማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዛሬው ዕለት ኡጋንዳ ገብተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ኡጋንዳ መግባታቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለከተው፡፡ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ባለፈው ጥር ወር ላይ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለ6ኛ ዙር ሀገሪቱን ለመምራት ዛሬ ቃለ መሃላ ይፈፅማሉ። \n \nጥያቄ: ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ኡጋንዳ የተገኙበት ምክንያት ምንድንነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ያሳዩበት መጽሐፋቸው ርእሱ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፓራዳይዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአንድ ወጣት ተማሪ ከወዳደቁ ቁሳቁሶች በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ መስራቱ ተገለጸ፡፡ ጌታባለው መኩሪያው የተባለው ወጣት በባህርዳር ዩኒቨርስቲ 3ኛ ዓመት የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሲሆን ወጣቱ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች እንዲሁም አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የብስክሌት አካላትን ተጠቅሞ ነው የብስክሌት ጀልባ (Pedal-Boat) መስራት የቻለው፡፡ ጌታባለው መኩሪያው ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የሰራውን የብስክሌት ጀልባ በውሃ ላይ በመንዳት ሙከራ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሆነው በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ የፈጠረው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጌታባለው መኩሪያው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ግብይት የሚያስፈጽመው ግዥና ሻጭን መድረክ ላይ በማገናኘት በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው፡፡ ይህ የተለመደው አሠራር የበለጠ ውጤታማ የሚሆነው ግን በድረ ገጽ ግብይት ሲደረግ በመሆኑ ይህንን የድረ ገጽ ግብይት ለማስጀመር ከሦስት ዓመት በፊት ሥራው የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ችሏል፡፡ በተለመደው የመድረክ የግብይት አሠራር በቀን የሚፈጸመው የግብይት መጠን ከ200 እስከ 300 የሚደርስ ነው፡፡ ይህም የግብይት መጠኑ ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የድረ ገጽ ግብይት መጀመሩ ግን ይህንን በመለወጥ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል፡፡ ይህም አሠራሩን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው ተቋም ጭምር ዕውቅና አግኝቶበታል፡፡ እንደ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያሉ ተቋማትም ይህንን አገልግሎት ፈትሸው ማረጋገጫ ተሰጥቶት እየተሠራበት ስለመሆኑም የምርት ገበያው የሥራ ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህንን ዘመናዊ አገልግሎት ሥራ ለማስጀመር ከመጀመሪያው ጀምሮ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) የተባለው ተቋም ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮጀክት 2.2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ይህ ግብይት በቡና የተጀመረ ሲሆን፣ ሁሉም በዚህ የግብይት ሥርዓት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ የግብይት ሥርዓቱ አዲስ በመሆኑ በዚህ ለመጠቀም ተገበያዮች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም 380 ተገበያዮች በድረ ገጽ ለመገበያየት ሥልጠና ወስደው ብቁ መሆናቸው ተረጋግጦ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የድረ ገጽ የግብይት ሥርዓትን ለማበልጸግ ከICF ምን ያህል ገንዘብ አገኘ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 2.2 ሚሊዮን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዩናይትድ ኪንግደም ዩናይትድ ኪንግደም ማለት የተባበረው ግዛት በተለመደው እንግሊዝ አገር ሲባል፣ እንዲያውም እንግሊዝ አገር ወይም ደግሞ «ኢንግላንድ» ከዩናይትድ ኪንግደም ዋና ክፍላገሮች አንዱ ብቻ ነው። ሌሎቹም፦ ስኮትላንድ ዌልስ ሰሜን አይርላንድ ናቸው። ከነዚህም እንግሊዝ፣ ስኮትላንድና ዌልስ አብረው «ታላቋ ብሪታንያ» የምትባል ደሴት ናቸው። ከ1699 ዓ.ም. (1707 እ.ኤ.አ.) አስቀድሞ፣ እንግሊዝና ስኮትላንድ የተለያዩ ንጉዛት ነበሩ። ከ1595 ዓ.ም. ጀምሮ ግን 2ቱ አገራት አንድ ንጉሥ ነበራቸውና በ1699 በመዋሐዳቸው አንድ ላይ «ዩናይትድ ኪንግደም» ሆነዋል። \n \nጥያቄ: ዓ.ም. (1707 እ.ኤ.አ.) አስቀድሞ፣ እንግሊዝና ስኮትላንድ ከተለያዩ ንጉሳት አስተዳደር ወጥተው በአንድ መተዳደር የጀመሩት በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ1595 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየቻይና ስነ ፈለክ ተመራማሪዎች የመጀመሪዋን ከፀሀይ ስርዓት ውጪ የሆች ኤክሶፕላኔት ማግኘታቸው ተገለፀ። በቻይና የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች የተገኘችው ይህች ፕላኔት “ወንግሹ” እና “ዢሂ” የሚል ስያሜ ተሰቷታል። ይህም ማለት የጨረቃ አምላክ ወይም የጸሃይ አምላክ የሚል ትርጉም አለው። ሁለቱ ስሞች የሚያሳዩት የኮኮብ እና ፕላኔትን ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ዩንቨርስን የማሳስ ሂደት የሚወክል ወይም ምሳሌ የሚሆን ነው ተብሏል። የፕላኔትዋ መጠን ከፀሐይ ሁለት እጥፍ የሚበልጥ ሲሆን፥ ከጁፒተርም በ2 ነጥብ 7 እጥፍ ትበልጣለች፤ በዚህም ከጸሃይ ስርዓት ውስጥ ትልቋ ነው የተባለችው በብሔራዊ የሥነ ፈለክ ምርምር ተቋም። የቻይና የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች በአውሮፓውያኑ በ2008 ከቻይና 10 ምርጥ የሥነ ፈለክ እድገቶች መካከል አንዱ ሆነው የተመረጡት ትልቁን ኤክስፕላኔት HD173416b’ን አገኝታለች። ምንጭ፡-ሲጂቲኤን በፌቨን ቢሻው \n \nጥያቄ: የቻይና የስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኟት ፕላኔት ስሟ ማነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ “ወንግሹ” እና “ዢሂ” ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የቪስቶሶሚሲስ የህመሙ ምልክት ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር። samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም። በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው። ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313 313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም። በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም። “ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር። ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። \n \nጥያቄ: በ18ኛው ክፍለ ዘመን ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ የአባይ ወንዝ መነሻ ጣና ሐይቅ ነው ያለው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጄምስ ብሩስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመጋቢት ፳፮ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት የመጀመሪያው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፱ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል። ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅት መሠረቱ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (የዓለም የንግድ ማዕከል) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል። ፲፱፻፷ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በሜምፊስ ከተማ በነፍሰ-ገዳይ እጅ ተገደለ። \n \nጥያቄ: አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ መቼ ተገደለ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፱፻፷ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና ከደቡብ አፍሪካ ጋር በየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ራስ ተፈሪ መኮንንና ልጅ እያሱ ያደረጉት ስምምነት ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: የ2022 የክረምት ኦሎምፒክ አዘገጋጅ ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቻይና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ሼል ኩባንያን ከገዛ በኋላ ያጋጠመው አለመግባባት ምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የታክስ ክርክር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: ዳግማዊ ምኒልክ አዲስ አበባን መች መሰረቷት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየአስትራዜኔካ የኮቪድ-19 ክትባት ላይ በአሜሪካ፣ በቺሊና በፔሩ በተደረገ ሙከራ የጎንዮሽ ጉዳት የሌለውና አስተማማኝ መሆኑን የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡ ዩኒቨርሲቲው በሶስቱ አገሮች በሁሉም የእድሜ ክልል በሚገኙ 32 ሺህ በጎ ፈቃደኛ ሰዎች ላይ ባደረገው ምርምር ክትባቱ ውጤታማና ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የሌለው መሆኑን ማረጋገጡን የሮይተርስን ዋቢ አድርጓ ኢዜአ ዘገቧል ፡፡ \n \nጥያቄ: የአስትራዜኔካ የኮቪድ-19 ክትባት በየት በየት አገሮች ተሞከረ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአሜሪካ፣ በቺሊና በፔሩ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፋሲለደስ ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው አፄ ሱሰኒዮስ እና እናታቸው ልዕልት ስልጣነ ምገሴ በመገዛዝ፣ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው። አፄ ፋሲል አዘዞ ተብላ በምትታወቀው ከጎንደር ከተማ 5 ማይል ርቃ በምትገኘው ከተማ ጥቅምት18፣1667 እ.ኤ.አ. (ጥቅምት 10፣ 1660) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አስከሬናቸውም የአገሪቱ መላ ህዝብ ባዘነበት ሁኔታ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ተብላ በምትታወቀው ደሴት የዘላለም እረፍት አገኘ። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲል መቼ ነው ለንግስና የበቁት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1630 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስ በአቴንስ መንግስት ሲከሰስ እድሜው ስንት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 70 ዓመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ የከፍተኛ ትምህርቷን የት ተማረች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ ተወዳጅ ስፖርቶች ምን ምን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። ባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። \n \nጥያቄ: ኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ላይ ምን ያህል የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ተሳተፉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 57 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: ደቡብ ሱዳን ተገንጥላ ሉዓላዊ ሀገረ ከመሆኗ በፊት የማን አካል ነበረች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የሱዳን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: ከግብጽ ከተሞች በሕዝብ ብዛት ሁለተኛ የሆነችው ከተማ ማናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አሌክሳንድሪያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ አዲስ የዲዛይን ክፍተት መገኘቱ ተገለፀ። የቦይንግ ኩባንያ እና የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍ.ኤ.ኤ) በትናንትናው እለት እንዳረጋገጡት በ737 ማክስ አውሮፕላን ዲዛይን ላይ የተገኘው አዲስ ክፍተት የኤሌክትሪክ ሽቦ መቀራረብ ችግር እንደሆነ አረጋግጠዋል። የቦይንግ ቃል አቀባይ ጎርዶን ጆንድሮ “ጉዳዩ የቦይንግ አስቸጋሪ ሂደት አካል ቢሆንም፤ ተገቢውን ትንተና ለማከናወን ከአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር ጋር በጋራ እየሰራን ነው፤ አሁን የተገኘው ክፍተት የዲዛይን ለውጥ ለማድረግ ያስገድዳል የሚያስብል ደረጃ ላይ ግን አልደረሰም”ብለዋል። የቦይንግ አውሮፕላን ላይ የተገኘው አዲሱ የዲዛይን ክፍተት የሁለት ሽቦዎች በጣም መቀራረብ መሆኑን በመግለጽ፤ አብራሪዎች ችግሩን ተረድተው በአፋጣኝ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋን ሊያስከትል ይችላል” ሲል የኒው ዮርክ ታይምስ አስነብቧል። የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሰጠው መግለጫ፥ በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ሊደረግ በታቀደው የዲዛይን ማሻሻያ ዙሪያ ኤጀንሲው እና የቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ ግኝቶችን እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል። ኤጀንሲው አክሎም “በዚህ ሂደት ወቅት ተለይተው የሚታወቁ የደህንነት ችግሮች በሙሉ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ይደረጋል ” ሲልም አስታውቋል። ቦይንግ በአሁኑ ጊዜ ተቀራርበዋል የተባሉ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ለመለየት እና ስህተቱን ተከትሎ የሚደርሰውን አደጋ በተመለከተ ሰፋ ያለ ትንተና እየሰራ መሆኑን አንድ የኩባንያው ባለስልጣን አስረድተዋል። ቦይንግ በአምስት ወራት ውስጥ በሁለት አደጋዎች 346 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የማክስ 737 አውሮፕላን ማምረት ማቆሙ ይታወሳል።   ምንጭ፡- ሲጂቲኤን \n \nጥያቄ: በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ምን አይነት የዲዛይን ክፍተት ነው የተገኘው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የኤሌክትሪክ ሽቦ መቀራረብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በ1996 እ.ኤ.ኣ. የሜሪላንድ ስቴት ሕዝብ ብዛት ስንት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 5,558,058 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኒሺ ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ (ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900) ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ሲሆን አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። እርግጥ ኒሺ፣ በነበረበትም ሆነ በኋላ ዘመኑ ብዙ ተቃዋሚወች ቢነሱበትም በዚያው ልክ ብዙ ሰወች ስራወቹን እንደ ታላቅ የፍልስፍና እና ስነ ጽሁፍ ስራ ይወስዷቸዋል። ኒትሸ አብዛኛው ጽሁፉ የሚያተኩረው ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ምክንያት እሱ ይኖርበት የነበረውን ዘመን የጀርመን ሥነ ምግባር (ኤቲክስ) በመንቀፍ ብዙ ጽፎአል። ሠናይ እና እኩይ (ጥሩና መጥፎ) ተብለው ተለይተው ይሰራባቸው የነበሩትን የጊዜውን ሥነ ምግባር ዋጋወች በመተቸት ሰወች አዲስ ሥነ ምግባር ፈጥረው ለሁሉም ምግባር አዲስ የሠናይነትና እኩይነት (ጥሩ እና መጥፎ) ዋጋ እንዲሰጡ በጽሑፎቹ ብዙ ሞክሯል።በዚህ መሰረት፣ ለምሳሌ፣ በክርስቲያኖች ዘንድ የሚሰራበትን ለደካሞች ማዘንን ሠናይነት ተቃውሟል። በሱ አስተያየት ደካሞች ሲታዘንላቸው የበለጠ ይዳከማሉ የሚል ነው ምክንያቱም በሱ አስተያየት ደካሞቹ በጠንካሮቹ ላይ የበለጠ ጥገኛ በመሆን መላው ህብረተሰብ ይዳከማል የሚል ነው። በተጨማሪም፣ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ተጨባጩን አለም መገንዘብ እና ክሁሉ በላይ ስለዚሁ ዓለም ማተኮር አለበት ብሏል። ሰማይና ሌሎች አለማትን በማጣጣል፣ የሰው ልጅ እነዚህን አይነት አለሞች የሚፈጥረው አሁን ያለበትን ተጨባጩ የውኑ አለም ችግሮች መፍታት ሲያቅተው ለመፈርጠጥ ነው በማለት የሰው ልጅ ስለዚህ ምድር ብቻ እንዲያስብ ይወተውታል። ኒሽ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል አጥብቆ ያምናል። በኒሺ ፍልስፍና፣ አንድ እራሱን ያሽነፈ ሰው በጣም የተለወጠ እና የተሻለ ስለሚሆን \"ሱፐር ማን\" ወይም \"የበላይ ሰው\" እንዲባል ሰይሟል። የበላይ ሰው እንግዴህ ጠንካራና በሌሎች ሰወች \"ሠናይ\" እና \"እኩይ\" ወይም ደግሞ \"ጥሩ\" ና \"መጥፎ\" ዋጋወች የማይመራ፣ ይልቁኑ የራሱን ሥነ ምግባር የሚፈጥር ነው። \n \nጥያቄ: ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ በምን የታወቀል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ በ2021 የሥነ ጽሑፍ ኖቤል ተሸላሚነታቸው የታወቀው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ ከተወለደች በኋላ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ለመጨመር ምን ያህል ጊዜ ያስፈልጋታል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በስድስት ወር ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየዲጂታል ኢኮኖሚውን የሚያጠናክር ሬድፎክስ የተሰኘ የመረጃ ቋት ማዕከል ይፋ ሆነ፡፡ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ መረጃ አዲሱ ነዳጅ መሆኑን ገልጸው፣ የዲጂታል መሰረተ ልማቱ መጠናከር በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና እና በሌሎች መስኮች ላይ አስተዋጽኦን ያሳርፋል ብለዋል፡፡ ሬድፎክስ ለረጅም ዓመታት በቴሌኮም ዘርፍና በመረጃ ቴክኖሎጂ ልምድ ባካበቱ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች የተቋቋመ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ሚኒስትር ዲኤታው ዳያስፖራዎቸ በዘርፉ ላይ በመሰማራታቸው ያላቸውን አድናቆት መግለጻቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: ሬድፎክስን ያቋቋሙ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎች በምን ዙሪያ ልምድ ያላቸው ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቴሌኮም ዘርፍና በመረጃ ቴክኖሎጂ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየቅርጫት ኳስ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬትቦል በዓለም ዙሪያ በቡድኖች የሚጫወት የኳስ እስፖርት ነው። ጨወታው በ1885 ዓም በካናዳዊው ዶ/ር ጄምስ ነይስሚስ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ። በመላው አለም ተወዳጅነትን ያተረፈ የቡድን ስፖርት አይነት ነው፡፡ ጨዋታው እኤአ በ1891 በካናዳዊው ዶ.ር ጀምስ ኒስሚዝ በአሜሪካ አገር ተፈጠረ፡፡ የቅርጫት ኳስ ወይም ባስኬት ቦል፡፡ ጨዋታው በእጅ የሚከናወን ሲሆን በመሰረታዊነት የ4 መአዘን ሬክታንግል ቅርፅ ያለው መጫወቻ ኮርት 5 ተጫዋቾ ያሉት ሁለት ቡድኖች እና በእጅ የሚወረወረው ድቡልቡል ኳስ ለጨዋታው አስፈላጊ የሆኑ ቁሶች ናቸው፡፡ 5ቱ ተጫዋቾ ሁልጊዜም የተጫዋቾችን ቦታ ይይዛሉ፡፡ ከተጫዋቾቹ በቁመት ረጅም የሆነው ተጫዋች አብዛኛውን ጊዜ የመሀል ቦታ ይይዛል፡፡ እኤአ በ1891 በካናዳዊው የጂም መምህር ጀምስ ኒስሚዝ በስፕንግ ፊልድ ማሳቹስትስ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ የተፈጠረው የቅርጫት ኳስ በአሁኑ ሰአት በአለማችን ላይ እጅግ ታዋቂና በመላው አለም በርካታ ተመልካቾች ያሉት የስፖርት አይነት ነው፡፡ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን ለአለም ፕፌሽናል ባስኬት ቦል በማሳደግና በማስተዋወቅ በክፍያ በተሰጥኦና በውድድር ብቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶለታል፡፡ ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ያሉ የብሄራዊ ሊግ መስፈርትን ያሟሉ ታላላቅ ክለቦች ለአህጉራዊ ቻምፒየን ሺፕ እንደ ኢሮሊግ እና FIBA አሜሪካ ሊግ የናሽናል ባስኬት ቦል አሶሴሽን አስተዋፅኦ ማሳያ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ የFIBA ባስኬት ቦል ወርልድ ካፕ እና men’s Olympic basketball ውድድር ዋና ዋና የአለማቀፍ ዝግጅቶችን እና የብሄራዊ ቡድኑ በርካታ ተጫዋቾችን መሳብ የቻሉ ውድድሮች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የቅርጫት ኳስ ጨዋታ በየት ሀገር ተፈጠረ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአሜሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የእስልምና ሃይማኖት በሴኔጋል የተዋወቀው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም ለከፍተኛ የቤተክርስቲያን ትምህርት ወዴት ተላኩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ወደ ጎንደር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ራስ ተፈሪ መኮንን የእንደራሴነት ስልንጣን የያዙት በስንት ዓመተ ምሕረት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲፱፻፱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአቡጊዳ አቡጊዳ (Ebugida) ማለት ፊደል ነው። ከልሳነ ግዕዝ የተነሣ ነው። ቢሆንም በቅርብ ጊዜ አንዳንድ የፈረንጅ አገር ሊቅ ይህን አባባል ለቋንቋዎች ጥናት ተበድሯል። በዚሁ አነጋገር \"አቡጊዳ\" ማለት በዓለም የሚገኙ ልዩ ልዩ አይነት ጽሕፈቶች ሊያመልከት ይችላል። በየአገሮቹ ፊደላቸው \"አቡጊዳ\" የሚባለው እያንዳንዱ ፊደል ለክፍለ-ቃል ለመወከል ሲሆን ነው እንጂ እንደ እንግሊዝኛ \"አልፋቤት\" ፊደሉ ለ1 ተነባቢ ወይም ለ1 አናባቢ ብቻ ሲሆን አይደለም። ስለዚህ የግዕዙ ፊደል ይሁንና ሌሎችም ለምሳሌ ብዙ የህንድ አገር አጻጻፎች ጨምረው አቡጊዳ በሚግድጅቭጅለው ስም ይታወቃሉ። ብራህሚክ ወይም ደቫናጋሪ በተባሉት የህንድ አጻጻፎች በኩል እያንዳንዱ ክፍለ-ቃል በተለየ ፊደል ሲወከል የአናባቢዎች መጠን የሚታየው የፊደሉን መልክ (እንደ ግዕዝ ወይም እንደ አማርኛ) ትንሽ በመቀየሩ ነው። ስለዚህ በቋንቋ ሊቃውንት ዘንድ 'አቡጊዳዎች' ይባላሉ። በተጨማሪ፣ በካናዳ አገር ለጥንታዊ ኗሪ (ቀይ ኢንዲያን የተባሉ) ጐሣዎች ያላቸው አጻጻፍ እንደዚህ አይነት ነው፤ አናባቢው በቅርጹ የሚታየው ፊደሉን በመዞር ወይም በመገልበጥ ነውና። በግእዝ አቡጊዳ ለሚለው የቃሉ መነሻ ከጥንታዊ የሴም ፊደል ተራ የሚለቀመው ነበር። በግሪክም ይህ ፊደል ተራ በ A, Β, Γ, Δ ጀመረ፤ ወይም በስም አልፋ፣ ቤታ፣ ጋማ፣ ዴልታ ናቸው። ይህ ፊደል ተራ በ ሀ ሁ ሂ ሃ በሚል ቅርጽ ማለት በግእዝ፣ በካዕብ፣ በሣልስ፣ በራብእ ውስጥ ገብቶ ሲሰካ፣ አ፣ ቡ፣ ጊ፣ ዳ የሚለውን ፊደል ተራ አስገኘ። \n \nጥያቄ: የአቡጊዳ ሥረ መሰረቱ ከየት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከልሳነ ግዕዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: አጼ ኃይለ ሥላሴ የንጉሠ ነገስትነት ማዕረግ ያገኙት ከማን ቀጥለው ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ንግሥት ዘውዲቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: በስድስተኛው ዓመተ ዓለም የአክሱም መንግሥት ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ማንን ያካተተ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የዛሬዋን የመን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየብረት ማዕድኖች የብረት ማዕድናት በሁለት ይከፈላሉ። እነሱም ፕሪሽየስ ሜታል መደብ እና ቤዝ ሜታል መደብ ናቸው። ወርቅ እንደ ሌሎቹ የብረታ ብረት ማዕድኖች የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በትሮይ አውንስ መጠን ነው። አንድ ትሮይ አውንስ ፤ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው። ትሮይ የሚባለውን ስም ያገኘው ከግሪክ አገር ሳይሆን ፤ በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ነው። የወርቅ ጌጥ ማድረግ ለሚወዱ ሰዎች ደግሞ ፤ የንፁህ ወርቅ መጠን በካራት ይለካል። በጣም ንፁህ የሆነው ሃያ አራት ካራት ሲሆን ከዚያ ዝቅ ያለ መጠን ያለው ደግሞ ከሌላ ብረት ማዕድን ጋር የተደባለቀው ነው። የዋጋውም ዓይነት በዚሁ መጠን በወርቅ ሰሪ ቤቶች ሱቅ ውስጥ ይለያያል። ብር የተባለው ማዕድን ደግሞ ተፈላጊነቱ በድሮ ጊዜ ለመገበያያነት ቀጥሎም ለተለያዩ የንብረት እቃዎችና የፋብሪካ ውጤቶች አገልግሎቱን የሚሰጥ የማዕድን ብረት ነው። ንፁህ ብር የሚባለው ብዙውን ጊዜ ዘጠና ሁለት ነጥብ አምስት ያክሉን ሲልቨር የሚይዘው ነው። የተቀረው ሰባት ነጥብ አምስት ከመዳብ (ኮፕር) - ወይንም ከሌላ የብረት ማዕድን ጋር የሚደባለቀው ነው። የአጠቃላይ ስሙም እስተርሊንግ ሲልቨር ይባላል። መደባለቁ የሚጠቅመው የብር ይዘቱን ለማጠንከር ወይንም በቀላሉ ከውስጡ ያሉትን ንጥረ ማዕድኖች በሙቀት ጊዜ ወይንም በቅዝቃዜ መጠናቸው እንዳይለወጥ ነው። \n \nጥያቄ: ንፁህ ብር ምን በመባል ይታወቃል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ እስተርሊንግ ሲልቨር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ ስሙ ለምን በዛብህ ተባለ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የማን ደቀመዝሙር ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል አብዱ ዲዮፍ ከመቼ ጀምሮ ነው ወደ ፕሬዝዳንትነት ስልጣን የመጡት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1981 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: ወንዱ ቀጭኔ ስንት ኪሎ ግራም ይመዝናል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 1,360 ኪሎግራም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ራስ ተፈሪ መኮንን በማን ዘመነ መንግሥት የእንደራሴነት ስልጣን ያዙ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ንግሥት ዘውዲቱ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ዘመነ ሰማዕታትን ያስቆመው ንጉሥ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቆስጠንጢኖስም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በአፍሪካ ምን ያህል ሕዝብ ይኖራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ869 ሚሊዮን በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ጋሊሊዮ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የፀሓይ ምርምር የጀመረው በምን እየታገዘ ነበር ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በቴሌስኮፕ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኮንታ የኮንታ ብሔረሰብ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ኮንቲኛ ሲሆን፣ ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ከንግግር ቋንቋነት ባሻገር የትምህርትና የሥራ ቋንቋ በመሆን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። አብዛኛው የብሔረሰቡ አባላት ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው በተጨማሪ ዳውሮኛ፣ ጋሞኛ፣ ወላይትኛና አማርኛ ይናገራሉ። የኮንታ ብሔረሰብ ባህላዊ አስተዳደር መዋቅር ተዋረዳዊ ኃላፊነትና ተግባር ባላቸው የተለያዩ ክፍሎች የተደራጀ ነው፡፡ በእዚህ መዋቅር የሁሉም የበላይ ካዎ ወይም ንጉስ በመባል የሚታወቅ ሲሆን ከማላ ጎሳ ይመረጣል፡፡ በኮንታ ብሔረሰብ ስድስት ባህላዊ የጋብቻ ዓይነቶች ያሉ ሲሆን፣ እነዚህም በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ቦሣ) የለፋ ጋብቻ (ላታ) በተጋቢዎች ስምምነት የሚፈጸም ጋብቻ (ማቆ) የቃል ጋብቻ (ያኤኤኩዎ) እና ሚሽቶ (የምትክ ጋብቻ) በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ ዓይነቶች በብዛት ሲከናወን የሚስተዋለው በቤተሰብ ስምምነት የሚፈጸመው የቦሣ ጋብቻ ነው፡፡ ከብሔረሰቡ ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ፂፄ፣ ጫቻ፣ ዛይ፣ዲንኬ እና ኡልዱዶ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህ የትንፋሽና የምት የሙዚቃ መሣሪያዎች ለለቅሶና ለደስታ ጊዜ ያገለግላሉ፡፡ በተለይ ኡላዱዶ የተሰኘው የትንፋሽ መሣሪያ ከድኩላ ቀንድ ተበስቶ የሚሠራ ሲሆን ከብቶቻቸው ሆራ (ጨውነት ያለው ውሃ) ሊያጠጡ የሚወስዱ እረኞች ይነፉታል፡፡ የኮንታ ባህላዊ የቤት አሠራር ከፍልጥ እንጨት፣ ከቀርከሀ ከሰንበሌጥና ከሣር የሚዘጋጅ ሲሆን በደጋውና በቆላው አካባቢ ልዩነት አለው፡፡ ሱልሶ፣ ሲሊሶ፣ ኡስታ፣ ጨዲያ፣ ኩበዋ፣ ቦሩዋ (ዱቢያ) እና ባጨራ የኮንታ ብሔረሰብ ዋነኛ ባህላዊ ምግቦች ናቸው፡፡ ሲልሶ ለአብነት ከምን እንደሚሠራ እንይ፡፡ ሲልሶ ከጥሬ ሥጋ፣ ከቅቤ፣ ከደም፣ ከሀሞት እና ከተለያዩ የማጣፈጫ ቅመሞች ከተዘጋጀ በኋላ ከተለበለበና በክብ በተቆረጠ የእንሰት ቅጠል ላይ ለቤተሰቡ አባላት ይቀርብና በቡላ ወይም በቆጮ ይበላል፡፡ በብሔረሰቡ ወንዶች ከአቡጀዲ በእጅ የተሰፋ እጀ ጠባብ ሸሚዝና ሱሪ እንዲሁም ሀሲያ የተባለ በእጅ የተፈተለ ልብስ ሲለብሱ ሴቶች በኋላ በኩል ባለወጥ ጥለት የሆነውን ማዳ የተባለ የእጅ ፈትል ይለብሳሉ፡፡ \n \nጥያቄ: በኮንታ ብሔረሰብ ስንት አይነት ጋብቻ አለ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ስድስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ ከምእራብ አቅጣጫ በማን ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ የመጀመሪያ ስራውን ያሳተመው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1869 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የአክሱም መንግስት የክርስትና ሃይማኖትን የተቀበለው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ4ኛው ምእተ-ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nህንድ ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ሰርታለች፡፡ ሃገሪቱ የሰራችው መመርመሪያ ልክ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ውጤቱን በፍጥነት ሊያሳይ የሚችል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ከአንድ ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ ውስጥ ውጤቱን እንደሚያደርስ ነው የተነገረው፡፡ በ2 ሺህ ህሙማን ላይ ምርመራ ተደርጎም ውጤታማነቱ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ ፌሉዳ የተባለው ይህ መመርመሪ ኪት ዋጋው 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የህንድ መንግስት ዋና የሳይንስ አማካሪ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን እንዳሉትም ሙከራው ቀላል ፣ ትክክለኛ፣ አስተማማኝ እና ወጪ ቆጣቢ ነው ፡፡ ህንድ በአሁኑ ጊዜ ከ1 ሺህ 200 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሏት ሲሆን በቀን 1 ሚሊየን ናሙናዎችን እየመረመረች ትገኛለች፡፡ \n \nጥያቄ: ሕንድ የሠራችውን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፌሉዳ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1399 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1948 ዓ.ም. የተሻሽለው ሕገ መንግሥት እስከ መቼ አገለገለ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እስከ 1967 አ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: በጎፋ ብሔረሰብ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ዓይነት ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የምትክ ጋብቻ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአራት ማዕዘን አራት ማዕዘን ማናቸውም አራት ቀጥተኛ መስመር የሆኑ \"ጎኖች\"ና አራት መገናኛወች ያላቸውን የሚወክል የሂሳብ ስያሜ ነው። እኒህ ጎኖች መነባበር ወይም አንዱ ባንዱ ላይ መንሳፈፈ የለባቸውም አለዚያ አራት ማዕዘን አይባሉም። የአራት ማዕዘን አራቱ ውስጣዊ ማዕዘኖች ሲደመሩ ምንጊዜም ውጤታቸው 360 ዲግሪ ነው። ፓራላሎግራም ሁለቱ ጎኑ ትይዩ የሆነ አራት ማዕዘን ፓርላሎግራም ይባላል። በፓራላሎግራም ስር የሚተድዳደሩ እንግዲህ ካሬ፣ ሬክታንግል፣ ሮምበስና ሮምባቶይድ ይባላሉ። ሮምበስ ማለት አራቱም ጎኑ እኩል የሆነ ፓራልላሎግራም ነው። በሌላ አነገጋገር ተጻራሪ ጎኖቹ ትይዩ ሲሆኑ ተጻራሪ ማዕዘኖቹ ደግሞ እኩል ናቸው፣ ወይም ደግሞ ዲያጎናሎቹ በ90 ደጊሪ እኩል ለኩል ይቋረጣሉ። ወይም በሌላ አባባል ወደጎን የተገፋ ካሬ ማለት ነው። ሮምባቶይድ ማለት ፓራሎግራም ሆኖ ተነካኪ ጎኖቹ እኩል ያልሆኑና ማዕዘኖቹ ኦብሊክ የሆኑ ማለት ነው። በሌላ አባባል የተገፋ ሬክታንግል ማለት ነው። ሬክታንግል ማለት አራቱም ማዕዘኖቹ 90ዲግሪ የሆነ አራት ማዕዘን ማለት ነው። በሌላ አባባል ዲያጎናሎቹ እኩል ሆነው እኩል የሚቋረጡ ማለት ነው። ካሬ አራቱም ጎኖቹ እኩል የሆኑ እንዲሁም አራቱም ማዕዘኖቹ 90 ዲግሪ የሆኑ ማለት ነው። በአንድ ጊዜ ሮምበስ እና ሬክታንግል የሆነ አራት ማዕዘን ምንጊዜም ካሬ ነው። \n \nጥያቄ: ፓራላሎግራም ምንድነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሁለቱ ጎኑ ትይዩ የሆነ አራት ማዕዘን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በ1981 እ.ኤ.ኣ. የተመረጠው የሴኔጋል ፕሬዝዳንት አብዱ ዲዮፍ በስልጣን ከመቼ እስከ መቼ ቆየ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 2000 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: የቻይና ዋና ከተማ ማን ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቤጂንግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም አባታቸው ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ አዲስ የዲዛይን ክፍተት መገኘቱ ተገለፀ። የቦይንግ ኩባንያ እና የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍ.ኤ.ኤ) በትናንትናው እለት እንዳረጋገጡት በ737 ማክስ አውሮፕላን ዲዛይን ላይ የተገኘው አዲስ ክፍተት የኤሌክትሪክ ሽቦ መቀራረብ ችግር እንደሆነ አረጋግጠዋል። የቦይንግ ቃል አቀባይ ጎርዶን ጆንድሮ “ጉዳዩ የቦይንግ አስቸጋሪ ሂደት አካል ቢሆንም፤ ተገቢውን ትንተና ለማከናወን ከአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር ጋር በጋራ እየሰራን ነው፤ አሁን የተገኘው ክፍተት የዲዛይን ለውጥ ለማድረግ ያስገድዳል የሚያስብል ደረጃ ላይ ግን አልደረሰም”ብለዋል። የቦይንግ አውሮፕላን ላይ የተገኘው አዲሱ የዲዛይን ክፍተት የሁለት ሽቦዎች በጣም መቀራረብ መሆኑን በመግለጽ፤ አብራሪዎች ችግሩን ተረድተው በአፋጣኝ ምላሽ የማይሰጡ ከሆነ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋን ሊያስከትል ይችላል” ሲል የኒው ዮርክ ታይምስ አስነብቧል። የአሜሪካ ፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሰጠው መግለጫ፥ በቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን ላይ ሊደረግ በታቀደው የዲዛይን ማሻሻያ ዙሪያ ኤጀንሲው እና የቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ ግኝቶችን እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል። ኤጀንሲው አክሎም “በዚህ ሂደት ወቅት ተለይተው የሚታወቁ የደህንነት ችግሮች በሙሉ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ይደረጋል ” ሲልም አስታውቋል። ቦይንግ በአሁኑ ጊዜ ተቀራርበዋል የተባሉ የኤሌክትሪክ ሽቦዎችን ለመለየት እና ስህተቱን ተከትሎ የሚደርሰውን አደጋ በተመለከተ ሰፋ ያለ ትንተና እየሰራ መሆኑን አንድ የኩባንያው ባለስልጣን አስረድተዋል። ቦይንግ በአምስት ወራት ውስጥ በሁለት አደጋዎች 346 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የማክስ 737 አውሮፕላን ማምረት ማቆሙ ይታወሳል።   ምንጭ፡- ሲጂቲኤን \n \nጥያቄ: በየትኛው የቦይንግ አውሮፕላን ላይ ነው አዲስ የዲዛይን ክፍተት መገኘቱ የተገለፀ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 737 ማክስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን በስንት ዓ.ም. ተመሠረተ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ እ.ኤ.አ. በ2004 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኮምፒዩተር ኮምፕዩተር ማለት ማንኛውንም ኢንፎርሜሽን ፕሮሰስ የሚያደርግ ማሽን ነው። ይህንም የሚያደርገው በተርታ የተቀመጡ ትዕዛዞች በመፈጸም ነው። ለብዙ ሰዎች ኮምፒዩተር ሲባል ዐዕምሯቸው ላይ የሚመጣው የግል (ፐርሰናል) ኮምፒዩተር ነው። ነገር ግን ኮምፒዩተር ሲባል በጣም ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። ላፕቶፕ ፣ ዴስክቶፕ ፣ ማይክሮ-ኮምፒዩተር ፣ ሱፐር-ኮምፒዩተር ፣ ካልኩሌተር ፣ዲጂታል ካሜራ እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ቀድሞ አስሊ ማለት አንድ በሒሳባዊ ትዕዛዝ የተለያዩ የጥንት መሣሪያዎችን እየተጠቀመ ቁጥሮችን የሚያሰላ ሰው ነበር። እስከ 20ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የተለያዩ ጠቃሚ መሣሪያዎች ተሰርተዋል። ከዛ በኋላ ትልልቅ ማሸኖች መሠራት ጀመሩ። እነዚህ ማሽኖች ከዛሬው ኮምፒዩተሮች(አስሊዎች) ጋር ሲወዳደሩ በጣም ትልቅና ቀርፋፋ ናቸው። የኮምፕዩተር የውስጥ ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1.ሞኒተር - የምንሰራውን ነገር እንዲያሳየን፤ምስል፣ጽሑፍ፣ ቪዲዮ ወይም ማንኛውም ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ሞኒተር 14 ኢንች፣ 15 ኢንች፣ ወዘተ. እየተባለ ይገላጻል፡፡ 2.ማዘርቦርድ - እናት ሰሌዳ ሁሉም የኮምፕዩተር ክፍሎች(ዕቃዎች)የሚቀዳጁበት 3.ሲፒዩ - የኮምፕዩተሩ አእማሮ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሲፒዩን ከሰው አእምሮ ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ 4.ሜሞሪ - የምንሰራውን ስራ ወይም ፋይል በጊዚያዊነት አስቀምጠንበት የምንሰራበት፡፡ ሜሞሪበባይት (Bytes) ይለካል፡፡ ከ Bytes ፊት Kilo፣ ማለትም ኪሎባይት (kilobytes)([1,024 ባይቶች ወይም Bytes ማለት ነው፡፡ ] ፣ Mega[1,048,576 ባይቶች ወይም Bytes ] ፣ Giga [1,073,741,824 ባይቶች ወይም Bytes]፣ ወዘተ የሚሉትን ቃላት በመጠቀም ኪሎባይት(kilobyte)፣ ሜጋባይት (megabyte)፣ ጊጋባይት (gigabyte) እያልን የኮምፒዩተር ሜሞሪ መግለፅ እንገልጻለን፡፡ ለምሳሌ 10 MegaBytes ወይም ባጭሩ ሲጸፍ 10MB ይህ ማለት 10,485,760 Bytes ይሆናል ማለት ነው፡፡ 5.ኤክስፓንሽ ስሎት 6.የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረቢያ (power supply) 7.የሲዲ ማሰሪያ (cd drive) 8.ሀርድ ዲስክ (የምንሰራውን ወይም የምንጠቀምበትን ፋይል በቋሚነት ለማስቀመጥ) 9. መሎጊያ (ማውስ) 10.የፊደል ገበታ (ኪቦርድ) የመጀመሪያቹ ኮምፕዩተሮች የሚሠሩት በእንግሊዝኛ ፊደል ብቻ ነበር። ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ኣገሮች ሊቃውንት በየራሳቸው ፊደላት እንዲሠሩ ኣደረጉ። ኮምፕዩተር በእያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኣበራ ሞላ ነው። በቅርቡም አያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት ዩኒኮድ የሚባል የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ መግባት ቀጥሏል። \n \nጥያቄ: መረጃን ፕሮሰስ ለማድረግ የምንጠቀምበት ኤሌክትሮኒክ መሳሪያ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኮምፕዩተር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: መንግስቱ ከተውኔቱ ውጪ የሚታወቅበት ሙያ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በስነ-ግጥም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸንፈው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የሆኑት መቼ በተካሄደው ምርጫ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1925 ምርጫ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: የአማራ ክልል ምጣኔ ሀብታዊ እንቅስቃሴ በአብዛኛው ምን ላይ የተመሰረተ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በግብርና እና ከብት እርባታ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒና በአትላንታ ኦሎምፒኮች በአሥር ሺህ ሜትር ሩጫ ያገኘው ውጤት ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ወርቅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ በተናጋሪ ብዛት ሦስተኛው ቋንቋ የቱ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አፍሪካንስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: መንግስቱ ለማ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 1924 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: የሴቷ ዋዝንቢት እንቁላል መጣያ አካል ቅርጹ ምን ዓይነት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መርፌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟ ምን እየሆነ ይሄዳል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እየጠቆረ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቱርክ በዊኪፒዲያ ላይ ላለፉት ሶስት ዓመታት ጥላው የነበረውን እገዳ በማንሳት ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት እንዲችሉ ፈቀደች። የሀገሪቱ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት እገዳው የመናገር መብትን ይጥሳል ሲል እግዱ እንዲነሳ ውሳኔ አሳልፏል። ዊኪፒዲያ በፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ አለመሆኑን ተከትሎ የቱርክ መንግስት እገዳ ማሳላፉ ይታወሳል። በወቅቱ በዊኪፒዲያ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ የቱርክ መንግስት ከአይ ኤስ እና አል ቃይዳ ጋር ትብብር አለው የሚል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። ይህንን ተከትሎም እገዳው ላለፉት 991 ቀናት ተግባራዊ ሆኖ መቆየቱን የኢንተርኔት ክትትል ተቋም የሆነው ኔትብሎክስ አስታውቋል። እገዳው በሂደት ቀስ በቀስ የሚነሳ በመሆኑ እና የተወሰኑ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች ዊኪፒዲያን ለመመለስ እየሰሩ በመሆኑ በቱርክ የሚገኙ ሁሉም ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት አይችሉም ተብሏል፡፡ ዊኪፒዲያ በበርካታ የዓለም ሀገራት ሳንሱር የሚደረግ ሲሆን በቻይና አሁንም ታግዶ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ዊክፒዲያ እስከ አሁን ድረስ እገዳ ላይ የሚገኘው በየት ሀገር ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በቻይና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nህንድ ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ሰርታለች፡፡ ሃገሪቱ የሰራችው መመርመሪያ ልክ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ውጤቱን በፍጥነት ሊያሳይ የሚችል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ከአንድ ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ ውስጥ ውጤቱን እንደሚያደርስ ነው የተነገረው፡፡ በ2 ሺህ ህሙማን ላይ ምርመራ ተደርጎም ውጤታማነቱ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ ፌሉዳ የተባለው ይህ መመርመሪ ኪት ዋጋው 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የህንድ መንግስት ዋና የሳይንስ አማካሪ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን እንዳሉትም ሙከራው ቀላል ፣ ትክክለኛ፣ አስተማማኝ እና ወጪ ቆጣቢ ነው ፡፡ ህንድ በአሁኑ ጊዜ ከ1 ሺህ 200 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሏት ሲሆን በቀን 1 ሚሊየን ናሙናዎችን እየመረመረች ትገኛለች፡፡ \n \nጥያቄ: ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ የሰራች ሀገር ማናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ህንድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nከ 60 ዓመት በኋላ ወባን ለማከም የሚረዳ ኪኒን በአሜሪካ ባለስልጣናት ፈቃድ አገኘ። መድሃኒቱ በየአመቱ 8 ሚሊየን ሰዎች ላይ የሚያገረሸውን የወባ አይነት ለማከም የሚረዳ ነው። ይህ አይነት የወባ በሽታ በጉበት ውስጥ ለረጅም ዓመት ተደብቆ የመቆየት ባህሪ አለው። ተመራማሪዎች ይህንን \"ድንቅ ስኬት ሲሉ አሞካሽተውታል\"። ደጋግሞ የሚያገረሽ የወባ በሽታ ፕላስሞዲየም ቪቫክስ በሚሰኝ ጥገኛ ተዋህሲያን የሚከሰት ሲሆን በአፍሪካ በዋናነት ከሚጠቀሱ የበሽታ አይነቶች መካከል አንዱ ነው። አሁን የአሜሪካው የምግብና የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ታፌኖኪውይን ለተሰኘው መድሃኒት እውቅና ሰጥቷል። መድሃኒቱ በሽታዋ ከተደበቀበችበት ጉበት አውጥቶ በመግደል ሰዎች በህመሙ ዳግመኛ እንዳይሰቃዩ ያደርጋል። በአሁን ሰዓት ጉበት ውስጥ የተደበቀች ወባን ለማከም የሚረዳ ፕሪማኪውን የተሰኘ መድሃኒት አለ። ነገር ግን አንድ ታፌንኪውንን ወስዶ ከሚገኘው ፈውስ ጋር ሲነፃፀር ፕሪማኪውንን ለ 14 ቀን መውሰድ ይጠይቃል። \n \nጥያቄ: በየዓመቱ የሚያገረሸው የወባ በሽታ አምጪ ህዋስ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፕላስሞዲየም ቪቫክስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጉሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ ያገኘው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1881 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጀስትን ቢበር ጀስትን ድሩ ቢበር (ተወለደ በ፲፻፱፻፹፮ በመጋቢት)፣ ካናዳዊ ዘፋኝ። ጀስትን ቢበር ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለመለው በአሜሪካዊው የቅጂ ድርጅት ባለቤት እስኩተር ብሮን ሲሆን የፈረመው ደግሞ ከአርቢኤምጂ የቅጂ ድርጅት በ፪፲፻ አመተ ምህረት ነው። በቀጣዩ አመት ማለትም በ፪፲፻፩ የመጀመሪያ ኢፒ(EP)ውን ለቆ እውቅናን እየተጎናፀፈ ብዙም ሳይቆይ እራሱን መገንባት እንደ ምርጥ ታዳጊ። የጀስትን ቢበር የመጀመሪያ አልበም (ማይ ወርልድ 2.0) በሁለት ሺ ሁለት ተለቀቀ፤ አልበሙም ቁጥር አንድ ሆኖ ላለፉት አርባ ሰባት አመታት (ማለትም ከሁለት ሺ ሁለት አመተ ምህረት ወዲያ ባሉ ጊዜያት) በማንም ታዳጊ ወጣት ሊያዝ ያልተቻለውን ደረጃ ይዞ አሳየ በዪናይትድ እስቴትስ። አልበሙም በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኘውን \"ቤይቢ\" የተሰኘውን ነጠላ ዘፈን ይይዛል፣ ይህም ዘፈን የምንጊዜም ከፍተኛ የምስክር \"ወረቀቶች\" ያገኘ ሊሆን ችሏል በተመሳሳይ ሀገር። የጀስትን ቢበር ቀጣይ አልበም (አንደር ዘ ሚስትልተው) በሁለት ሺ ሶስት ፡ የመጀመሪያው የገና አልበም ነበር በወንድ አንደኛ ለመሆን ከቢልቦርድ መቶ አልበሞች። በቀጣይ አመት (ሁለት ሺ አራት) ሶስተኛ አልበሙን ተከትሎ ጀስትን ቢበር ከህዝብ ጋር ያለው ግንኙነት በሻካራ ሁኔታ ተቀየረ የተለያዩ ክርክሮች በመነሳታቸው እና በህጋዊ ጉዳዮቹ ምክኛት (በሁለት ሺ አምስት እና ስድስት አመት ውስጥ) ፡ እንዲያውም ሮልንግ እስቶን የተባለ ታዋቂ የመረጃ ድርጅርት ጀስትን ቢበርን \"መጥፎ ልጅ\" ብሎ ሰየመው በመጋቢት ሁለት ሺ ስድስት ጉዳዩ። ይሁን እንጂ ከሁለት ሺ ስምንት ጀምሮ ጀስትን ቢበር ተቀዳሚነቱን ለዳግም ህዝባዊ ግንኙነቱ ሲያውል ነበር ፡ ሲያውል ነበር ለአይምሮው ጤንነት። የካቲት ሁለት ሺ ስምንት ጂኪው የተባለ ታዋቂ የመረጃ ተቋም ስለ ጀስትን ቢበር ራስ ማደስ ተነሳሽነት አስመልክቶ ፅሑፍ ይዞ ሊወጣም ችሏል። \n \nጥያቄ: ጀስቲን ቢበር መቼ ተወለደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ፲፻፱፻፹፮ በመጋቢት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የደቡብ ክልል አፈ ጉባኤ ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ወይዘሮ ሄለን ደበበ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን በአርካንሳው ዩኒቨርሲቲ የሠሩበት ሙያ ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የሕግ ፐሮፌሰር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል የቆዳ ስፋቷ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 197,000 ካሬ ኪ.ሜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በመልክአ ምድር አቀማመጥ አፍሪካ ከአሜሪካ የሚለያት ባህር ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ያከተመው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፱፻፴፯ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ የላከው ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኸርበርት አይቭስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ6 አመት ጦርነት በኋላ ገላውዲወስ ተገደለና ሚናስ ስልጣን ላይ ወጣ። ለሚቀጥሉት 4 አመታት፣ እንደቀደመችው ንግስት እሌኒ በመንግስቱ ውስጥ ከፍተኛ ተሰሚነትን አገኘች። ቀጥሎም በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ሃይማኖት መካከል በተነሳው ሽኩቻ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን በመደገፍ በጽናት ቆማለች። ይሁንና በዚህ ምክንያት በተነሳው ጸብ የፖርቹጋል ካቶሊኮች ሊገደሉ ሲሉ በማማለድ ስራ ጉዳት እንዳይደርስባቸው አድርጋለች። ቤርሙዴዝ የተባለው ታውቂው የፖርቹጋል ተጓዥም ንጉሱን ገላውዲወስን በማናደዱ ከመገደል የተረፈው በሰብለ ወንጌል ተራዳኢነት ነበር። የስፔኑ ጀስዊት ፓትሪያርክ ኦቨዶም ከሞት የተረፈው በንግስቲቱ ምክንያት ነበር። ሠርፀ ድንግልን ወደስልጣን እንዲወጣም ከጦረኞቹ በላይ ያገዘችው እናት ንግስት ሰብለ ወንጌል ነበረች። ይህ ምርጫዋ የተሳካ ነበር ምክንያቱም ሰርጸ ድንግል ለ34 አመት ሲገዛ አገሪቱን በመከላከል ወደ ሰላም አሸጋግሯል። ሰብለ ወንጌል በአጼሠርፀ ድንግል ዘመን፣ በ1560 ዓ.ም. አመድ በር በተባለ ቦታ አረፈች። አጼ ልብነ ድንግል የራሱንና የሰብለ ወንጌልን ምስሎች የክሪት ሠዓሊ በመቅጥር ካሳለ በኋላ ግብጽ ወደ ሚገኘው ቅዱስ አትናቲዮስ ገዳም እንዳስላከው ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰብለ ወንጌል በየት አረፈች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አመድ በር በተባለ ቦታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ግብይት የሚያስፈጽመው ግዥና ሻጭን መድረክ ላይ በማገናኘት በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው፡፡ ይህ የተለመደው አሠራር የበለጠ ውጤታማ የሚሆነው ግን በድረ ገጽ ግብይት ሲደረግ በመሆኑ ይህንን የድረ ገጽ ግብይት ለማስጀመር ከሦስት ዓመት በፊት ሥራው የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ችሏል፡፡ በተለመደው የመድረክ የግብይት አሠራር በቀን የሚፈጸመው የግብይት መጠን ከ200 እስከ 300 የሚደርስ ነው፡፡ ይህም የግብይት መጠኑ ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የድረ ገጽ ግብይት መጀመሩ ግን ይህንን በመለወጥ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል፡፡ ይህም አሠራሩን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው ተቋም ጭምር ዕውቅና አግኝቶበታል፡፡ እንደ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያሉ ተቋማትም ይህንን አገልግሎት ፈትሸው ማረጋገጫ ተሰጥቶት እየተሠራበት ስለመሆኑም የምርት ገበያው የሥራ ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህንን ዘመናዊ አገልግሎት ሥራ ለማስጀመር ከመጀመሪያው ጀምሮ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) የተባለው ተቋም ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮጀክት 2.2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ይህ ግብይት በቡና የተጀመረ ሲሆን፣ ሁሉም በዚህ የግብይት ሥርዓት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ የግብይት ሥርዓቱ አዲስ በመሆኑ በዚህ ለመጠቀም ተገበያዮች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም 380 ተገበያዮች በድረ ገጽ ለመገበያየት ሥልጠና ወስደው ብቁ መሆናቸው ተረጋግጦ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የድረ ገጽ ሽያጭ ከመጀመሩ በፊት ገዥና ሻጭን እንዴት ነበር የሚያገበያየው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚለው መፈክር ትርጉም ምን ማለት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nህንድ ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ሰርታለች፡፡ ሃገሪቱ የሰራችው መመርመሪያ ልክ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ውጤቱን በፍጥነት ሊያሳይ የሚችል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ከአንድ ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ ውስጥ ውጤቱን እንደሚያደርስ ነው የተነገረው፡፡ በ2 ሺህ ህሙማን ላይ ምርመራ ተደርጎም ውጤታማነቱ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ ፌሉዳ የተባለው ይህ መመርመሪ ኪት ዋጋው 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የህንድ መንግስት ዋና የሳይንስ አማካሪ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን እንዳሉትም ሙከራው ቀላል ፣ ትክክለኛ፣ አስተማማኝ እና ወጪ ቆጣቢ ነው ፡፡ ህንድ በአሁኑ ጊዜ ከ1 ሺህ 200 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሏት ሲሆን በቀን 1 ሚሊየን ናሙናዎችን እየመረመረች ትገኛለች፡፡ \n \nጥያቄ: ሕንድ የሠራችውን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ በስንት ሰዎች ላይ ሞከረች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ2 ሺህ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nባቢሌ የዝሆን መጠለያ ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከአዲስ አበባ ወደ ጅጅጋ መስመር፣ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ይህ መጠለያ በቆዳ ስፋት ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር የሚመዘን ሲሆን፣ ከጠቅላላ ስፋቱም ውስጥ ፸፯ ከመቶ ያህሉ በአሁኑ አጠራር ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ይገኛል። የአካባቢው የኦሮሚያ ብሔር ተወላጆች ‹‹ወረ-ሃርባ›› (ባለዝሆኖቹ) በማለት የሚጠሩትና በፌዴራል የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሥር የሚተዳደረው የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት፣ በ፲፱፻፷፪ ነው የተመሠረተው። የምሥረታውም ዋነኛ ዓላማ፥ በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ ሲሆን ባሁን ጊዜ መጠለያው በተጨማሪም ከ፴ በላይ ጡት አጥቢ የዱር እንስሳት፣ ከ፪መቶ ፶ በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች፣ ፫መቶ ያህል የዕፅዋት ዝርያዎች የሚገኙበት ነው። ከሌሎች አዕዋፍ እና የዱር አራዊት ዝርያዎች ደግሞ ከገጸ ምድር የመጥፋት አደጋ ላይ ያለው የሳልቫዶሪ ዘረ-በል ወፍ እና ባለጥቁር ጎፈር አንበሳ በዚህ መጠለያ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያን የሚካፈሉት ክልሎች እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኤስፔራንቶ ኤስፔራንቶ (Esperanto) ከሁሉም አለማቀፋዊ ሠው ሰራሽ ቋንቋዎች እጅጉን የተስፋፋ ቋንቋ ነው። በ1859 እ.ኤ.አ. በዛሬይቷ ፖሎኝ የተወለደውና በሞያው የአይን ሀኪም የሆነው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ በ1887 እ.ኤ.አ. ቋንቋውን ለህዝብ አሳወቀ። አላማው ኤስፔራንቶን በቀላሉ ሊማሩት የሚቻል፣ የጋራ የሆነና ለአለማቀፋዊ መግባባት የሚረዳ ግን ያሉትን ቋንቋዎች የማይተካ ቋንቋ ማድረግ ነበር። ኤስፔራንቶ ከ1,600,000 በላይ ተናጋሪዎች ቢኖሩትም የቋንቋው ደጋፊ ያልሆኑ እንግሊዝኛን ከመስፋፋቱ አንፃር ለአለማቀፋዊ ቋንቋነት በተሻለ ይመርጡታል። \n \nጥያቄ: ኤስፔራንቶ የተሰኘውን ዓለም አቀፋዊ ቋንቋ ያስተዋወቀው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ ሙያው ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአይን ሀኪም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: የቶማስ ጄፈርሰን ወላጅ አባት ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፒተር ጄፈርስን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር ምን ያህል አይሁዶችን አስገደለ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 6 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ ከቀይ ባህር ጋር የምትዋሰነው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሰሜን-ምስራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nባቢሌ የዝሆን መጠለያ ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ ከአዲስ አበባ ወደ ጅጅጋ መስመር፣ ፭መቶ ፶ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ይህ መጠለያ በቆዳ ስፋት ፮ሺ ፱መቶ ፹፪ ካሬ-ሜትር የሚመዘን ሲሆን፣ ከጠቅላላ ስፋቱም ውስጥ ፸፯ ከመቶ ያህሉ በአሁኑ አጠራር ”በሶማሌያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ሲካለል፤ ቀሪው ፳፫ ከመቶ ያህሉ ደግሞ ”በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት” ሥር ይገኛል። የአካባቢው የኦሮሚያ ብሔር ተወላጆች ‹‹ወረ-ሃርባ›› (ባለዝሆኖቹ) በማለት የሚጠሩትና በፌዴራል የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሥር የሚተዳደረው የባቢሌ ዝሆኖች መጠለያ በዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት፣ በ፲፱፻፷፪ ነው የተመሠረተው። የምሥረታውም ዋነኛ ዓላማ፥ በምሥራቅ አፍሪካ ብቻ የሚገኙትን “ሎክሶዳንታ አፍሪካና ኦርሊያንሲ” የተባሉትን ንዑስ የዝሆን ዝርያ ለማልማትና ለመጠበቅ ሲሆን ባሁን ጊዜ መጠለያው በተጨማሪም ከ፴ በላይ ጡት አጥቢ የዱር እንስሳት፣ ከ፪መቶ ፶ በላይ የአዕዋፍ ዝርያዎች፣ ፫መቶ ያህል የዕፅዋት ዝርያዎች የሚገኙበት ነው። ከሌሎች አዕዋፍ እና የዱር አራዊት ዝርያዎች ደግሞ ከገጸ ምድር የመጥፋት አደጋ ላይ ያለው የሳልቫዶሪ ዘረ-በል ወፍ እና ባለጥቁር ጎፈር አንበሳ በዚህ መጠለያ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ባቢሌ የዝሆኖች መጠለያ መቼ ተመሰረተ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲፱፻፷፪ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: የጨረቃን ምድር በእግራቸው ለመርገጥ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አርምስትሮንግና አልድሪን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፍሪካ አፍሪካ (አፍሪቃ) ከዓለም ሁለተኛ ትልቅ አህጉር ነች። ከ869 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በዚች አህጉር የሚኖር ሲሆን በጠቅላላ 54 ሀገሮች ይገኛሉ። ከእነዚህም ሀገሮች መሀል ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት (127 ሚሊዮን) የመጀመሪያውን ደረጃ ስትይዝ፤ ግብፅና ኢትዮጵያ በ73 ሚሊዮን እና በ72 ሚሊዮን ህዝብ በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት የህዝብ ብዛት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ከሌሎች የፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ጋር በመደማመር ድህነትን በማባባስ ደረጃ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ጂዎግራፊና ሕዝብ ከስድስቱ ዓለማት አንዱ አፍሪካ ነው። አፍሪካ ሰፊ ነው። የዓለምም አራተኛ ክፍል ይሆናል። ከኤውሮጳ የሚለየው በሜዴቲራኒያን ባሕር ነው። ከአሜሪካም በአትላንቲክ ውቅያኖስ ይለያል። ከኒው ዮርክም ቢሆን ወይም ከቦስቶን ከአሜሪካ የሚቀርበው ክፍል ሦስት ሺህ ማይል ይሆናል። ነገር ግን በጊብሮልታር (ጂብራልታር) በኩል የሆነ እንደ ሆነ ለኤውሮጳ በጣም ቅርብ ነው። ከእስያ በኤርትራ ባሕር ይለያያል። የሆነ ሆኖ እስያ ባንድ ወገን ሱዝ ካናል በሚባለው በኩል ከአፍሪካ ጋር ተጋጥሞአል። ሙሴ ሌስፖስ መርከብ እንዲተላለፍ ብሎ አስቆፍሮ ያስከፈተው በዚህ በኩል ነው። \n \nጥያቄ: በአፍሪካና በእስያ አሕጉር መካከል ያለው መተላለፊያ ሱዝ ካናልን ያሰራው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሙሴ ሌስፖስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ ለጦር ኃይል ከፍተኛ ገንዘብ በማውጣት ከዓለም በስንተኛ ደረጃ ትገኛለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በአራተኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው የቀለም ቴሌቪዥን ስርጭት ሙከራ የተደረገው መች ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን የሰጠችው በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፴፯ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ 100,000 ያህል ተናጋሪዎች ያሉት በየት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በፓኪስታን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን የመናገሻ አምባ ማርያምን ገዳም እያስተዳደሩ ሳሉ፤ ከዚህ ሥልጣናቸው በተጨማሪ የአዲስ አበባ መንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም መምህርነት በየካቲት ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ/ም ተሰጣቸው። ከዚያም ቀጥሎ መጋቢት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፭ዓ/ም በኢየሩሳሌም ያሉ የኢትዮጵያን ገዳማት በመንፈሳዊ መሪነት አስተዳዳሪ ሆነው ተሹመው ለሁለት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ ወደአገራቸው ተመለሱ። የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፯ ዓ/ም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት መንበር፥ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ዘነበረ በመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተብለው፥ አምሣ-ዘጠነኛው ዕጨጌ ሆነውተሽሙ። በዚሁ በዕጨጌነታቸው ዘመን የፋሺስት ወረራ ኢትዮጵያን ባጠቃ ጊዜ፣ በጦርነቱ ግምባር ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ተሰልፈው አብያተ ክርስቲያናትንና መጻሕፍትን የሚያቃጥል የምእመናንን ዘር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና በሃይማኖት፤ በጸሎት፣ በምህላ በርታ እያሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲያጽናኑ ቆዩ። በጦርነቱም ጊዜ የተቀመጡበት በቅሎ በአረር ተመቶ እስኪወድቅና የለበሱትም ካባ አምስት ላይ በጥይት እስኪበሳሳ ድረስ ከንጉሠ ነገሥቱ ሳይለዩ የቆራጥነት ሥራ ሠርተዋል። ሠራዊቱም ድል ህኖ በተፈታ ጊዜ ክንጉሠ ነገሥቱ ጋር በስደት ወደኢየሩሳሌም አቅንተው እስከ ድል ጊዜ ድረስ በስደት ቆይተዋል። በዚሁ በስደት ዘመናቸውም ሳሉ በርካታ ሐዋሪያዊ መልእክቶችን ለአርበኞችም፤ ለሕዝቡም በመላክ የማጽናናትና የሃይማኖታዊ ጣምሮችን ያስተላልፉ ነበር። ንጉሠ ነገሥቱ በስደት ከነበሩበት ከ’ባዝ’ (ብሪታንያ) ፥ ጥር ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ/ም በጊዜው በስደት ኢየሩሳሌም ለነበሩት ወደ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ አንድ ፅላትና ለአገልግሎት የሚበቁ አምስት መነኮሳትን ወደ እንግሊዝ አገር እንዲልኩላቸው በአባ ሐና ጅማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት፣ ዛሬ ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም የተባለውን የመድኀኔ ዓለምን ጽላት ወደንጉሠ ነገሥቱ ወዳሉበት ባዝ የላኩት እሳቸው ነበሩ፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፥ ጥር ፲፪ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በኢትዮጵያ ጠረፍ በኡም-ኢድላ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ-ዓላማ ሲተክሉ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስም አብረዋቸው ነበሩ። \n \nጥያቄ: ንጉሰ ነገስቱ በስደት የት ሃገር ነበሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ’ባዝ’ (ብሪታንያ) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: የጋሊልዮ ሁሉም ክብደት ያላቸው ነገሮች በእኩል ሰዓት መሬት ይደርሳሉ የሚለው አስተሳሰብ ያረጋገጠው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኢሳቅ ኒውተን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: ላይቤሪያ በአፍሪካ በየትኛው ክፍል ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: በጣልያን ፋሺስት ወረራ ጊዜ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወዴት ሀገር ነበር የተሰደዱት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እንግሊዝ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) ኡበርና ሃዩንዳይ በራሪ ታክሲዎችን በጋራ ሊሰሩ መሆኑን አስታወቁ። ሁሉቱ ኩባንያዎች አዲስ የሚሰሩትን በራሪ ተሽከርካሪ በላስ ቬጋሱ የንግድ ትርኢት ይዘው እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል። አራት ተሳፋሪዎችን የሚይዘው በራሪ ታክሲ በሰዓት እስከ 320 ኪሎ ሜትር መጓዝ እንደሚችል ተገልጿል። ሁለቱ ኩባንያዎች በዚህ ሳምንት በላስ ቬጋስ በሚደረገው የንግድ ትርኢት ላይ የታክሲ አገልግሎት ይሰጣል ያሉትን በራሪ ተሽከርካሪ ሞዴል ይፋ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። ኡበር በፈረንጆቹ 2023 ለደንበኞቹ የበራሪ ታክሲ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ነው የገለጸው። \n \nጥያቄ: ኡበርና ሃዩንዳይ ሊሰሩት ያሰቡት በራሪ ታክሲ በሰዓት ምን ያህል ርቀት ይጓዛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 320 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በደቡብ ኮሪያና በኢትዮጵያ ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ ያሉት ሳተላይቶች ስንት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየናሳ ተመራማሪዎች ሱፐር ኧርዝ ሲሉ የሰየሟትን አዲስ ፕላኔት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡ በመጠኗ የመሬትን እጥፍ ታክላለች የተባለችው አዲሷ ፕላኔት ከከዋክብቷ አንፃር ለህይወት ተስማሚ በሆነ ርቀት ውስጥ እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡ ይህም በፕላኔቷ ላይ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚል ተስፋ አሳድሯል ነው የተባለው፡፡ ፕላኔቷ አለታማ አሊያም እንደኔፕቲዩን በጋዝ የበለፀገች ልትሆን እንደምትችል የናሳ ተመራማሪዎች የገለጹ ሲሆን ፕላኔቷ ያልተለመደችና ከቀድሞ ፕላኔቶች ልዩ እንደሆነች በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ \n \nጥያቄ: የየት ተመራማሪዎች ሱፐር ኧርዝ የተሰኘች አዲስ ፕላኔት አገኙ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የናሳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየህንዱ ኩባንያ በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን ጉማሬ ወረዳ ጥቅጥቅ ደን ውስጥ 3,012 ሔክታር መሬት ለሻይ ቅጠል ልማት ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ቦታ መሰጠቱ አግባብ አለመሆኑ ተጠቅሶ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስን ጨምሮ የአካባቢው ነዋሪዎችና የአካባቢ ጉዳይ ተሟጋቾች ቅሬታ ቢያቀርቡም፣ መሬቱን የሰጠው ግብርና ሚኒስቴር ቦታው ላይ ያሉት ዛፎች ትልልቅ ሳይሆኑ ቁጥቋጦ ናቸው በማለት ሲቀርብ የነበረውን ቅሬታ ውድቅ አድርጓል፡፡ ነገር ግን ኩባንያው ጣውላ በሕገወጥ መንገድ ሲያመርት በመገኘቱ የኩባንያው ሥራ አስኪያጅ ሰኔ 14 ቀን 2004 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሦስት ዓመታት በኋላ ቬርዳንታ ሐርቨስት በዓለም አቀፍ ሕግጋትም ሆነ በኢትዮጵያ ሕግ በፅኑ የተከለከለውን የሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ማካሄዱ፣ በአካባቢው ባለሥልጣናት ቁጣ መቀስቀሱ እየተነገረ ነው፡፡ ‹‹ሠራተኛ መቅጠር ከፈለገ በሠራተኛና በአሠሪ ሕግ መሠረት መሆን ይኖርበታል፤›› በማለት አቶ ዮናስ ኩባንያው የፈጸመው ተግባር ሕገወጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ የተጠየቁት የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋት ሉዋክ ቱሉና ምክትላቸው ኢንጂነር ኦሌሮ ኤፒዮ በጉዳዩ ላይ መረጃው እንዳልቀረበላቸው ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በቬርዳንታ ሐርቨስት ለሻይ ቅጠል ልማት የተሰጠው ቦታ ስፋቱ ምን ያህል ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 3,012 ሔክታር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: መቼ የተካሄደው የኦሎምፒክ ውድድር ነው ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቭዥን የተሰራጨው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1936 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ማማዱ ዲያ መፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ ያደረገው በማን ላይ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: የቀድሞው የናዋትል ቋንቋ አጻጻፍ ተቃጥሎ የጠፋው በማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በካቶሊኮች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: አንበሶች ክብደታቸው እስከ ስንት ኪሎ ግራም የሆኑ እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም አላቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዋትስ አፕ የተሰኘው የፅሁፍ እና የምስል መልዕክት መለዋወጫ መተግበሪያ በሚሊየን በሚቆጠሩ ዘመናዊ ስልኮች ላይ ሲሰጥ የነበረውን አገልግሎት ሊያቋርጥ መሆኑን አስታወቀ። ዕቅዱ በተለይም ኦፕሬቲንግ ሲስተማቸውን ማዘመን ባልቻሉ የአንድሮይድ እና አይፎን ስልኮች ላይ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ ነው የተገለጸው። እርምጃው የደንበኞችን የመረጃ ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንም ኩባንያው ገልጿል። በዚህ መሰረት መተግበሪያው አይፎን ኦፕሬቲንግ ሲስተም አይ ኦ ኤስ 8ን ጨምሮ ከዚያ በፊት በተመረቱ ተመሳሳይ መለያ ባላቸው ስልኮች ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት እንደሚያቆም ተገልጿል። እንዲሁም አንድሮይድ 2፣3፣7 እና ከዚያ በፊት ያሉትን ያልዘመኑ ኦፕሬቲንግ ሲስተሞች የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮች ላይ የሚሠጠውን እንደሚያቋርጥም ተነግሯል። በመተግበሪያው ላይ ማሻሻያ እያደረገ መሆኑን የገለጸው ኩባንያው፥ ይህም የመረጃ ደህንነትን ከማስጠበቅ ባለፈ ደንበኞች ሀሰተኛ ገጽ በመክፈት የተዛቡ መረጃዎችን እና የጥላቻ ንግግሮችን እንዳያሰራጩ የሚያግዝ ነው መሆኑን አስታውቋል።   ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision   \n \nጥያቄ: ዋትስ አፕ መተግበሪያው አይፎን ኦፕሬቲንግ ሲስተም ከዓይነት ስንት በታች ባላቸው ስልኮች ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማቆም አቅዷል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አይ ኦ ኤስ 8ን ጨምሮ ከዚያ በፊት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጾመ ነቢያት በአራቱም ዘመናት ምን ጊዜም ኅዳር ዐሥራ አምስት እንዲጾም ተወስኗል፡፡ ጾመ ገሀድ የምትክ ጾም ነው፡፡ ይህ ጾም ዓርብንና ሮብን የሚያሽር በዓል በዓርብና በሮብ ሲውል በምትኩ በዋዜማው የሚጾም ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ጥምቀት ዓርብ ቢውል ሐሙስ ጾመ ገሀድ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አበው ለጾም ማድላት አለብን በማለት ጾመ ገሀድ ምንጊዜም ጥምቀት በጾም ቀን ዋለም አልዋለም በዋዜማው እንዲጾም ወስነዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ትንሣኤ ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ዕርገት ይፈጸማል፡፡ \n \nጥያቄ: ጾመ ፍልሰታ መቼ ይጀምራል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ነሐሴ አንድ ቀን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳምሰንግ ኩባንያ በተጠናቀቀው የፈረንጆች ዓመት 6 ነጥብ 7 ሚሊየን አምስተኛ ትውልድ (5ጂ) ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮችን ለደንበኞቹ ሸጧል። ኩባንያው በዓመቱ 4 ሚሊየን 5ጂ ስማርት ስልኮችን ለመሸጥ አቅዶ 6 ነጥብ 7 ሚሊየን ስልኮችን በተሳካ ሁኔታ መሸጡን አስታውቋል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው 5ጂ ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ስልኮችን በደንበኞች እጅ በማድረስ ከተቀናቃኞቹ የተሻለው ሆኗል። በዓመቱ ለገበያ ከቀረቡ ዘመናዊ ስልኮች ውስጥ ሳምሰንግ ኤስ ኤስ ኤን አል ኤፍ የተሰኘው ሞዴል ብባዛት መሸጡ ተመላክቷል። እንዲሁም ሳምሰንግ ጋላክሲ ኖት 10ጂ፣ 10+5ጂ፣ ኤ90 5ጂ እና የመተጣጠፍ ችሎታ ያለው ጋላክሲ 5ጂ በዓመቱ ለገበያ የቀረቡ ሞዴሎች ናቸው። ሳምሰንግ በአዲሱ የፈረንጆች ዓመትም ለኩባንያው የመጀመሪያ የሆነውን ኤስ6 የተሰኘ 5ጂ ኢንተርኔት የሚጠቀም ታብሌት ለገበያ እንደሚያቀርብ ገልጿል።   ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: ሳምሰንግ በተጠናቀቀው የፈረንጆቹ ዓመት ምን ያህል አምስተኛ ትውልድ ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮችን ሸጠ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 6 ነጥብ 7 ሚሊየን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎጉል እና አፕል ለስለላ ጥቅም ላይ ይውላል በማለት የጠረጠሩትን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን መተግበሪያ ቶቶክን ማስወገዳቸው ተገለፀ፡፡ ቶቶክ የተሰኘው ይህ መተግበሪያ ሰዎች በቀላሉ በተንቀሳቃሽ ምስል እና በፅሁፍ እንዲያወሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ ኔውዮር ታይምስ አንደዘገበው ከዋትስ አፕ ጋር ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጠው ቶቶክ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ለስለላ መሳሪያት ጥቅም ላይ ይውላል ተብሏል፡፡ ኔውዮርክ ታይምስ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ በዘገባው እንዳሰፈረው ቶቶክ የተሰኘው መተግበሪያ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሰላዮች የተጠቃሚዎችን ውይይት ፣ እንቅስቃሴ እና ፎቶ መሰል የግል መረጃዎች አሳልፎ ይሰጣል፡፡ ጎግል ይህን መተግበሪያ ባለፈው ሀሙስ ማጥፋቱ የተገለፀ ሲሆን አፕልም ጎግልን በመከተል በቀጣዩ ቀን ከመተግበሪያ ዝርዝሮቹ ውስጥ ማጥፋቱ ተጠቁሟል፡፡ ቶቶክ መተግበሪያ ለተጠቃሚዎቹ በቅርቡ በአፕ ስቶር እንደሚመለስ አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ባስተላለፈው መልዕክት በጎግል ስቶር እና በአፕል ስቶር በጊዜያዊነት እንደማይገኝ የገለፀ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ የቴክኒክ ጉዳይ መሆኑን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡- ቢቢሲ በፌቨን ቢሻው   \n \nጥያቄ: ጎጉል እና አፕል ቶቶክ የተሰኘው መተግበሪያ ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሰላዮች ምን ምን ፋይሎችን አሳልፎ ይሰጣል ብሎ ነው ያስወገደው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የተጠቃሚዎችን ውይይት ፣ እንቅስቃሴ እና ፎቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል። ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ። \n \nጥያቄ: ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ ካሉ ቋንቋዎች ከፍተኛ ተናጋሪዎች ያለው የቱ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኳዙሉ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማይክሮሶፍት ለዊንዶውስ-10 የሚያቀርብውን የደህንነት ጥገና በ2025 ማቅረብ እንደሚያቆም እና በዚህ ወር መጨረሻ የዊንዶውስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ዋና ማሻሻያ ይፋ ለማድረግ መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ ኩባንያው ከዚህ ቀደም ዊንዶውስ 10 ማሻሻያ ይፋ ሲያደርግ የመጨረሻው ኦፕሬቲንግ ሲስተም ነው ቢልም አሁን ላይ ግን ሃሳቡን እንደቀየረ ይፋ አድርጓል። ከዚህ ጋር ተያይዞም ኩባንያው ከፈረንጆቹ ጥቅምት 14 ቀን 2025 ጀምሮ ለሆምም ሆነ ለፕሮፌሽናል ቨርዥኖች አዳዲስ ዝመናዎች ወይም የደህንነት ጥገናዎች አይኖሩም ብሏል፡፡ ምንም እንኳን የዊንዶው-7 ተጠቃሚዎች ከፈረንጆቹ 2020 ወዲህ የደህንነት ዝመና ቢቋረጥም የንግድ ድርጅቶች ለዊንዶውስ-7 ፕሮፌሽናል እና ዊንዶውስ 7 ኢንተርፕራይዝ ዝመናዎችን ለማግኘት ለማይክሮሶፍት ክፍያ እየፈጸሙ ነው። አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች እንደተናገሩት አዲሱ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ከ11 ቁጥር ይልቅ ስም እንደሚሰጠው እየገለጹ መሆኑን ቢቢሲ በድረ-ገጹ ማስነበቡን ኢመደኤ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ማይክሮሶፍት ለየትኛው ዊንዶ የሚያቀርብውን የደህንነት ጥገና በ2025 እንደሚያቆም ያሳወቀው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ለዊንዶውስ-10 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በ1996 በሜሪላንድ ስቴት ከሚኖሩ ነዋሪዎች በመቶኛ ምን ያህሎቹ የሌላ ስቴት ወይም ሀገር ተወላጆች ነበሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 10.6 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም. በምሥራቅ አፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ያዘጋጀችው ሲምፖዚየም ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ የነበሩበት ከተማ እንዴት ደብረ ብርሃን ብለው ሊያወጡለት ቻሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ታሊዝ የተወለደበት ቦታ አሁን በየትኛው ሀገር ክልል ውስጥ ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቱርክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር አባታችው የሚወለዱበት ጎሳ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሴሬር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጎግል ስለኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ለማቅረብ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ። ኩባንያው በትናንትናው ዕለት ወደ ስራ ያስገባው ማንቂያ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ አስፈላጊ መረጃዎችን ለማድረስ ያግዛል ተብሏል። ስለኮሮና ቫይረስ እና ተያያዥ ጉዳዮች ሰዎች መረጃዎችን በሚፈልጉበት ወቅት ጎግል “በነጭ ካርድ መደብ” ላይ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያውን በማሳየት ተፈላጊውን መረጃ ለተጠቃሚዎቹ በቀጥታ ያጋራልም ነው የተባለው። ጎግል ለዓለም አቀፍ መረጃ ፈላጊዎች በማንቂያው ላይ የዓለም ጤና ድርጅት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራሎችን አድራሻ ማካተቱንም አስታውቋል። አስፈላጊ ከሆነም በሂደት ማንቂያውን ለአካባቢያዊ መረጃ ፈላጊዎች በሚሆን መልኩ እንደሚያካትትም ገልጿል። በቀጣይም ስለ ኮሮና ቫይረስ ጠቃሚ መረጃ፣ ያለበትን ሁኔታ እና ጥያቄና መልሶችን ያካተቱ አንቀጾች ያሉበት “የእርዳታ እና መረጃ” ማፈላለጊያን ከዓለም ጤና ድርጅት አድራሻ ጋር በማያያዝ አቀርባለሁ ብሏል። ኩባንያው በአስፈላጊ እና ወሳኝ ወቅት ላይ ተጨማሪ የመረጃ ማሻሻያ እንደሚያደርግ በመግለፅ የማንቂያ ስርዓቱ ለኮሮና ቫይረስ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲገኙ ያስችላል ነው ያለው። በሞባይሎች እና ድረ ገፆች ላይ የሚገኘው ኤስ ኦ ኤስ ማንቂያ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች በሚፈጠሩበት ወቅት እንዲሁም በአጠቃላይ የሰዎች ደህንነት አደጋ ላይ በሚሆንበት ወቅት ጥቅም ላይ የሚውል ነው። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው ለቻይና የቀይ መስቀል ማህበር የ250 ሺህ ዶላር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፥ በመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በተከፈተ ዘመቻ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ምንጭ፦ ጎግል \n \nጥያቄ: ኤስ ኦ ኤስ ማንቂያ ምን ዓይነት ችግሮች በሚፈጠሩበት ወቅት ስራ ላይ የሚውል ማንቂያ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል። ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማራያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል። ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ ይኖራል። አልፎም በግራኝ አህመድ ዘመን በእሳት ጋይቶ የነበረችውን አክሱም ፂዮን በአዲስ መሰረት እንደገና ማሰራት ችሎአል። ፋሲለደስ በዘመኑ እጅግ ተወዳጅ ንጉስ ቢሆንም አመጽ መነሳቱ አልቀረም። በላስታ ለምሳሌ በ1637 መልክዓ ክርስቶስ በተባለ ሰው መሪነት ጦርነት ተነስቶ አፄ ፋሲልን ስጋት ላይ ቢጥልም በሚቀጥለው አመት በተደረገው ጦርነት አመፁ ሊገታ ችሎአል። ፋሲለደስ ፖርቱጋሎችን ቢያባርርም ከውጭው አለም ጋር ብዙ ግንኙነት ያደርግ ነበር። ለምሳሌ በ1664-5 የህንድ ንጉስ አውራንግዘብ ሲነግስ መልካም ምኞትን በመልክተኞቹ ለሙግሃሉ መሪ ልኮ ነበር። በ1666 ልጁ ዳዊት ሲያምጽ፣ ወህኒ ተብሎ ወደሚታወቀው አገር በግዞት ልኮት ነበር። ይህም ከጥንቶቹ የኢትዮጵያውን ነገሥት ተፎካካሪያቸውን ወደ አምባ ግሽን በግዞት እንደሚልኩት ስርዓት ነበር። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲል ልጃቸውን ዳዊትን መቼ ወደ ግዞት ቤት ወሰዱት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1666 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nስታምፎርድ ብሪጅ (የእግር ኳስ ሜዳ) ስታምፎርድ ብሪጅ በፉልሃም ለንደን የሚገኝ የቼልሲ እግር ኳስ ቡድን የእግር ኳስ ሜዳ ነው። የእግር ኳስ ሜዳው የሚገኘው በሙር ፓርክ ኢስቴት (በሌላ አጠራር በዋልሃም ግሪን) ወይም በተለምዶ ዘ ብሪጅ ተብሎ በሚጠራ ቦታ ነው። ይህ የእግር ኳስ ሜዳ 41,798 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን፣ ከፕሪሚየር ሊጉ ስምንተኛ ትልቅ የእግር ኳስ ሜዳ ያደርገዋል። የተከፈተው እ.ኤ.አ በ1877 ሲሆን እስከ 1905 ድረስ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ይጠቀምበት ነበር። ሜዳው ብዙ ለውጦችን አካሂዷል። በቅርቡ ደግሞ (እ.ኤ.አ 1990ዎቹ) ወደ ዘመናዊና ለሁሉም ተመልካቾች መቀመጫ ያለው ሆኖ ተሠርቷል። ስታምፎርድ ብሪጅ የተለያዩ የእንግሊዝ ዓለም አቀፋዊ ጨዋታዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜዎችን ፣ የኤፍ ኤ ካፕ ግማሽ ፍጻሜዎችን እና የቻሪቲ ፊልድ ጨዋታዎችን አስተናግዷል። ለተለያዩ ስፖርቶችም እንደ ክሪኬት ፣ ራግቢ ዩኒየን ፣ ስፒድዌይ ፣ ግሬይሃውንድ ሬሲንግ ፣ ቤዝቦል እና የአሜሪካን ፉትቦል ጨዋታዎችን ለማስተናገድ ጥቅም ላይ ውሏል። የስታዲየሙ ትልቁ ኦፊሲዬላዊ የታዳሚዎች ቁጥር 82,905 ሲሆን ፤ ይህ የሆነው ቼልሲ ከአርሰናል እ.ኤ.አ በኦክቶበር 12 1935 ባካሄዱት የሊግ ጨዋታ ነበር። ስታምፎርድ ብሪጅ ፤ የለንደን አትሌቲክስ ክለብ ስታዲየም ሆኖ እ.ኤ.አ በ1877 ተከፈተ። በዚያ ሜዳ ላይ ታላላቅ የእግር ኳስ ጨዋታዎችን ለማዘጋጀት የፈለጉ ገስ እና ጆሴፍ ሚየርስ የተባሉ ወንድማማቾች ኮንትራቱን እስካገኙበት ጊዜ ድረስ ለለንደን አትሌቲክስ ክለብ እስከ እ.ኤ.አ 1904 ድረስ አገልግሏል። \n \nጥያቄ: በፉልሃም ለንደን የሚገኝ የቼልሲ እግር ኳስ ቡድን የእግር ኳስ ሜዳ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ስታምፎርድ ብሪጅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: ዋዝንቢት ለምን ተግባር ድምጽ ሊያወጣ ይችላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር በገዛ ፈቃዳቸው ሥልጣን የለቀቁት መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1980 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየስማርት ምሰሶ ቴክኖሎጂ ስማርት ከተሞችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አንዱ ግብዓት መሆኑን ስማርት ሲቲ ፕረስ ያትታል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም ደምበኞች የዳታ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸውን ስማርት ምሰሶ በእንጦጦ ፓርክ ማስመረቁ ይታወሳል፡፡ የስማርት ምሰሶ ቴክኖሎጂ ከተለመዱት የመንገድ ዳር ምሰሶዎች ጋር የሚመሳሰል ነገር ግን ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የያዘ ነው፡፡ ከሚሰጠው አገልግሎት መካከል አንዱ፥ ሰፊ አካባቢን መሸፈን የሚችል እጅግ ፈጣን የአራተኛ ትውልድ (4ጂ)፣ አምስተኛ ትውልድ ( 5ጂ) እና የዋይፋይ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ሌላው መኪና እና ታርጋን በቀላሉ መለየት የሚችሉ፣ የፊት ገፅታ ልየታን የሚያከናውኑ፣ ከፍተኛ የሆነ የቀለም ጥራት እና አጉልቶ የማሳየት አቅም ያላቸው የደህንነት ካሜራዎች ይኖሩታል፡፡ በተጨማሪም የአየር እና የድምፅ ብክለትን የሚለዩ፣ አደጋዎችን እና ወንጀሎችን በፍጥነት ለይቶ በመጠቆም የድንገተኛ ጊዜ ምላሽ አሰጣጡን የሚያቀላጥፉ መጠቆሚያዎችን ይይዛል፡፡ እንዲሁም የመንገድ መጨናነቅ እና አደጋን የመሰሉ እንዲሁም ሌሎች የድንገተኛ ጊዜ መልዕክቶች የሚሰራጩበት ዲጂታል ስክሪንም የሚኖረው ይሆናል፡፡ የስማርት ምሰሶ አገልግሎቶች በዚህ ብቻ የተገደበ ሳይሆን “ሁሉን በአንድ” በሚለው የቴክኖሎጂው መርህ መሰረት ሰዎች ከያዙት መሳሪያ ጋር በቀላሉ ተናቦ ለሌሎች አገልግሎቶች እንደሚውል ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮ ቴሌኮም በእንጦጦ ፓርክ ያስመረቀው ምንድን ነው ለደንበኞች ምን ዓይነት ጥቅም ያስገኛል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የስማርት ምሰሶ ቴክኖሎጂ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመዓዛ ብሩ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ታቀርባቸው የነበሩት ሥራዎች ይዘት ማህበራዊ ሕይወት እንዲሠምር በመጣር ላይ ያተኮሩ ሆነው ግልጽ፣ ቀላልና ለዛ ያልተለያቸው ስለነበሩ ከሶስት አሥርት ዓመታት በኋላም ትውስታቸው ከአድማጭ ህሊና አልጠፉም፡፡ በዚሁ ፕሮግራም ላይ መዓዛ ካበረከተቻቸው የፈጠራ ሥራዎቿ ውስጥ ጎልቶ የሚታወሰው “የአዲሱ ቤተሰብ” የተሰኘ ባለ ሰማንያ ስድስት ክፍል ድራማ ሲሆን በዘመኑ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም የሚያደምጠው ተወዳጅ የቤተሰብ ድራማ ነበር፡፡ መዓዛ በ “መርሀ ስፖርት” እና በሬዲዮ መካከል ሆና ከአራት ዓመት በላይ ከቆየች በኋላ በ1979 ዓ.ም የባህል ሚኒስቴርን ለቃ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀጠረች፡፡ አዲሱን መስሪያ ቤቷን ከተቀላቀለችበት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከሬዲዮ እየራቀች መጣች፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየችው ለሶስት ዓመታት ያህል ሲሆን ከዚያ በኋላ የግሏን የማስታወቂያ ሥራ ድርጅት መሥርታ የራስዋ ተቀጣሪ ሆናለች፡፡ ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1992 ዓ.ም ባሉት የአስራ ሶስት ዓመታት ጊዜ ግን መዓዛና ሬዲዮ ተራራቁ፡፡ መዓዛና ሬዲዮ ዳግም የተዋደዱት ከላይ እንደተገለጸው በ1992 ዓ.ም ሳምንታዊውን የ “ጨዋታ” ፕሮግራም በኤፍ ኤም 97.1 ከተፈሪ ዓለሙ ጋር በጋራ ማቅረብ ሲጀምሩ ነበር፡፡ የ “ጨዋታ” ፕሮግራም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ በአድማጮቹ እንደተወደደ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ላይ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የኤፍ ኤም ሬዲዮ ፈቃዶችን ለግሉ ዘርፍ ለመስጠት ሲዘጋጅ፣ ዝርዝር የሥራ እቅድ አቅርባ ባመለከተችው መሠረት፤ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ ከአስር አመልካቾች መካከል አንዷ ሆና የመጀመሪያ የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ባለቤት ያደረጋትን ፈቃድ ተቀበለች፡፡ መዓዛ የሬዲዮ ማሰራጫ መሳሪያዎችን ውድነት፣ የማሰራጫ ቦታ እና የባለሙያ እጦትን ተቋቁማ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮን በታህሳስ 1999 ዓ.ም አበረከተችልን፡፡ ባለትዳርና የሶስት ልጆች እናት የሆነችው መዓዛ እንደ ባለቤት፣ ሥራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ በመሆን በኢትዮጵያ ተወዳጁንና የመጀመሪያውን የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ትመራለች፡ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!”እያለች:: \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ የየትኛው ኤፍ ኤም ራድ ጣቢያ ባለቤት ነች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ በዓለም ዉስጥ ክሚገኙ ጥንታዊ አገሮች ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ አስቆጥራለች፡፡ በግእዝ/ዓማርኛ እና በመጽሀፍ ቅዱስ ከተመዘገቡት ተጨባጭ መረጃዎች በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን (ድንቅነሽን) አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡ ግብጽን ሲገዛ የነበረው ሄሮደስ የሚባለው ንጉስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታሪክ ፀሀፊ የጥንቷን ኢትዮጵያ በጽሁፎቹ ላይ ይገልፃታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይም ብዙ ግዜ የምትወሳ ስትሖን በተለይም ብሉይ ኪዳን ላይም የንግስት ሳባ (መከዳ) ኢየሩሳሌም መሄድና ለንጉስ ሰለሞን ከባድ የሆኑ ጥያቄዎች ማንሳቷ ተጽፏል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ያላትን መልክ እንድትይዝ ያደረጋት ንጉስ ሚኒሊክ የንግስት ሳባና የንጉስ ሰለሞን ዘር ናቸው፡፡ የንግስት ሳባ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም አካባቢ ይገኛል፡፡ ክርስትናን ኢትዮጵያዉያን ከመቀበላቸዉ በፊት (ኣስቅድመዉ) የኦሪትን ህግ ሰለሚያዉቁ ኣመተ ዓለምን ወደታች እየቆጠሩ የጌታን መወለድ ይጠብቁ ሰለነበረ ክርስትናን ለመቀበል ኣላስቸገራቸዉም፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትያን ርቃ ቆይታለች፡፡ \n \nጥያቄ: ንግስት ሳባ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ሄዳ ጥያቄ ስለማቅረቧ የሚያወሳው ታሪክ በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ብሉይ ኪዳን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: አልፍሬድ ኢልግ የምን ሀገር ዜጋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የስዊትዘርላንድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሃይማኖት ሃይማኖት አንድ ሕብረተሠብ የሚያምንባቸው ጽኑ እምነቶች መሠረት ነው። በዓለም ውስጥ በርካታ ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች አሉ። ዋና ዓለማዊ ሃይማናቶች ክርስትና፣ እስልምና፣ አይሁድና፣ የሕንዱ ሃይማኖት እና ቡዲስም ናቸው። እነዚህ ሃይማኖቶች በአንዳንድ አገር በይፋ የመንግሥት ሃይማኖት ሁኔታ አላቸው። ከነዚህ መጀመርያ ሦስቱ. ክርስትና፣ እስልምናና አይሁድና፣ ሁላቸው ከአብርሐም ስለ ተነሡ፣ «አብርሃማዊ ሃይማኖቶች» ተብለዋል። ሒንዱኢዝምና ቡዲስም ግን ከሕንድ ተነሡና «ሕንዳዊ» ወይም «ዳርማዊ ሃይማኖቶች» ተብለዋል። ሌሎች ሃይማኖቶች በአሁኑ ሰዓት በየትም አገር የመንግሥት ሃይማኖት ባይሆኑም፣ ባለፉት ዘመናት በታሪክ መንግሥታት ይኖራቸው ነበር፦ በተለይ ዛርጡሽና፣ ጃይኒስም፣ ሲኪስም፣ ዳዊስም፣ የኮንግ-ፉጸ ትምህርት፣ ሺንቶና የተለያዩ ኗሪ ወይም አረመኔ ሃይማኖቶች የቀድሞ መንግሥታት ነበሯቸው፤ የጠፉት ሃይማኖቶች ማኒኪስም እና አሪያኒስም ደግሞ የቀድሞ መንግስታት ነበሯቸው። በተጨማሪ መቸም መንግስት ያልነበረላቸው በርካታ ሌሎች አነስተኛ ሃይማኖቶች ወይም እምነቶች አሉ ወይም በታሪክ ተገኝተዋል። \n \nጥያቄ: አብርሃማዊ ሃይማኖቶች ተብለው የሚታወቁት የትኞቹ ሃይማኖቶች ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ክርስትና፣ እስልምና፣ አይሁድና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: እቴጌ ጣይቱ አዲስ አበባ የሚለውን ስም ለከተማዋ የሰጡት መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአመራር ክፍሎች ናይጄሪያ በሠላሳ ስድስት ክፍላገራት እና አንድ የፌዴራል ግዛት ተከፍላለች። እነዚህ ክፍላገራት ወደ ፯፻፸፬ የአካባቢ ግዛቶች ተከፍለዋል። ስድስት የናይጄሪያ ከተሞች ከአንድ ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች አሉባቸው። እነዚህም ሌጎስ፣ ካኖ፣ ኢባዳን፣ ካዱና፣ ፖርት ሀርኮርት እና ቤኒን ከተማ ናቸው። ሌጎስ ከ፰ ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሲኖሩባት ከሣህራ በታች በአፍሪካ ትልቁ ከተማ ናት። ብሔረሰቦች በናይጄሪያ ውስጥ ከ፪፻፶ በላይ ብሔሮች ይገኛሉ። ትልቆቹ ብሔሮች ፉላኒ ወይም ሀውዛ፣ ዮሩባ እና ኢግቦ ናቸው። ከእነሱ ቀጥሎ ደግሞ ኤዶ፣ ኢጃው፣ ካኑሪ፣ ኢቢብዮ፣ ኑፔ እና ቲቭ ይገኛሉ። በናይጄሪያ ውስጥ የተቆጠሩት ቋንቋዎች ፭፻፳፩ ይሆናሉ። ከእነዚህም ውስጥ ፭፻፲ቹ መደበኛ ተናጋሪዎች አሏቸው። ሁለት ቋንቋዎች እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ብቻ ነው የሚነገሩት። ዘጠኙ ደግሞ ተናጋሪ የሌላቸው የጠፉ ቋንቋዎች ናቸው። ከእንግሊዝኛ በኋላ ዋናዎቹ ልሳናት ዮሩብኛ፣ ሐውዝኛና ኢግቦኛ ናቸው። \n \nጥያቄ: በናይጄሪያ ምን ያህል የታወቁ ቋንቋዎች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፭፻፳፩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: በ፲፱፻፵፱ ዓ/ም የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ኢትዮጵያን የጎነኙት ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሪቻርድ ኒክሰን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: ከማአንያን ቋንቋ በየት አካባቢ የተገኘ ቋንቋ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዝግመተ ለውጥ የአንድ ሕይወት ያለው ማህብረሰብ የዘር ውርስ ባህሪይ ከትውልድ ወደትውልድ እየተቀየረ መሄዱ ዝግመተ ለውጥ ይባላል። ቻርለስ ዳርዊን ይህን ኩነት በማስተዋልና በሳይንሳዊ አመክንዮ አሰደግፎ በመተንተኑ የመጀመሪያው ሰው ነው። ዳርዊን በተጨማሪ የተፈጥሮ ምርጫ ባለው ኅልዮቱ ሕይወት ያላቸው ማህበረሰቦች ዝግመተ ለውጥ እሚያካሂዱት ምንም እንኳ በዘፈቀደ ስህተት እየፈጸሙ ቢሆንም፣ ተፈጥሮ እራሷ በምትፈጥረው መሰናክሎች እኒህን መሰናክሎች አልፈው የሚሄዱትን በመምረጧ ነው። ዳርዊን የተፈጥሮ ምርጫን አስተሳሰብ ከ፫ የሚታዩ ነገሮች አንጥሮ ነበር ያወጣው፦ ፩) እንስሳትም ሆነ እጽዋት ወደፊት ሊኖር ከሚችሉ ዘሮች በላይ አተረፍርፈው ነው እሚራቡት ፪) ሕይወት ያላቸው እያንዳንዳቸው ነገሮች ሁልጊዜ የተለያየ ጸባይ ነው ያላቸው፣ ስለሆነም እያንዳንዳንቸው በቀጣይ የመኖር ዕድላቸው የተለያየ ነው ፫) ስለሆነም የአንድ ማህበረሰብ አባላት ሲሞቱ፣ የሚገላቸውን ነገር ጠንክረው እሚቋቋሙት ግለሰቦች ብቻ በሕይወት ቆይተው ወደፊት መራባች ይችላሉ። ስለሆነም ቀስ በቀስ እነዚህ በህይወት ያሉ፣ በህይወት የሌሉትን አይነቶች እየተኩ ይሄዳሉ። በ፳ኛው ክፍለ ዘመን ጄኔቲክስ (ሥነ በራሂ) እና ዝግመተ ለውጥ ተዋህደው ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ እሚባለውን ጥናት ለመፍጠር ችለዋል። አንድ ማህበርሰብ ለየት ያለ ግለሰቦችን ለመፍጠር ከሚያስችሉት መንገዶች አንዱ ሙቴሽን የተባለው ሂደት ሲሆን፣ ሙቴሽን እሚፈጠረው የዚያ ግለሰብ ዲ ኤን ኤ ከወላጆች ሲወረስ በሚደረግ ስህተት (ወይም እቅድ) ነው። \n \nጥያቄ: የአንድ ሕይወት ያለው ማህብረሰብ የዘር ውርስ ባህሪይ ከትውልድ ወደትውልድ እየተቀየረ መሄድ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዝግመተ ለውጥ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሊቢያ ኦይል ዓመታዊ ሽያጩ ስንት ደርሷል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 13 ቢሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአረማይክ አረማይክ ወይም አራማይስጥ፣ የሶርያ ቋንቋ ከሴማዊ ቋንቋዎች አንዱ ሲሆን በመካከለኛ ምሥራቅ ከጥንት ጀምሮ ታውቋል። መጀመርያ የአረማይክ ጽሑፎች ከ1000 ዓክልበ. ግድም በፊንቄ አልፋቤት ነበሩ፤ ይህም የአራም ሕዝብ የተናገሩት ጥንታዊ አራማይስጥ ነበር። በአንድ አስተሳሰብ ቋንቋቸው ከ1100 ዓክልበ. አስቀድሞ ሑርኛ ይሆን ነበር፤ የአሦርም መንግሥት ከገዙአቸው በኋላ እንደ አካድኛ ሴማዊ ሆነ። ከ800 ዓክልበ. አካባቢ በኋላ የራሱ አረማይክ አልፋቤት ከፊንቄ አልፋቤት ተለማ። በ740 ዓክልበ. የአሦር ንጉሥ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር አረማይስጥ ከአሦርኛ (አካድኛ) ጋር ይፋዊና መደበኛ ቋንቋ አደረገው። ከዚያ ጀምሮ የአረማይስጥ ጥቅም እየተስፋፋ የአካድኛ ጥቅም በየጊዜ ይቀነስ ነበር። ከአሦር ውድቀት (617 ዓክልበ.) በኋላ በባቢሎኒያ መንግሥት፣ ከባቢሎኒያም ውድቀት (547 ዓክልበ.) በኋላ በፋርስ አሓይመኒድ መንግሥት ውስጥ፣ አረማይክ መደበኛና ይፋዊ ቋንቋ ተደረገ፣ ስለዚህ ጥቅሙ በሰፊ ከግብጽ እስከ ባክትሪያ ድረስ ይዘረጋ ነበር። በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ የተገኘው አራማይክ በተለይ በትንቢተ ዳንኤል ከዚሁ ዘመን ነው። \n \nጥያቄ: አረማይክ የምን ቋንቋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የሶርያ ቋንቋ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች የካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች በካናዳ አገር 1974 ዓ.ም. ሕገ መንግስት ሥር ኢንዲያን (መጀመሪያ አገሮች የተባሉ)፤ ሜቲ (ክልሶች)፤ እና እኑዊት (ወይም ኤስኪሞ) ናቸው። እነዚህ 3 ክፍሎች አንድ ላይ ደግሞ መጀመርያ ሕዝቦች ይባላሉ። በካናዳ በተደረገው 1993 ቆጠራ ዘንድ፣ የጥንታዊ ኗሪዎች ብዛት ከ900,000 በለጠ። በዚህ ቁጥር ውስጥ 600,000 ከመጀመርያ አገሮች ዘር፤ 290,000 ሜቲ፣ እና 45,000 እኑዊት ይከተታሉ። የጥንታዊ ኗሪዎች ማህበራዊ ወኪሎች በካናዳ እንዲህ ናቸው፤ የመጀመርያ አገሮች ስብሰባ ለመጀመርያ አገሮች፤ እኑዊት ታፒሪት ካናታሚ ለእኑዊት፤ የሜቲ ብሔራዊ ጉባኤ ለሜቲ ናቸው። ባለፈው ዐሥር አመት የካናዳ መንግሥት የዘውድ ጉባኤ ስለ ጥንታዊ ኗሪዎች ሰበሰበ። ይህ ጉባኤ ያለፉትን መንግስት ዐቅዶች ስለ ጥንታዊ ኗሪዎች ለምሳሌ የሚሲዮን ተማሪ ቤቶች አመዛዝኖ ብዙ የአቅዋም ምክሮች ለካናዳ መንግስት አቀረበ። ብዙ መጀመርያ አገሮች የሚኖሩት በተከለለ ቦታ ሲሆን፣ ብዙ ኗሪዎች ደግሞ ከቦታዎቹ ውጭ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: በካናዳ 1974 ዓ.ም. ሕገ መንግስት ሥር ኢንዲያን፣ ሜቲ፣ እና ኤስኪሞዎች እንዲካተቱ የተደረጉት ነዋሪዎች ምን በመባል ይታወቃሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2012(ኤፍ ቢሲ) አሜሪካ የሁዋዌ የአምስተኛ ትውልድ ኔትወርክን (5G) መጠቀም እብደት ነው ስትል ብሪታኒያን አስጠነቀቀች፡፡ አሜሪካ የቻይና ኩባንያዎች አገልግሎት መጠቀም ሊያስከትል የሚችለውን የደህንነት ስጋት የሚያሳይ አዲስ ማስረጃ ለብሪታኒያ አቅርባለች፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጉዳዩ ዙሪያ በሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ላይ ጫና ለማሳደር እንደሚፈልጉ ተጠቁሟል፡፡ በዚህ ወር ሁዋዌ ኩባንያ ለብሪታኒያ የኔትወርክ ዝርጋት አንዳንድ “መሠረታዊ ያልሆኑ” ክፍሎችን ያቀርብ አያቅርብ የሚል ውሳኔ ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የሁዋዌ ቃል አቀባይ ባለፉት 15 ዓመታት ለብሪታኒያ የ3ጂ ፣ 4ጂ እና ብሮድባንድ መሳሪያዎችን ሲያቀርብ የቆየ የግል ኩባንያ መሆኑን በመግለፅ በዚህም የሃገሪቱ ባለሙያዎች ቴክኖሎጂያቸው የደህንነት ስጋት እንደማያመጣ ማረጋገጣቸውን ጠቁመዋል፡፡ አሜሪካ ባለፈው ዓመት በደህንነት ስጋት ምክንያት ለሁዋዌ እና 68 ተዛማጅ ኩባንያዎች የቴክኖሎጂና ሌሎች መሳሪያዎችን እንዳይሸጡ ገደብ መጣሏ የሚታወስ ነው፡፡ ምንጭ፡-ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አሜሪካ የሁዋዌን አምስተኛ ትውልድ ኔትወርክን እንዳትጠቀም ያስጠነቀቀቻት አውሮፓዊ ሀገር ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ብሪታኒያን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: በቀጭኔ ክብደት ላይ እስከ አሁን በሪከርድነት የተያዘው ከፍተኛው ክብደት ስንት ኪ.ግ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 2000ኪ.ግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: የተፈሪ መኮንን ወላጅ አባታቸው ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከልዑል ራስ መኰንን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ወደ ዚምባቡዌ ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት በብረት ዘመን የፈለሱት ሰዎች የምን ቋንቋ ተናጋሪዎች ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የባንቱ ቋንቋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የ2021 የሥነ ጽሑፍ ኖቤል ተሸላሚ ማናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአል የተባለ ሰው ሰራሽ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ከሐኪሞች በተሻለ ትክክለኛ መሆኑን አንድ ጥናት አመለከተ። ሰው ሰራሹ መሳሪያ የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያን በማንበብ ረገድ ሁለት ሐኪሞች በጋራ ከሚሰሩት በተሻለ መልኩ ትክክለኛ መሆኑን ባለሙያዎቹ አረጋግጠናል ብለዋል። ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጣው ቡድን አል የተባለው ሰው ሰራሽ መሳሪያን ይዘው በ29 ሺህ ሴቶች ላይ ሙከራ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። በዚህም መሳሪያው የጡት ካንሰርን በመለየት ረገድ የስድስት ራዲዮሎጂ ባለሙያዎችን ያክል ውጤታማ መሆኑንም ገልጸዋል። ይህም ሁለት የዘርፉ ሐኪሞች (ዶክተሮች) ከሚሰሩት ስራ ጋር እኩል ውጤት ያለው ስለመሆኑም በጥናት ውጤታችን አረጋግጠናል ነው ያሉት። ከዚህ ባለፈም መሳሪያው እንደ ሐኪሞቹና ራዲዮሎጂስቶቹ የግለሰቧን የቀደመ የጤና ሁኔታ የሚገልጽ መረጃ ሳይኖረው የጡት ካንሰሩን መለየት መቻሉም የተሻለ ስለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ባለው አሰራር ሁለት የራዲዮሎጂ ባለሙያዎች ችግሩን ለመለየት የጡት ካንሰር መለያ መሳሪያውን የሚያነቡ ሲሆን፥ ባልተስማሙባቸው ጉዳዮች ላይ ሦስተኛ ሐኪም ተጨምሮ ምስሎቹን እንዲገመግም ይደረጋል። አዲሱ መሳሪያ ራሱን ችሎ ከማንበቡም በላይ ችግሩን ለይቶ በመረዳት በኩል ውጤታማ ስለመሆኑ በባለሙያዎቹ ተመስክሮለታል። መሳሪያው የጡት ካንሰር ምርመራ ውጤት ላይ ከባለሙያዎቹ የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡም ተገልጿል፤ በዚህም ለታካሚዋ የጡት ካንሰር አለብሽ በሚል በባለሙያ የሚነገራትን ሃሰተኛ የምርመራ ውጤት በ1 ነጥብ 2 በመቶ ቀንሷል። ከዚህ ባለፈም በምርመራ ወቅት የጡት ካንሰር የለም በሚል የሚነገር የተሳሳተ ውጤት ደግሞ ከባለሙያ አንጻር መሳሪያው በ2 ነጥብ 7 በመቶ መቀነሱን ባለሙያዎቹ ገልጸዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አል የተባለው የጡት ካንሰር መመርመሪያ መሳሪያ በስንት ሰዎች ላይ ሙከራ ተደርጎ ነው ውጤታማነቱ የተረጋገጠው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ29 ሺህ ሴቶች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ የት ተወለዱ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በዛንዚባር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: ኩሻዊ የቋንቋ መደብ ውስጥ የሚጠቃለሉ የኢትዮጵያ ቋንቋዎችን ዘርዝር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት የተኖቹ አናብስት ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሴቶቹ አንበሶች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፄ ይስሐቅ ቀዳማዊ አጼ ይሥሓቅ በዙፋን ስማቸው \"ዳግማዊ ገብረ መስቀል\" ሲባሉ እ.ኤ.አ ከ1414-1429 የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የነበሩ ናቸው። የቀዳማዊ አጼ ዳዊት ሁለተኛ ወንድ ልጅ ሲሆኑ የቀዳማዊ ቴዎድሮስ ታናሽ ወንድም ናቸው። ከአክሱም ነገሥታት በኋላ የመጀመሪያውን ከአውሮጳውያን መሪወች ጋር ግንኙነት ያደረገው ይሄው ንጉስ ነበር። ለምሳሌ ለአራጎን መሪ ለነበርው አልፎንሶ አምስተኛ በ1428 ዓ.ም. በእስላሞች ላይ የተባበረ ሃይልን ለመመስረት ደብዳቤ ልኳል። በዚሁ ደብዳቤ የጋብቻን ነገር ያወሳ ሲሆን ህጻኑ ዶን ፔድሮ ከእጅ ጥበብ አዋቂወች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የይስሓቅን ሴት ልጅ እንዲያገባ ያትታል። አልፎንሶ ለይስሓቅ የመለሰለት ደብዳቤ ባይገኝም ለይስሓቅ ተከታ ለአጼ ዘርዓ ያዕቆብ በ1450 በደረሰ ደብዳቤ ደህንነታቸው እስከተጥበቀ ድረስ እጅ ጥበበኞችን በደስታ ወደኢትዮጵያ እንደሚልክና ከአሁን በፊት የላካቸው 13 ጥበበኞቹ በመንገድ ላይ እንደጠፉ ሳይጠቅስ አላለፈም። በኒሁ ንጉስ ዘመን በፈላሾች በተነሳ አመጽ ምክንያት ንጉሱ ወደወገራ ዘምተው አመጸኞቹን ኮሶጌ ላይ በማሸነፍ አመጹን አረገቡ። በዚያውም ደብረ ይሥሓቅ የተሰኘውን ቤተክርስቲያን ለድሉ ማስታወሻ ኮሶጌ ላይ አሰሩ። . ንጉሱ ተመልሰው ከአገው ምድር ባሻገር ያለውን የሻንቅላ ምድር ላይ ዘመቻ አካሂደዋል። በደቡብ ምስራቅ ደግሞ ከአረብ አገር የተመለሱትን የሳድ አዲን ፪ኛ ልጆች ወግተዋል። ታሪክ አጥኝው ታደሰ ታምራት ይስሓቅ ከመስሊሞች ጋር ሲዋጋ ወደቀ ይበል እንጂ ዋሊስ በድጅ በርግጥም በወንጀል እንደተገደለና በተድባባ ማርያም እንደተቀበረ ይናገራል። \n \nጥያቄ: አፄ ይስሐቅ በኮሶጌ ያሰሩት ቤተክርስቲያን ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ደብረ ይሥሓቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: የአባይ ፏፏቴ ላይ ውሃው ወደ ታች ምን ያህል ርቀት ይወረወራል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 37 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሩሲያ ለአለም አቀፍ በይነመረብ አማራጭ የሚሆን አር ዩ ኔት የተሰኘ ኢንተርኔት በተሳካ ሁኔታ መሞከሯን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል ፡፡ ይሁን እንጂ የተከናወነውን ሙከራ በተመለከተ ዝርዝር መረጃ አለመሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። እንደ ሀገሪቱ ኮሙኒኬሽን ሚኒስቴር መረጃ ፥ማንኛውም ተጠቃሚ በተደረገው ሙከራ ወቅት ምንም አይነት ለውጥ ማስተዋል አለመቻሉን አስታውቋል፡፡ የሙከራ ውጤቱም ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ይቀርባል ነው የተባለው ፡፡ ምሁራኖችበ አንዳንድ ሀገሮች በበይነ መረብ የሚደርስ ጥፋትን እንዳለ ይጠቅሳሉ። በጥናቱ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒተር ሳይንቲስት የሆኑት ፕሮፌሰር አላን ውድዋርድ እንዳሉት፥ በሚያሳዝን ሁኔታ የበይነመረብ ሰርጎ ገቦች መበራከት የሩሲያ የጉዞ አቅጣጫ ሌላ ደረጃ እያደረሰ ነው። ቁጥራቸው እየጨመረ ያሉ ሃያላን መንግስታት ዜጎች የሚያዩትን መቆጣጠር የሚፈልጉ ስለመሆናቸው ከኢራን እና ከቻይና መመልከት ይቻላል። ይህ ማለት ሰዎች ሀገራቸው ውስጥ ስለሚሆነው ነገር የመነጋገር እድል አይኖራቸውም፡፡ የተገኘው ውጤት እንደሚያሳየው ባለስልጣኖች እና የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ውጤታማ ምላሽ በመስጠት አደጋዎች እና ስጋቶችን ማስወገድ እንዲሁም በሁለቱም በይነመረብ እና ቴሌኮሙዩኒኬሽን አውታር መረብ ውስጥ የተስተካከለ አሠራር በሩሲያ ፌዴሬሽን እንዲኖር ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸው ተነግሯል። \n \nጥያቄ: የሩሲያ ፕሬዝደንት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ቭላድሚር ፑቲን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ሬይን ሜከርስ በ1996ዓ.ም. ለመትከል ካቀዱት ምን ያህሉን አሳኩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሀያ ከመቶው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ሆኖ በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ የሚሆነው ምን ላይ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሬቴ ሚራቢሌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ሣህሌ ደጋጎ የአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች የሚያንቆረቁሩት በየትኛው የራዲዮ ጣቢያ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየኩላሊት ጠጠር የኩላሊት ጠጠር የሚባለው በኩላሊት ውስጥ የጠጣር ነገሮች መጋገር ወይም መሰብሰብ ሲሆን የጠጣር ነገሮቹም ምንጭ በሽንት ውስጥ የሚገኙ የምግብ ንጥረ ነገሮች ናቸው። ፹ በመቶ (80%) ወንዶች በአብዛኛው የኩላሊት ጠጠር ህመም ከ ፴(30)-፵(40) ባለው እድሜአቸው ሲጀምራቸው ሴቶች ላይ ግን ዘግይቶ ይከሰታል። የኩላሊት ጠጠሮች በአመዛኙ ምንም የህመም ስሜትና ጉዳት ሳያስከትሉ በሽንት መስመር ውስጥ አልፈው ከሰውነት ይወገዳሉ ነገር ግን ጠጠሮቹ በመጠን ከጨመሩ (፫(3) ሚሜ አካባቢ ከደረሱ) የሽንት ትቦ ሊዘጉ ይችላሉ የሽንት ትቦ በጠጠር መዘጋት ሽንት በቀላሉ እንዳይተላለፍ (ፓስቴርናል አዞቶሚያ) ብሎም ሽንት ወደ ሁዋላ በመመለስና በኩላሊት ውስጥ በመከማቸት ሃይድሮኔፕሮሊስ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል:: ይሄ ችግር (ሃይድሮኔፕሮሊስ) ከታችኛው የጎድን አጥንት አንስቶ እስከ የዳሌ አጥንት ድረስ ባለው ቦታ በብሽሽትና በታችኛው የምግብ መፍጫ ክፍሎች አካባቢ ለህመም ስሜት (ሬናል ኮሊክ) ይዳርጋል። የኩላሊት ጠጠር ከማቅለሽለሽና የማስታወክ ስሜቶች ትኩሳት በሽንት ውስጥ ደም መኖር በሽንት ውስጥ መግል የሚመስል ፈሰሽ እና በሽንት ጊዜ ከከፍተኛ የህመም ስሜት ጋር ሊያያዝ ይችላል። የኩላሊት ጠጠር መኖር በሰውነት አቁዋም ምርመራዎች (ፊዚካል ኤግዛሚኔሽን) በሽንት ምርመራ በራጅ ምርመራ እንዲሁም በበሽተኛው የበፊት የጤና ምርመራ ውጤቶች ድጋፍ ይታወቃል። የአልትራሳውንድ እና የደም ምርመራዎችም የኩላሊት ጠጠር በሽታ መኖሩን ለማወቅ አጋዥ ይሆናሉ። ለኩላሊት ጠጠር መፈጠር ምክንያት ሊሆኑ ከሚችሉ የአመጋገብ ልምዶች መካከል፤ ውሃ በበቂ አለመጠጣት፣ ከፍተኛ የሆነ የእንሥሳት ሥጋ (ፕሮቲን) መመገብ፣ ጨው (ሶዲየም)፣ የተጣሩ ስኳሮች፣ የፍራፍሬ ስኳር (ፍሩክቶስ)፣ ኦክሳሌት የያዙ ምግቦች (ኦክሳሌት በብዙ ዕፅዋት ውሥጥ የሚገኝ ንጥረ ነገር ሲሆን በተለይም በሰባ ዶሮ፣ በጥቀር አዝሙድ፣ ፐርስሊ፣ ስፒናች፣ ካካዎ፣ ቸኮላት፣ ኦቾሎኒ፣ አብዛኛዎቹ እንጆሬዎች ውስጥ ይገኛል)፣ የአፕል ጭማቂ እና የኮላ መጠጦች ናቸው። \n \nጥያቄ: ወንዶች አብዛኛውን የኩላቲት ጠጠር ህመም የሚከሰትባቸው በየትኛው እድሜ ክልል ውስጥ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ ፴(30)-፵(40) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአራተኛ አልበሙ \"ፐርፐዝ\" በሁለት ሺ ሰባት ተለቀቀ እነዚህንም ቀጥር አንድ የሆኑ ሙዚቃዎች ያዝሉለታል፦ \"ዋት ዱ ዩ ሚን\"፣ \"ሶሪ\" እና \"ሎቭ ዩርሰልፍ\"። \"ዌር ኧር ዩ ናው\" ከአሜሪካው የኢዲኤም ቡድን ጃክ ዩጋ የሰራው ይህ ነጠላ ዘፈን በግራሚ ምርጥ ዳንስ ቅጅ በሚለው ፈርጅ ሊሸለም ችሏል። በቀጣይ ጊዜያት ጀስትን ቢበር አነዚህ ሙዚቃዎች ላይ ድምፁን አዋጣ ከተለያዩ አርቲስቶችጋ፣ ሙዚቃዎቹ፦ \"ኮልድ ዋተር\"፣ \"ለት ሚ ሎቭ ዩ\"፣ \"አይ አም ዘ ዋን\"፣ እና \"አይ ዶንት ኬር\" ፡ ሙዚቃዎቹም በአሜሪካ የደረጃ ሰንጠረዥ አምስት ውስጥ ሊገቡ ቻሉ። \"ደስፓሲቶ\" ለተሰኘው ሙዚቃም ድምፁን ሙዚቃው ከተለቀቀ በኋላ በማከል ዋና ዘፋኞቹን ደገፈ ፡ ሙዚቃውም ለብዙ ሳምንታት ከፍታ ላይ ቆየ በቢልቦርድ። \"ተን ታውዘንድ አወርስ\" ሙዚቃ ላይም በድምፅ ተሳትፏል ሙዚቃው ጥንድ/ቡድን በተሰኘ ፈርጅ ግራሚ ሊያሸንፍ ቻለ። አራተኛ አልበሙን ከለቀቀ አምስት አመት በኋላ ጀስትን በ፪፲፻፲፪ አምስተኛ አልበሙን በተለየ የሙዚቃ አቀራረብ ለቀቀ ከአልበሙም እነዚህ የአርኤንድቢ ሙዚቃዎች አምስት ውስጥ ሊገቡለት ቻሉ ፡ \"የሚ\" እና \"እንተንሽንስ\"። ከአለም ምርጥ ሻጭ አርቲስቶች አንዱ የሆነው ጀስትን ከአንድ መቶ ሀምሳ ሚልየን ቅጂዎች በላይ ሸጦ እናም የተለያዩ አያሌ ሽልማቶችን ሊያገኝ ችሏል ተካተው፦ ሀያ ሶስት የአለም ጊነስ ርኮርዶች፣ ሁለት ግራሚ፣ አንድ የርኮርድ ትወኒዋ ኤም ቲቪ ዩሮፕ ሚውዚክ፣ ሀያ የቢልቦርድ፣ አስራ ስምንት የሜሪከን ሚውዚክ አዋርድስ፣ ሁለት የብርት አዋርድስ፣ አራት የኤም ቲቪ ሚውዚክ ቪድዮ ሽልማቶችና አንድ ደግሞ የላቲን ግራሚ ሽልማ። \"ታይም\" የተባለ ታዋቂ የመረጃ ተቋም የአለማችን መቶ ከፍተኛ ተፅእኖ ፈጣሪ ሰዎች ብሎ ካወጣቸው ውስጥ ጀስትን ቢበር አንዱ ነበር በሁለት ሺ ሶስት። \n \nጥያቄ: ጀስቱን ቢበር በግራሚ ምርጥ የዳንስ ቅጅ በሚባል ፈረጅ ሊሸለም ያረገው ዘፈኑ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዌር ኧር ዩ ናው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበኦስትሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ላይ ከባድ የሳይበር ጥቃት መፈጸሙ ተሰምቷል። የሳይበር ጥቃቱ በሌላ ሀገር አማካኝነት የተቀነባበረ ሳይሆን እንዳልቀረ የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አስታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመውም አረንጓዴ የተሰኘው የኦስትሪያ ፓርቲ ከወግ አጥባቂ ፓርቲዎች ጋር ጥምረት ለመመስረት የቀረበው ሃሳብ በደገፈበት ቀን ነው ተብሏል። የሳይበር ጥቃቱ ትናንት ማታ የተጀመረ ሲሆን፥ በቀጣይ ቀናት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል። የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጠው መግለጫ፥ የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ክስተቱን በፍጥነት በመረዳት አስፈላጊ እርምጃዎች መወሰዳቸውን አስታውቋል። ይን እንጂ መስሪያ ቤቱ በተፈጸመው የሳይበር ጥቃት ምን ያህል ጉዳት ስለመድረሱ ያለው ነገር የለም። በሌላ በኩል አሁን ላይ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ከማድረግ ባለፈ ወደ ፊት ሊፈጸም የሚችልን የሳይበር ጥቃት መቶ በመቶ መቆጣጠር አስቸጋሪ መሆኑ ተመላክቷል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጀምሮ የአውሮፓ ሀገራት በርካታ የሳይበር ጥቃቶችን እያስተናገዱ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ። ምንጭ ፦ቢቢሲ   \n \nጥያቄ: በየትኛዋ የአውሮፓ ሀገር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ላይ ነው ከባድ የሳይበር ጥቃት የተፈጸመው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በኦስትሪያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን የት ተከታተሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በናዝሬት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nታሊየም የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ መረጃ መዝባሪዎች ቡድን ሚስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር እንደተቆጣጠረው ማይክሮ ሶፍት አስታወቀ፡፡ መቀመጫው ሰሜን ኮሪያ እንደሆነ የታመነው ይህ መረጃ መዝባሪ ቡድን የመንግስት ሰራተኞችን ፣ የዩኒቨርሲቲ ሰራተኞችን ፣ የኒውክሌር ሙያተኞችን እና የጥናት ተቋማንን ኢላማ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የመረጃ መዝባሪ ቡድኑ በዋነኝነት ኢላማ ያደረገው በአሜሪካ የሚገኙ ተቋማትን ሲሆን በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚገኙ ተቋማንንም ኢላማ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡ ታሊየም በመጀመሪያ እይታ ትክክለኛ ሆነው የሚታዩ የኢሜል አድራሻዎችን በመጠቀም መረጃ ሲመዘብር ነበር ተብሏል፡፡ ማይክሮሶፍትም በአሁን ወቅት መረጃ መዝባሪ ቡድኑ የሚጠቀምባቸውን 50 የድር ጎራዎች መቆጣጠሩን የገለፀ ሲሆን በምሥራቃዊ ቨርጂኒያ አውራጃ በሚገኝ ፍርድ ቤት በጠለፋ ቡድን ላይ ክስ መመስረቱን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡-ሮይተርስ \n \nጥያቄ: ታሊየም የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ መረጃ መዝባሪዎች ቡድን ምን ዓይነት መረጃዎችን ነው የሚመዘብረው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሚስጢራዊ መረጃዎችን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጀስትን ቢበር ጀስትን ድሩ ቢበር (ተወለደ በ፲፻፱፻፹፮ በመጋቢት)፣ ካናዳዊ ዘፋኝ። ጀስትን ቢበር ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለመለው በአሜሪካዊው የቅጂ ድርጅት ባለቤት እስኩተር ብሮን ሲሆን የፈረመው ደግሞ ከአርቢኤምጂ የቅጂ ድርጅት በ፪፲፻ አመተ ምህረት ነው። በቀጣዩ አመት ማለትም በ፪፲፻፩ የመጀመሪያ ኢፒ(EP)ውን ለቆ እውቅናን እየተጎናፀፈ ብዙም ሳይቆይ እራሱን መገንባት እንደ ምርጥ ታዳጊ። የጀስትን ቢበር የመጀመሪያ አልበም (ማይ ወርልድ 2.0) በሁለት ሺ ሁለት ተለቀቀ፤ አልበሙም ቁጥር አንድ ሆኖ ላለፉት አርባ ሰባት አመታት (ማለትም ከሁለት ሺ ሁለት አመተ ምህረት ወዲያ ባሉ ጊዜያት) በማንም ታዳጊ ወጣት ሊያዝ ያልተቻለውን ደረጃ ይዞ አሳየ በዪናይትድ እስቴትስ። አልበሙም በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኘውን \"ቤይቢ\" የተሰኘውን ነጠላ ዘፈን ይይዛል፣ ይህም ዘፈን የምንጊዜም ከፍተኛ የምስክር \"ወረቀቶች\" ያገኘ ሊሆን ችሏል በተመሳሳይ ሀገር። የጀስትን ቢበር ቀጣይ አልበም (አንደር ዘ ሚስትልተው) በሁለት ሺ ሶስት ፡ የመጀመሪያው የገና አልበም ነበር በወንድ አንደኛ ለመሆን ከቢልቦርድ መቶ አልበሞች። በቀጣይ አመት (ሁለት ሺ አራት) ሶስተኛ አልበሙን ተከትሎ ጀስትን ቢበር ከህዝብ ጋር ያለው ግንኙነት በሻካራ ሁኔታ ተቀየረ የተለያዩ ክርክሮች በመነሳታቸው እና በህጋዊ ጉዳዮቹ ምክኛት (በሁለት ሺ አምስት እና ስድስት አመት ውስጥ) ፡ እንዲያውም ሮልንግ እስቶን የተባለ ታዋቂ የመረጃ ድርጅርት ጀስትን ቢበርን \"መጥፎ ልጅ\" ብሎ ሰየመው በመጋቢት ሁለት ሺ ስድስት ጉዳዩ። ይሁን እንጂ ከሁለት ሺ ስምንት ጀምሮ ጀስትን ቢበር ተቀዳሚነቱን ለዳግም ህዝባዊ ግንኙነቱ ሲያውል ነበር ፡ ሲያውል ነበር ለአይምሮው ጤንነት። የካቲት ሁለት ሺ ስምንት ጂኪው የተባለ ታዋቂ የመረጃ ተቋም ስለ ጀስትን ቢበር ራስ ማደስ ተነሳሽነት አስመልክቶ ፅሑፍ ይዞ ሊወጣም ችሏል። \n \nጥያቄ: ጀስቲን ቢበር እውቅናን እንዴት አገኘ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፪፲፻፩ የመጀመሪያ ኢፒ(EP) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: አፈወርቅ ተክሌ መች ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር በ1931 የተመረቁበት ትምህርት ቤት ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮጵያ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል። ባለፈው አመት የመጠቀችው “ETRSS-1” የሚል ስያሜ የተሰጣት ምድርን እየቃኘች ፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው ሳተላይት በሀገራችን የዕድገት ጉዞ ላይ ቁልፍ ሚና እንደሚኖራት መነገሩ አይዘነጋም። መረጃ መላክ የጀመረችው ይች ሳተላይት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ አሁን ደግሞ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን ነው ኢንስቲትዩቱ ያስታወቀው። \n \nጥያቄ: በ2012 ዓ.ም የመጠቀችው የኢትዮጵያ ሳተላይት ምን ስያሜ ተሰጣት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ETRSS-1 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ የተመረጠው ድርጅት ማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አማን እና ዊትኒ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. መሠረቱ። ከምዕራቡ ሮማ መንግሥት ውድቀት ደግሞ ወደ ተረፈው ሕዋእ ውስጥ ከፈለሱት ጀርመናውያን ወገኖች አብዛኛው የራሳቸውን ሕጎች ዝርዝር በጽሑፍ አወጡ። በተለይ የሚታወቁም የቪዚጎቶች አለቃ ዩሪክ ሕግ (463 ዓ.ም.)፣ የቡርጎንዳውያን ሕግጋት (እኚህ ለጀርመናውያንና ለሮማውያን የተለያየ ፍትሕ ነበራቸው)፣ የአላማናውያን ሕግጋትና፣ የፍራንኮች ሕግጋት ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ የተጻፉት ከ492 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በ498 ዓ.ም. የቪዚጎቶች አለቃ 2ኛ አላሪክ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስና አንዳንድ የተለያዩ የቀድሞ ሮማ ሐገጋት አከማችተው አዋጁአቸው። ከዚህም በኋላ የታዩ ሕጎች የሎምባርዶች ሕግጋት (635 ዓ.ም.)፣ የቪዚጎቶች አዳዲስ ሕግጋት (646 ዓ.ም.)፣ የአላማናውያን አዳዲስ ሕግጋት (722 ዓ.ም.) እና የፍሪዝያውያን ሕግጋት (777 ዓ.ም.) አሉ። በአውሮፓ አኅጉር ላይ የተጻፉት እነኚህ ፍትሖች ሁሉ በሮማይስጥ ቢጻፉም፣ በእንግሊዝ አገር ግን የተጠቀሙት ሕጎች ከኬንት ንጉሥ ኤጠልቤርት ሕጎች (594 ዓ.ም.) ጀምሮ በጥንታዊ እንግሊዝኛ የተቀነባበሩ ነበሩ። በ885 ዓ.ም. ታላቁ አልፍሬድ ይህንንና ሁለት የድሮ ፍትሖች ከሕገ ሙሴና ከሕገ ወንጌል ጋራ አጋጥመው የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ዶም ቦክ ሠርተዋል። \n \nጥያቄ: በሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት የታወጀው መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ264 አክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኢትዮጵያ በዓለም ዉስጥ ክሚገኙ ጥንታዊ አገሮች ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ አስቆጥራለች፡፡ በግእዝ/ዓማርኛ እና በመጽሀፍ ቅዱስ ከተመዘገቡት ተጨባጭ መረጃዎች በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን (ድንቅነሽን) አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡ ግብጽን ሲገዛ የነበረው ሄሮደስ የሚባለው ንጉስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታሪክ ፀሀፊ የጥንቷን ኢትዮጵያ በጽሁፎቹ ላይ ይገልፃታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይም ብዙ ግዜ የምትወሳ ስትሖን በተለይም ብሉይ ኪዳን ላይም የንግስት ሳባ (መከዳ) ኢየሩሳሌም መሄድና ለንጉስ ሰለሞን ከባድ የሆኑ ጥያቄዎች ማንሳቷ ተጽፏል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ያላትን መልክ እንድትይዝ ያደረጋት ንጉስ ሚኒሊክ የንግስት ሳባና የንጉስ ሰለሞን ዘር ናቸው፡፡ የንግስት ሳባ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም አካባቢ ይገኛል፡፡ ክርስትናን ኢትዮጵያዉያን ከመቀበላቸዉ በፊት (ኣስቅድመዉ) የኦሪትን ህግ ሰለሚያዉቁ ኣመተ ዓለምን ወደታች እየቆጠሩ የጌታን መወለድ ይጠብቁ ሰለነበረ ክርስትናን ለመቀበል ኣላስቸገራቸዉም፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትያን ርቃ ቆይታለች፡፡ \n \nጥያቄ: ወደ ንጉሥ ሰለሞን በመሄድ ጥያቄ ያቀረበችው ኢትዮጵያዊት ንግሥት ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ንግስት ሳባ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ596 ዓ.ም. በጃፓን 17 አንቀጽ ያለ ሕገ መንግሥት በልዑል ሾታኩ እንደተጻፈ ይታመናል። እንዲሁም በ614 ዓ.ም. ከነቢዩ መሐመድ የወጣው የመዲና ሕገ መንግሥት ዕጅግ ጥንታዊ ምሳሌ ነው። በዌልስ በ940 ዓ.ም. አካባቢ ንጉስ ህወል ዳ ሕጎቹን ጻፉ። በዛሬው ሩሲያ ደግሞ የክዬቭ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ጥበበኛው ፕራቭዳ ያሮስላቫ የተባለውን ሕገ መንግሥት በ1009 ዓ.ም. ያህል ሠሩ። ይህ ሕግ በ1046 ታድሶ በኪዬቭ ሩስ በሙሉ ህጝ ሆነ። በስሜን አሜሪካ የኖሩ ኗሪ ጎሣ ሆደነሾኒ 'የአፈ ቃል' ሕገ መንግሥት «ጋያነሸጎዋ» የነበራችው ከ1080-1140 ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ እንደሆነ ይታመናል። ይህ ሕግ በከፊል ለአሜሪካ ሕገ መንግሥት ተጽእኖ እንደነበረው ይታመናልና የአሜሪካ ምክር ቤት በ1981 ዓ.ም. ይህንን ግንዛቤ አስታወቀ። በእንግሊዝ አገር በ1092 ዓ.ም. ንጉስ 1 ሄንሪ የነጻነት ሥርአት የተባለውን ሰነድ አዋጀ። ይህ መጀመርያ የንጉሱን ሥልጣን ወሰኖ ንጉሡ ለቤተ ካህናትና ለቤተ መሳፍንት ወገኖች የሚገባውን እንቅብቃቤ ገለጸ። ይህም መሰረት በመኳንንቱ ሲዘረጋ በ1207 ዓ.ም. የእንግሊዝ ንጉሱን ዮሃንስ (ጆን) ማግና ካርታ («ታላቅ ሥርዓት») የሚባለውን ሰነድ እንዲፈርሙት አስገደዱዋቸው። ከዚሁ መሃል ቁም ነገር የሆነው ንጉሡ ያለ ሕጋዊ ሂደት ማንንም ሰው እንዳይገድሉ፣ ከአገር እንዳያሳደዱ፣ ወይም እስር ቤት እንዳያስገቡ ከለከላቸው። በዚያ ወቅት ያ ሰነድ በእንግሊዝ አገር የነጻነት መሠረት ሆነ። በ1212 እና 1222 ዓ.ም. መካከል አንድ የሳቅሰን አስተዳዳሪ አይከ ቮን ረፕጎቭ ያቀነባበረው ሕግጋት ሳቅሰንሽፒግል በአንዳንድ ጀርመን ክፍላገር እስከ 1892 ዓ.ም. ድረስ ላይኛ ሕገ መንግሥት ሆነ። በ1228 ዓ.ም. ሱንዲያታ ከይታ ማሊ መንግሥትን ለማወሐድ የ'አፈ ቃል' ሕገ መንግሥት አወጡ። ይህ ሕግ 'ኩሩካን ፉጋ' ተብሎ ነበር። \n \nጥያቄ: በ1009 ዓ.ም. የክዬቩ ታላቅ መስፍን ያሮስላቭ ያዘጋጀው ሕገ መንግሥቱ ጥቅም ላይ የዋለው የት ሀገር ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሩሲያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከ6 አመት ጦርነት በኋላ ገላውዲወስ ተገደለና ሚናስ ስልጣን ላይ ወጣ። ለሚቀጥሉት 4 አመታት፣ እንደቀደመችው ንግስት እሌኒ በመንግስቱ ውስጥ ከፍተኛ ተሰሚነትን አገኘች። ቀጥሎም በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ሃይማኖት መካከል በተነሳው ሽኩቻ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን በመደገፍ በጽናት ቆማለች። ይሁንና በዚህ ምክንያት በተነሳው ጸብ የፖርቹጋል ካቶሊኮች ሊገደሉ ሲሉ በማማለድ ስራ ጉዳት እንዳይደርስባቸው አድርጋለች። ቤርሙዴዝ የተባለው ታውቂው የፖርቹጋል ተጓዥም ንጉሱን ገላውዲወስን በማናደዱ ከመገደል የተረፈው በሰብለ ወንጌል ተራዳኢነት ነበር። የስፔኑ ጀስዊት ፓትሪያርክ ኦቨዶም ከሞት የተረፈው በንግስቲቱ ምክንያት ነበር። ሠርፀ ድንግልን ወደስልጣን እንዲወጣም ከጦረኞቹ በላይ ያገዘችው እናት ንግስት ሰብለ ወንጌል ነበረች። ይህ ምርጫዋ የተሳካ ነበር ምክንያቱም ሰርጸ ድንግል ለ34 አመት ሲገዛ አገሪቱን በመከላከል ወደ ሰላም አሸጋግሯል። ሰብለ ወንጌል በአጼሠርፀ ድንግል ዘመን፣ በ1560 ዓ.ም. አመድ በር በተባለ ቦታ አረፈች። አጼ ልብነ ድንግል የራሱንና የሰብለ ወንጌልን ምስሎች የክሪት ሠዓሊ በመቅጥር ካሳለ በኋላ ግብጽ ወደ ሚገኘው ቅዱስ አትናቲዮስ ገዳም እንዳስላከው ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰብለ ወንጌል መቼ አረፈች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1560 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: የራስ መኮንን አርባ በአዲስ አበባ የተደረገበት ዕለቱ ምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ካሉ ወንዞች ትልቁ ወንዝ የቱ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አባይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ ዜግነቱ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኢትዮጵያዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: አብዱልራዛቅ ጉራህ በአፍሪካ የኖቤል የሥነ ጽሑፍ ሽልማት ያገኙት ከማን ቀጥለው ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዎሌ ሾይንካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት ከመቼ እስከ መቼ አገልግሎት ሲሰጥ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 54-373 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ አየር ኃይል ውስጥ ለ25 ዓመታት ያገለገሉት ብርጋዴር ጄነራል መአሾ ሀጎስ ስዩም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የደቡብ ሱዳን ሰላም ማስከበር ተልእኮ አዛዥ ሆነው ተሰየሙ። ብርጋዴየር ጄነራል መአሾ በተመድ የላይቤሪያ እንዲሁም ዳርፉር ሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ማገልገላቸውም ታውቋል። አዲሱን ሹመት ከጥር 04 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንደተሰጣቸውም በተመድ መረጃ ላይ ተገልጿል። \n \nጥያቄ: ብርጋዴር ጄነራል መአሾ ስዩም ከዚህ በፊት የት ሠርተዋል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በተመድ የላይቤሪያ እንዲሁም ዳርፉር ሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላ የተሳተፈበት የመጽሐፍ ርዕስ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እቴጌ ዘውዲቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በ1980 እ.ኤ.ኣ. ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው የለቀቁት የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር እርሳቸውን እንዲተኳቸው የመረጡት ማንን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አብዱ ዲዮፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: ዩኒሴፍ በአይቬሪኮስት ከኮሎምቢያው ኩባንያ ጋርበተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች የመማሪያ ክፍሎችን በመገንባቱ ለምን ያህል ህጻናት እድል ይፈጥራል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ለ25 ሺህ ህጻናት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየብረት ማዕድኖች የብረት ማዕድናት በሁለት ይከፈላሉ። እነሱም ፕሪሽየስ ሜታል መደብ እና ቤዝ ሜታል መደብ ናቸው። ወርቅ እንደ ሌሎቹ የብረታ ብረት ማዕድኖች የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በትሮይ አውንስ መጠን ነው። አንድ ትሮይ አውንስ ፤ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው። ትሮይ የሚባለውን ስም ያገኘው ከግሪክ አገር ሳይሆን ፤ በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ነው። የወርቅ ጌጥ ማድረግ ለሚወዱ ሰዎች ደግሞ ፤ የንፁህ ወርቅ መጠን በካራት ይለካል። በጣም ንፁህ የሆነው ሃያ አራት ካራት ሲሆን ከዚያ ዝቅ ያለ መጠን ያለው ደግሞ ከሌላ ብረት ማዕድን ጋር የተደባለቀው ነው። የዋጋውም ዓይነት በዚሁ መጠን በወርቅ ሰሪ ቤቶች ሱቅ ውስጥ ይለያያል። ብር የተባለው ማዕድን ደግሞ ተፈላጊነቱ በድሮ ጊዜ ለመገበያያነት ቀጥሎም ለተለያዩ የንብረት እቃዎችና የፋብሪካ ውጤቶች አገልግሎቱን የሚሰጥ የማዕድን ብረት ነው። ንፁህ ብር የሚባለው ብዙውን ጊዜ ዘጠና ሁለት ነጥብ አምስት ያክሉን ሲልቨር የሚይዘው ነው። የተቀረው ሰባት ነጥብ አምስት ከመዳብ (ኮፕር) - ወይንም ከሌላ የብረት ማዕድን ጋር የሚደባለቀው ነው። የአጠቃላይ ስሙም እስተርሊንግ ሲልቨር ይባላል። መደባለቁ የሚጠቅመው የብር ይዘቱን ለማጠንከር ወይንም በቀላሉ ከውስጡ ያሉትን ንጥረ ማዕድኖች በሙቀት ጊዜ ወይንም በቅዝቃዜ መጠናቸው እንዳይለወጥ ነው። \n \nጥያቄ: የብረት ማዕድናት በስንት ይከፈላሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሁለት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአልፍሬድ ኢልግ ቢትወደድ አልፍሬድ ኢልግበዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኑሮውን ኢትዮጵያ ውስጥ የመሠረተ፤ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነበር። ኢልግ በምሕንድስና ሙያው ባቡር እና የቧንቧ ውሐ ለአገራችን ካስተዋወቃቸው ብዙ ዘመናዊ የሥልጣኔ መስመሮች ሁለቱ ሲሆኑ በንጉሠ ነገሥቱ ፊት ታላቅ ታማኝነትን በማፍራቱ የዘውድ አማካሪ እና የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ እስከመምራትም የበቃ ሰው ነበር። ቢትወደድ ኢልግ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ብዙ ሚና ከተጫወቱ አውሮፓውያን መሃል ባገሪቱ ባሳለፋቸው ሃያ ሰባት ዓመታት እና ባስቀመጣቸው የልማት አሻራዎቹ የታሪክ ሥፍራው በጣም የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን። ኢልግ በስዊትዘርላንድ፣ ፍራውንፌልድ በሚባል ከዙሪክ ከተማ በሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በሚገኝ ሥፍራ በ መጋቢት ወር ፲፰፻፵፮ ዓ/ም ተወልዶ በስድሳ ሁለት ዓመቱ የገና ዕለት (ታሕሣሥ ፳፱ ቀን) ፲፱፻፰ ዓ/ም ዙሪክ ላይ በልብ ምታት ምክንያት አረፈ። ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሪቻርድ ፓንክኸርስት ዳግማዊ ምኒልክ ገና በልጅነታቸው የዓፄ ተዎድሮስ እስረኛ በነበሩ ጊዜ ቴዎድሮስ አጠገባቸው የነበሩትን አውሮፓዊ ወንጌላያን መድፍና መሣሪያዎች እንዲሠሩላቸው ማግባባታቸውን ልብ አድርገው ነበርና የሸዋ ንጉሥ ሲሆኑ በ ኤደን ላይ የነበረ አንድ የስዊትዘርላንድ ዜጋ ነጋዴ ምሕንድስና የሚያውቁ አውሮፓውያን ባለሙያዎችን እንዲፈልግላቸው ጠይቀውት ነበር ይላል። ኢልግ እና ሁለት የአገሩ ሰዎች በ፲፰፻፸ ዓ/ም አካባቢ ጉዞዋቸውን ወደኢትዮጵያ አምርተው ሸዋ ሲገቡ ንጉሥ ምኒልክ መጫሚያ እንዲሠራላቸው ያዙትና ሠርቶ ባበረከተላቸውም መጫሚያ እጅግ እንደተደሰቱ ይነገራል። በሌላ ዘገባ ደግሞ ንጉሡ ኢልግን ጠመንጃ እንዲሠራላቸው አዘዙት። ኢልግ ጠመንጃ ለመሥራት ሙያ እንደሌለውና ከውጭ የሚመጣ መሣሪያ እሱ ከሚሠራው እጅግ የላቀ እንደሚሆን ቢያስረዳም፤ ምኒልክ ኃሳባቸውን የማይለውጡ ሆኑ። እሱም እንደተጠየቀው የሙከራውን ውጤት ሲያሳቸው ንጉሡ ተደስተው ይሄንኑ ጠመንጃ በግምጃ ቤታቸው የክብር ቦታ ሰጡት። ያም ሆነ ይህ ኢልግ በንጉሡ በኩል ዘለቄታ የነበረው የበጎ አስተያየትን እንዳተረፈ ግልጽ ነው። ወዲያው በምሕንድስና ሥራ በደሞዘኝነት ቀጥረውት በየወሩ ሰባት ወይም ስምንት ፓውንድ በጠገራ ብር ይከፍሉት እንደነበር ፓንክኸርስት ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ንጉስ ምኒልክ ኢልግ እንዲሰራላቸው ያዘዙት ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጠመንጃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ ጅቡቲን የምትጎራበተው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በደቡብ-ምስራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴት ተማሪዎች በትርፍ ጊዜያቸው ችግር ፈቺ የሞባይል አፕሊኬሽን እና ኮዲንግ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ የሚያግዝ ስምምነት መፈረሙን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ስምምነቱ የተፈረመውም ከኮኖቬሽን ኢንተርፕረንርሺፕ ዲቨሎፕመንት ከተባለ ድርጅት ጋር መሆኑ ተነግሯል፡፡ ስምምነቱን የፈረሙት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ÷ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ሲመደቡላቸው ተቀብሎ ከማስተማር ጎን ለጎን በአከባቢያቸው ካሉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር ትስስር በመፍጠር ፣ተማሪዎችን በቀጣይ የዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ውጤታማ የሚያደርጉና በሳይንስ ዘርፉም ፍላጎት እንዲያድርባቸው የሚያግዙ ስራዎችን ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። ዩኒቨርሲቲዎች በአይሲቲ ዘርፍ ያላቸውን አቅርቦት ለስልጠናው በማመቻቸትና መምህራንንም በማሳተፍ ሴት ተማሪዎች በሞባይል አፕሊኬሽን እና ኮዲንግ ላይ የሚሰጣቸውን ስልጠና ይደግፋሉ፡፡ ይህ ስምምነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዩኒቨርሲቲዎች ባሉበት አከባቢ የማህበረሰብ አገልግሎት እንዲሰጡ ለሚሰራው ስራ እና የሳይንስ ባህል ግንባታ ላይ የሰጠው ትኩረት አንድ አካል ነው ብለዋል፡፡ የኮኖቬሽን ኢንተርፕረንርሺፕ ዲቨሎፕመንት በኢትዮጵያ አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ገብረሚካኤል÷ ሴት ተማሪዎች በሳይንስ ዘርፍ ያላቸው ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆኑን አንስተዋል። ፕሮጀክቱ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸው ጀምሮ ሳይንስ ውስጥ እንዲገቡ የሚያግዙ ስልጠናዎችን በማመቻቸት በሳይንስ ዘርፍ የሚመረቁ ሴት ተማሪዎችን ቁጥር ከፍ የማድረግ ዓላማ አለው ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱን እውን ለማደረግ የዩኒቨርሲቲዎች ድጋፍ ወሳኝ መሆኑንና በፕሮግራሙ ታቅፈው ስልጠናውን ተከታትለው ጥሩ ውጤት ለሚያስመዘግቡ ሴት ተማሪዎችም የነፃ ትምህርት እድሎችን እንደሚያመመቻቹ ገልጸዋል፡፡ ፕሮጀክቱን ለመጀመሪያ ጊዜ በተመረጡ ዩኒቨርስቲዎች እንደሚጀምሩና ከዚያም በመነሳት በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የማስፋፋት እቅድ እንዳላቸውም አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል፡፡ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ተማሪዎች የአይ ሲ ቲ ስልጠናዎችን እንዲያገኙ ማመቻቸቱን አስታውቀዋል፡፡ በተለይም ዲጂታል ሊትሬሲ በሚል የክረምት የስልጠና ፕሮግራም በሁሉም ዩኒቨርስቲዎች በማካሄድ የተለያዩ የማህበረሰብ አካላት መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል። በቀጣይም የዚህ አይነት ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ፕሮፌሰር አፈወርቅ መግለጻቸውን ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: ሴት ተማሪዎች በትርፍ ጊዜያቸው ምን ዓይነት የስልጠና ድጋፍ እንዲያገኙ ነው የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ስምምነት ያደረገው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ችግር ፈቺ የሞባይል አፕሊኬሽን እና ኮዲንግ ስልጠናዎችን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nብርቱካን ብርቱካን (ወይም ኦሬንጅ) ማለት የዛፍ አይነትም ሆነ በተለይ የዚሁ ዛፍ ፍሬ ማለት ነው። የሌሎች አትክልት ክልስ ሆኖ ከጥንት እንደ ለማ ይታሥባል። እርዝማኔው እስከ 10 ሜትር ድረስ ቢደርስም ዛፉ ትንሽ ይባላል፤ ቡቃያው እሾህ አለበትና ቅጠሎቹ ከ4 እስከ 10 ሳንቲሜትር ድረስ የሚዘረጉ እንደ ጥድም ወገን መቸም የማይረግፉ ናቸው። የፍሬው መጀመርያ ትውልድ በደቡብ-ምሥራቃዊ እስያ በህንደኬ፣ በቬትናም ወይም በደቡብ ቻይና ተገኘ። የብርቱካን እርሻ በብዙ አገሮች ምጣኔ ሀብት በጣም ታላቅ የንግድ ሥራ ነው። እዚህ ማለት በአሜሪካ፣ በሜዲቴራኔያን አገሮች፣ በሮማንያ፣ በደቡብ አፍሪካ፣ በቻይና፣ በአውስትራልያም ይከትታል። \n \nጥያቄ: የብርቱካን ዛፍ ቅጠሎች ምን ያህል ስፋት አላቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ4 እስከ 10 ሳንቲሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በስንት ዓመቱ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን አሻሻለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፴፫ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ በአሜሪካ ጎዳናዎች ላይ ሙከራ እንዲያደርግ ፈቃድ አገኘ። ተሽከርካሪው የአሽከርካሪ ወይም የሰው እገዛ ሳያስፈልገው አገልግሎት ይሰጣል ነው የተባለው። ኑሮ በተባለው ኩባንያ የተሰራው ተሽከርካሪ መሪን ጨምሮ ለመሽከርከር የሚያገለግሉት የነዳጅ መስጫና ፍሬን እንዲሁም የእይታ መስታወትን (ስፖኬ) ያለ አሽከርካሪ በራሱ ይጠቀማል። የአሜሪካ የትራንስፖርት ሚኒስቴርም ተሽከርካሪው በቴክሳስ ሙከራውን እንዲያደርግ ፈቃድ ሰጥቶታል። አር 2 የሚል ስያሜን ያገኘው ይህ የእቃ ማመላለሻ፥ የኩባንያው ሁለተኛው ትውልድ ተሽከርካሪ ሲሆን በሆስተን ቴክሳስ ሙከራ እንደሚያደርግ ነው የተነገረው። የእቃ ማመላለሻውን ለመሞከር ተሽከርካሪውን መቆጣጠር የሚያስችሉ ክፍሎችን ማሟላት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል። ሆኖም የእቃ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ፍጥነት በሰዓት ከ25 ኪሎ ሜትር እንዳይበልጥ የአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር አስጠንቅቋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ ፍቃድ የተሰጠው የተሽከርካሪው የፍጥነት መጠን በሰዓት ከስንት እንዳይዘል ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ25 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር። ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች ኮሞዲቲ ገንዘብ መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ ከብትና እህል (ገብስ) መደበኛ ነበሩ። በተለይ ዛጎል በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። መዳብ፣ ብረት፣ ብርና ወርቅ በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረታብረት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ። በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ የፈተና ደንጊያ ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሳንቲም እና የብር ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ልድያውያን ነበር።. በኢትዮጵያም በአክሱም ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል። ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው ተወካይ ገንዘብ የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። ሆኖም ስዊድን የወረቀት ብር ያወጣው ምክንያት ጦርነት ለማድረግ ፈልጎ በቂ ወርቅ ወይም ሌላ ገንዘብ በአገሩ ስላልነበረው ነው። አሁን ወዲያው የስዊድን መንግሥት ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ሥራተኖች መክፈል ቻለ። በጥቂት ዓመት ውስት የስዎድን ወረቀት ገንዘብ ወደቀ። ነገር ግን ከትንሽ በኋላ የእንግላንድ መንግሥት በፈረንሣይ ላይ በጦርነት ተይዞ ለጦርነትም ያህል በቂ ሀብት ባለመኖሩ እንዲህ አይነት መፍትሄ መረጡ፤ የኢንግላንድ ፓውንድ ድፍን ጀመሩ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አገራት ፈቃዳቸውን ለመፈጽም አዲስ የወርቅ ወይም የብር ማዕድን ማግነት አስፈላጊ አልነበረም። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ይህ በወርቅ የተደገፈ የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በይፋ በመላው ዓለም ተንሰራፋ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብሬቶን ውድስ ስብሰባ፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች ፊያት ገንዘብን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር። በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታት እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው። \n \nጥያቄ: በቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው የወረቀት ገንዘብ ምን ይባል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ያወዚ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኒሺ ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ (ኦክቶበር 15, 1844 - ኦገስት 25, 1900) ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ሲሆን አለምን ይቀይራሉ ብሎ ያመነባቸውን ብዙ መጻህፍት በመድረስ ይታወቃል። እርግጥ ኒሺ፣ በነበረበትም ሆነ በኋላ ዘመኑ ብዙ ተቃዋሚወች ቢነሱበትም በዚያው ልክ ብዙ ሰወች ስራወቹን እንደ ታላቅ የፍልስፍና እና ስነ ጽሁፍ ስራ ይወስዷቸዋል። ኒትሸ አብዛኛው ጽሁፉ የሚያተኩረው ሰወች እንዴት ሊኖሩ ይገባቸዋል? በሚለው ጥያቄ ነው። በዚህ ምክንያት እሱ ይኖርበት የነበረውን ዘመን የጀርመን ሥነ ምግባር (ኤቲክስ) በመንቀፍ ብዙ ጽፎአል። ሠናይ እና እኩይ (ጥሩና መጥፎ) ተብለው ተለይተው ይሰራባቸው የነበሩትን የጊዜውን ሥነ ምግባር ዋጋወች በመተቸት ሰወች አዲስ ሥነ ምግባር ፈጥረው ለሁሉም ምግባር አዲስ የሠናይነትና እኩይነት (ጥሩ እና መጥፎ) ዋጋ እንዲሰጡ በጽሑፎቹ ብዙ ሞክሯል።በዚህ መሰረት፣ ለምሳሌ፣ በክርስቲያኖች ዘንድ የሚሰራበትን ለደካሞች ማዘንን ሠናይነት ተቃውሟል። በሱ አስተያየት ደካሞች ሲታዘንላቸው የበለጠ ይዳከማሉ የሚል ነው ምክንያቱም በሱ አስተያየት ደካሞቹ በጠንካሮቹ ላይ የበለጠ ጥገኛ በመሆን መላው ህብረተሰብ ይዳከማል የሚል ነው። በተጨማሪም፣ የሰው ልጅ የሚኖርበትን ተጨባጩን አለም መገንዘብ እና ክሁሉ በላይ ስለዚሁ ዓለም ማተኮር አለበት ብሏል። ሰማይና ሌሎች አለማትን በማጣጣል፣ የሰው ልጅ እነዚህን አይነት አለሞች የሚፈጥረው አሁን ያለበትን ተጨባጩ የውኑ አለም ችግሮች መፍታት ሲያቅተው ለመፈርጠጥ ነው በማለት የሰው ልጅ ስለዚህ ምድር ብቻ እንዲያስብ ይወተውታል። ኒሽ የሰው ልጅ እራሱን በራሱ ማሸነፍ እንዲችል አጥብቆ ያምናል። በኒሺ ፍልስፍና፣ አንድ እራሱን ያሽነፈ ሰው በጣም የተለወጠ እና የተሻለ ስለሚሆን \"ሱፐር ማን\" ወይም \"የበላይ ሰው\" እንዲባል ሰይሟል። የበላይ ሰው እንግዴህ ጠንካራና በሌሎች ሰወች \"ሠናይ\" እና \"እኩይ\" ወይም ደግሞ \"ጥሩ\" ና \"መጥፎ\" ዋጋወች የማይመራ፣ ይልቁኑ የራሱን ሥነ ምግባር የሚፈጥር ነው። \n \nጥያቄ: ፍሬደሪክ ዊልሄልም ኒትሸ ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጀርመናዊ ጻህፊና ፈላስፋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ መቼ ተሰደዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: በሀገራችን ታሪክ የመጀመሪያው ሕገ መንግሥት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ተወዳጅነት ካተረፈበት ስራዎቹ መካከል በ1971 ያሳተመውጀ ድርሰቱ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየብረት ማዕድኖች የብረት ማዕድናት በሁለት ይከፈላሉ። እነሱም ፕሪሽየስ ሜታል መደብ እና ቤዝ ሜታል መደብ ናቸው። ወርቅ እንደ ሌሎቹ የብረታ ብረት ማዕድኖች የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በትሮይ አውንስ መጠን ነው። አንድ ትሮይ አውንስ ፤ ሠላሳ አንድ ነጥብ አስር ግራም ነው። ትሮይ የሚባለውን ስም ያገኘው ከግሪክ አገር ሳይሆን ፤ በፈረንሳይ አገር ከሚገኘው ከዘመናት በፊት የወርቅና የብር እንዲሁም የተለያዩ የከበሩ ማዕድናት ይሸጥበት ከነበረው ትሮይስ ከተማ ነው። የወርቅ ጌጥ ማድረግ ለሚወዱ ሰዎች ደግሞ ፤ የንፁህ ወርቅ መጠን በካራት ይለካል። በጣም ንፁህ የሆነው ሃያ አራት ካራት ሲሆን ከዚያ ዝቅ ያለ መጠን ያለው ደግሞ ከሌላ ብረት ማዕድን ጋር የተደባለቀው ነው። የዋጋውም ዓይነት በዚሁ መጠን በወርቅ ሰሪ ቤቶች ሱቅ ውስጥ ይለያያል። ብር የተባለው ማዕድን ደግሞ ተፈላጊነቱ በድሮ ጊዜ ለመገበያያነት ቀጥሎም ለተለያዩ የንብረት እቃዎችና የፋብሪካ ውጤቶች አገልግሎቱን የሚሰጥ የማዕድን ብረት ነው። ንፁህ ብር የሚባለው ብዙውን ጊዜ ዘጠና ሁለት ነጥብ አምስት ያክሉን ሲልቨር የሚይዘው ነው። የተቀረው ሰባት ነጥብ አምስት ከመዳብ (ኮፕር) - ወይንም ከሌላ የብረት ማዕድን ጋር የሚደባለቀው ነው። የአጠቃላይ ስሙም እስተርሊንግ ሲልቨር ይባላል። መደባለቁ የሚጠቅመው የብር ይዘቱን ለማጠንከር ወይንም በቀላሉ ከውስጡ ያሉትን ንጥረ ማዕድኖች በሙቀት ጊዜ ወይንም በቅዝቃዜ መጠናቸው እንዳይለወጥ ነው። \n \nጥያቄ: ወርቅ የይዘቱ ሚዛን የሚለካው በምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በትሮይ አውንስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: በ2015 ለፕሬዝዳንትነት እንደሚወዳደረ ያሳወቁት የትኛውን የፖለቲካ ፓርቲን በመቀላቀል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የሪፐብሊካን ፓርቲን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ መቼ አገቡ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1434 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ውስጥ በምን ሙያ ያገለግል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአርታኢነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል በኢትዮጵያ በ2007 ዓ.ም በ50 ሚልየን ብር ያስገነባው ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፓርጦሎን ፓርጦሎን በአየርላንድ ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ ከማየ አይኅ ጥቂት ክፍለ ዘመናት ቀጥሎ መጀመርያው በአይርላንድ ደሴት ላይ የደረሱት ሰፈረኞች መሪ ወይም ንጉሥ ነበር። የፓርጦሎን ስም በታሪክ መጻሕፍት መጀመርያው የሚታወቅ በ820 ዓ.ም. አካባቢ በሮማይስጥ በተጻፈው ሂስቶሪያ ብሪቶኑም («የብሪታንያውያን ታሪክ») ሊገኝ ይችላል። በዚሁ ጽሁፍ መሠረት፣ «ፓርጦሎሙስ» ከ1 ሺህ ሠፈረኞች (ወንዶችና ሴቶች) ጋር ደረሰ፣ እስከ 4 ሺህም ድረስ ቶሎ ተባዙ፣ ነገር ግን ድንገት በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁላቸው ከቸነፈር ሞተዋልና አገሩ እንደገና ባዶ ሆነ። ይኸው መጽሐፍ በአየርላንድኛ ትርጉም ደግሞ ቸነፈሩ በፓርጦሎን ሕዝብ ላይ የመጣበት ጠንቅ ፓርጦሎን ከኗሪ አገሩ ገና ሳይወጣ ወላጆቹን ገድሎአቸው ስለ ነበር የአምላክ ፍርድ ነው በማለት ይጨምራል። ከዚህ በላይ የፓርጦሎን መነሻ አገር እስኩቴስ እንደ ነበር፣ የማጎግ ተወላጅ እንደ ነበር ይታመን ነበር። የስኮት (በስኮትላንድና ቀድሞ በአይርላንድ የተገኘ) ብሔር ስም ከዚህ እስኩቴስ እንደ መጣ በድሮው መጻሕፍት በሰፊው ይጻፍ ነበር። \n \nጥያቄ: የፓርጦሎን ስም የተጠቀሰበት መጽሃፍ በምን ቋንቋ ነበር የተጻፈው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሮማይስጥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: ኤዎስጣጤዎስ ያረፉት በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አርሜኒያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአፕል ኩባንያ ተጠቃሚዎች በድምፅ ማዘዝ የሚችሉት ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ወይንም ኢርፎን ይፋ አደረገ፡፡ ይህም ተጠቃሚዎች ምንም አይነት ነገር ሳይጫኑ ሃይ ሲሪ የሚል ድምፅ በማሰማት ብቻ የድምፅ ማዳመጫውን ማዘዝ እንደሚችሉ ነው የተነገረው፡፡ ከዚህ ባለፈ ኤርፖድስ የተባለው ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ተጠቃሚዎች ባትሪ ካለቀባቸው እንዲያስተካክሉ ተጨማሪ ሰዓትን በቅድሚያ እንደሚሰጥ ነው የተነገረው፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት የሰጡ ባለሙያዎች ኤርፖድስ የተሰኘው የድምፅ ማዳመጫ በእጅጉ እየዘመነ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ ይህ አዲሱ ድምፅ ማዳመጫ 159 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ሲሆን ገመድ አልባ ቻርጀርን የሚያካትት ከሆነ ተጨማሪ 40 ዶላር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: አፕል ኩባንያ ያቀረበው የተባለ ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኤርፖድስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን ያወጀች መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፹፪ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: አዶልፍ ሂትለር የመጨረሻ ባለቤቱ ማን ትባላለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኤቫ ብራውን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ አዲስ አበባ መጥተው ትምህርታቸውን የት ተከታተሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የከተማዋ የዝናብ መጠን በአማካኝ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 900 ሚሊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአማ አታ አዪዶ ክሪስቲና አማ አታ አዪዶ በማርች 23፣ 1942 እ.ኤ.አ. ጋና ውስጥ ተወለደች። ትምህርቷን በዌስሊ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት፣ በመቀጠልም በጋና ዩኒቨርስቲ ተከታትላ በ1964 ዓ.ም በእንግሊዝኛ ቋንቋ የመጀመሪያ ዲግሪዋን ተቀብላለች። የመጀመሪያ የድርሰት ስራዋ የሆነውን «The Dilemma of a Ghost»ን በዚያ ዓመት ለማጠናቀቅ የበቃች ሲሆን ይሄው ድርሰቷ በሎንግማን አሳታሚ ድርጅት አማካይነት በቀጣዩ ዓመት ታትሞላታል። አዪዶ በልብ-ወለድ ደራሲነት ብቻ አይደለም እውቅናን ያተረፈችው፤ በጸሃፌ-ተውኔትነት እና ገጣሚነትም እንጂ። ጽሁፎቿ በአብዛኛው የዘመኑ የአፍሪካ ሴቶች ስላላቸው ሚና እና የምእራባዊው ባህል ስለሚያሳድርባቸው ኢርቱእ ተጽኖ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። አዪዶ በ1982 የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና ብትሾምም በስራው ላይ የቆየችው ለ18 ወራት ያህል ብቻ ነው። በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ክፍል ውስጥ ተጋባዥ ፕሮፌሰር በመሆን ትሰራለች። \n \nጥያቄ: አማ አታ አዪዶ ክሪስቲና የጋና የትምህርት ሚኒስትር ሆና የተሸመችው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1982 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመስከረም 22/2012 በአገሪቷ ወጥ የምርምር ስርአት ለመዘርጋት ብሄራዊ የሳይንስና ምርምር ካውንስል ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑን የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ አስታወቀ። በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ የሳይንስና ምርምር አውደ ጥናት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል። በአውደ ጥናቱ ላይ ከከፍተኛ ትምህርት ፣ ከምርምር ተቋማትና ከሞያ ማህበራት የተውጣጡ ተመራማሪዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል። የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረ ማርያም እንደተናገሩት በአገሪቷ በሳይንስ ዘርፉ ብቃትና አቅም ያላቸው ተማራማሪዎች ቢኖሩም ምርምሮች ወጥ ባልሆነና ቅንጅት በጎደለው መልኩ እየተከናወኑ ይገኛል። በመሆኑም በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮችን በተቀናጀ መልኩ ለማከናወንና ምርምሮች ላይ ድጋፍና ክትትል የሚያደርግ ብሄራዊ የሳይንስና ምርምር ካውንስል ማቋቋም ያስፈልጋል ብለዋል። የካውንስሉ መቋቋም በአገሪቷ ወጥ የሆነ የምርምር አሰራር ስርአት ለመዘርጋት፣ በዘርፉ ያለውን የሰው ኃይል፣ በጀትና የምርምር መሰረተ ልማቶችን በአግባቡ ለመጠቀም እንደሚያስችል ጠቁመዋል። በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስቴር የሳይንስና የምርምር ዘርፍ ጉዳዮች ዳይሬክተር ዶክተር ሰለሞን ቢኖር በበኩላቸው ካውንስል ቢቋቋም የሳይንስ ዘርፍ ለአገሪቷ ዕድገትና ልማት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል። በሳይንስ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ አገራት ተሞክሮም የካውንስሉን መቋቋም ጠቀሜታ ያረጋግጣል ብለዋል። የሚንስቴሩን አደረጃጀት የመፈተሽና በተገቢው መልኩ የማዋቀር ምርምሮችን ለመከታተል የሚያስችል የመረጃ ስርዓት የመዘርጋት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል። በአገር ወስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎችን ጥራት ለማሳደግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት የመዘርጋት እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል። የዩንቨርስቲ ኢንደሰትሪ ትስስር ያለመጎልበት፣ የምርምር ተቋማት ቅንጅት ክፍተት፣ በሳይንስ ፖሊሲና አገራዊ ልማት አጀንዳ ላይ የምሁራን ተሳትፎ ዝቅተኛ መሆን በዘርፉ ከሚጠቀሱ ችግሮች መሆናቸውንም ዶክተር ሰለሞን አብራርተዋለ። የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚንስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም እንዳሉትም የሳይንስና ምርምር አውደ ጥናቱ ዋነኛ ትኩረት በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ ምርምሮች ጥራት፣ በጀት፣ ስርጭትና ውጤቶችን ለመዳሰስ ነው። በዘርፉ ያሉ ማነቆዎችን መለየትና በተለያዩ ተቋማት የሚከናወኑ ምርምሮች ተግባራዊነትን መዳሰስም የአውደ ጥናቱ ትኩረት መሆኑን አንስተዋል። ከአውደ ጥናቱ በሳይንስ ዘርፉ ያሉ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው ዘርፉን ለማሳደግ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጽጌ ገብረ ማርያም ያሉበት ኃላፊነት ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያን ከ1881 እስከ 1905 ያስተዳደሩት ንጉሥ ማን ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኩባንያው በ124 ሚሊዮን ብር የሞተር ዘይቶችና ቅባቶች ማምረቻ ለማቋቋም፣ የቡታ ጋዝ ማከፋፈል ሥራ ለመጀመር፣ የሬንጅ አቅርቦት ሥራውን ለማሳደግና የኢንዱስትሪ ኬሚካሎች ለማቅረብ ማቀዱንም ገልጸዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በአውሮፕላን ነዳጅ አቅርቦት ላይ በስፋት እየሠራ እንደሆነ አቶ ዘካሪያስ ተናግረዋል፡፡ በአውሮፕላን ነዳጅ ገበያ የ42 በመቶ የገበያ ድርሻ እንዳለው ጠቁመው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ለ30 ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ እንደሚያቀርብ ገልጸዋል፡፡ ኩባንያው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚገኘውን የአውሮፕላን ነዳጅ ዴፖ ማስፋፋቱን፣ አምስት ዘመናዊ የአውሮፕላን ነዳጅ መሙያ ማሽኖች ገዝቶ ጥቅም ላይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ለቀለምና ፕላስቲክ ፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች ለማቅረብ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ‹‹ለጊዜው ኬሚካሎቹን ከውጭ በማስገባት የምናከፋፍል ሲሆን፣ በሒደት አገር ውስጥ የማምረት ዕቅድ አለን፤›› ብለዋል አቶ ዘካሪያስ፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ነዳጅ አቅራቢ ማነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሊቢያ ኦይል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጎግል በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በቻይና የሚገኘውን ቢሮውን በጊዜያዊነት መዝጋቱን አስታወቀ። የመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከቻይና በተጨማሪ በሆንኮንግ እና ታይዋን የሚገኙ አገልግሎት መስጫ ቢሮዎቹን መዝጋቱንም አስታውቋል። ከጎግል በተጨማሪ አማዞን እና ማይክሮሶፍትን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሰራተኞቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ በሚል ተመሳሳይ እርምጃ ውስጥ መግባታቸው ተገልጿል። ጎግል ሰራተኞቹ ወደ ቻይና እና ሆንግ ኮንግ ከሚያደርጉት ጉዞ እንዲታቀቡና በቻይና የሚገኙትም በተቻለ ፍጥነት እንዲወጡ መምከሩም ተነግሯል። ባለፈው ሳምንት ፌስቡክ ሰራተኞቹ ወደ ቻይና እንዳይጓዙ ያስጠነቀቀ ሲሆን፥ ተሽከርካሪ አምራቹ ጄኔራል ሞተርስም ፋብሪካዎቹን ዘግቷል። ከዚህ በተጨማሪም የጃፓኑ ቶዮታ እስከ ፈረንጆቹ የካቲት 9 ድረስ በቻይና አገልግሎት መስጠት ማቆሙን አስታውቋል። የፈረንሣዩ ፒ ኤስ ኤ እንዲሁም የጃፓኖቹ ሆንዳ እና ኒሳን ሰራተኞቻቸውን ከቻይና የማስወጣት እቅድ እንዳላቸው ተነግሯል። ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተገኘባት ውሃን ከተማ መቀመጫቸውን ያደረጉ ዓለም አቀፍ አምራቾችም ሰራኞቻቸውን ከቻይና ማስወጣት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ውሃን የቻይና ሰባተኛ ትልቋ ከተማ እና ዋነኛ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያዎች መቀመጫ ናት። ምንጭ፦ ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: የኮሮና ቫይረስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው የት ሀገር ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቻይና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲ የሚጠራበት ቅፅል ስሙ ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሕንድ አባት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር በሀገሪቱ በየት አቅጣጫ ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ምዕራብ ጫፍ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በቡሩንዲ ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን በመፈንቅለ መንግሥት ስልጣን የያዘው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፸፱ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ምን በመባል ይጠራል ከየትኛው የ ቋንቋ ቤተሰብ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጎፍኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: አሁን ቱርክመንኛ የሚጻፈው በምን ፊደላት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በላቲን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: ቱርክመንኛ በፊት በየትኞቹ ቋንቋዎች ፊደላት ነበር የሚጻፈው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን የተቀበለችው በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፯፻፵፬ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ህይወቱ መቼ አለፈ ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሰኔ 27 2006 አ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: የአሪዞና ስቴት ከየትኞቹ ስቴቶች ጋር ይዋሰናል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል ከማሊ ጋር ከየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ክምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከአፍሪካ ህዝብ ውስጥ 24 በመቶ ብቻ የኢንተርኔት ተጠቃሚ መሆናቸውን ዓለም ባንክ አስታወቀ፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት አለመስፋፋት በአህጉሪቱ አዳዲስ ዲጂታል ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ የስራ ዕድል ፈጠራዎችን ለማስፋፋት አዳጋች እንደሚሆን ነው ባንኩ የገለጸው፡፡ በአፍሪካ እኤአ ከ2015 እስከ 2035 ባለው ጊዜ ውስጥ 450 ሚሊዮን ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሊኖሩ እንደሚችሉ የዓለም ባንክና የአፍሪካ ልማት ባንክ በጥምረት ያወጡት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ እንደ ኢኮሜርስ እና ፋይናንስ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂ የስራ ዘርፎችን በአፍሪካ በማስፋፋት ከፍተኛ የስራ እድልን መፍጠር እንደሚቻል ተጠቅሷል፡፡ በዚህም፣ ወጣቶች በተለያዩ የስራ ዘርፎች በቂ እውቀት እንዲኖራቸው በማድረግ ማሰማራት እንደሚገባ ተነግሯል፡፡ \n \nጥያቄ: በአፍሪካ አህጉር ውስጥ 450 ሚሊየን ያህል ስራ ፈላጊ ሰዎች ከመቼ እስከ መቼ ይኖራሉ ተብሎ ተገምቷል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እኤአ ከ2015 እስከ 2035 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሁዋዌ የተሰኘው ግዙፍ የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑ ተሰምቷል። የብሪታኒያው ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ሀገራቸው ከሁዋዌ ቴክኖሎጂ ኩባንያ ጋር በቅንጅት ለመስራት ፍላጎት ያላት መሆኑን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ኩባንያው በቀጣይ በብሪታኒያ የ5ጂ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት በሚችልበት ሁኔታ ላይ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ነው የገለጹት። ሁዋዌ ቻይና ከአሜሪካ ጋር የንግድ ጦርነት ውስጥ መግባቷን ተከትሎ በዩናይትድ ስቴትስ አገልግሎት እንዳይሰጥ ክልከላ የተደረገበት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው አገልግሎት በሚሰጥባቸው ሀገራት በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጣልቃ ይገባል በሚል ካናዳ እና አውስትራሊያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት መሻከሩ ይታወቃል። ብሪታኒያ ከኩባንያው ጋር በቅንጀት ለመስራት እና አገልግሎቱን ለመጠቀም መፈለጓም ከአሜሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ሊያሻክረው እንደሚችል ተሰግቷል። ምንጭ፦ሲ ጂ ቲኤ ን \n \nጥያቄ: ቦሪስ ጆንሰን የብሪታንያ ምንድን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጠቅላይ ሚኒስትር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ1913 በፕሬዝዳንት ዋረን ሃርዲንግ ዘመን ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ሆኑ። በሃርዲንግ ተከታይ በፕሬዝዳንት ካልቪን ኩሊጅ ዘመን ደግሞ እንዲህ ያለን ማዕረግ ይዘው አገለገሉ። የንግድ ሚኒስትር እየሆኑ ሃይለኛ ሰው ነበሩ። የንግድ ዘርፍና መንግሥት አንድላይ ይሠሩ የሚለውን ተስፋ በመያዛቸው በዚህ አንጻር ብዙ አደረጉ። በማዶ ባሕርና በውጭ አገር ለባለጉዳዮች ምክርና እርዳታ የሚሰጡ መሥርያ ቤቶች በማስከፈቱ የአለም አቀፍ ንግድ በጉልበት አስለሙ። በተለይም የሆሊዉድ ፊልም ማዶ ባሕር ለመግፋፋት ጉጉ ነበሩ። ዜጎችም ቤት እንዲያገነቡና የራሳቸው መሬት ባለአባት እንዲሆኑ አበረታቷቸው። ስለ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የክላርክ ሰነድ በ1920 ተጽፎ ሁቨር ፕሬዝዳንት እየሆኑ በ1922 ግልጽ ሆኖ ወጣ። በዚህ ሰነድ ዘንድ፥ አውሮጳ በላቲን አሜሪካ ላይ ዛቻ ካልጣለች በተቀር አሜሪካ በውጭ አገር ጥልቅ ለማለት ሕጋዊ መብት አልነበራትም የሚል ማስታወሻ ነበር። በዚያን ጊዜ አሜሪካ ሠራዊት በኒካራጓና በሃይቲ ነበራት። ስለዚህ ሁቨር ከነዚህ አገራት የሠራዊቱን ቁጥር ቀነሱ። በላቲን አሜሪካ ውስጥ የጦርነት መሣርያ እንዳይደርስ ማዕቀብ ለመጣል አሠቡ። በ1924 ጃፓን ማንቹርያን በወረረ ጊዜ አዲስ ፖሊሲ አወጡ። እሱም በግፍና በወረራ የሚገኝ የመሬት ለውጥ ሁሉ አናከብርም የሚል ነበር። ከታላቁ ጭፍግግ የተነሣ ብዙ ባንክ ቤቶች ስለወደቁ አንዳችም ብድር ለማግኘት ከባድ ሆነ። ብዙ ሰዎች ሥራ ፈት ሆኑ። በአውሮፓም ምጣኔ ሃብቱ ችግር ውስጥ ስለ ገባ ሁቨር ጀርመን ስለመጀመርያው ጦርነት ለፈረንሳይ ከምትከፍል ካሣ ለአንድ አመት ይቅር ትበል የሚል ዕቅድ አዋጁ። በሚከተለውም አመት የጀርመን ዕዳ በሙሉ ተሰረዘ። በ1925 ምርጫ ተቃራኒው ፍራንክሊን ሮዘቨልት በሰፊ መጠን አሸነፉና በሳቸው ፈንታ ፕሬዚዳንት ሆኑ። ሁቨር ፕሬዚዳንት ከሆኑ በኋላ ረጀም ዕድሜ ነበራቸው። እስከ 1957 ዓ.ም. ድረስ ኖሩ። ከ2ኛ አለማዊ ጦርነት ቀጥሎ በ1939 ስለ ቀድሞው ልምዳቸው ፕሬዚዳንት ሃሪ ትሩማን የአውሮፓ ምግብ ፍላጎት ለመወሰን ወደ አውሮፓ ላኳቸው። \n \nጥያቄ: በ1913 የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበረው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዋረን ሃርዲንግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጥንታውያን የግብጽ ባለሥልጣኖች በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ከማየ አይኅ ቀጥሎ መጀመሪያ የአፍሪካ ሕዝብ የኖኅ ልጅ የካም ዘሮች ናቸው፤ ይህ አገር ሰናዖር ለሚሉት ቅርብ ስለ ነበር የባብል ግንብ ከተሠራ በኋላ ከዚህ ተነስተው ወደ ግብፅ ወረዱ። የግብጽ ቀድሞ ዘመን መንግሥት ዋና ጥንታዊ ነው፤ የመሠረተውም ፈርዖን ሜኒስ የተባለው ነው። ጸሓፊው ጊዮርጊስ ስንቄሎስ (፰፻ ዓ.ም. አካባቢ የጻፈው) ይህ ፈርዖን ሜኒስ በዕውነት የካም ልጅ ምጽራይም እንደ ነበረ ገመተ። ዳሩ ግን አባ አውሳብዮስ በጻፉት ዜና መዋዕል ዘንድ (፫፻፲፯ ዓ.ም. ተጽፎ)፣ የድሮ ግብጻዊው ባለታሪክ ማኔጦን (፫ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ.) ስለ ኋለኞቹ ግብጻውያን ሲጽፍ፣ ይኮሩበት የነበረው የታላቁ ጥንት ዘመን ከማየ አይህ አስቀድሞ እንዳለፈ፣ በኋላም በዚያው አገር ዳግመኛ ከሠፈረበት ከካም ልጅ ምጽራይም በውኑ እንደ ተወለዱ ጽፎ ነበር። ተመሳሳይ ታሪክ በእስላም ጸሐፊዎች በግብጻዊው እብን አብድ ኤል-ሀከም እና በፋርሳውያን አል-ታባሪና ሙሐመድ ቈንዳሚር መጻሕፍት ሲገኝ፣ ፒራሚዶች፣ እስፊንክስ ወዘተ. ሁሉ የተሠሩ ከጥፋት ውኃ በፊት በኖሩት ክፉ ዘሮች ሆኖ፣ ከዚያ በኋላ ግን አገሩ ለካም ተወላጅ ለምጽራይም ('ማሣር' ወይም 'መሥር') ተሠጠ ብለው ጻፉ። \n \nጥያቄ: በመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት ከማየ አይኅ በኋላ መጀመሪያ በአፍሪካ የሰፈሩት ሕዝቦች እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የካም ዘሮች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ከኢጣልያ ጋር በተደረገው ጦርነት ራስ መኮንን ምን ያህል የጦር ሠራዊት ይመሩ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየኮምፒዩተር አውታር የኮምፒዩተር አውታር (ኔትወርክ) ማለት ሁለት ወይም ከሁለት በላይ የሆኑ ኮምፒዩተሮችን ማገናኘት ነው። እነዚህ ኮምፒዩተሮች ሲገናኙ መረጃ መለዋወጥ ይቻላል። አውታሩ ውስጥ ያሉት ኮምፒዩተሮች በአንደ ክፍል ውስጥ ወይም በጣም በተራራቁ ሕንጻዎች ውስጥ ሊገኙ ይችላሉ። ኮምፒዩተሮቹ በኤሌትሪክ ገመድ ፣ በገመድ የለሽ ግንኙነት ወይም በሞደም ሊገናኙ ይችላሉ። አውታሩ ላይ ሌሎች የኮምፒዩተር መሣሪያዎችንም መግጠም ይቻላል። ለምሳሌ አንድ ፕሪንተር አውታር ውስጥ አገናኝቶ አውታሩ ውስጥ ከሚገኝ ማንኘውም ኮምፒዩተር ወደዛ ፕሪንተር ማተም ይቻላል። የአውታሩን ኮምፒዩተሮች ሁሉንም እኩል ሥልጣን መስጠት ይቻላል ወይም ለአንዳንድ ኮምፒዩተሮች የተለዩ ሥራዎች መሥራት እንዲችሉ ማድረግ ይቻላል። ሁለተኛው ዘዴ ክላየንት-ሰርቨር ይባላል። አብዛኛው ጊዜ ሰርቨሮቹ ሀይለኛና ትልቅ ሲሆኑ ክላየንቶቹ ደግሞ አነስተኛ ናቸው። \n \nጥያቄ: በኮምፒዩተሮች አውታር ምን ማድረግ ይቻላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መረጃ መለዋወጥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳምሱ-ዲታና ሳምሱ-ዲታና ከ1538 እስከ 1507 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር) ድረስ የባቢሎን ንጉሥ ነበር። የአሚ-ሳዱቃ ልጅና ወራሽ ሲሆን፣ ሳምሱ-ዲታና የባቢሎን (የሃሙራቢ ሥርወ መንግሥት) መጨረሻ ንጉሥ ነበረ። የዘመኑ አመት ስሞች ምንም ዘመቻ ስለማይጠቅሱ ሰላማዊ ዘመን ይመስል ነበር፣ ወደ ደቡቡ ግን የባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት ንጉሥ ጉልኪሻር ከሳምሱ-ዲታና ጋር እንደ ታገለ በአንድ ታሪክ ጽላት ተቀረጸ። በ1507 ዓክልበ. የሐቲ (ኬጥያውያን) ንጉሥ 1 ሙርሲሊ እስከ ባቢሎን ድረስ ዘመተና ከተማውን ዘርፎ አቃጠለው። የኬጥያውያን ሠራዊት የባቢሎን ምስሎች (ጣኦታት) ወደ ሐቲ አገር ወሰዱ፤ ሳምሱ-ዲታናም እንደ ተገደለ ይመስላል። ይህ የሚታወቀው ከባቢሎን ዜና መዋዕል «በሳምሱ-ዲታና ዘመን፣ ኬጥያውያን ወደ አካድ መጡ» ሲዘገብ፣ ደግሞ በኬጥኛ የተለፒኑ ዜና መዋዕል እንደሚለው «እርሱ (ሙርሲሊ) ወደ ሐላብ ሔዶ አጠፋው፤ የሐላብን ምርኮ ወደ ሐቱሻ ወሰደ፤ ከዚያም እስከ ባቢሎን ድረስ ሔዶ አጠፋው፣ ሑራውያንንም አሸነፋቸው፣ የባቢሎንን ምርኮ ወደ ሐቱሻ ወሰደው።» \n \nጥያቄ: ሳምሱ-ዲታና የማን ልጅ እና ወራሽ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የአሚ-ሳዱቃ ልጅና ወራሽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጁፒተር እና ሳተርን ጁፒተር እና ሳተርን ከ4 መቶ አመት በሆላ ትላንት ምሽት በአንድ ላይ ገጥመው አንድ ፕላኔት መስለው ታይተዋል፡፡ ፕላኔቶቹ ከቀን ቀን እየተቀራረቡ መጥተው ትላንት ምሽት በአንድ ላይ በመግጠም ደማቅ ብርሃን ፈንጥቀዋል፡፡ የሁለቱ ግዙፍ ፕላኔቶች ምህዋር በየ20 ዓመቱ የሚገናኙ ሲሆን ክስተቱ በብዛት በቀን ውስጥ ስለሚሆን በዓይን ለማየት ከባድ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ‘ዘ ስታር ኦፍ ቤቴልሄም’ ወይም የቤቴልሄም ኮከብ ተብሎ በሚጠራው በዚህ ክስተት ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ሰማይ ላይ እጅግ ደማቅ ብርሃን ታይቶ እንደነበር ሳይንቲስቶች መናገራቸውን ዘ ጋርዲያን አስነብቧል፡፡ \n \nጥያቄ: የጁፒተር እና ሳተርን ምህዋር በየስንት አመቱ ይገናኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በየ20 ዓመቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቅዱስ ላሊበላ ቅዱስ ላሊበላ በ 1101 አ.ም ትህሳስ 29 ቀን ከ እናቱ ከኬርዮርና ከአባቱ ዛንስዮም ላሰታ ቡግና ወረዳ ሮሃ ከተባለች ቦታ ከፍልፍል ቤተ መቅደስ ውስጥ ተወለደ በዚህ ፍልፍል ቤተ-መቅደስ ውስጥ እድገቱን አደረገ ስድስት አመት ሲሞላው ቤተ-መንግስት አባ ዳንእል የተባሉ መምህር ተቀጥረውለት ከ ፊደል እስከ ዳዊት አጠናቆ ከዚያም የተማረውን የዕሁፍ ጥበብ በቤተ ጎሎጎታ ደብረ ሲና በሚገኘው ከ ኪዳነ ምህረት መንበር ታቦት ዙሪያ ላይ እራሱ የተዓፋቸው የሚዐለይበት ዕሁፎቸች ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ላሊበላ 12 አመት ሲሞላው አባቱ ዘንሳዮም 40 አመት ነግሶ በተወለደ በ 76 አመቱ ከዚህ አለም በ ሞት ተለየ ወድያው ብዙም ሳይቖይ እናቱ ኬርዮርና በሞት ተለየች፡፡ ቅዱስ ላሊበላ በ እናቱ ና አባቱ ህልፈተ ህይወተ በደረሰበት ሀዘን የተነሳ ሁሉን ነገር ለመርሳት ና የትምህርት ፍላጎት ለሞሞላት ጉዞውን ወደ ጎጃም በማድረገ አለም ስላሴ ከተባለው ደብር ከመምህር ኬፋ ሃዲሳቱን አጠናቖ በመመረቅ ወደ ሀገሩ ተመለሰ፡፡ በወቅቱም በኤትዮጵያ ላይ ነግሶ የነበረው ታላቅ ወንድሙ ቅዱሰ ገብረ ማሪያም ነበር ይህ እንዲህ እያለ በእህቱ ላይ እሱ ሊነግስ መሆኑ ቅናት አሳደረባት ቅዱስ ላሊበላ ሁሌም እሚጠጣው ባህላዊ መድሃኒት ውስጥ መርዝ በመጨመር ታስቀምጥለታለች አትሙት ያላት ነፍስ ግን የሃገሬውን በሃል ምክንያት አድርጎ ሳይቀመስ አይሰጥምና አብሮት የነበረው ዲያቖን የተቀመጠውን መድሃኒት ቀምሶ ወደ ነበረበት ጠረቤዛ ላይ አንዳሰቀመጠው ወድያውኑ ህይወቱ ታልፋለች ቅዱስ ላሊበላ ይህን ባየ ጊዚ እኔን ለማጥፋት የመጣው መድሃኒት የሌላውን ነፍስ አጠፋች በማለት የቀረውን መድሃኒት በመጠጣት ለሶሰት ለሊት እንደ ወደቀ ቀረ ከዚያም ነዋሪው ገንዞ ለመቅበር ሲዘጋጁ የሰውነቱ ሙቀት አልተለየውም ነበር ይሄን ጊዜ ወድያው ቅዱስ ላሊበላ ነቃ የተመለከቱት ሰዎች ተደናገጡ ከዚያም ይህ ሁሉ ነገር በእህቱ መደረጉ ያሳዘነው ቅዱስ ላሊበላ በመነሳት ጉዞውን ወደ ጫካ አደረገ ኑሮውንም ለረጅም አመት እዚያው አደረገ ይህ እንዲ እንዳለ ሚስት እምትሆነውን ሴት አገኝ ቤተሰቧን በማስጠየቅ በቤተክርስትያን ስርአት ተጋብተው ጥቂት አመት እንደቆዩ ጉዞውን እየሩሳሌም አደረገ ለተከታታይ 13 አመታትም ቆይታ በኋላ ወደ ባለቤቱ ተመልሶ ከወንድሙ ከ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ጋር እርቅ በማውረድ ቅዱስ ገብረ ማሪያም ንግስናውን ለቅዱስ ላሊበላ በተወለደ በ57 አመቱ በማስረከብ ኑሮውን በገዳም አደረገ፡፡ \n \nጥያቄ: ቅዱስ ላሊበላ የት ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ላሰታ ቡግና ወረዳ ሮሃ ከተባለች ቦታ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ የደበደቡት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 1946 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: አፕል ኩባንያ በፈረንሳይ ሀገር ለምን ያህል ሰዎች የሥራ እድል ፈጥሯል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ለ240 ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2012(ኤፍ ቢሲ) አሜሪካ የሁዋዌ የአምስተኛ ትውልድ ኔትወርክን (5G) መጠቀም እብደት ነው ስትል ብሪታኒያን አስጠነቀቀች፡፡ አሜሪካ የቻይና ኩባንያዎች አገልግሎት መጠቀም ሊያስከትል የሚችለውን የደህንነት ስጋት የሚያሳይ አዲስ ማስረጃ ለብሪታኒያ አቅርባለች፡፡ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጉዳዩ ዙሪያ በሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን ላይ ጫና ለማሳደር እንደሚፈልጉ ተጠቁሟል፡፡ በዚህ ወር ሁዋዌ ኩባንያ ለብሪታኒያ የኔትወርክ ዝርጋት አንዳንድ “መሠረታዊ ያልሆኑ” ክፍሎችን ያቀርብ አያቅርብ የሚል ውሳኔ ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የሁዋዌ ቃል አቀባይ ባለፉት 15 ዓመታት ለብሪታኒያ የ3ጂ ፣ 4ጂ እና ብሮድባንድ መሳሪያዎችን ሲያቀርብ የቆየ የግል ኩባንያ መሆኑን በመግለፅ በዚህም የሃገሪቱ ባለሙያዎች ቴክኖሎጂያቸው የደህንነት ስጋት እንደማያመጣ ማረጋገጣቸውን ጠቁመዋል፡፡ አሜሪካ ባለፈው ዓመት በደህንነት ስጋት ምክንያት ለሁዋዌ እና 68 ተዛማጅ ኩባንያዎች የቴክኖሎጂና ሌሎች መሳሪያዎችን እንዳይሸጡ ገደብ መጣሏ የሚታወስ ነው፡፡ ምንጭ፡-ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አሜሪካ የሁዋዌን አምስተኛ ትውልድ ኔትወርክን ብሪታንያ እንዳትጠቀም ያለችው የምን ስጋት ይኖረዋል ብላ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የደህንነት ስጋት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ መደብ የሚካተቱ ቋንቋዎች እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዐምደ ጽዮን ቀዳማዊ አጼ ዐምደ ጽዮን (የዙፋን ስም ገብረ መስቀል) ከ1314 እስከ 1344 ዓ.ም. የነገሡ ሲሆን በጥንቱ ዘመን ከተነሱ ነገሥታት ውስጥ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ሰፋ ያለ አሻራ ትተው ካለፉት (ለምሳሌ፦ ዘርአ ያዕቆብ) ጎን ወይም በላይ ስማቸው ይጠቀሳል። አጼ ዐምደ ጽዮን የአጼ ይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅና የአጼ ወድም አራድ ልጅ እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ይኩኖ አምላክ አዲሱን የሰሎሞን ስርወ መንግስት ቢመሰርቱም፣ በልጅ ልጆቻቸው የነበረው ፉክክርና አዲስ ከሚስፋፋው የእስልምና ሃይማኖት የሚሰነዘረው ጥቃት ስርዓቱን ስጋት ላይ የጣለ ነበር። አጼ አምደ ጽዮን ይህን ፉክክር በማስቆምና በዘመናት በማይደበዝዘው ጀግንነታቸው የኢትዮጵያን ድንበር ከሞላ ጎደል አሁን በሚታወቀው መልኩ በማስቀመጥ፣ የአዲሱን ስርወ መንግስት መሰረት በማጽናት እንዲሁም በማረጋጋት ዝናቸው በጥንቱ አለም ክአፍሪቃ ቀንድ እስከ አውሮጳ የተንሰራፋ ነበር። \n \nጥያቄ: የአጼ ዐምደ ጽዮን አባት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የአጼ ይኩኖ አምላክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: ኦሮሚኛ፣ ሶማልኛ፣ አፋርኛ፣ ሲዳምኛ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ የምን ቋንቋ ወገን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኩሻዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: እቴጌ ጣይቱ በምን ሙያ ይታወቁ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በበገና ቅኝትና ድርደራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ ስንት ልጆች አሉዋቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: የጋሊልዮ ጥናት ትክክለኛ እንደነበር በማመን የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን ወክለው ስለደረሰበት ግፍ ይቅርታ የጠየቁት ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት ሰባት ወራት 169 ቢሊየን 501 ሚሊየን 789 ሺህ 893 ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ አፈፃጸሙ ከዕቅድም ሆነ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ የታየበት መሆኑን ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው አስታውቀዋል፡፡ ሚኒስቴሩ 169 ቢሊየን ብር 408 ሚሊየን 889 ሺህ 4 ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የእቅዱን 100 ነጥብ 5 በመቶ ማሳካት መቻሉንም ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት ሰባት ወራት ምን ያህል ገንዘብ ሰበሰበ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 169 ቢሊየን 501 ሚሊየን 789 ሺህ 893 ብር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢትዮጵያ በዓለም ዉስጥ ክሚገኙ ጥንታዊ አገሮች ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ከሁሉም የበለጠ ረጅም እድሜ አስቆጥራለች፡፡ በግእዝ/ዓማርኛ እና በመጽሀፍ ቅዱስ ከተመዘገቡት ተጨባጭ መረጃዎች በተጨማሪ አምስት ሚሊዮን አመት የሚሆነውና በጣም ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የሰው ቅሪት የተገኘው በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ሲሆን ይህም፣ 3.2 ሚሊዮን አመት የሆነውን እዛው አካባቢ የተገኘውን የሉሲን (ድንቅነሽን) አጽም በእድሜ ይበልጣል፡፡ ግብጽን ሲገዛ የነበረው ሄሮደስ የሚባለው ንጉስ ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ክፍለ ዘመን የነበረው ታሪክ ፀሀፊ የጥንቷን ኢትዮጵያ በጽሁፎቹ ላይ ይገልፃታል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ላይም ብዙ ግዜ የምትወሳ ስትሖን በተለይም ብሉይ ኪዳን ላይም የንግስት ሳባ (መከዳ) ኢየሩሳሌም መሄድና ለንጉስ ሰለሞን ከባድ የሆኑ ጥያቄዎች ማንሳቷ ተጽፏል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬ ያላትን መልክ እንድትይዝ ያደረጋት ንጉስ ሚኒሊክ የንግስት ሳባና የንጉስ ሰለሞን ዘር ናቸው፡፡ የንግስት ሳባ ቤተ መንግስት ፍርስራሽ ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በአክሱም አካባቢ ይገኛል፡፡ ክርስትናን ኢትዮጵያዉያን ከመቀበላቸዉ በፊት (ኣስቅድመዉ) የኦሪትን ህግ ሰለሚያዉቁ ኣመተ ዓለምን ወደታች እየቆጠሩ የጌታን መወለድ ይጠብቁ ሰለነበረ ክርስትናን ለመቀበል ኣላስቸገራቸዉም፡፡ ነገር ግን በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በእስልምና መስፋፋት ምክንያት ኢትዮጵያ ከአውሮፖውያኑ ክርስትያን ርቃ ቆይታለች፡፡ \n \nጥያቄ: አምስት ሚልዮን ዓመታት ቆይታ ያለው የሰው ልጅ ቅሪተ አካል የተገኘበት ቦታ የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኢትዮጵያ አዋሽ ሸለቆ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን የመጽሐፉ ርዕስ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ስሙር መሬት (The Good Earth) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኩባንያው በ124 ሚሊዮን ብር የሞተር ዘይቶችና ቅባቶች ማምረቻ ለማቋቋም፣ የቡታ ጋዝ ማከፋፈል ሥራ ለመጀመር፣ የሬንጅ አቅርቦት ሥራውን ለማሳደግና የኢንዱስትሪ ኬሚካሎች ለማቅረብ ማቀዱንም ገልጸዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በአውሮፕላን ነዳጅ አቅርቦት ላይ በስፋት እየሠራ እንደሆነ አቶ ዘካሪያስ ተናግረዋል፡፡ በአውሮፕላን ነዳጅ ገበያ የ42 በመቶ የገበያ ድርሻ እንዳለው ጠቁመው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ለ30 ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ አየር መንገዶች የአውሮፕላን ነዳጅ እንደሚያቀርብ ገልጸዋል፡፡ ኩባንያው በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሚገኘውን የአውሮፕላን ነዳጅ ዴፖ ማስፋፋቱን፣ አምስት ዘመናዊ የአውሮፕላን ነዳጅ መሙያ ማሽኖች ገዝቶ ጥቅም ላይ ማዋሉን ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ለቀለምና ፕላስቲክ ፋብሪካዎች በግብዓትነት የሚያገለግሉ ኬሚካሎች ለማቅረብ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ‹‹ለጊዜው ኬሚካሎቹን ከውጭ በማስገባት የምናከፋፍል ሲሆን፣ በሒደት አገር ውስጥ የማምረት ዕቅድ አለን፤›› ብለዋል አቶ ዘካሪያስ፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ምን ያህል ዘመናዊ የአውሮፕላን ነዳጅ መቅጃ ማሽኖች ተጠቀመ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አምስት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት ለምን ያህል ጊዜ ሴኔጋልን መሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ1960 እስከ 1980 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: የራስ መኮንን አርባ በአዲስ አበባ የት ቦታ ተደረገ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሰኢ ሜዳ ላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፄ ይስሐቅ ቀዳማዊ አጼ ይሥሓቅ በዙፋን ስማቸው \"ዳግማዊ ገብረ መስቀል\" ሲባሉ እ.ኤ.አ ከ1414-1429 የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት የነበሩ ናቸው። የቀዳማዊ አጼ ዳዊት ሁለተኛ ወንድ ልጅ ሲሆኑ የቀዳማዊ ቴዎድሮስ ታናሽ ወንድም ናቸው። ከአክሱም ነገሥታት በኋላ የመጀመሪያውን ከአውሮጳውያን መሪወች ጋር ግንኙነት ያደረገው ይሄው ንጉስ ነበር። ለምሳሌ ለአራጎን መሪ ለነበርው አልፎንሶ አምስተኛ በ1428 ዓ.ም. በእስላሞች ላይ የተባበረ ሃይልን ለመመስረት ደብዳቤ ልኳል። በዚሁ ደብዳቤ የጋብቻን ነገር ያወሳ ሲሆን ህጻኑ ዶን ፔድሮ ከእጅ ጥበብ አዋቂወች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ የይስሓቅን ሴት ልጅ እንዲያገባ ያትታል። አልፎንሶ ለይስሓቅ የመለሰለት ደብዳቤ ባይገኝም ለይስሓቅ ተከታ ለአጼ ዘርዓ ያዕቆብ በ1450 በደረሰ ደብዳቤ ደህንነታቸው እስከተጥበቀ ድረስ እጅ ጥበበኞችን በደስታ ወደኢትዮጵያ እንደሚልክና ከአሁን በፊት የላካቸው 13 ጥበበኞቹ በመንገድ ላይ እንደጠፉ ሳይጠቅስ አላለፈም። በኒሁ ንጉስ ዘመን በፈላሾች በተነሳ አመጽ ምክንያት ንጉሱ ወደወገራ ዘምተው አመጸኞቹን ኮሶጌ ላይ በማሸነፍ አመጹን አረገቡ። በዚያውም ደብረ ይሥሓቅ የተሰኘውን ቤተክርስቲያን ለድሉ ማስታወሻ ኮሶጌ ላይ አሰሩ። . ንጉሱ ተመልሰው ከአገው ምድር ባሻገር ያለውን የሻንቅላ ምድር ላይ ዘመቻ አካሂደዋል። በደቡብ ምስራቅ ደግሞ ከአረብ አገር የተመለሱትን የሳድ አዲን ፪ኛ ልጆች ወግተዋል። ታሪክ አጥኝው ታደሰ ታምራት ይስሓቅ ከመስሊሞች ጋር ሲዋጋ ወደቀ ይበል እንጂ ዋሊስ በድጅ በርግጥም በወንጀል እንደተገደለና በተድባባ ማርያም እንደተቀበረ ይናገራል። \n \nጥያቄ: የቀዳማዊ አጼ ዳዊት ሁለተኛ ወንድ ልጅ እና የቀዳማዊ ቴዎድሮስ ታናሽ ወንድም ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አጼ ይሥሓቅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: በፓንታይኖስ መሪነት ተቋሙ በትምህርቱ ታዋቂ የሆነው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 173-182 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአቡነ ቴዎፍሎስ አቡነ ቴዌፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ጎጃም በሚገኝው በዝነኛው ደብረ ኤሊያስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ማርያም ውቤ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘርትሁን አደላሁ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፲፱፻፪ ዓ/ም ተወለዱ። ሲወለዱም የተሰጣቸው ስም መልእክቱ ወልደ ማርያም ነበር። በልጅነታቸው ንባብ እና ዜማን በመምህር መሪ ጌታ ረዳኸኝ እና ግራ ጌታ ሣህሉ እዚያው የተወለዱበት አካባቢ ተምረዋል። ኋላ የቅኔ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ዝንባሌ ስላደረባቸው እዚያው ደብረ ኤሊያስ ደብር መምህር ገብረ ሥላሴ በሚባሉ ሊቅ ሥር መማር ጀመሩ። በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው ፍትሐ ነገሥትና አዲስ ኪዳንን በመምህር ተክሌ (ነቡረ ዕድ በኋላ ቢትወደድ አቡነ ዮሐንስ) በመባል የሚታወቁት መሪነት ሲከታተሉ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የኃይማኖት ችግሮችን ለማወቅ ይፈልጉ እንደነበርና ሰፋ ያለ ዕውቀት እንደነበራቸው ይነገራል። በተጨማሪ የኃይማኖት ችግሮችን የሚመለከቱ መጻሕፍትን ሳይታክቱና ሳይሰለቹ ያነቡም ነበር። መልእክቱ ወልደ ማርያም በ፲፱፻፴ ዓ/ም ይህን ዓለም በቃኝ ብለው ደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰው ገቡ። ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀሳውስቱ በዘመናዊ የኃይማኖት ትምህርት እንዲሠለጥኑ በነበራቸው ሀሳብ መሠረት ፳ የሚሆኑ ሊቃውንት መርጠው በቤተ መንግሥቱ አካባቢ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። ከነኚህም አንዱ አባ መልእክቱ ወልደ ማርያም ናቸው። ቀደም ብሎ በኢትዮጵያና በግብጽ በተደረገው ስምምነት መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ጳጳሶች ሲሾሙ ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ ወልደ ማርያም ለሹመት ከተመረጡት አምስት አባቶች አንዱ ሲሆኑ ወደግብጽ ተጉዘው በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ እጅ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ “ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ” ተብለው የሐረርጌ ጳጳስ ሆኑ። \n \nጥያቄ: አቡነ ቴዎፍሎስ የሐረርጌ ጳጳስ ሆነው የተሾሙት በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማይክሮሶፍት ለዊንዶውስ-10 የሚያቀርብውን የደህንነት ጥገና በ2025 ማቅረብ እንደሚያቆም እና በዚህ ወር መጨረሻ የዊንዶውስ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ዋና ማሻሻያ ይፋ ለማድረግ መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡ ኩባንያው ከዚህ ቀደም ዊንዶውስ 10 ማሻሻያ ይፋ ሲያደርግ የመጨረሻው ኦፕሬቲንግ ሲስተም ነው ቢልም አሁን ላይ ግን ሃሳቡን እንደቀየረ ይፋ አድርጓል። ከዚህ ጋር ተያይዞም ኩባንያው ከፈረንጆቹ ጥቅምት 14 ቀን 2025 ጀምሮ ለሆምም ሆነ ለፕሮፌሽናል ቨርዥኖች አዳዲስ ዝመናዎች ወይም የደህንነት ጥገናዎች አይኖሩም ብሏል፡፡ ምንም እንኳን የዊንዶው-7 ተጠቃሚዎች ከፈረንጆቹ 2020 ወዲህ የደህንነት ዝመና ቢቋረጥም የንግድ ድርጅቶች ለዊንዶውስ-7 ፕሮፌሽናል እና ዊንዶውስ 7 ኢንተርፕራይዝ ዝመናዎችን ለማግኘት ለማይክሮሶፍት ክፍያ እየፈጸሙ ነው። አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች እንደተናገሩት አዲሱ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ከ11 ቁጥር ይልቅ ስም እንደሚሰጠው እየገለጹ መሆኑን ቢቢሲ በድረ-ገጹ ማስነበቡን ኢመደኤ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ማይክሮሶፍት ለዊንዶውስ-10 የሚያቀርብውን የደህንነት ጥገና መቼ አቆማለው አለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ2025 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: በሽሬ ከተማ የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ አሻሽሎ የሰራው ወጣት ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ወጣት ዕበ ለገሰ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: የመለጋሲ ቋንቋ ከየት ቤተሰብ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከአውስትሮኔዚያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የደአማት መንግስት መናገሻ ከተማ ማን ነበረች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሀ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያን ለረጅም ዘመን ያስተዳድር የነበረው የሰለሞን ስርወ መንግስት መቀመጫው በየት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ካላት ሕዝብ ብዛት ምን ያህሉ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 94% ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ግብይት የሚያስፈጽመው ግዥና ሻጭን መድረክ ላይ በማገናኘት በድምፅ ዋጋ በመንገርና በመጫረት ነው፡፡ ይህ የተለመደው አሠራር የበለጠ ውጤታማ የሚሆነው ግን በድረ ገጽ ግብይት ሲደረግ በመሆኑ ይህንን የድረ ገጽ ግብይት ለማስጀመር ከሦስት ዓመት በፊት ሥራው የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ሥራው ተጠናቅቆ ወደ ትግበራ ሊገባ ችሏል፡፡ በተለመደው የመድረክ የግብይት አሠራር በቀን የሚፈጸመው የግብይት መጠን ከ200 እስከ 300 የሚደርስ ነው፡፡ ይህም የግብይት መጠኑ ውሱን መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የድረ ገጽ ግብይት መጀመሩ ግን ይህንን በመለወጥ ከፍተኛ አቅም ይሰጣል፡፡ ይህም አሠራሩን ተግባራዊ ከማድረጉ በፊትም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ባለው ተቋም ጭምር ዕውቅና አግኝቶበታል፡፡ እንደ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ያሉ ተቋማትም ይህንን አገልግሎት ፈትሸው ማረጋገጫ ተሰጥቶት እየተሠራበት ስለመሆኑም የምርት ገበያው የሥራ ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡ ይህንን ዘመናዊ አገልግሎት ሥራ ለማስጀመር ከመጀመሪያው ጀምሮ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው የኢንቨስትመንት ክላይሜት ፋሲሊቲ ፎር አፍሪካ (ICF) የተባለው ተቋም ሲሆን፣ ለዚህ ፕሮጀክት 2.2 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ይህ ግብይት በቡና የተጀመረ ሲሆን፣ ሁሉም በዚህ የግብይት ሥርዓት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡ የግብይት ሥርዓቱ አዲስ በመሆኑ በዚህ ለመጠቀም ተገበያዮች ሥልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡ እስካሁንም 380 ተገበያዮች በድረ ገጽ ለመገበያየት ሥልጠና ወስደው ብቁ መሆናቸው ተረጋግጦ ሰርተፊኬት ተሰጥቷቸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የገጽ ለገጽ የግብይት ሥርዓቱ በቀን ምን ያህል ያገበያይ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ200 እስከ 300 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እያደራጀ ያለው ምንድነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የምርምርና የልህቀት ማእከላት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአክሱም አክሱም በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክ/ሃገር ከአድዋ ተራራዎች አጠገብ የምትገኝ ከተማ ነች። በክርስቶስ ልደት በፊት ተመስርቶ የነበረው የአክሱም ስርወ መንግስት ማእከል ነበረች የአክሱም ስርወ መንግስት በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ እየተዳከመ ሲመጣ የማእከላዊው መንግስት ወደ ደቡብ ተንቀሳቀሰ። ሰባ አምስት በመቶ የሚሆነው የከተማው ነዋሪ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ነው። የተቀሩት ነዋሪዎች የሱኒ እስልምና ተከታዮች ናቸው። ባላቸው ታሪካዊ ተፈላጊነት ከተማ ውስጥ የሚገኙት የአክሱም ስርወ መንግስት ቅሪቶች UNESCO በ1980 የአለም ቅርስ ቦታ ተብለው ተሰይመዋል ። አክሱም በኢትዮጵያ የ ትግራይ ክልል ከተማ ሲሆን በማዕከላዊ ዞንና በላዕላይ ማይጨው ወረዳ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አክሱም በኢትዮጵያ በየትኛው ክልል ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በትግራይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ የተሠራው ስያሜ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኢቮ ኦሊቬቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የእንስሳት ህክምና ትምህርታቸውን በአሜሪካ በሚገኘው ማን ዩኒቨርሲቲ ተማሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: በፕሬዝደንት ትራምፕ ትእዛዝ የተገደሉት ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን የየት ሀገር ጄነራል ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የኢራኑ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል በሰሜን በኩል በማን ትዋሰናለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሞሪታንያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ከየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከሰሜን-ምሥራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ በሰሜን በኩል በማን ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሜዲቴራንያን ባህር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየንግዱን ዘርፍ በማዘመን ሸማችን ከአምራች ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ የኤሌክትሮኒክስ ግብይት (ኢ-ኮሜርስ) ይፋ ሆነ:: በአሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አ.ማ የበለፀገው የኢ-ኮሜርስ ቴክኖሎጂ የኢንተርኔት አገልግሎት በሚገኝበት አካባቢ አምራችን በቀላል እንዲሁም ቀጥተኛ በሆነ መንገድ የሚያገናኝ ቴክኖሎጂ መሆኑ ተገልጿል:: ቴክኖሎጂው የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር የዋጋ ንረትን በማስቀረት ረገድ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል:: ዘመኑን የዋጀ የግብይት ሥርአትን መፍጠር የንግድ ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ አበርክቶው የላቀ በመሆኑ የኢ-ኮሜርስም የሀገርን ምጣኔ ሀብት የማሳደግ አቅም እንዳለው ከግምት ውስጥ በማስገባት የንግዱ አለም ተዋናዮች ተግባራዊ ሊያደርጉት ይገባል ተብሏል:: \n \nጥያቄ: የኢ-ኮሜርስ ንግድ ለማካሄድ ከመተግበሪያው በተጨማሪ ሌላ ምን ያስፈልጋል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የኢንተርኔት አገልግሎት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: ኤዎስጣጤዎስ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: ገብረሃና ገብረማሪያም የአለቅነት ማዕረጋቸውን እንዴት አገኙ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ላ ምን ምን አሉበት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየጥምቀት በዓል በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው ያሳልፋሉ።በከተሞች ግን ሰው ሰራሽ ግድብ ይሰራል። ጥር ፲፩ ቀን የጥምቀት ዕለት፤ በገጠር፣ ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት መሪነት ሁሉም ወደከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል። ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬ፣ ወንዱ በሆታ፤ ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው ይመለሳሉ። በየዓመቱ በመላ ኢትዮጵያ የሚከበረው የጥምቀት በዓል፣ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው፣ በየጥምቀተ ባሕሩ የሚከበሩ በመኾናቸው፣ ሀገሬውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መስህብ በመፍጠሩ፣ ቱሪስቶችን መሳቡ አልቀረም። ጥቁርና ነጭ፣ ቀይና ብጫ ያለም ዘር፣ ከአዲስ አበባ እስከ ላሊበላ፣ ከአክሱም እስከ ጎንደር በሁሉም ሥፍራዎች በዚሁ ዓይነት ደምቆ ይከበራል። የምእመናኑም ሆነ የካህናትና ዲያቆናት አለባበስ ፍፁም በሚማርክ ባህላዊ አልባሳት የተዋበ በመሆኑ ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ ለሚመጡ ጎብኚዎች ሁል ጊዜ አዲስ ነው። ሊቃውንቱ እንደሚናገሩት፣ ዘመነ አስተርእዮ የሚባለው፣ ከጥር ፲፩ ቀን ጀምሮ እስከ ጾመ ነነዌ ያለው ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ አምላክ ሰው ሆኖ በሥጋ መገለጡ፣ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር መታወቁ፣ በቃና ዘገሊላ በተደረገው ሠርግ ላይ የመጀመሪያው ተዐምር በመፈጸሙ፣ አምላካዊ ኃይሉ መገለጡ፣ እየታሰበ ምስጋና ይቀርባል። ይህ ሁነት ኢትዮጵያ ብሂልን ከባህል ጋር አዛምዳ ከሌላው የክርስቲያን ዓለም በተለየ አከባበር በዓሉን ማክበሯ፣ አያሌ ቱሪስቶችን ለመሳብ አስችሏታል። \n \nጥያቄ: የከተራ በዓል መች ይከበራል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጥር ፲ ቀን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አቶ ታምራት ዲላ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: አዲስ ዘመን ጋዜጣ በይ ስራውን የጀመረው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: በጣና ሐይቅ ከሚገኙ ደሴቶች 22ቱ ምንድን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nካሣ አያሌው ካሣ ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ሽሮ ሜዳ ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ነው። አባቱ አቶ አያሌው ካሣ እና እናቱ ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ በጋብቻ ከተጣመሩ አንስቶ ቤታቸው የልጅ ፍሬ ማግኘት ሳይችል ረጅም ዓመታትን ቆይቷል። በዚህ ምክንያት እናቱ መካን እንደሆኑ ታምኖ የአብራካቸውን ክፋይ እንደማያገኙ እርግጠኛ ሆነዋል። ነገር ግን የወላጆቹ እርግጠኛ የሆኑበት ጉዳይ ከአምላክ ዘንድ ከተፈቀደው የሚገናኝ ሆኖ እስከ መጨረሻው አልዘለቀም። ልክ እንደ ካህኑ ዘካርያስና ኤልሳቤት የልጅ ፍሬን ማየት ተስፋ በመነመነበት ትዳር ውስጥ ያልተጠበቀውና ያልታሰበው ተስፋ ባልተጠበቀና ባልታሰበ ቸጊዜ ከተፍ አለ። «መካን» ተብለው የተቆጠሩትና እርሳቸውም ይህንኑ አምነው የተቀበሉት ወ/ሮ በላይነሽ ተ/ወልድ በሆዳቸው ፅንስ ቋጠሩ። እርግዝናቸው እውን ሆኖ የቤቱን ተስፋ አንሰራራው። በዘጠነኛ ወራቸው የካቲት 8/ 1974ዓ.ም ለእኝህ እናቱ የመጀመሪያም የመጨረሻም የሆነው ልጃቸው ካሣ አያሌውን ተገላገሉ። \n \nጥያቄ: ካሣ አያሌው የልደት ቀኑ መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የካቲት 8/ 1974ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ምን ያህል የፖለቲካ ድርጅቶች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከ፹ በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች የካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች በካናዳ አገር 1974 ዓ.ም. ሕገ መንግስት ሥር ኢንዲያን (መጀመሪያ አገሮች የተባሉ)፤ ሜቲ (ክልሶች)፤ እና እኑዊት (ወይም ኤስኪሞ) ናቸው። እነዚህ 3 ክፍሎች አንድ ላይ ደግሞ መጀመርያ ሕዝቦች ይባላሉ። በካናዳ በተደረገው 1993 ቆጠራ ዘንድ፣ የጥንታዊ ኗሪዎች ብዛት ከ900,000 በለጠ። በዚህ ቁጥር ውስጥ 600,000 ከመጀመርያ አገሮች ዘር፤ 290,000 ሜቲ፣ እና 45,000 እኑዊት ይከተታሉ። የጥንታዊ ኗሪዎች ማህበራዊ ወኪሎች በካናዳ እንዲህ ናቸው፤ የመጀመርያ አገሮች ስብሰባ ለመጀመርያ አገሮች፤ እኑዊት ታፒሪት ካናታሚ ለእኑዊት፤ የሜቲ ብሔራዊ ጉባኤ ለሜቲ ናቸው። ባለፈው ዐሥር አመት የካናዳ መንግሥት የዘውድ ጉባኤ ስለ ጥንታዊ ኗሪዎች ሰበሰበ። ይህ ጉባኤ ያለፉትን መንግስት ዐቅዶች ስለ ጥንታዊ ኗሪዎች ለምሳሌ የሚሲዮን ተማሪ ቤቶች አመዛዝኖ ብዙ የአቅዋም ምክሮች ለካናዳ መንግስት አቀረበ። ብዙ መጀመርያ አገሮች የሚኖሩት በተከለለ ቦታ ሲሆን፣ ብዙ ኗሪዎች ደግሞ ከቦታዎቹ ውጭ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: የካናዳ ጥንታዊ ነዋሪዎች በሀገሪቱ ሕገ-መንግስት ሥር የተካተቱት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 1974 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የቪስቶሶሚሲስ በሽታ ምን ሊያጠቃ ይችላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: ነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ ማን ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ነው ጃን ፖል አካዬሱ ላይ የፈረደበት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው በምን ዘርፍ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በትምህርት አስተዳደር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nእንቁላሎቿን ሆዷ ውስጥ የምትታቀፈው የአውስትራሊያ የእንቁራሪት ዝርያ (ጋስትሪክ ብሩዲንግ ፍሮግ) ያልተለመደ ዓይነት የመራቢያ ሥርዓት አላት፤ የዚህች እንቁራሪት ዝርያ ከ2002 ጀምሮ እንደጠፋ ይታሰባል የሚለው ጄደብሊው ዶት ኦርግ ድረ ገጽ ነው። \n \nጥያቄ: እንቁላሏን በሆዷ የምትታቀፈው የእንቁራሪት ዓይነት ምን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጋስትሪክ ብሩዲንግ ፍሮግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: በመለጋሲ ቋንቋ በአረፍተ ነገር ውስጥ ከሁሉ የሚቀድመው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ግሡ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ የተገደበት መጽሐፍ በድጋሚ ለገበያ የቀረበው በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ አዲስ የቴሌግራፍ መስመር መቼ ተዘረጋ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፰፻፶ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጮቄ ወረዳ ተፋሰሶች ለአባይ ወንዝ ምን ያህል ድርሻ አላቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 9.5% ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: የአሪዞና ሕግ አስፈጻሚ ዘርፍ አስተዳዳሪ ለስንት ዓመት ስልጣን ላይ ይቆያል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለ4 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአክሱም አክሱም በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክ/ሃገር ከአድዋ ተራራዎች አጠገብ የምትገኝ ከተማ ነች። በክርስቶስ ልደት በፊት ተመስርቶ የነበረው የአክሱም ስርወ መንግስት ማእከል ነበረች የአክሱም ስርወ መንግስት በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ እየተዳከመ ሲመጣ የማእከላዊው መንግስት ወደ ደቡብ ተንቀሳቀሰ። ሰባ አምስት በመቶ የሚሆነው የከተማው ነዋሪ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ነው። የተቀሩት ነዋሪዎች የሱኒ እስልምና ተከታዮች ናቸው። ባላቸው ታሪካዊ ተፈላጊነት ከተማ ውስጥ የሚገኙት የአክሱም ስርወ መንግስት ቅሪቶች UNESCO በ1980 የአለም ቅርስ ቦታ ተብለው ተሰይመዋል ። አክሱም በኢትዮጵያ የ ትግራይ ክልል ከተማ ሲሆን በማዕከላዊ ዞንና በላዕላይ ማይጨው ወረዳ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የአክሱም ስርወ መንግስት ቅሪት አካሎች በመያዟ በዩኔስኮ የቅርስ ቦታ ተብላ የተመዘገበችው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1980 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) ኡበርና ሃዩንዳይ በራሪ ታክሲዎችን በጋራ ሊሰሩ መሆኑን አስታወቁ። ሁሉቱ ኩባንያዎች አዲስ የሚሰሩትን በራሪ ተሽከርካሪ በላስ ቬጋሱ የንግድ ትርኢት ይዘው እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል። አራት ተሳፋሪዎችን የሚይዘው በራሪ ታክሲ በሰዓት እስከ 320 ኪሎ ሜትር መጓዝ እንደሚችል ተገልጿል። ሁለቱ ኩባንያዎች በዚህ ሳምንት በላስ ቬጋስ በሚደረገው የንግድ ትርኢት ላይ የታክሲ አገልግሎት ይሰጣል ያሉትን በራሪ ተሽከርካሪ ሞዴል ይፋ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። ኡበር በፈረንጆቹ 2023 ለደንበኞቹ የበራሪ ታክሲ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ነው የገለጸው። \n \nጥያቄ: ኡበርና ሃዩንዳይ ሊሰሩት ያሰቡት በራሪ ታክሲ የት ለማስተዋወቅ አቅደዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በላስ ቬጋስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: አብዱልራዛቅ ፓራዳይዝ የተሰኘውን ልብ ወለድ መጻሐፋቸውን ያሳተሙት እ.ኤ.አ. መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1994 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ ከተማ አዛዥ ሆኖ በተሾመበት ወቅት ልዑለ አለማየሁ የስንት ዓመት ልጅ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የ8 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ ብዙ ተናጋሪ ያለው ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሉጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ እ.ኤ.አ. በ1948 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ላሉት መጻሕፍት አርእስት የሰጡት ሠለስቱ ምዕት ናቸው፡፡ በምን ምክንያት ቢሉ ድዮቅልጥያኖስ መክስምያኖስ የሚባለ ሁለት ዓላውያን ነገስታት ተነስተው \"አብያተ ጣዖታት ይትረኃዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትዓፀዋ\" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ አብያተ ክርስቲያናትና ቅዱሳት መፃህፍት ተዘረፉ፤ ተቃጠሉ፡፡ ከምዕመናን ወገን ብዘዎች ሞቱ የተረፉትም ተሰደዱ፡፡ እጅግ ከፍተኛ እልቂትና ስደት በቤተክርስቲያን ላይ ሆነ፡፡ ከመከራው ጽናት የተነሳ ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ተባለ (ከ285 - 395)፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር መፍቀሬ ሃይማኖት የሆነውን ቆስጠንጢኖስን አነገሰው፡፡ የቆስጠንጢኖስ አባቱ ኮስታንዲዮስ(ቁንስጣ) ሲሆን እናቱ ደግሞ እላኒ ትባላለች፡፡ ቆስጠንጢኖስም የድዮቅልጥያኖስን አዋጅ በአዋጅ ሽሮ \"አብያተ ክርስቲያናት ይትረኃዋ አብያተ ጣዖታት ይትዓፀዋ\" ብሎ አወጀ፡፡ በዘመኑ አርዮስ የተባለ መናፍቅ ወልድ ፍጡር በመለኮቱ ብሎ ተነሳ፡፡ በዚህ ጊዜ ጉባኤ በኒቂያ ተደረገ፡፡ ሶስት መቶ ዓሥራ ስምንት የቤተክርስቲያን ሉቃውንት ተሰብስበው አርዮስን በማውገዝ ሃይማኖትን አጽንተው በሚለያዩበት ጊዜ ለመጻህፍት ሁሉ አርእስት ሰጥተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በቅድስት ቤተክርስቲያንና በምእመናን ላይ ከባድ መከራ የደረሰበት ወቅት ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዘመነ ሰማዕታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ የትውልድ ቦታው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: በኦርቶዶክስ እምነት ለበዓላትና አጽዋማት ማውጫ መነሻ ነጥብ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መባጃ ሐመር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ከፍተኛ የሆነ የፖለቲካ ተጽእኖ ያላቸው የእስልምና ሃይማኖት መሪዎች ምን ተብለው ይጠራሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማራባውት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: ከፓንታይኖስ በኋላ የእስክንድርያ ትምህርት ተቋሙ ማን መምራት ጀመረ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: የአፓሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈርይዞ የተጓው ሮኬት ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሮኬት ሳተርን ፬ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን ነፃ የወጣችው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በግብጽ ዋናዋ የወደብ ከተማ ማን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አሌክሳንድሪያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን በኢራቅ የት ቦታ ተገደሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአንጎላ አንጎላ፣ በይፋ የአንጎላ ሪፑብሊክ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ስትሆን ከናሚቢያ ፣ ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ፣ እና ከዛምቢያ ጋር ድንበር ትጋራላች። በምዕራብ ጫፍ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር ትገናኛለች። የፖርቹጋል ቅኝ-ተገዥ ነበረች። ነዳጅ እና አልማዝ ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የሚመደቡ ናቸው። የአንጎላ የሕግ-አስፈጻሚ ፕሬዝዳንቱን ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና የሚኒስትሮች ካውንስሉን ያጠቃልላል። ሁሉም ሚኒስትሮችና ምክትል ሚኒስትሮች የሚኒስተሮች ካውንስሉን ሲሰሩ በየጊዜው እየተሰበሰቡ ስለተለያዩ የፖለቲካ ጉዳዮች ውሳኔ ይሰጣሉ። የአስራ ስምንቱ ክልሎች መሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚመረጡት። በ1992 እ.ኤ.ኣ. የወጣ ሕገ-መንግስት የመንግስቱን አወቃቀር እና የዜጎችን መብትና ግዴታ ይዘረዝራል። ፕሬዝዳንቱ መንግሥቱ በ2006 እ.ኤ.ኣ. ምርጫ ለማድረግ ዕቅድ እነዳለው ገልጸዋል። ይህ ምርጫ ከ1992 አ.ኤ.ኣ. በኋላ የመጀመሪያው ምርጫ ነው የሚሆነው። አንጎላ ውስጥ ሶስት ዋና ብሔረሰቦች ይገኛሉ። ኦቪምቡንዱ 37% ፣ ኪምቡንዱ 25% ፣ እና ባኮንጎ 13%። ሌሎች ብሔረሰቦች ቾክዌ (ሉንዳ)፣ ጋንጉዌላ፣ ንሀኔካ-ሁምቤ፣ አምቦ፣ ሄሬሮ፣ እና ዢንዱንጋን ያጠቃልላሉ። በተጨማሪም ክልሶች (አውሮፓና አፍሪካዊ) 2% ይሆናሉ። ፖርቱጋሎች አንጎላዊ ካልሆኑ ሰዎች ብዙዎቹ ናቸው። ታሪክ በአንጎላ መጀመሪያ የሠፈሩት የኮይሳን ሰዎች ነበሩ። በባንቱ ፍልሰቶች ጊዜ እነዚህ ሰዎች ወደ ደቡብ አንጎላ ሄዱ። በ1483 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋሎች በኮንጎ ወንዝ አጠገብ ሠፈሩ። በ1575 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋል ካቢንዳ ጋር በባሪያ ንግድ ላይ ያቶከረ ግዛት መሠረተች። በ16ኛው ክፍለ ዘመን፣ ፖርቱጋል የአንጎላ የባህር ጠረፍን ተቆጣጠረች። በተለያዩ ውሎችና ጦርነቶች የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት አንጎላ ተስፋፋ። የፖርቱጋል መመለሻ ጦርነትን ምክኒያት በማድረግ የደች ሪፐብሊክ ሏንዳን ከ1641 እስከ 1648 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ተቆጣጠረች። \n \nጥያቄ: በአንጎላ መጀመሪያ የመጡት ነዋሪዎች እነማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የኮይሳን ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአቡነ ቴዎፍሎስ አቡነ ቴዌፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ጎጃም በሚገኝው በዝነኛው ደብረ ኤሊያስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ማርያም ውቤ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘርትሁን አደላሁ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፲፱፻፪ ዓ/ም ተወለዱ። ሲወለዱም የተሰጣቸው ስም መልእክቱ ወልደ ማርያም ነበር። በልጅነታቸው ንባብ እና ዜማን በመምህር መሪ ጌታ ረዳኸኝ እና ግራ ጌታ ሣህሉ እዚያው የተወለዱበት አካባቢ ተምረዋል። ኋላ የቅኔ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ዝንባሌ ስላደረባቸው እዚያው ደብረ ኤሊያስ ደብር መምህር ገብረ ሥላሴ በሚባሉ ሊቅ ሥር መማር ጀመሩ። በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው ፍትሐ ነገሥትና አዲስ ኪዳንን በመምህር ተክሌ (ነቡረ ዕድ በኋላ ቢትወደድ አቡነ ዮሐንስ) በመባል የሚታወቁት መሪነት ሲከታተሉ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የኃይማኖት ችግሮችን ለማወቅ ይፈልጉ እንደነበርና ሰፋ ያለ ዕውቀት እንደነበራቸው ይነገራል። በተጨማሪ የኃይማኖት ችግሮችን የሚመለከቱ መጻሕፍትን ሳይታክቱና ሳይሰለቹ ያነቡም ነበር። መልእክቱ ወልደ ማርያም በ፲፱፻፴ ዓ/ም ይህን ዓለም በቃኝ ብለው ደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰው ገቡ። ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀሳውስቱ በዘመናዊ የኃይማኖት ትምህርት እንዲሠለጥኑ በነበራቸው ሀሳብ መሠረት ፳ የሚሆኑ ሊቃውንት መርጠው በቤተ መንግሥቱ አካባቢ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። ከነኚህም አንዱ አባ መልእክቱ ወልደ ማርያም ናቸው። ቀደም ብሎ በኢትዮጵያና በግብጽ በተደረገው ስምምነት መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ጳጳሶች ሲሾሙ ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ ወልደ ማርያም ለሹመት ከተመረጡት አምስት አባቶች አንዱ ሲሆኑ ወደግብጽ ተጉዘው በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ እጅ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ “ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ” ተብለው የሐረርጌ ጳጳስ ሆኑ። \n \nጥያቄ: አቡነ ቴዎፍሎስ የሐረርጌ ጳጳስ ሆነው የተሾሙት መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በዓለም ከሚገኙ ሰው ሰራሽ ሐይቆች ትልቁ የት ሀገር ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በጋና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአንኮበር በ፲፯፻፳ ዓ/ም በሸዋው ነጋሲ በመርድ አዝማች አብዬ የተመሠረተችና በአልጋ ወሪሹ መርድ አዝማች አምኀ ኢየሱስ የተስፋፋች የሸዋ ከተማ ስትሆን ከደብረ ብርሃን ምስራቃዊ አቅጣጫ ፵፫ ኪሎ ሜትር ርቀት የስምጥ ሸለቆው አፋፍ ላይ ትገኛለች። አንኮበር ከዓፄ ይኵኖ አምላክ (፲፪፻፸-፲፪፻፹፭ ዓ/ም) ዘመን ጀምሮ ለኢትዮጰያ ነገሥታት በማረፊያነት አገልግላለች። ዓፄ አምደ ጽዮን ፲፫፻፲፬-፲፫፻፵፬ ዓ/ም የድንኳን ከተማቸውን እንደተከሉባት ይነገራል። አስቲት ኪዳነ ምሕረት የርሳቸው ትክል ናት። ጦረኛዉ ዓፄ አምደ ጽዮን በ፲፫፻፴፭ ዓ/ም አዳልን ለማስገበር የዐማራን፣ የዳሞትን፣ የጐዣምን ሠራዊት ይዘው አንኮበር ሠፈሩ።ለ፬ ወራት ያህል እስከ ዘይላና በርበራ ድረስ በመዝለቅ ድል አድርገው አስገብረውታል። ዓፄ ልብነ ድንግል (፲፭፻፰-፲፭፻፵ ዓ/ም) ደግሞ በተሻለ ሁኔታ በቦለድ የባለወልድን ቤተ ክርስቲያን ለማነጽ ጀምረው እንደነበር የሚጠቁሙ መረጃዎች አሉ። የከተማነት ታሪኳ የጐላው ግን ከግራኝ ወረራ በኋላ ተበታትኖ የቆየውን የጥንታዊ ሸዋን ግዛት አንድ ለማድረግ የሸዋ ስርወ-መንግሥት በአቤቶ ነጋሲ በመንዝ አጋንቻ ላይ በ፲፮፻፷፭ ዓ/ም ተጀምሮ በተከታታይ እስከ ፲፰፻፹፩ ዓ.ም የጥንት ኢትዮጶያ ግዛትን ለማስመለስ በተደረገው እንቅስቃሴ ነው። የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ወደ ፲፫ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሥር መሠረቱ የረር | እንጦጦ እስከዞረበትና በኋላም አዲስ አበባ እስከተቆረቆረችበት ጊዜ ድረስ በቀዝቃዛ አየሯ የምትታወቀው አንኮበር ለአምስት የሸዋ ነገሥታት በማእከልነት አገልግላለች። \n \nጥያቄ: አንኮበር ከተማን ያስፋፋት ማነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መርድ አዝማች አምኀ ኢየሱስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቱርክ በዊኪፒዲያ ላይ ላለፉት ሶስት ዓመታት ጥላው የነበረውን እገዳ በማንሳት ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት እንዲችሉ ፈቀደች። የሀገሪቱ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት እገዳው የመናገር መብትን ይጥሳል ሲል እግዱ እንዲነሳ ውሳኔ አሳልፏል። ዊኪፒዲያ በፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ አለመሆኑን ተከትሎ የቱርክ መንግስት እገዳ ማሳላፉ ይታወሳል። በወቅቱ በዊኪፒዲያ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ የቱርክ መንግስት ከአይ ኤስ እና አል ቃይዳ ጋር ትብብር አለው የሚል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። ይህንን ተከትሎም እገዳው ላለፉት 991 ቀናት ተግባራዊ ሆኖ መቆየቱን የኢንተርኔት ክትትል ተቋም የሆነው ኔትብሎክስ አስታውቋል። እገዳው በሂደት ቀስ በቀስ የሚነሳ በመሆኑ እና የተወሰኑ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች ዊኪፒዲያን ለመመለስ እየሰሩ በመሆኑ በቱርክ የሚገኙ ሁሉም ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት አይችሉም ተብሏል፡፡ ዊኪፒዲያ በበርካታ የዓለም ሀገራት ሳንሱር የሚደረግ ሲሆን በቻይና አሁንም ታግዶ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ ያልሆነው ድኅረ ገጽ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዊኪፒዲያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: የማሊ ሪፐብሊክ መሪ የነበረው ማውሳ ትራዎሬ ከስልጣን የወረደው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1991 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የዓለም ጤና ድርጅት በቲቢ በሽታ የሚያዙ ሰዎችን ከ100 ሺህ አስር ለማድረስ ያሰበው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ2032 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: አዲስ ዘመን ጋዜጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለህትመት ሲበቃ የነበረው የገፅ ብዛት ስንት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ባለሁለት ገፅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nክዋሜ ንክሩማህ የተወለዱት በ1909 እ.ኤ.አ. ደቡባዊ ምዕራብ ጋና (ቀደም ሲል ጎልድ ኮስት) ንክሮፉል በምትባል ከተማ ነው። ንክሩማህ በካቶሊክ ሚሽነሪ ትምህርት ቤት ይማሩበት በነበረ ወቅት ብሩህ አዕምሮ እንደነበራቸው የተመሰከረላቸው ሲሆን ገና በአሥራዎቹ እድሜ ውስጥ እያሉ ነው በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አስተማሪ የሆኑት። ይሁንና ያለሥልጠና የጀመሩትን ትምህርት በ1926 እ.ኤ.አ. የአክራውን አቺሞታ ኮሌጅ ተቃለቅለው የመምህርነት ምሥክር ወረቀት በማግኘት በተለያዩ የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች አስተምረዋል። በ1935 እ.ኤ.አ. ወደ አሜሪካ በማቅናትም የፔንሴልቬኒያውን ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተቀላቅለው በኢኮኖሚክስና ሶሲዮሎጂ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን በ1939 የተቀበሉ ሲሆን በ1942ም በሥነ-መለኮት ሌላ ድግሪ ከዚሁ ዪኒቨርሰቲ አግኝተዋል። በ1942 እና በ1943ም የማስተርስ ድግሪያቸውን ከፔንሴልቬኒያ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ትምህርትና በፍልስፍና ሠርተዋል። በአሜሪካ ቆይታቸውም በግራ ዘመም አሰተሳሰቦች በመማረከቸው የተነሳ በወቅቱ በሥርነቀል ለውጥ ፈላጊነታቸው ከሚታወቁ ምሁራን ጋር ቅርብ ግንኙነት መሥርተው ነበር። አፍሪካውያንን ያሰባሰበ የተማሪዎች እንቅስቃሴ መሥራችና ግንባር ቀደም ተናጋሪ እንዲሁም የአፍሪካ አገራት ነፃ እንዲወጡና የአውሮፓ ቅኝ ግዛት እንዲያበቃ ቁርጠኛ አቋም ነበራቸው። ከዚሁ ጎን ለጎንም የተባበረች አፍሪካ አስፈላጊነትን በማመን አፍሪካውያንና የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው ሕዝቦች በአንድነት እንዲቆሙ የሚሰብከው ፓንአፍሪካኒዝም አቀንቃኝ ነበሩ። በ1945 ወደ ለንደን ሕግና ኢኮኖሚክስ ለማጥናት ባመሩበት ወቅትም በማንችስተር እንግሊዝ የተካሄደውን 5ኛው የፓን አፍሪካን ጉባዔ እንዲካሄድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል። የአፍሪካን ከቅኝ ግዛት የመውጣት እንቅስቃሴ ለማስተባበርና ቅኝ አገዛዝን ለመቃውም የተደራጀው ጉባዔ ንክሩማህ ታዋቂ የጥቁር መብት ታጋዮችና የፀረ-ቅኝ ግዛት ንቅናቄ መሪዎች ጋር እንዲገናኙ ዕድል የሰጣቸው ሲሆን በ1946ም ጥናታቸውን ትተው በ5ኛው ጉባኤ የተቋቋመው የምዕራብ አፍሪካ ብሔራዊ ጽ/ቤት ዋና ጸኃፊና የምዕራብ አፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር ምክትል ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግለዋል። \n \nጥያቄ: የተክዋሜ ንክሩማህ የት ተወለደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ደቡባዊ ምዕራብ ጋና ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ የኖቤል የሥነ ጽሑፍ ተሸላሚ ከመሆናቸው ከ35 ዓመት በፊት ይህንን ሽልማት ያገኙት አፍሪካዊ ማን ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዎሌ ሾይንካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ2010 ጀምሮ በፋይናንሱ ዘርፍ ስኬታማ ለውጦች መመዝገባቸውን ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፋይናንስ ዘርፍ ዐበይት ስኬቶች በሚል በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ እንዳስታወቁት የታክስ ገቢ በ2010 ከነበረበት 229 ቢሊየን ብር በ2012 የ36 በመቶ ጭማሪ በማሳየት 311 ቢሊየን ማድረስ ተችሏል። \n \nጥያቄ: የታክስ ገቢ ከ2010-2012 በመቶኛ የምን ያህል መጠን እድገት አሳየ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የ36 በመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ በመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ላስመዘገበችው ውጤት ሩዋንዳ በተዘጋጀው የአፍሪካ የጤና ኮንፍራስ ላይ እውቅናን አግኝታለች :: በሀገር አቀፍ ደረጃ ሞዴል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያ የሆነችው ወ/ሮ ሰናይት 40,000 የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በመወከል ሽልማቱን ተቀብላለች:: \n \nጥያቄ: በሀገር አቀፍ ደረጃ ሞዴል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያ የሆነችው ወ/ሮ ሠናይት ስንት የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን ወክላ ነው በአፍሪካ የጤና ኮንፈረንስ ላይ የተቀበለችው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 40,000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመስከረም 24 ቀን 2012 የደቡብ ክልልን ሁለንተናዊ መረጃ የያዘ አትላስ እና የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ሥርአት ተመርቀው ለአገልግለት ተዘጋጁ፡፡ በደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ አማካይነት በአዲስ መልክ ተዘጋጅቶ ትናንት የተመረቀው አትላስ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክአ-ምድራዊ መረጃዎችን አካቶ መያዙ ተገልጿል። የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርአቱም (የመረጃ ቋቱ) ላለፉት 10 ተከታታይ ዓመታት የነበሩ ሁለንተናዊ መረጃዎችን በድህረ-ገጽ አማካይነት ለማሰራጨት የሚያስችል ነው፡፡ በምርቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የደቡብ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሄለን ደበበ የስታቲስቲክስና መልክዐ-ምድር መረጃ ሥርዐት አስተዳደር የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ከያዛቸው የትኩረት አቅጣጫዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ታምራት ዲላ ከዚህ በፊት የነበረው የክልሉን አኮኖሚያዊ ፣ ማህበራዊ ፣ ዲሞግራፊያዊና መልክዐ ምድራዊ መረጃዎችን የያዘ አትላስ ላለፉት 15 ዓመታት ማገልግሉንና በአሁኑ ወቅት ያለውን ሁለንተናዊ የክልሉን እድገት ያካተተ እንዳልሆነ ተናግረዋል። ዛሬ ይፋ የተደረገው አትላስ አስከ 2009 ዓ.ም ያለውን ክልላዊ መረጃ የያዘ እንደሆነ ገልጸው አጠቃላይ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የመሰረተልማት ስርጭቶችን፣ ዴሞግራፊያዊ፣ መልክዐ-ምድራዊና ሌሎች መረጃዎችን ማካተቱን ተናግረዋል ፡፡ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ በበኩላቸው ከዚህ በፊት ለዕቅድ መነሻ የሚሆኑ መረጃዎች ታች ካሉ መዋቅሮች ብቻ እንደሚሰበሰቡ ገልፀው ይህም ተአማኒ መረጃ ለማግኘት የሚስቸግር አሰራር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይፋ የተደረጉት አትላስና የመረጃ ቋት ይህንን የመረጃ ክፍተት የሚሸፍኑና በቀላሉም ተደራሽ የሚሆኑ በመሆናቸው በፍትሀዊነት ላይ የተመሰረቱ ዕቅዶችን ለማዘጋጀት ትልቅ እገዛ ያደርጋሉ ብለዋል ፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዐቱ ላይ የደቡብ ክልል፣ የዞኖችና የልዩ ወረዳዎች አመራሮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላት ተገኝተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የደቡብ ክልል በአዲስ መልክ ሁለንተናዊ መረጃ አያያዝ አትላስና የመረጃ አስተዳደር ሥርዓት የተመረቀው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መስከረም 24 ቀን 2012 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ያለው ትርጉሙ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመለጋሲ መለጋሲ (Malagasy) ከአውስትሮኔዚያን የቋንቋ ቤተሠብ ቋንቋዎች ሁሉ ምእራበኛው ሲሆን የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ነው። 1500-2000 አመታት ከዛሬ በፊት ከእንዶኔዚያ የመጡ የማዳጋስካር ኗሪዎች ቋንቋ በመሆኑ፣ ከቃላቱ መዝገብ 90% ከመቶ በቦርኔዮ እንዶኔዚያ ከተገኘው ቋንቋ ከማአንያን ጋራ ተመሳሳይ ነው። የቀሩትም 10% ቃላት በተለይ ከአፍሪቃ ቋንቋዎች (ከባንቱ) እና ከአረብኛ ተበድረዋል። በአረፍተ ነገር ውስጥ ግሡ ከሁሉ ይቀድማል። ይህ ተራ እንደ ዕብራይስጥ ይመስላል እንጂ ለብዙዎች ቋንቋዎች የተለመደ አይደለም። በየቃሉ ውስጥ ከመጨረሻው ክፍለ-ቃል በፊት የሆነው ክፍለ-ቃል አናባቢ ይጠበቃል፤ ሌሎቹ አናባቢዎችም ይነበነባሉ (በሙሉ አይስሙም)፤ ስለዚህ \"Malagasy\" እንደ ፈረንሳይኛ አጻጻፉ \"Malgache\" (መልጋሽ) ይመስላል። \n \nጥያቄ: የማዳጋስካር መደበኛ ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መለጋሲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጨረቃ ላይ መውጣት ጨረቃ ላይ መውጣት የምንለው ማናቸውም ሰው ሰራሽ መንኮራኩሮች ጨረቃ ገጽ ላይ ሲያርፉ ያለውን ክንውን ነው። ይህ እንግዲህ ሰውንም ሆነ ያለሰው የተደረጉ በጨረቃ የማረፍ ክንውኖችን ይጠቀላላል። ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰራሽ የሆነ ነገር ጨረቃ ላይ ያረፈው በመስከረም 13፣ 1959 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውም የሶቭዬት ህብረት ሉና 2 ሚሲዮን ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ልጅ እራሱ ጨረቃ ላይ የወጣው ሐምሌ 20፣ 1969 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውን በአሜሪካው የአፖሎ 11 ሚሲዮን መንኮራኩር ነበር። ባጠቃላይ 24 አሜሪካውያን ወደጨረቃ ተጉዘዋል፣ 12ቱ የጨረቃን ምድር በእግራቸው ረግጠዋል። በዚህ ወቅት ሶቪየት ህብረትም የራሷን ጠፈርተኞች ለመላክ ሞክራለች። ለዚህ እንዲረዳት ጨረቃ ላይ አራፊ LK የተሰኘ መንኮራኩር ሰራች፣ ሆኖም ግን ይህን መንኮራኩር ወደ ጨረቃ የሚወስድ ከባድ ሃይል ያለው ሮኬት ከአሜሪካ ቀድማ መስራት ስላልቻለች ተቀደመች። ዩጂን ከርናን የጨረቃን ምድር የረገጠው የመጨረሻው ሰው ነው። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃ ላይ ያረፈው ሰው ሰራሽ ነገር መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በመስከረም 13፣ 1959 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበዚህ በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. ላይ የቱርክ፣ የመስኮብ፤ የጀርመን፤ የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይና የኤስፓኝ መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት መቆጠራቸው አልቀረም። ነገር ግን ከነዚህ ሁሉ የፖርቱጋል መንግሥት በሌላው እንኳን ባይሆን በመርከብና አገር በመያዝ ከቀሩት ይበልጥ ነበር። የቀሩት የኤውሮፓ መንግሥታት እዚያው ወሰናቸው ላይ ገዥነታቸውን ለማጽደቅ እርስ በርሳቸው ሲጨቃጨቁ የፖርቱጋል መንግሥት ግን ደኅና ደኅና መርከቦችን አዘጋጅቶ እየላከ ከመንግሥቱና ከኤውሮፓ ርቆ የሚገኘውን የአሜሪካን፤ የእስያን፤ የአፍሪካን አገሮች ያስመረምር ነበር። መርማሪዎቹም እነቫስኮ ደጋማ፤ እነፔሬዝ፤ እነአንድራድ፤ እነካብራል በመርከብ እየሄዱ ለመከላከል ጉልበት የሌለውንና በጠባዩ ሀብት ያለበትን አገር መርምረው ሲመለሱ መንግሥቱ ወታደር በመርከብ እየላከ ብዙ አገር ያዘ። በሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፭፻ እ.ኤ.አ. ፔድሮ አልቫሬዝ ካብራል የተባለው የፖርቱጋል መኮንን በትልቅ መርከብ ሄዶ ይን ጊዜ ለቀረው ዓለም ያልታወቀውን የብራዚልን አገር አስገበረና በፖርቱጋል መንግሥት ስም ቅኝ አገር አደረገው። ከዚያም አገር በተገኘው ወርቅ መንግሥቱ ሀብታም ሆነ። እንደዚሁም የመጀመሪያ የንጉሥ እንደራሴ የተባለው ፍራንቼስኮ ዳልሜዳ ወደ ህንድ አገር ሄዶ አገሩን ያዘ። ከተማውንም በጎአ አድርጎ ህንድንም የፖርቱጋል የቄሣር ግዛት አደረገና አገር ገዥውም የንጉሥ እንደራሴ ይባል ጀመር። ከዚያም በትልቁ ውቅያኖስ ውስጥ የሚገኙትን ደሴቶች ኑቤል ጉኔንና ዛሬ ፊሊፒን የሚባለውን አገር በየጊዜው በጦር ኃይል አስገበራቸው። በዚሁ አኳኋን ወደ ኢትዮጵያም እነኮቪልሐኦ ቀደም ብለው በዓፄ እስክንድር ዘመን መጥተው እንደመረመሩትና የኢትዮጵያ መንግሥት በዚያ ጊዜ በነሱ አጠራር የቄሱ የዮሐንስ መንግሥት አለ ብለው አውርተው እንደነበረ ሌላ የፖርቱጋል የጦር መርከብ በአፍሪካ ድንበር በቀይ ባሕር ላይም እየተመላለሰ አስቀድሞ ከያዙት ከቱርኮችና ከግብጾች እየተዋጋ አንድ ጊዜም እየተሸነፈ አንድ ጊዜም እያሸነፈ ብዙ ጊዜ ተመላለሰ። በዚህ ሁሉ ምክንያት የፖርቱጋል መንግሥት ታላቅነት በሌላው ዓለም እንደ ታወቀ እንደዚሁም ፩ኛ ትልቅ መንግሥት መሆኑ ፪ኛ ክርስቲያን መሆኑ ኢትዮጵያ ባሉት የውጭ አገር ሰዎች አፍ እየተነገረ ዝናው በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ዘንድ መሰማት ቻለ። \n \nጥያቄ: በ፲፭ኛው መቶ ዓ.ም. መንግሥታት እንደ ኃያላን መንግሥታት ከሚቆጠሩት ውስጥ የፖርቱጋል መንግሥት ከሌሎቹ የሚለየው በምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ መርከብና አገር በመያዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: የኬንያ ዋና መዲና ማናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ናይሮቢ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) ኡበርና ሃዩንዳይ በራሪ ታክሲዎችን በጋራ ሊሰሩ መሆኑን አስታወቁ። ሁሉቱ ኩባንያዎች አዲስ የሚሰሩትን በራሪ ተሽከርካሪ በላስ ቬጋሱ የንግድ ትርኢት ይዘው እንደሚቀርቡ አስታውቀዋል። አራት ተሳፋሪዎችን የሚይዘው በራሪ ታክሲ በሰዓት እስከ 320 ኪሎ ሜትር መጓዝ እንደሚችል ተገልጿል። ሁለቱ ኩባንያዎች በዚህ ሳምንት በላስ ቬጋስ በሚደረገው የንግድ ትርኢት ላይ የታክሲ አገልግሎት ይሰጣል ያሉትን በራሪ ተሽከርካሪ ሞዴል ይፋ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል። ኡበር በፈረንጆቹ 2023 ለደንበኞቹ የበራሪ ታክሲ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ነው የገለጸው። \n \nጥያቄ: ኡበር በራሪ ታክሲዎችን መቼ ለደንበኞቹ ለማቅረብ አቅዷል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በፈረንጆቹ 2023 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቴክኖ ካሞን 17 በዘጋቢ ፊልም ታግዞ ወደ ገበያ መግባቱን ኩባንያው አስታወቀ :: በዓለም አቀፍ ደረጃ በአዲሱ ትውልድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ቴክኖ ሞባይል ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም በለቀቀው አዲሱ የCAMON 17 ተከታታይ ስልክ የብዙዎችን ቀልብ መሳብ መቻሉን ኩባንያው አስታውቋል:: ይህ ፈጠራ የታከለበት ቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ማጠንጠኛውን በሰልፊ ላይ ባደረገ ዘጋቢ ፊልም የተመረቀ ሲሆን ድርጅቱ ምርቱን ከማስተዋወቅ ባለፈ በኢንዱስትሪ፣ በማኅበራዊና በሰብዓዊነት ዘርፎች ላይ የበለጠ ጥረት ለማድረግ ያለውን ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል:: “The Rise of Selfie” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ዘጋቢ ፊልም ፊልም በማስመረቂያ ፕሮግራሙ ላይ የቀረበ ሲሆን ታዳሚዎቹ በእርግጥም ቴክኖ የዚህን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት በተጨባጭ እና በስሜት እየሰራ መሆኑን ስለመገንዘባቸው ድርጅቱ ገልጿል:: አዲሱ የቴክኖ የንግድ አምባሳደር ክሪስ ኢቫንስ “ሕያው እና በስሜት የተሞላ ምስል ትፈልጉ ይሆናል፣ ነገር ግን መልካም ምስል የሚያደርገው ‘እጅግ ግለሰባዊ’ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ ሁሌም ቴክኖ በፅኑ ከሚያምንበት እና ከሚታወቅበት ሃሳብ ጋር ይጣጣማል ብለዋል፡፡ የስማርት ስልክ ፅንሰ ሃሳብ ብራንዱ ላይ ሳይሆን ተጠቃሚው ላይ ማውጠንጠን እንዳለበትም ነው የንግድ አምባሳደሯ የጠቆሙት፡፡ የፋሽን ሞዴል የሆኑት ሣራ በፊልሙ ላይ እንዳሉት እንደ ቴክኖ ካሞን 17 ያሉ የሰልፊ ስልኮች ተጠቃሚዎች የራሳቸውን ምስል ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተወዳጅ ፎቶዎችን በማንሳት ምስላቸውን እንዲቆጣጠሩ ያስችላቸዋል:: በተጨማሪም የተሻለ ማንነት እንዲኖር ለማድረግ እዲሁም በደመነብስ ወደተሻለ እኛነት እንድንመጣ ለራሳችን የምንጠቁምበት መንገድ ነው ብለዋል:: ቴክኖ ካሞን 17 ሁልጊዜ “በልባቸው ወጣት” ለሆኑ እና ለአዳዲስ ነገሮች ራሳቸውን ለሚያነሳሱ ተጠቃሚዎች ምልክት ለመሆን የተሰራ ነው ያለው ድርጅቱ፥ ሰዎች ራሳቸውን በይበልጥ ለመግለጽ እንዲችሉ ያስችላቸዋልም ብሏል፡፡ ኮቪድ19 ባስከተለው ተጽዕኖ ሰዎች ከሚወዷቸው ሰዎች ጋር ለመገናኘት ሰልፊን ማዘውተራቸው የሰልፊን ተግባር ይበልጥ አስፈላጊ ያደረገው በመሆኑ ጉዳዩን ቴክኖ እና ሌሎች የስልክ አምራቾች በአጽንኦት እንዲያጤኑት አድርጓቸዋል:: በቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ሰዎች ህይወት ያላቸው የሚመስሉ ፎቶዎችን ማጣጣም ብቻ ሳይሆን በFHD ስክሪን ላይ በጣም ግልጽ የሆነ ምስልን ማየት እንደሚያስችላቸው ነው የተገለጸው:: ይህ ከፍተኛ ጥራት ያለው ስክሪን ተጠቃሚዎች በቪዲዮ ጥሪዎች ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ተወዳዳሪ የሌለው ግልጽነት የሚሰጣቸው ሲሆን ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎችን መመልከት እና ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ጌሞችን መጫወት እንደሚችሉም ነው ኩባንያው የገለጸው፡፡ ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!   \n \nጥያቄ: በዘጋቢ ፊልም ታጅቦ የቀረበው አዲስ የቴክኖ ሞባይል ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቴክኖ ካሞን 17 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በስንት ዓመተ ምሀርት ተረከቡ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፳፩ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሊቢያ ኦይል ሊሚትድ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ ሥራ ለማስፋፋት መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ዱባይ ከሚገኘው የሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ ዋና መሥሪያ ቤት ወደ አዲስ አበባ የመጣው ኮርፖሬት ማኔጅመንት፣ ከሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴል የአንድ ሳምንት ጉባዔ አካሂዷል፡፡ ከ18 የአፍሪካ አገሮች የሊቢያ ኦይል ሥራ አስኪያጆች በስብሰባው ላይ ተሳትፈዋል፡፡ የሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ የሽያጭና ማርኬቲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካሪያስ ወሊቃ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ማኔጅመንቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ዕድገት በመገምገም ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ኢንቨስትመንትና የነዳጅ ንግድ እንቅስቃሴ ለማስፋፋት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች ካፀደቁት ኢትዮጵያ ውስጥ የ150 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ለማካሄድ አቅዷል፡፡ \n \nጥያቄ: የሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ የሽያጭና ማርኬቲንግ ኃላፊ ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አቶ ዘካሪያስ ወሊቃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ሰዎች በንዴቤሌ ብሔር የተወረሩት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1828 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የዓለም ጤና ድርጅት የቲቢን በሽታ ስርጭት ለመቀነስ የጀመረው እንቅስቃሴ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቲቢን እናስቁም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ በተናጋሪ ሰዎች ብዛት ስንተኛ ደረጃ ይዟል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 23ኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: በሞሪታንያ ከ5ኛው እስከ 7ኛው ክፍለ ዘመን የነበሩ ሕዝቦች ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ባፎሮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጥንቱ ጎፋ ግዛት ስር የነበሩ ክልሎች እንዴት ይተዳደሩ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቶክ ፒሲን ቶክ ፒሲን (Tok Pisin) በስሜን ፓፑዋ ኒው ግኒ የሚናገር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ዲቃላ ነው። ከእንግሊዝኛ ስዋሰው በጣም ተለውጧልና ዛሬ እንደ ራሱ ቋንቋ ይቆጠራል። የፓፑዋ ኒው ግኒ መደበኛ ቋንቋ ሆኖ በ120,000 ያሕል ተናጋሪዎችና በ4 ሚሊዮን እንደ 2ኛ ቋንቋ ይነገራል። የቶክ ፒሲን አጀማመር በፓሲፊክ ውቅያኖስ ደሴቶች ላይ የሚኖሩ የተላያዩም ልሣናት የሚችሉ ሰራተኞች አንድላይ ለአትክልት ስፍራዎች ሲሰሩ ነበር። ብዙ ጊዜ የእነዚህ ሰራተኞች የጋራ ቋንቋ ጥቂት ቀላል እንግሊዝኛ ቃሎች ብቻ ነበር። ስለዚህ አዲስ \"የቋንቋ ዲቃላ\" ተወለደ። ከእንግሊዝኛ ብቻ ሳይሆን ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከደሴተኞቹ ቋንቋዎች፣ ከጀርመንኛ፣ ወይም ከፖርቱጊዝ ነበር። ይህ ቋንቋ \"ፕጅን\" ተብሎ አሁን ሶስት ተወላጆች አሉት፣ እነሱም ቢስላማ (በቫኑዋቱ) ፒጂን (በሰሎሞን ደሴቶች) እና ቶክ ፒሲን ይባላሉ። ቶክ ፒሲን በአንዳንድ ትምህርት ቤት የትምህርት ቋንቋ ነው። \n \nጥያቄ: በስሜን ፓፑዋ ኒው ግኒ የሚነገረው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ድቅል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቶክ ፒሲን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ለወጣት ለአዛውንት የሚመቹ ደግ እናት፡፡ በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ ስም ያተረፉ፡፡ ለምርምር የማይደክሙ፡፡ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን እነሆ ታሪካቸውን አቀረበ፡፡ ጋዜጠኛዋ በ79 አመታቸው ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው አልፏል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ በ1934 አመተ ምህረት ከአባታቸው ከአቶ መኩሪያ ወልደስላሴ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ ተወለዱ፡፡ እናታቸው ወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ልጅ ናቸው፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ነበር የተከታተሉት፡፡ ወይዘሮ እሌኒ ያደጉት ካዛንቺስ አካባቢ ሲሆን የልጅነት ዘመናቸው በደስታ የተሞላ ነበር፡፡ በተለይ በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ጥሩ የእንግሊዝኛ ችሎታቸውን ከማዳበራቸው በላይ ደስ የሚል የመዝናኛ ጊዜን አሳለፈው ነበር፡፡ ቴኒስ መጫወት ፤ ዋና መዋኘት ፣ ቴአትር ማየት እና መተወን ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም ለልኡል መኮንን ሆስፒታል ማሰሪያ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ቴአትር መስራታቸውን ወይዘሮ እሌኒ በህይወት በነበሩ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ በተለይ አያታቸው ክቡር ሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ዳንስ ያለማምዷቸው እንደነበር አይዘነጉትም፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ፣ ማህበራዊ ሳይንስ የማጥናት ግብ ቢኖራቸውም ቤሩት የነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ወደዚያ በ1951 ግድም ያቀናሉ፡፡ ነገር ግን የነርስነትን ትምህርት ቢጀምሩም አቋርጠው ወደ እናት ሀገራቸው ይመለሳሉ፡፡ በመቀጠልም ወደ ብስራተ ወንጌል ሬድዮ በማቅናት በእንግሊዝኛው ክፍል ተቀጠሩ፡፡ ያኔ በሬድዮ ከወይዘሮ እሌኒ ጋር ይሰሩ ከነበሩት ባለሙያዎች መካከልም ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ኩምሳ ይጠቀሳል፡፡ ወይዘሮ እሌኒና ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ዜና ሲያቀርቡ ያለበት ቪድዮ ከዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ ዘንድ ይገኛል፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ቻርተር በግንቦት 18 1955 ሲፈረም ጋዜጠኛ ከነበሩት መካከል ወይዘሮ እሌኒ ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱ ገና የ21 አመት ወጣት የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መሪዎች ሲመጡ የተደረገውን ታሪካዊ አቀባበል በፍጹም አይዘነጉትም፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ ከማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ በየት የነፃ የትምህርት እድል ደረሳቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቤሩት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ታሊዝ ዓለምና በውስጧ ያሉ ነገሮች ከምን እንደተፈጠሩ ነበር የሚያምነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከውሃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ለአርካንሳው አስተዳዳሪነት ተወዳድረው የተሸነፉት በማን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በፍራንክ ዲ ዋይት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች አሉ። እነዚህም መሣሪያዎች የጅማት፣ የትንፋሽና የምት ተብለው ወደ ሶስት ይከፈላሉ። የክር ሙዚቃ መሣሪያዎች ድምጽ የሚሰጡት በንዝረት ነው፤ ክራር መሰንቆ ከዚህ የሙዚቃ መሳርያዎች ወገን ይመደባሉ፡፡ የትንፋሽ ሙዚቃ መሣሪያዎች ድምጽ የሚሰጡት በትንፋሽ ኃይል ነው ምሳሌ ዋሽንት። የምት የሙዚቃ መሣርያ እንደ ከበሮ ሲመቱ ድምጽ የሚያወጡ ናቸው። \n \nጥያቄ: የክር ሙዚቃ መሳሪያዎች ድምፅ የሚሰጡት እንዴት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በንዝረት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቻይና በማርስ ላይ የምታካሂደውን የመጀመሪያ ሳይንሳዊ ጥናት የፊታችን ሃምሌ ወር እንደምትጀምር ይፋ አድርጋለች። ጥናቱን የምታከናውነው ሳተላይት ሎንግ ማርች 5-ዋይ 4 በተሰኘ ሮኬት ወደ ህዋ እንደምትላክም የቻይና የጠፈር ምርምር ተቋም አስታውቋል። ሮኬቱ ተልዕኮውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቅ የሚያሰችል አቅም እንዳለው በሙከራ ተረጋግጧልም ነው የተባለው። ከሃይድሮጅን እና ኦክስጅን ጋዞች የተሰራ ሞተር ያለው ሮኬት በተያዘው ዓመት በርካታ ሳተላይቶችን ወደ ህዋ ያደርሳል ተብሎ ታምኖበታል። ወደ ህዋ የምትላከው ሳተላይትም በማርስ ፕላኔት ዙሪያ በርካታ አዳዲስ ግኝቶች እና መረጃዎችን ለምርምር ተቋሙ ታደርሳለች ተብሎ ይጠበቃል። \n \nጥያቄ: ሎንግማርች 5 ወይ 4 የተሰኘ ሮኬት እንደምትለቀቅ ማነው ያሳወቀው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የቻይና የጠፈር ምርምር ተቋም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል። ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ። \n \nጥያቄ: ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ለምን ወደ ቁስጥጥኒያ ሄዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ውስጥ በወተት ምርታቸው የታወቁት የየት አካባቢ ከብት ዝርያዎች ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የፎገራ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ለመጀመረያ ጊዜ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የታወጀው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1923 አመተ ምኅረት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: ዋዝንቢት ባለ ስንት አጽቄ ነፍሳት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሦስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: ሴት አንበሶች በአብዛኛው በምን ያህል ጊዜ ይወልዳሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በየሁለት ዓመቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ራስ መኮንን የውጫሌ ስምምነት መፍረሱን የተረዱት በየት ሀገር ጉብኝት ሲያደርጉ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኢጣሊያን ሲጎበኙ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ወላጅ እናት ናሳን ያገለገለችው በምን ሙያ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: ከ173-182 ዓም በማን መሪነት ነበር ተቋሙ በትምህርቱ ታዋቂ የሆነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በፓንታይኖስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሃሙራቢ ሃሙራቢ (አካድኛ፤ ከአሞርኛ አሙራፒ) ከ1705 እስከ 1662 ዓክልበ. ድረስ ('ኡልትራ አጭር አቆጣጠር') የባቢሎን ንጉሥ ነበረ። አባቱ ሲን-ሙባሊት ማዕረጉን ከተወ በኋላ ወራሹ ሃሙራቢ የባቢሎንን መንግሥት ግዛት በሜስፖጦምያ በጦርነት አስፋፋ። ሃሙራቢ በተለይ የሃሙራቢ ሕገ ፍትሕ ስለሚባለው የ1704 ዓክልበ. ሕገ ፍትሕ ይታወቃል። ሕግጋቱ የተቀረጹ ቁመቱ 2.4 ሜትር በሆነ ድንጋይ ሲሆን በ1893 ዓ.ም. ለሥነ ቅርስ ተገኝቷል። ሃሙራቢ እንደ ሕግ-ሰጪ ንጉሥ ዝነኛ ስለሚሆን፣ ምስሉ በአሜሪካ መንግስት ቤቶች ዛሬው ሊታይ ይችላል። ዋሺንግተን ዲሲ በአሜሪካ ምክር ቤት ውስጥ በእብነ በረድ ተቀርጸው ከ23 ታሪካዊ ሕግ-ሰጪዎች ምስሎች መካከል የሃሙራቢ ምስል አንዱ ነው። በአሜሪካ ላይኛ ችሎት ቤት ውስጥ በደቡብ ግድግዳ ላይ ሃሙራቢ ከታሪካዊ ሕግ-ሰጪዎች ጋራ የሚያሳይ ትርዒት አለ። \n \nጥያቄ: የሃሙራቢ ወራሽ ከሆነ በኃላ በሜስፓጦምያ በጦርነት የትኛውን መንግስት አስፍፍ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የባቢሎንን መንግሥት ግዛት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በተማሩበት ካሊፎርኒያ ዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከ1980-2006 ከምን እስከ ምን ማዕረግ ደረሱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ ጡረታ ከወጡ በኃላ ስንት ታላላቅ የታሪክ ስራዎችን ሰርተዋል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሦስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: ቱርክመንኛ በላቲን ፊደላት እንዲጻፉ ያወጀው ሳፓርሙራት ኒያዞቭ ኃላፊነቱ ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የቱርክመኒስታን መሪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጀስትን ቢበር ጀስትን ድሩ ቢበር (ተወለደ በ፲፻፱፻፹፮ በመጋቢት)፣ ካናዳዊ ዘፋኝ። ጀስትን ቢበር ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለመለው በአሜሪካዊው የቅጂ ድርጅት ባለቤት እስኩተር ብሮን ሲሆን የፈረመው ደግሞ ከአርቢኤምጂ የቅጂ ድርጅት በ፪፲፻ አመተ ምህረት ነው። በቀጣዩ አመት ማለትም በ፪፲፻፩ የመጀመሪያ ኢፒ(EP)ውን ለቆ እውቅናን እየተጎናፀፈ ብዙም ሳይቆይ እራሱን መገንባት እንደ ምርጥ ታዳጊ። የጀስትን ቢበር የመጀመሪያ አልበም (ማይ ወርልድ 2.0) በሁለት ሺ ሁለት ተለቀቀ፤ አልበሙም ቁጥር አንድ ሆኖ ላለፉት አርባ ሰባት አመታት (ማለትም ከሁለት ሺ ሁለት አመተ ምህረት ወዲያ ባሉ ጊዜያት) በማንም ታዳጊ ወጣት ሊያዝ ያልተቻለውን ደረጃ ይዞ አሳየ በዪናይትድ እስቴትስ። አልበሙም በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኘውን \"ቤይቢ\" የተሰኘውን ነጠላ ዘፈን ይይዛል፣ ይህም ዘፈን የምንጊዜም ከፍተኛ የምስክር \"ወረቀቶች\" ያገኘ ሊሆን ችሏል በተመሳሳይ ሀገር። የጀስትን ቢበር ቀጣይ አልበም (አንደር ዘ ሚስትልተው) በሁለት ሺ ሶስት ፡ የመጀመሪያው የገና አልበም ነበር በወንድ አንደኛ ለመሆን ከቢልቦርድ መቶ አልበሞች። በቀጣይ አመት (ሁለት ሺ አራት) ሶስተኛ አልበሙን ተከትሎ ጀስትን ቢበር ከህዝብ ጋር ያለው ግንኙነት በሻካራ ሁኔታ ተቀየረ የተለያዩ ክርክሮች በመነሳታቸው እና በህጋዊ ጉዳዮቹ ምክኛት (በሁለት ሺ አምስት እና ስድስት አመት ውስጥ) ፡ እንዲያውም ሮልንግ እስቶን የተባለ ታዋቂ የመረጃ ድርጅርት ጀስትን ቢበርን \"መጥፎ ልጅ\" ብሎ ሰየመው በመጋቢት ሁለት ሺ ስድስት ጉዳዩ። ይሁን እንጂ ከሁለት ሺ ስምንት ጀምሮ ጀስትን ቢበር ተቀዳሚነቱን ለዳግም ህዝባዊ ግንኙነቱ ሲያውል ነበር ፡ ሲያውል ነበር ለአይምሮው ጤንነት። የካቲት ሁለት ሺ ስምንት ጂኪው የተባለ ታዋቂ የመረጃ ተቋም ስለ ጀስትን ቢበር ራስ ማደስ ተነሳሽነት አስመልክቶ ፅሑፍ ይዞ ሊወጣም ችሏል። \n \nጥያቄ: ጀስቲን ቢበር ከህዝብ ጋር መቼ ተጋጨ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሁለት ሺ አራት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኒኑስ ኒኑስ በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ የነነዌ መስራችና የአሦር ንጉስ ነበረ። ለዘመናዊ ሥነ ቅርስ የታወቀ አንድ ግለሰብ አይመስልም፤ ዳሩ ግን የአያሌ ታሪካዊ ወይም አፈ ታሪካዊ ግለሰቦች ትዝታ በአንድ ስም በግሪኮች በኋለኛ ዘመን እንደ ተዘከረ አሁን ይታስባል። የንጉሥ ኒኑስና ሚስቱ ንግሥት ሴሚራሚስ ስሞች በጽሁፍ መጀመርያ የተገኘው ክቴስያስ ዘክኒዱስ (400 ዓክልበ. ገዳማ) በጻፈው በፋርስ አገር ታሪክ ነው። ክቴስያስ ለ2 አርጤክስስ (2 አርታሕሻጽታ) የመንግሥት ሀኪም ሆኖ የፋርስ ነገሥታት ታሪካዊ መዝገቦች አንብቤያለሁ ብሎ አሳመነ። ከዚህ በኋላ የግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ የክቴስያስን ወሬ አስፋፋ። የአለም ታሪክ ሊቃውንት እስከ 1880ዎቹ ድረስ የኒኑስ ታሪክ ዕውነት መሆኑን ይቈጠሩት ነበር። በዚያን ጊዜ የኩኔይፎርም ጽሕፈት ፍች ስለ ተፈታ፣ በሜስፖጦምያና በነነዌ ብዙ ቅርሶችም በመገኘታቸው፣ የአሦር ትክክለኛ ታሪክ ዕውቀት ተጨመረልን። ኒኑስ የቤሉስ ወይም ቤል ልጅ ተባለ፤ ይህም ምናልባት በሴማዊ ቋንቋ ሥር «ባል» (ጌታ) የመሰለ ማዕረግ ሊሆን ይችላል። በካስቶር ዘሮድስ ዘንድ ኒኑስ ለ52 ዓመታት ነገሰ፤ ክቴስያስም እንዳለው መጀመርያው ዓመተ መንግሥቱ 2198 ዓክልበ. ነበረ። በ17 አመታት ውስጥ ኒኑስ በአረቢያ ንጉስ አርያዎስ እርዳታ ምዕራብ እስያን በሙሉ እንዳሸነፈ ተብሏል። ከዚህ ቀጥሎ የአርመን ንጉስ ባርዛኔስን (ይቅርታ የሰጠውን) እና የሜዶን ንጉስ ፋርኖስን (በስቅለት ይሙት በቃ የሰጠውን) ድል በማድረግ የአለም መጀመርያ ንጉሠ ነገስት እንደ ሆነ ተብሏል። \n \nጥያቄ: ኑኒስ ለስንት አመት ነገሰ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለ52 ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ ኪስዋሂሊ ቋንቋ በስፋት ለምን አገልግሎት እያገለገለ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የንግድ ቋንቋ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየጥምቀት በዓል በክርስትና ኃይማኖት ተከታዮች በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ በዓል ነው። መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው። በአገራችን፣ ጥር ፲ ቀን፣ በከተራ፣ በገጠር ወራጅ ውሃ የሚከተርበት፣ ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደሚከበርበት ቦታ በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው ያሳልፋሉ።በከተሞች ግን ሰው ሰራሽ ግድብ ይሰራል። ጥር ፲፩ ቀን የጥምቀት ዕለት፤ በገጠር፣ ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት መሪነት ሁሉም ወደከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል። ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬ፣ ወንዱ በሆታ፤ ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው ይመለሳሉ። በየዓመቱ በመላ ኢትዮጵያ የሚከበረው የጥምቀት በዓል፣ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው፣ በየጥምቀተ ባሕሩ የሚከበሩ በመኾናቸው፣ ሀገሬውን ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፋዊ መስህብ በመፍጠሩ፣ ቱሪስቶችን መሳቡ አልቀረም። ጥቁርና ነጭ፣ ቀይና ብጫ ያለም ዘር፣ ከአዲስ አበባ እስከ ላሊበላ፣ ከአክሱም እስከ ጎንደር በሁሉም ሥፍራዎች በዚሁ ዓይነት ደምቆ ይከበራል። የምእመናኑም ሆነ የካህናትና ዲያቆናት አለባበስ ፍፁም በሚማርክ ባህላዊ አልባሳት የተዋበ በመሆኑ ከውጭም ሆነ ከአገር ውስጥ ለሚመጡ ጎብኚዎች ሁል ጊዜ አዲስ ነው። ሊቃውንቱ እንደሚናገሩት፣ ዘመነ አስተርእዮ የሚባለው፣ ከጥር ፲፩ ቀን ጀምሮ እስከ ጾመ ነነዌ ያለው ጊዜ ነው። በዚህ ጊዜ ውስጥ አምላክ ሰው ሆኖ በሥጋ መገለጡ፣ በዮርዳኖስ በተጠመቀ ጊዜ የአንድነትና የሦስትነት ምሥጢር መታወቁ፣ በቃና ዘገሊላ በተደረገው ሠርግ ላይ የመጀመሪያው ተዐምር በመፈጸሙ፣ አምላካዊ ኃይሉ መገለጡ፣ እየታሰበ ምስጋና ይቀርባል። ይህ ሁነት ኢትዮጵያ ብሂልን ከባህል ጋር አዛምዳ ከሌላው የክርስቲያን ዓለም በተለየ አከባበር በዓሉን ማክበሯ፣ አያሌ ቱሪስቶችን ለመሳብ አስችሏታል። \n \nጥያቄ: ኤጲፋንያ ምን ማለት ነዉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መገለጥ፣ መታየት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በእስክንድርያ፣ ግብጽ በጥንት (54-373 ዓም ያህል) የተገኘ የክርስትና ሥነ መለኮት ትምህርት ተቋም ነበረ። ተቋሙን የመሠረተው የኢየሱስ ሐዋርያ እና መጀመርያው የእስክንድርያ ጳጳስ፣ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በ54 ዓም እንደ ሆነ ተጽፏል። የተቋሙ መጀመርያው መሪ በኋላ የእስክንድያ ፮ኛው ጳጳስ የሆነው ዩስቱስ እንደ ተሾመ ይታመናል። ተቋሙ ያስተማረው ከሥነ መለኮት፣ መጽሐፍ ቅዱስና ክርስትናን ጭምር፣ የግሪክኛና የሮማይስጥ ስነ ጽሁፍ፣ ሥነ ጥበብ፣ ስነ አመክንዮ፣ ሥነ ቁጥርና ስነ-ተፈጥሮ ጥናቶች ነበሩ። ለዕውሮችም ማስተማርያ አገልግሎት አቀረቡ። በፓንታይኖስ መሪነት (173-182 ዓም) ተቋሙ ስለ ትምህርቱ ዝነኛ ሆነ። ፓንታይኖስ በክርስትና ከመጠመቁ በፊት፣ የግሪኮች «ስቶዊሲሲም» ፍልስፍና ተከታይ ሆኖ ነበር። ፓንታይኖስ የግሪክ ፍልስፍና ከክርስትና ርዕዮተ አለም ጋር እንዳዋሐደ ይታስባል። ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ ከ182-194 ዓም በተቋሙ መሪነት ተከተለው። ብዙ አረመኔዎች በዚያን ጊዜ ለትምህርት ስለመጡ ከፍልስፍና መሠረት ጀምሮ የክርስትናን ትምህርት ያሳውቃቸው ነበር። በ194 ዓም የሮሜ መንግሥት ቄሣር በክርስቲያኖች ላይ ስላዘረጋው ማሳደድ፣ ቀሌምንጦስ ለጊዜው ከእስክንድርያ ሸሸ። እሱም የጻፋቻው ትልቅ መጻሕፍት ተርፈውልናል። የቀሌምንጦስ ተከታይ ኦሪገኔስ በመከራ ጊዜ ቢሆንም ተቋሙን በ195 ዓም ዳግመኛ አቆመ። ኦሪገኔስ ደግሞ ብሉይ ኪዳን በስድስት ትይዩ ዕብራይስጥና ግሪክኛ ትርጉሞች (ሄክሳፕላ) ያሳተመው እና ብዙ አንድምታ የጻፈው ዝነኛ መምህር ነው። በ373 ዓም በተካሄደው በቁስጥንጥንያ ጉባኤ፣ የጵጵሳት ቅድምንትነት ለሮሜ ፓፓ፣ ከርሱም ቀጥሎ ለአንጾኪያ ጳጳስ እንዲሰጥ የሚል ብያኔ ወረደ። ስለሆነም፣ የእስክንድርያ ጳጳስ የቀድሞ ቀድምትነቱን በማጣቱ፣ በእስክንድርያ ከተማ ውስጥ ትልቅ ሁከት ደረሰ። በዚያም ጊዜ በተደረገው ጉዳት የማስተማርያ ተቋሙ ጠፋ። \n \nጥያቄ: የእስክንድርያ ማስተማርያ ቤት በየት የሚገኝ ትምህርት ቤት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በእስክንድርያ፣ ግብጽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ ከግብጾቹ ጳጳሳት ጋር ተገናኝተው የቤተ-ክርስቲያንን ችግር የፈቱት መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1450 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: አልጄርያ በሜድትራንያን ባህር ጋር ከየት በኩል ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከሰሜን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ካምፓላና እንትቤን በየት ሀገር የሚገኙ ከተሞች ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በዩጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን በስንት ዓመታቸው ትዳር መሰረቱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሀያ አራት ዓመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ብሔራዊ ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፈረንሳይኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት ያሸነፈችው ማንን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጣልያንን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nለሚያንኮራፉ ሰዎች መፍትሄ ይሆናል የተባለው አዲሱ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ይፋ ተደርጓል። ሚሊዮኖች የሚሰቃዩበት ማንኮራፋት ከጤና መቃወስ ጋር በተያያዘ በቂ የሆነ እንቅልፍ ከመከልከሉ በተጨማሪ በአካባቢው የሚገኙትን ሰዎች በመረበሽ ማህበራዊ ኑሯችንን ያውካል፡፡ መንስኤዎቹ የመተንፈሻ አካላት የተፈጥሮ ሁኔታና ህመም ሲሆኑ ከ60 እሰከ 80 በመቶ ከ50 አመት በላይ በሆኑ ወንዶች ላይ አንደሚከሰት ጥናቱ ያመላክታል፡፡ አዲሱ ፈጠራም የመተንፈሻ አካላትን የአተነፋፈስ ስረዓት በማሻሻል እና በማገዝ ማንኮራፋትን የሚያስወግድ ነው ተብሏል፡፡ ቴክኖሎጂው በአፍንጫ የሚቀመጥ ሲሆን ነርቮችን በማነቃቃት የአተነፋፈስ ስርዓትን በማስተካከል አየር በአግባቡ እንዲዘዋወርና ማንኮራፋትን በማስወገድ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት ያስችላል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ማንኮራፋት የሚያመጣው ጉዳት ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በቂ የሆነ እንቅልፍ ከመከልከሉ በተጨማሪ በአካባቢው የሚገኙትን ሰዎች በመረበሽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፀሐይ ፀሓይ በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። \n \nጥያቄ: በምድር ስርዓት ፈለክ መሀል ላይ የምትገኘው ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፀሓይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ራስ መኮንን ወልደሚካኤል መቼና የት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎግል በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በቻይና የሚገኘውን ቢሮውን በጊዜያዊነት መዝጋቱን አስታወቀ። የመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከቻይና በተጨማሪ በሆንኮንግ እና ታይዋን የሚገኙ አገልግሎት መስጫ ቢሮዎቹን መዝጋቱንም አስታውቋል። ከጎግል በተጨማሪ አማዞን እና ማይክሮሶፍትን ጨምሮ ሌሎች ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሰራተኞቻቸውን ደህንነት ለመጠበቅ በሚል ተመሳሳይ እርምጃ ውስጥ መግባታቸው ተገልጿል። ጎግል ሰራተኞቹ ወደ ቻይና እና ሆንግ ኮንግ ከሚያደርጉት ጉዞ እንዲታቀቡና በቻይና የሚገኙትም በተቻለ ፍጥነት እንዲወጡ መምከሩም ተነግሯል። ባለፈው ሳምንት ፌስቡክ ሰራተኞቹ ወደ ቻይና እንዳይጓዙ ያስጠነቀቀ ሲሆን፥ ተሽከርካሪ አምራቹ ጄኔራል ሞተርስም ፋብሪካዎቹን ዘግቷል። ከዚህ በተጨማሪም የጃፓኑ ቶዮታ እስከ ፈረንጆቹ የካቲት 9 ድረስ በቻይና አገልግሎት መስጠት ማቆሙን አስታውቋል። የፈረንሣዩ ፒ ኤስ ኤ እንዲሁም የጃፓኖቹ ሆንዳ እና ኒሳን ሰራተኞቻቸውን ከቻይና የማስወጣት እቅድ እንዳላቸው ተነግሯል። ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ በተገኘባት ውሃን ከተማ መቀመጫቸውን ያደረጉ ዓለም አቀፍ አምራቾችም ሰራኞቻቸውን ከቻይና ማስወጣት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ውሃን የቻይና ሰባተኛ ትልቋ ከተማ እና ዋነኛ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያዎች መቀመጫ ናት። ምንጭ፦ ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: ውሃን ከተማ ከተማ የቻይና ስንተኛ ትልቋ ከተማ ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሰባተኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር፣ በጠላት ወረራ ዘመን የተመሠረተ ድርጅት ሲሆን፤ እስከ አሁን ድረስ ያሉት አዛውንት አባላቱ በዚያው የአምሥት ዓመት ትግል ዘመናት፣ መኳንንቱ፤ የጦር መሪዎቻቸውና ንጉሠ ነገሥቱም ጭምር እነዚያን ወጣት ኢትዮጵያውያን አንጀታቸውን ለረሀብ፤ እግራቸውን ለሾኽ ለጠጠር፤ ግንባራቸውን ለእርሳስ አጋልጠዋቸው በካዷቸው መራር ዘመን፤ ሞትም ቢመጣ እናት አገራችንን አሳልፈን ለጠላት አንሰጥም፤ ነፃነታችንን ለጊዜያዊ ሹመት፣ ሽልማት አንለውጥም ብለው የተጋፈጡ ጀግኖች ናቸው። ደጃዝማች ከበደ ተሰማ፤ “የታሪክ ማስታወሻ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ፤ ይህ ማኅበር በአርበኝነት ዘመን በሸዋ ክፍለ ሀገር በ፲፱፻፴፩ ዓ/ም «የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር» በሚል ስም ተሠይሞ የተቋቋመ ማኅበር እንደነበርና ዓላማውም «የአርበኞችን ክብ በማበረታታትና በየሀገሩ ካሉ አርበኞች ጋር በመላላክ የሚገኘውን ሥራ ፍሬ» እርስ በርስም ሆነ በስደት ላይ ከነበሩት ንጉሠ ነገሥት ጋርም መካፈል እንደነበር ይገልጻሉ። ከመሥራች ማኅበረተኞቹ በከፊሉ፦ ራስ አበበ አረጋይ፤ ወንድማማቾቹ ደጃዝማች ፀሐዩ እና ደጃዝማች ተስፋዬ ዕንቁ ሥላሴ፤ አቶ እምአእላፍ ኅሩይ፤ ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ፤ ደጃዝማች ታከለ ወልደሐዋርያት ይገኙባቸዋል። በመጀመሪያ ጊዜ የነበሩት መሥራቾች ሃያ ዘጠኝ አባላት ሲሆኑ በኋላ ጊዜ ግን ብዙ ማኅበረተኞች እየተጨመሩ የአባሎቹ ቁጥር ከሦስት መቶ በላይ ሆኖ ነበር። የጠላት ኃይል ተሸንፎ የአገሪቱ ነፃነት ከተመለሰ በኋላ፣ አርበኞቹ በየአውራጃውና በየጠቅላይ ግዛቱ ተሰማርተው ስለነበረና ማኅበሩም በመከራው ዘመናት የተቋቋመበት ዓላማ በነፃነት ጊዜ አላስፈላጊ በመሆኑ፤ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ሳያሳይ ብዙ ዓመታት አሳለፈ። ሆኖም በሚያዝያ ወር ፲፱፻፶፬ ዓ/ም ጄኔራል ነጋ ኃይለ ሥላሴ «ከሥራ ባልደረቦቻቸውና ከዕውቅ አገር አፍቃሪዎች ጋራ፥ \"ጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበርን\" በታደሰ ሀገራዊ ዓላማና በተሻሻለ ደንብ አቋቋሙ። ኾኖም፥ ድርጅቱ እስከ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ድረስ ከመንግሥት ዕውቅናን ስላላገኘ ሥራው በዚሁ ምክንያት ለጊዜው ተገታ።» ጄኔራል ነጋ በዚህ ዕለት ሕጋዊ ዕውቅና ያገኘውንና ለፍጹም ሰላማዊና ሀገራዊ ዓላማ፤ ለበጎ አድራጎት የተጀመረውን የጥንታዊት ኢትዮጵያ ሀገራዊ የዠግኖች ማኅበር፤ ጠቅላይ ሥራ አመራር ሸንጎ ሊቀ-መንበር ኾነው የማኅበሩን ሥራ በሰፊው በማንቀሳቀስ ባጭር ጊዜ ውስጥ ፬ሺ የፈረሙ አባላትን ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ እንዳስገኙ፥ አሁንም መንግሥታዊ እንቅፋት ገጥሞት ከሕገ-ወጥ በሆነ እርምጃ ፥ የድርጅቱ ጽሕፈት ቤት በጸጥታ ኀይሎች እንዲዘጋ ተደረገ። \n \nጥያቄ: የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ለመጀመሪያ ጊዜ ማህበሩን የመሰረቱት መሥራቾች ስንት ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሃያ ዘጠኝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሰብለ ወንጌል እቴጌ ሰብለ ወንጌል (1482- 1560ዓ.ም.) የዓፄ ልብነ ድንግል ሚስት ስትሆን ከንግስት እሌኒ ሞት በሁዋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ የነበራት ሴት መሪ ናት። የነበረችበት ዘመን፣ የአህመድ ግራኝ ጦር በቱርክ ጠመንጃ አንጋቢወች ታግዞ ብዙ የኢትዮጵያን ክፍል የተቆጣጠረበት ወቅት ነበር። በዚህ የጦርነት ዘመን የመጀምሪያ ልጇ ፍቅጦር ሲገደል አራተኛው ልጇ ( የወደፊቱ አጼ ሚናስ ) በምርኮ ወደ የመን ተግዞ ነበር። ዓፄ ልበነ ድንግል በ1540 ዓ.ም. በደብረ ዳሞ በህመም ከሞተ በኋላ ሳይቀር እጅ ሳትሰጥ ከተራራው ምሽግ ወርዳ የፖርቱጋልን ጦር በመቀላቀል የአዳልን ጦር እስከመጨረሻው ታግላ አታግላለች። ባሏ 1540 ሲሞት ሁለተኛ ልጇ አጼ ገላውዲወስ ንጉስ ሆነ። ይህ ልጇ በደቡብ ክፍል ውጊያ ከፍቶ በመታገል ላይ እያለ በክሪስታቮ ደጋማ የሚመራው የፖርቹጋል ጦር ምጽዋ ላይ አረፈ። ይህ የሆነው እቴ ሰብለ ወንጌል ደብረ ዳሞ ተራራ ላይ ለአንድ አመት እጅ ሳትሰጥ በአህመድ ግራኝ ተከባ ከተቀመጠች በኋላ ነበር። ከተራራው ምሽጓ ላይ ሆና ከፖርቹጋሎቹ ጋር በመደራደር ወጃጅ መሆናቸውን ካረጋገጠች በኋላ ከፖርቹጋሎቹ የጦር ቀጠና ጋር ተቀላቀለች። ከበቅሎዋ ላይ ቁጭ ብላም የፖርቹጋሎቹ 400 ውታደሮች በፊቷ ሲያልፉ ትመረምር እንደነበር ታሪክ ያትታል። የንግስቲቷን ድጋፍ ተከትሎ የአካባቢው ህዝብ ለፖርቹጋሎቹ ምግብና እርዳታ እንዳደረገ፤ ብዙወችም ይህን ሰራዊት እንደተቀላቀሉ ይነገራል። ቁስለኛውን በማከም፣ የለበሰችውንም ጥምጣም በመቅደድ ባንዴጅ በመስራት፣ ለሞቱትም በማልቀስ በጦር ውሎው ሁሉ ተሳታፊ ነበረች። በ1543 የክሪስታቮና ከደቡብ በኩል የመጣው የገላውዲወስ ሃይሎች ተገናኝተው በማበር አህመድ ግራኝን አሸነፍው ገደሉት። የግራኝ ሚስት ባቲ ድል ወምበሬ ብታመልጥም ልጇ መሃመድ ግን ተማርኮ ነበር። በዚህ ጊዜ የመን የተጋዘውን የልጇን የሚናስን ጉዳይ ለመፈታት ከድል ወምበሬ ጋር በመልዕክተኛ ለመወያየት ችላለች። ሚናስ በዚህ ጊዜ ለቱርኩ መሪ ሱልጣን ሱሊማን በየመን ተልኮ ነበር። ይህ የተጋዘው ልጇ በድርድሩ መሳካት ምክንያት አይባ ላይ ከእናቱ ከሰብለ ወንጌል ሊቀላቀል ችሏል። \n \nጥያቄ: የኒሽ አቁዋም ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የዓፄ ልብነ ድንግል ሚስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ በሽቦ ያስተላለፈው ተንቀሳቃሽ ምስል በሰከንድ ምን ያህል የምስል ገጽታ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 16 የምስል ገጽታ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ዳኞች የሚሾሙት በማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በፕሬዝዳንቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: የወ/ሮ እሌኒ ስርአተ ቀብርራቸው መቼ ተፈፀመ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በምን ያህል ከፍታ ላይ ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 4088 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: የግብጽ ዋና መዲና ማናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ካይሮ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: የእቴጌ ጣይቱ እናት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ወይዘሮ የውብ ዳር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከዛሬ ፶00 ዓመት በፊት የሶሎሞን ስረወ መንግስት ሸዋ (መንዝንና ተጉለት) ላይ ሆኖ ለረጅም ዘመን ኢትዮጵያን ካስተዳደረ በሁዋል የግራኝ መሃመድ ወረራ በአጼ ልብነድንግል ዘመን ተካሄደ። ኢትዮጵውያን በግራኝ መሃመድ ወረራ የተነሳ ከፖርቱጋሎች ጋር ግንኙነትን መሰረቱ፡ በ፩፮፴ ተጀምሮ ለረጅም ጊዜ የተካሄደው ግጭት ከውጪ የመጡትን ሚሲዮናዊያን በሙሉ ከኢትዮጵያ በማባረር ሰላም ተመልሷል፡፡ ይህ የከፋ የግጭት ጊዜ ኢትዮጵያ የውጭ ክርስትያኖች ላይ እና አውሮፖውያኖች ላይ እስከ ሀያኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ፊቷን እንድታዞር አስተዋጾ ከማድረጉም በተጨማሪ እስከ 19ኛው ክ/ዘመን አጋማሽ ድረስ ኢትዮጵያ ከመላው አለም ተገልላ እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ከ1700 ጀምሮ 100 ለሚሆኑ አመታት ኢትዮጵያ ማዕከላዊ አገዛዝ ሳይኖሯት ቆይታለች፡፡ ይህም “ዘመነ መሳፍንት” ሲሆን በ1869 አፄ ቴዎድሮስ መሳፍንቶቹን ሁሉ አስገብረው ኢትዮጵያን አንድ አድርገዋል \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ዘመነ መሳፍንት ያበቃበት ዓመተ ምሕረት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1869 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል። ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማራያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል። ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ ይኖራል። አልፎም በግራኝ አህመድ ዘመን በእሳት ጋይቶ የነበረችውን አክሱም ፂዮን በአዲስ መሰረት እንደገና ማሰራት ችሎአል። ፋሲለደስ በዘመኑ እጅግ ተወዳጅ ንጉስ ቢሆንም አመጽ መነሳቱ አልቀረም። በላስታ ለምሳሌ በ1637 መልክዓ ክርስቶስ በተባለ ሰው መሪነት ጦርነት ተነስቶ አፄ ፋሲልን ስጋት ላይ ቢጥልም በሚቀጥለው አመት በተደረገው ጦርነት አመፁ ሊገታ ችሎአል። ፋሲለደስ ፖርቱጋሎችን ቢያባርርም ከውጭው አለም ጋር ብዙ ግንኙነት ያደርግ ነበር። ለምሳሌ በ1664-5 የህንድ ንጉስ አውራንግዘብ ሲነግስ መልካም ምኞትን በመልክተኞቹ ለሙግሃሉ መሪ ልኮ ነበር። በ1666 ልጁ ዳዊት ሲያምጽ፣ ወህኒ ተብሎ ወደሚታወቀው አገር በግዞት ልኮት ነበር። ይህም ከጥንቶቹ የኢትዮጵያውን ነገሥት ተፎካካሪያቸውን ወደ አምባ ግሽን በግዞት እንደሚልኩት ስርዓት ነበር። \n \nጥያቄ: በ1637 አፄ ፋሲል ላይ ያመፁት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ መልክዓ ክርስቶስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ የመሬት ስፋቱዋ ምን ያህል ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፈረንሳይ የዜጎቿን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ በመፈተሽ ግብር ሰዋሪዎችን ልትለይ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ይህም ባለፈው ሳምንት ከግብር ክፍያ ጋር በተያያዘ የወጣው ሕግ አካል ሲሆን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በገፃቸው ላይ የሚለጥፉትን የግል መረጃ ዝርዝር በማየት ነው ግብር የከፈለ እና ያልከፈለ የሚለየው፡፡ እርምጃው የዜጎች ራስን በነፃነት የመግለጽ እና የግላዊነት መብት ላይ ጫና ሊያሳድር ቢችልም ድንጋጌው የሚተገበርበት ቅድመ ሁኔታዎች አሉ ተብሏል። ከቅድመ ሁኔታዎቹ አንዱ በሚስጥራዊ ይለፍ ቃል የተቆለፉ ገጾችን ሰብሮ አለመግባት ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ለሕዝብ ይፋ የተደረጉ መረጃዎችን መጠቀም እንደሚችል ነው የተነገረው። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የፈረንሳይ የመረጃ ደህንነት ክፍል ሕጉ እንደሚያሰጋቸው ተናግረዋል። የበጀት ሚንስትሩ ጄራልድ ዳርማኒን በበኩላቸው አጭበርባሪዎችን የምንገታበት አንድ መንገድ ነው ብለዋል፡፡ ምንጭ፡-ቢቢሲ በፌቨን ቢሻው \n \nጥያቄ: ፈረንሳይ የዜጎች የግብር ስወራን ለማስቀረት ምን ዓይነት ዘዴን ልትጠቀም ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የዜጎቿን የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ በመፈተሽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: የአክሱም መንግስት በዘመኑ ከየትኞቹ ጠንካራ መንግሥታት ጋር የሚነጻጸር ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ በደብረ ወርቅ ሳለ በማን ቤት ተጠግቶ ኖረ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት ተግባር ላይ ያዋለው ሰው ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፊሎ ፍራንስዎርዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nደስታ ተክለወልድ አለቃ ደስታ ተክለወልድ የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ነበሩ። ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ የተወለዱት አለቃ ደስታ፣ ያረፉት ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን ከአጥቢያቸው ጀምሮ እስከ ደብረ ሊባኖስ የቅኔና የዜማ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ቀለምን ፈጥኖ በመቀበልና በማስተዋል ችሎታቸው የተመሰከረላቸው አለቃ ደስታ የመጻሕፍት አንድምታ ትርጓሜን አደላድለዋል፡፡ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የሠሩ ሲሆን፣ በእርሳቸው አረጋጋጭነት በርካታ መጸሕፍት ለሕትመት በቅተዋል፡፡ በሀገረ ጀርመን በታተመው ኢንሳይክሎፔዲያ ኢትዮፒካ እንደተዘገበው፣ ወደ ድሬዳዋ በመሄድ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ሥራቸውን የቀጠሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው ከሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መተዋወቃቸው ነበር፡፡ ከ30 ዓመት በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምን እየሠሩ ዐምድ አጋጣሚውን እንዲህ ያስታውሰዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ ያረፉት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበማደግ ላይ ባሉ አገራት የሚኖሩ ህዝቦች ግንባር ቀደም ገዳይ ከሚባሉት በሽታዎች አንዱ የሆነውን የቲቢ በሽታ ለማስቆም የሚያስችል ”EndTB” የተሰኘ ንቅናቄ ተካሄደ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ባለፈው ረቡዕ በሒልተን ሆቴል በይፋ ያስጀመረው ቲቢን እናስቁም ንቅናቄ እ.ኤ.አ በ2032 በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100 ሺህ አስር ብቻ ለማድረስ የታለመ ነው፡፡ ከአዳሱ የፈረንጆች ዓመት እስከ 2032 ዓ.ም ይደረጋል በተባለው በዚሁ “ቲቢን እናስቁም” ንቅናቄ፤ አገራት ሁሉ፤ ተሳታፊ በመሆን በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለውን የቲቢ በሽታ ለመግታትና በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በትጋት እንደሚሰራ ተገልጿል፡፡ በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ፕሮግራም ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት የግሎባል ቲቢ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶ/ር ማርዮ ራቨግሊዮን እንደገለፁት፤ በሽታው በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ስርጭት 133 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ሲሆን በኢትዮጵያ ቁጥሩ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ይደርሳል ብለዋል፡፡ በሽታውን ለማስቆም በተያዘው ዕቅድ መሰረትም፤ እ.ኤ.አ ከ2016-2032 ዓ.ም ድረስ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ከ100ሺ አስር ለማድረስ መታቀዱንም ተናግረዋል፡፡ ዕቅዱ እንዲሳካም አገራት ከፍተኛ ሥራ እንደሚጠበቅባቸውና ለተግባራዊነቱም የመንግስታቱን ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የቲቢ በሽታ በኢትዮጵያ ያለው ስርጭት ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 200 ሰዎች ከ100 ሺህ ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን ሲያሻሻል እድሜው ምን ያህል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፴፫ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እንግሊዝ ሀገር አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቅደላ የነበረውን እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችለው በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ እናገኛለን፡፡ በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ያዘወትር ነበር፡፡ 1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡ በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ ተደረገ፡፡ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት በመርዝ ተመረዘ። መርዙ ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ ከዚህ አለም እንዲሰናበት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ ከመደበኛ ትምህርቱ ውጪ ምን ያዘወትር ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአኩሪ አተር አኩሪ አተር የአባዝርት አትክልት ዝርያ ነው። በየጊዜው አኩሪ አተርን መመገብ ለሴቶች ጉዳት ባያደርግም፣ ለወንዶች ጤናማ እንደማይሆን በሰፊ ቢታወቅም በአንዳንድ አገር ባሕል አመጋገብ በብዛት ይጨመራል። ከ20ኛዉ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ አሜሪካን ዉስጥ ወርቃማዉ ወይም ተዓምረኛዉ እህል የሚል ስያሜ አግኝቷል። አኩሪ አተር በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር የለም። ባለሙያ ካገኘም ለመጠጣትም ለመበላትም የሚችል የእህል ዘር ነዉ። ስለአኩሪ አተር ሲወሳ ብዙዎች የሚያስታዉሱት ለሕፃናት አካል ግንባታ ጠቃሚ መሆኑ ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአኩሪ አተር ወተት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በኢትዮጵያዉያን የምግብ ጣዕም ለዛ ተላብሶ በተለያየ ምግብነት መቅረብ እንደሚችል እየታየ ነዉ። አኩሪ አተር ወደኢትዮጵያ የገባዉ በ1950ዎቹ መሆኑን ነዉ በእህሉ ላይ ምርምር የሚያደርጉት ባለሙያዎች የሚያስረዱት። በአኩሪ አተር ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተደረገዉ ዝርያ የማዉጣት ምርምርም 22 ዓይነት ዘሮች እስካሁን ተገኝተዋል። አኩሪ አተርን በሀገር ዉስጥ በ12 የምርምር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ፤ መካከለኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ እና ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርምሩ ይካሄዳል። አኩሪ አተር ሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረተዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነዉ። አኩሪ አተርን በብዛት ከሚያመርቱ ሃገራት ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ቀዳሚዎቹ ናቸዉ። ከአኩሪ አተር ወተት ለማዘጋጀት ሲታሰብ እህሉን ከአንድ ቀን በፊት ለቅሞና አጥቦ ለ15 ደቂቃ ያህል መቀቀል ያስፈልጋል። ከዚያም አዉጥቶ ተዘፍዝፎ ያድራል። ከዚያም የራሰዉን አኩሪ አተር ልጣጩን በሚገባ በዉኃ አስለቅቆ በትንሽ በትንሹ እየቆነጠሩ ፈጭቶ እንደእህሉ መጠን ዉኃ ጨምሮ መቀቀልና መጭመቅ ነዉ። እንደባለሙያዉ ከሆነም ለአንድ ኪሎ አኩሪ አተር ስምንት ሊትር ዉኃ ያስፈልጋል። ተፈጥሮን ተከትሎ የማይበቅል እህልም ሆነ በተፈጥሮ ሥርዓት ያላደጉ እንስሳትን መመገብ ለጤና አደገኛ መሆኑን በተግባር የተረዳዉ ምዕራቡ ዓለም በአሁኑ ጊዜ ፊቱን ከእንስሳት ተዋፅኦ ወደተክሎችና ሰብሎች አዙሯል። በዚህ ምክንያትም ከአኩሪ አተር የሚገኙ የምግብ ተዋፅኦዎች ተመራጭነትን እያገኙ ነዉ። ከአኩሪ አተር ወተት እና አይቡ እንደሚገኝ ሁሉ የአኩሪ አተር ሥጋም አለዉ። \n \nጥያቄ: አኩሪ አተር በአለም ላይ በብዛት የት ይመረታል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኬንያ የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከደብረ ኬንያ ተራራ ነው። በዚሁ ተራራ ዙሪያ የሚኖሩት ነገዶች ስሙን «ኪኛ» (በካምባኛ)፣ «ኪሪማራ» (በአመሩኛ)፣ «ኪሬኛ» (በኤምቡኛ)፣ «ኪሪኛጋ» (በኪኩዩ)፣ ወይም «ኬሪ» (በመዓሳይኛ) ይሉታል። የነዚህ ስሞች ሁሉ ትርጉሞች «ቡራቡሬ» ሲሆኑ ይህም ደግሞ «ሰጎን» ማለት ነው፤ አመዳይ ያለበት የተራራው ጫፍ ለተመልካች ቡራቡሬ ወንድ ሰጎንን ያሳስባልና። በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ። እንዲሁም ቱሪስምና ፔትሮሊየም አቢይ ዘርፎች ናቸው። \n \nጥያቄ: ኬንያ የምትገኘው በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በምስራቅ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: የፀሓይ ብርሃን ጨረር መሬት ላይ በምን ያህል ፍጥነት ይደርሳል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 8.5 ደቂቃ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በደቡብ ኮሪያና በኢትዮጵያ ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ ያሉት ሳተላይቶች ምን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሊትል ስታር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ ከ70 በላይ ስራዎቿን ለንባብ አቅርባ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1973 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ተርሚናል ዛሬ ተመረቀ። ተርሚናሉ በ12 ሂክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ 800 ከባድ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑ ተገልጿል። የዲቾቶ የከባድ ተሽከርካሪ ተርሚናል 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ወጭ ተደረጎበት መገንባቱ ተነግሯል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተመረቀው ተርሚናል ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nካሣ አያሌው ገና የአራት ዓመት ህፃን ልጅ ሳለ በወቅቱ የትምህርት ገበታን መቋደስ የሚጀመርበት የቄስ ትምህርት ቤት ተልኮ ፊደል መቁጠር ጀምሯል። በዚህ ቆይታው ከፊደል ቆጠራ እስከ ዳዊት ንባብ በአግባቡ ለመማር በቅቷል። በኋላም በጊዜው እንጦጦ አምባ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተብሎ ይጠራ የነበረው ት/ቤት በመዝለቅ ዘመናዊ ትምህርቱን አንድ ብሎ ጀምሯል። ካሣ በዚህ ት/ቤት ሳለ ነበር ውስጡ ከነበረው የህይወት መክሊቱ ጋር የተገናኘው። የሦስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ በት/ቤታችን የሚገኘውን ሚኒ ሚዲያ የምቀላቀልበት ዕድል ተፈጠረ። ይህ ዕድል የተገኘው በክፍሌ ውስጥ ተማሪዎች ፊት ቆሜ ጋዜጣ ሳነብ ድንገት ክፍላችን በተገኙት የት/ቤታችን ም/ርዕሰ መምህር አማካኝነት ነው። ስማቸው መምህር ግርማ ይገዙ ይባላል። አነባበቤን አይተው ስለወደዱት እርሳቸው ይመሩት የነበረውን የሚኒ ሚዲያ ክበብ እንድቀላቀል አደረጉ። በዚህ ክበብ ውስጥ ሆኜ በትምህርት ቤቱ እንቅስቃሴ ላይ ያተኮሩ ዜናዎችን እየዘገብኩ ዘወትር ማለዳ የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር እየተዘመረ ሰንደቅ ዓላማ በሚሰቀልበት የተማሪዎች ሰልፍ ላይ ማንበብ ጀመርኩ» በማለት ካሣ የጋዜጠኝነት ህይወት መስመሩ አንድ ብሎ የተጀመረበትን ሁኔታ ያስታውሳል። ካሣ አያሌው ካሣ የዘጠነኛ ክፍል ትምህርቱን በእንጦጦ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት /ቲ ኤም ኤስ/ ከጀመረ አንስቶ ሙሉ ትኩረቱን የቀለም ትምህርቱ ላይ አድርጎ ቆይቷል። በዚህ ቆይታው ከማህበራዊ ሳይንስ ይልቅ የተፈጥሮ ሳይንስን ምርጫው አድርጎ ትምህርቱን ተከታትሏል። የአስራ ሁለተኛ ክፍል መልቀቂያ አገር ዓቀፍ ፈተና ሲወስድም እንደ ተለመደው ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ከፍተኛ ትምህርት የሚሸጋገርበት ዕድል አግኝቷል። በወቅቱ የከፍተኛ ትምህርት ምደባ የሚሰጠው በዕጣ ስለነበር ካሣ በዚህ አመዳደብ መሰረት የኢንጂነሪንግ ትምህርት እንዲማር የአዳማ ቴክኒክ ኮሌጅን እንዲቀላቀል ምደባ ወጥቶለታል። ምደባውን ተከትሎ ወደ አዳማ በማቅናት የቴክኖሎጂ ትምህርቱን መከታተል ቢጀምርም ቅሉ ሁኔታው ምቾት እንዳሳጣውና እንዳሎደደው ካሣ ይናገራል። ካሣ በ2005ዓ.ም ላይ ከፍቅረኛው ሊና ኑር አሕመድ ጋር በጋብቻ የተሳሰረ ሲሆን ቀዳማዊትና ለዕልና የተባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዷል። በትዳር ህይወቱ እጅግ የተሳካለት እንደሆነ በቅርበት የሚያውቁት ጓደኞቹ ይመሰክራሉ። ከስራ ውጪ ያለ ሰዓቱን ሁሉ ከቤተሰቦቹ ጋር ማሳለፍ እንደሚያስደስተው ሁሉም ይመሰክሩለታል። \n \nጥያቄ: የካሣ የትዳር አጋር ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሊና ኑር አሕመድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: መባጃ ሐመር ሳያስፈልጋቸው ቋሚ ጊዜ ጠብቀው የሚጀምሩ አጽዋማት ስንት ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሦስቱ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኮምፒዩተር ኮምፕዩተር ማለት ማንኛውንም ኢንፎርሜሽን ፕሮሰስ የሚያደርግ ማሽን ነው። ይህንም የሚያደርገው በተርታ የተቀመጡ ትዕዛዞች በመፈጸም ነው። ለብዙ ሰዎች ኮምፒዩተር ሲባል ዐዕምሯቸው ላይ የሚመጣው የግል (ፐርሰናል) ኮምፒዩተር ነው። ነገር ግን ኮምፒዩተር ሲባል በጣም ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። ላፕቶፕ ፣ ዴስክቶፕ ፣ ማይክሮ-ኮምፒዩተር ፣ ሱፐር-ኮምፒዩተር ፣ ካልኩሌተር ፣ዲጂታል ካሜራ እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ቀድሞ አስሊ ማለት አንድ በሒሳባዊ ትዕዛዝ የተለያዩ የጥንት መሣሪያዎችን እየተጠቀመ ቁጥሮችን የሚያሰላ ሰው ነበር። እስከ 20ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የተለያዩ ጠቃሚ መሣሪያዎች ተሰርተዋል። ከዛ በኋላ ትልልቅ ማሸኖች መሠራት ጀመሩ። እነዚህ ማሽኖች ከዛሬው ኮምፒዩተሮች(አስሊዎች) ጋር ሲወዳደሩ በጣም ትልቅና ቀርፋፋ ናቸው። የኮምፕዩተር የውስጥ ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1.ሞኒተር - የምንሰራውን ነገር እንዲያሳየን፤ምስል፣ጽሑፍ፣ ቪዲዮ ወይም ማንኛውም ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ሞኒተር 14 ኢንች፣ 15 ኢንች፣ ወዘተ. እየተባለ ይገላጻል፡፡ 2.ማዘርቦርድ - እናት ሰሌዳ ሁሉም የኮምፕዩተር ክፍሎች(ዕቃዎች)የሚቀዳጁበት 3.ሲፒዩ - የኮምፕዩተሩ አእማሮ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሲፒዩን ከሰው አእምሮ ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ 4.ሜሞሪ - የምንሰራውን ስራ ወይም ፋይል በጊዚያዊነት አስቀምጠንበት የምንሰራበት፡፡ ሜሞሪበባይት (Bytes) ይለካል፡፡ ከ Bytes ፊት Kilo፣ ማለትም ኪሎባይት (kilobytes)([1,024 ባይቶች ወይም Bytes ማለት ነው፡፡ ] ፣ Mega[1,048,576 ባይቶች ወይም Bytes ] ፣ Giga [1,073,741,824 ባይቶች ወይም Bytes]፣ ወዘተ የሚሉትን ቃላት በመጠቀም ኪሎባይት(kilobyte)፣ ሜጋባይት (megabyte)፣ ጊጋባይት (gigabyte) እያልን የኮምፒዩተር ሜሞሪ መግለፅ እንገልጻለን፡፡ ለምሳሌ 10 MegaBytes ወይም ባጭሩ ሲጸፍ 10MB ይህ ማለት 10,485,760 Bytes ይሆናል ማለት ነው፡፡ 5.ኤክስፓንሽ ስሎት 6.የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረቢያ (power supply) 7.የሲዲ ማሰሪያ (cd drive) 8.ሀርድ ዲስክ (የምንሰራውን ወይም የምንጠቀምበትን ፋይል በቋሚነት ለማስቀመጥ) 9. መሎጊያ (ማውስ) 10.የፊደል ገበታ (ኪቦርድ) የመጀመሪያቹ ኮምፕዩተሮች የሚሠሩት በእንግሊዝኛ ፊደል ብቻ ነበር። ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ኣገሮች ሊቃውንት በየራሳቸው ፊደላት እንዲሠሩ ኣደረጉ። ኮምፕዩተር በእያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኣበራ ሞላ ነው። በቅርቡም አያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት ዩኒኮድ የሚባል የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ መግባት ቀጥሏል። \n \nጥያቄ: ማንኛውም በኮምፒዩተር ፕሮሰስ የሚያደረጉ ነገሮችን የሚከውን የኮምፒዩተሩ ክፍል ወይም አንጎል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሲፒዩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: የሰብለ አጎት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጉዱ‌ ‌ካሳ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በዚምባቡዌ አራት አምስተኛ የሚሆኑት ሰዎች የምን ሰዎች ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የሾና ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች የራሳቸው ዘመናዊ ሙዚቃ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ «ኳይቶ» ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፯ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፴፯ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፪ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፱ ቀናት፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፰ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፭፻ ዓ/ም - በስመ መንግሥት አንበሳ በፀር ይባሉ የነበሩት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አርፈው የ፲፪ ዓመት ልጃቸው ዓፄ ልብነ ድንግል ወናግሰገድ ተብለው ነገሡ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በኩባ ደሴት በእስፓኝ እና በአሜሪካ መኻል የነበረው የማስተዳደር ፍልሚያ ትግል አከተመ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ከፈረንሳይ ቅኝ ተገዢነት ነፃነቷን አወጀች። ዴቪድ ዳኮ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፭፻ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ነሐሴ ሰባት 336ኛው ቀን ሲሆን ለክረምት ስንተኛው ቀን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፵፪ኛው ቀን ነው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጉል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ የዋለው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 2014 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: በባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት የወረሳቸው የነዳጅ አቅራቢ ድርጅቶች እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር በከተሞቹ መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ ስንት ይቀንሰዋል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 47 ደቂቃ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ወደ ጃፓን ለመጀመሪያ ጊዜ የላከችው መዳብ የተገኘው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የድባሮ መዳብ ማዕድን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. መሠረቱ። ከምዕራቡ ሮማ መንግሥት ውድቀት ደግሞ ወደ ተረፈው ሕዋእ ውስጥ ከፈለሱት ጀርመናውያን ወገኖች አብዛኛው የራሳቸውን ሕጎች ዝርዝር በጽሑፍ አወጡ። በተለይ የሚታወቁም የቪዚጎቶች አለቃ ዩሪክ ሕግ (463 ዓ.ም.)፣ የቡርጎንዳውያን ሕግጋት (እኚህ ለጀርመናውያንና ለሮማውያን የተለያየ ፍትሕ ነበራቸው)፣ የአላማናውያን ሕግጋትና፣ የፍራንኮች ሕግጋት ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ የተጻፉት ከ492 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በ498 ዓ.ም. የቪዚጎቶች አለቃ 2ኛ አላሪክ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስና አንዳንድ የተለያዩ የቀድሞ ሮማ ሐገጋት አከማችተው አዋጁአቸው። ከዚህም በኋላ የታዩ ሕጎች የሎምባርዶች ሕግጋት (635 ዓ.ም.)፣ የቪዚጎቶች አዳዲስ ሕግጋት (646 ዓ.ም.)፣ የአላማናውያን አዳዲስ ሕግጋት (722 ዓ.ም.) እና የፍሪዝያውያን ሕግጋት (777 ዓ.ም.) አሉ። በአውሮፓ አኅጉር ላይ የተጻፉት እነኚህ ፍትሖች ሁሉ በሮማይስጥ ቢጻፉም፣ በእንግሊዝ አገር ግን የተጠቀሙት ሕጎች ከኬንት ንጉሥ ኤጠልቤርት ሕጎች (594 ዓ.ም.) ጀምሮ በጥንታዊ እንግሊዝኛ የተቀነባበሩ ነበሩ። በ885 ዓ.ም. ታላቁ አልፍሬድ ይህንንና ሁለት የድሮ ፍትሖች ከሕገ ሙሴና ከሕገ ወንጌል ጋራ አጋጥመው የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ዶም ቦክ ሠርተዋል። \n \nጥያቄ: የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. የታወጀው በማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሕንድ ንጉሥ አሾካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጣና ሐይቅ ጣና ሐይቅ ቅዱሱ ሐይቅም ይባላል። ከኢትዮጵያ አንደኛ እና ትልቁ ሐይቅ ነው። 84 ከ.ሜ. ረጅም እና 66 ኪ.ሜ. ሰፊ ነው። ባጠቃላይ 3,500 ካሬ ኪ.ሜ. ይሸፍናል። በቁጥር ከ35 በላይ ደሴቶች በሐይቁ ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ ውስጥም 22ቱ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት ናቸው። ባንዳንዶቹ ላይም (ለምሳሌ በዳጋ ደሴት) የድሮ የኢትዮጵያ መሪዎች መቃብሮች ሲገኙ ኢትዮጵያ ውስጥ ክርስትናን ለመጀመሪያ ያስተዋወቀው አቡነ ሰላማ መቃብርም በዚሁ ሃይቅ ይገኛሉ። የጣና ሃይቅን የሚመግቡ 3ቱ ዋና ወንዞች ርብ፣ ጉማራ ወንዝ ና ትንሹ አባይ በመባል ይታወቃሉ። አሁን ባለው ይዞታ የጣና ሃይቅ 1,454 ቶን አሳ በአመት ይመረታል። ነገር ግን ይሄ የምርት ሃይቁ ያለምንም ችግር ሊያስተናግድው ከሚችለው 15 በመቶው ያህል ብቻ ነው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ በመጠኑ አንደኛ የሆነው ሐይቅ የቱ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጣና ሐይቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: በሜክሲኮ የናዋትል ቋንቋ የነዋሪዎቹ መደበኛ መግባቢያነቱ የቀነሰው እነማን ከወረሯቸው በኋላ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እስፓንያውያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአረማይክ አረማይክ ወይም አራማይስጥ፣ የሶርያ ቋንቋ ከሴማዊ ቋንቋዎች አንዱ ሲሆን በመካከለኛ ምሥራቅ ከጥንት ጀምሮ ታውቋል። መጀመርያ የአረማይክ ጽሑፎች ከ1000 ዓክልበ. ግድም በፊንቄ አልፋቤት ነበሩ፤ ይህም የአራም ሕዝብ የተናገሩት ጥንታዊ አራማይስጥ ነበር። በአንድ አስተሳሰብ ቋንቋቸው ከ1100 ዓክልበ. አስቀድሞ ሑርኛ ይሆን ነበር፤ የአሦርም መንግሥት ከገዙአቸው በኋላ እንደ አካድኛ ሴማዊ ሆነ። ከ800 ዓክልበ. አካባቢ በኋላ የራሱ አረማይክ አልፋቤት ከፊንቄ አልፋቤት ተለማ። በ740 ዓክልበ. የአሦር ንጉሥ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር አረማይስጥ ከአሦርኛ (አካድኛ) ጋር ይፋዊና መደበኛ ቋንቋ አደረገው። ከዚያ ጀምሮ የአረማይስጥ ጥቅም እየተስፋፋ የአካድኛ ጥቅም በየጊዜ ይቀነስ ነበር። ከአሦር ውድቀት (617 ዓክልበ.) በኋላ በባቢሎኒያ መንግሥት፣ ከባቢሎኒያም ውድቀት (547 ዓክልበ.) በኋላ በፋርስ አሓይመኒድ መንግሥት ውስጥ፣ አረማይክ መደበኛና ይፋዊ ቋንቋ ተደረገ፣ ስለዚህ ጥቅሙ በሰፊ ከግብጽ እስከ ባክትሪያ ድረስ ይዘረጋ ነበር። በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ የተገኘው አራማይክ በተለይ በትንቢተ ዳንኤል ከዚሁ ዘመን ነው። \n \nጥያቄ: አረማይክ ቋንቋን ይፋዊ ቋንቋ ያደረገው የአሦር ንጉሥ ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቴልጌልቴልፌልሶር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ በአሜሪካ ጎዳናዎች ላይ ሙከራ እንዲያደርግ ፈቃድ አገኘ። ተሽከርካሪው የአሽከርካሪ ወይም የሰው እገዛ ሳያስፈልገው አገልግሎት ይሰጣል ነው የተባለው። ኑሮ በተባለው ኩባንያ የተሰራው ተሽከርካሪ መሪን ጨምሮ ለመሽከርከር የሚያገለግሉት የነዳጅ መስጫና ፍሬን እንዲሁም የእይታ መስታወትን (ስፖኬ) ያለ አሽከርካሪ በራሱ ይጠቀማል። የአሜሪካ የትራንስፖርት ሚኒስቴርም ተሽከርካሪው በቴክሳስ ሙከራውን እንዲያደርግ ፈቃድ ሰጥቶታል። አር 2 የሚል ስያሜን ያገኘው ይህ የእቃ ማመላለሻ፥ የኩባንያው ሁለተኛው ትውልድ ተሽከርካሪ ሲሆን በሆስተን ቴክሳስ ሙከራ እንደሚያደርግ ነው የተነገረው። የእቃ ማመላለሻውን ለመሞከር ተሽከርካሪውን መቆጣጠር የሚያስችሉ ክፍሎችን ማሟላት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል። ሆኖም የእቃ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ፍጥነት በሰዓት ከ25 ኪሎ ሜትር እንዳይበልጥ የአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር አስጠንቅቋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ በማን ኩባንያ ተሰራ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኑሮ በተባለው ኩባንያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየሕገ መንግሥት ታሪክ የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና በ2093 ዓክልበ. ያሕል ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው። ሰነዱ እራሱ ገና አልተገኘም፤ ነገር ግን ለዜጎቹ አንዳንድ መብት እንደ ፈቀደላቸው ይታወቃል። ለምሳሌ ለመበለትና ለደሀ አደጎች ቀረጥ እንዳስቀረላቸው ድሆችንም ከሃብታሞች አራጣ እንደጠበቃቸው ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ብዙ መንግሥታት በተጻፈ ሕግ እንዲገዙ ልዩ ስርዓት ነበራቸው። ከተገኙት ሕግጋት ሁሉ ጥንታዊ የሆነው በ1983 ዓክልበ. የገዙ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው። በተለይ ዕውቅ የሆኑ የጥንት መንግሥት ሕጎች የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት (1832 ዓክልበ.) ፤ የኤሽኑና ሕግጋት (ምናልባት 1775 ዓክልበ. ግድም)፤ የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ.) እና፤ ሕገ ሙሴ ለእስራኤል (1661 ዓክልበ.) ናቸው። ሕገ ሙሴ በተለይ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 ያህዌ አስተካክሎ ከነዚህ ሁሉ የተሻሸሉት ብያኔዎች ይጠቅልላል። በኋላ ኬጢያውያን (1488 ዓክልበ. ግድም) እና አሦር (1080 ዓክልበ. ግድም) በበኩላቸው ለራሳቸው ሕግጋት አወጡ። \n \nጥያቄ: በጽኹፍ ከተገኙ ሕግጋት ጥንታዊው ሕግ መች ነበር የተጻፈው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1983 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ በአፍሪካ በየትኛው ክፍል ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመዓዛ ብሩ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ታቀርባቸው የነበሩት ሥራዎች ይዘት ማህበራዊ ሕይወት እንዲሠምር በመጣር ላይ ያተኮሩ ሆነው ግልጽ፣ ቀላልና ለዛ ያልተለያቸው ስለነበሩ ከሶስት አሥርት ዓመታት በኋላም ትውስታቸው ከአድማጭ ህሊና አልጠፉም፡፡ በዚሁ ፕሮግራም ላይ መዓዛ ካበረከተቻቸው የፈጠራ ሥራዎቿ ውስጥ ጎልቶ የሚታወሰው “የአዲሱ ቤተሰብ” የተሰኘ ባለ ሰማንያ ስድስት ክፍል ድራማ ሲሆን በዘመኑ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሁሉም የሚያደምጠው ተወዳጅ የቤተሰብ ድራማ ነበር፡፡ መዓዛ በ “መርሀ ስፖርት” እና በሬዲዮ መካከል ሆና ከአራት ዓመት በላይ ከቆየች በኋላ በ1979 ዓ.ም የባህል ሚኒስቴርን ለቃ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተቀጠረች፡፡ አዲሱን መስሪያ ቤቷን ከተቀላቀለችበት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከሬዲዮ እየራቀች መጣች፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ የቆየችው ለሶስት ዓመታት ያህል ሲሆን ከዚያ በኋላ የግሏን የማስታወቂያ ሥራ ድርጅት መሥርታ የራስዋ ተቀጣሪ ሆናለች፡፡ ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1992 ዓ.ም ባሉት የአስራ ሶስት ዓመታት ጊዜ ግን መዓዛና ሬዲዮ ተራራቁ፡፡ መዓዛና ሬዲዮ ዳግም የተዋደዱት ከላይ እንደተገለጸው በ1992 ዓ.ም ሳምንታዊውን የ “ጨዋታ” ፕሮግራም በኤፍ ኤም 97.1 ከተፈሪ ዓለሙ ጋር በጋራ ማቅረብ ሲጀምሩ ነበር፡፡ የ “ጨዋታ” ፕሮግራም እስከ 1999 ዓ.ም ድረስ በአድማጮቹ እንደተወደደ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ላይ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ መንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የኤፍ ኤም ሬዲዮ ፈቃዶችን ለግሉ ዘርፍ ለመስጠት ሲዘጋጅ፣ ዝርዝር የሥራ እቅድ አቅርባ ባመለከተችው መሠረት፤ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ ከአስር አመልካቾች መካከል አንዷ ሆና የመጀመሪያ የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ባለቤት ያደረጋትን ፈቃድ ተቀበለች፡፡ መዓዛ የሬዲዮ ማሰራጫ መሳሪያዎችን ውድነት፣ የማሰራጫ ቦታ እና የባለሙያ እጦትን ተቋቁማ ሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮን በታህሳስ 1999 ዓ.ም አበረከተችልን፡፡ ባለትዳርና የሶስት ልጆች እናት የሆነችው መዓዛ እንደ ባለቤት፣ ሥራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ በመሆን በኢትዮጵያ ተወዳጁንና የመጀመሪያውን የግል የኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ትመራለች፡ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!”እያለች:: \n \nጥያቄ: መኣዛ ብሩ በኢትዮጵያ ሬድዮ ካበረከተቻቸው አንጋፋ ስራዎች አንዱ የትኛው ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ “የአዲሱ ቤተሰብ” የተሰኘ ባለ ሰማንያ ስድስት ክፍል ድራማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: ናዋትል በምን ቋንቋ ቤተሠብ ውስጥ ይመደባል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኡቶ-አዝቴካዊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ 250,000 ያህል ተናጋሪዎች ያሉት በየት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በታንዛኒያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: አንበሶች በሰዓት እስከ ስንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 59 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ ሸክላ የሚሰሩበት መንገድ ምን ጥቅም አስገኝቶላቸዋል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቱሪስት መሳቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቅልልቦሽ ቅልልቦሽ የኢትዮጵያ ህጻናት በጠጠር የሚጫወቱት ሲሆን አጨዋወቱም አንዱዋን ጠጠር ወደአየር በማጉናት እሱዋ ባየር ላይ እያለች የተቻለን ያክል ጠጠር ከመሬት ማፈስ ነው። ባየር ላይ ያለችው ጠጠር ስትመለስ በተጫዋቹ እጅ \"መቀለብ\" ወይም \"መያዝ\" ይኖርባታል። ሳትያዝ መሬት ላይ ከወደቀች፣ ጨዋታው አለቀ ማለት ነው። ጨዋታው \"ጠጠር\" በመባልም ይጠራል። ብዙ አይነት የቅልልብልቦሽ ጨዋታዎች ሲኖሩ፡ በጣም የታወቀው \"ዓይጥ አለብሽ\" በመባባል የሚጫወቱት ነው። ልጆቹ ሁለት ወይም ሶስት ይሆኑና፡ አምስት ቆንጆ ድብልብል ጠጠሮች፡ ስፋትና ርዝመታቸው ከግማሽ ኢንች የማይበልጡ፡ ይለቅሙና መሬት ይቀመጣሉ። ቀድሞ \"ብጀ\" ያለ መጀመርያ ይጀምራል። ብጀ ማለት ብጀምር ማለት ነው። ያንን ለማለት እሽቅድምድም ነው።\"ብቀ\" ያለ ከርሱ የሚከተል ነው ማለት ነው፡፡ ብቀ ማለት ብቀጥል ማለት ነው። ሁለት ልጆች እኩል \"ብቀ\" ካሉ በድምጽም ቢሆን ቀድሞ \"ብ!\" ከአፉ የወጣው ሰው ሁለተኛነቱን ያገኛል። \"ብቀጣጥል!\" ያለ ሶስተኛ ነው። \"እንጀራ ብጋግር!\" ያለ አራተኛ ነው። አምስተኛ ካለ \"ወጥ ብሰራ!\" ብሎ ተራውን ያሳውቃል። በዚህ ተራ ተስማምተው ጀማሪው ይጀምራል። \n \nጥያቄ: በቅልብልቦሽ ጨዋታ አምስተኛ ለሆነ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወጥ ብሰራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበደቡብ ሱዳን መከላከያ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ጆንሰን ጁማ ኡኮት የተመራ ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ልዑኩ አዲስ አበባ ሲገባ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀኔራል ብርሀኑ ጁላ እና በሌሎች ከፍተኛ የመከላከያ አዛዦች አቀባበል ተደርጎለታል፡፡ በቆይታቸውም በሁለቱ ሀገራት የመከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክሩ ከመከላከያ ሰራዊት ገጽ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: ጄኔራል ጆንሰን ጁማ ኦኮት በየት ሀገር ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በደቡብ ሱዳን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ1240 አካባቢ በግብጽ አገር ቅብጡ አቡል ፋዳዒል እብን አል-አሣል ፍትሐ ነገሥት በአረብኛ ጻፉ። እብን አል-አሣል ሕጎቹን የወሰዱት በከፊል ከሃዋርያት ጽህፈቶችና ከሕገ ሙሴ፤ በከፊልም ከድሮ ቢዛንታይን ነገስታት ሕጎች ነበር። መጽሐፉ በግዕዝ ተተርጉሞ ወደ ኢትዮጵያ የገባበት ወቅት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን በ1450 አከባቢ እንደነበር የሚል ታሪካዊ መዝገብ አለ። ቢሆንም መጀመርያ እንደ ሕገ ምንግሥት መጠቀሙን የተመዘገበው በዓፄ ሠርፀ ድንግል ዘመን (ከ1555 ጀምሮ) ነው። ፍትሐ ነገስት እስከ 1923 ዓ.ም. የብሄሩን ዋና ሕግ ሆኖ ቆየ። በ1904 ዓ.ም. ዐጼ 2 ምኒልክ የዘመናዊ ሕገ መንግሥት ፅንሰ ሀሳብ ተረድተው በጸሀፊው መምሬ ብስራት አንድ ሕገ መንግሥት የሚመስል ሰነድ ታተመ፤ ይህ ግን በውነት ሕገ መንግሥት አይባልም። «በምኒሊክ ስለተቋቋሙት ሚኒስቴሮች በምሳሌ የቀረበ ጽሑፍ» በምሳሌና በትርጓሜ የእያንዳንዱን ሚኒስቴር ሥራ እንደ ሰውነት አካላት አስመሰለ። ለምሳሌ፦ ኢትዮጵያ መጀመርያ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የተቀበለችው በ1923 አመተ ምኅረት በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የታወጀ ሲሆን የሕግ አማካሪ ቤቶች በሁለት ያስከፈለ ነው። ይህ የመንግሥታቸው ዋና መሠረት ሆኖ እስከ 1948 አ.ም. አገለገለ፤ በዚያ አመት ተሻሽሎ በወጣ ሕገ መንግሥት ሕዝቦች በመንግሥት ሥራ የሚጫወቱት ሚና እንደገና ተስፋፋ። ይህ ብቻ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ሆኖ እስከ 1967 አ.ም. ቆየ፤ የዛኔ በደርግ (በሕገ መንግስት እራሱ ባልሆነ ሂደት) ተሰረዘ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ለመጀመረያ ጊዜ ዘመናዊ ሕገ መንግሥት የታወጀው በማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአጼ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: ጋሊልዮ በስንት ዓ.ም ሞተ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጥር 8, 1642 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ በመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ላስመዘገበችው ውጤት ሩዋንዳ በተዘጋጀው የአፍሪካ የጤና ኮንፍራስ ላይ እውቅናን አግኝታለች :: በሀገር አቀፍ ደረጃ ሞዴል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያ የሆነችው ወ/ሮ ሰናይት 40,000 የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በመወከል ሽልማቱን ተቀብላለች:: \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በመሠረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ላስመዘገበችው ውጤት ምን ተጠቅማለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሩዋንዳ በተዘጋጀው የአፍሪካ የጤና ኮንፍራስ ላይ እውቅናን አግኝታለች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ ስለሚያገኙት የሽልማት ገንዘብ መጠን የገለጸው የመገናኛ ተቋም ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቢቢሲ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። ባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። \n \nጥያቄ: በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት ምን ለመስራት አስቧል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር መቼ ተመረቀ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1887 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ስያሜውን ያገኘው ንጉሰ ነገስቱ የተናገሩት ንግግር ምን የሚል ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የሆነው የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ላይ የሚታየው መንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኤስፔራንቶ ኤስፔራንቶ (Esperanto) ከሁሉም አለማቀፋዊ ሠው ሰራሽ ቋንቋዎች እጅጉን የተስፋፋ ቋንቋ ነው። በ1859 እ.ኤ.አ. በዛሬይቷ ፖሎኝ የተወለደውና በሞያው የአይን ሀኪም የሆነው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ በ1887 እ.ኤ.አ. ቋንቋውን ለህዝብ አሳወቀ። አላማው ኤስፔራንቶን በቀላሉ ሊማሩት የሚቻል፣ የጋራ የሆነና ለአለማቀፋዊ መግባባት የሚረዳ ግን ያሉትን ቋንቋዎች የማይተካ ቋንቋ ማድረግ ነበር። ኤስፔራንቶ ከ1,600,000 በላይ ተናጋሪዎች ቢኖሩትም የቋንቋው ደጋፊ ያልሆኑ እንግሊዝኛን ከመስፋፋቱ አንፃር ለአለማቀፋዊ ቋንቋነት በተሻለ ይመርጡታል። \n \nጥያቄ: ኤስፔራንቶ የተሰኘውን ዓለም አቀፋዊ ቋንቋ ያስተዋወቀው ሉድዊክ ሌይዛር ዛመንሆፍ የተወለደው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፖሎኝ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጮቄ ወረዳ በምን ይታወቃል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን መቼ ሞቱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን ሜሪ ቶድን መቼ አገቡ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1834 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ የሆነው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1943 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nነሐሴ ፯ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፴፯ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፪ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፱ ቀናት፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፰ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፭፻ ዓ/ም - በስመ መንግሥት አንበሳ በፀር ይባሉ የነበሩት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አርፈው የ፲፪ ዓመት ልጃቸው ዓፄ ልብነ ድንግል ወናግሰገድ ተብለው ነገሡ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በኩባ ደሴት በእስፓኝ እና በአሜሪካ መኻል የነበረው የማስተዳደር ፍልሚያ ትግል አከተመ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ከፈረንሳይ ቅኝ ተገዢነት ነፃነቷን አወጀች። ዴቪድ ዳኮ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፭፻ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: በኩባ በእስፓኝ እና በአሜሪካ መካከል የነበርው የማስተዳደር ፍልሚያ የተቋጨው በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፲፰፻፺ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአኩሪ አተር አኩሪ አተር የአባዝርት አትክልት ዝርያ ነው። በየጊዜው አኩሪ አተርን መመገብ ለሴቶች ጉዳት ባያደርግም፣ ለወንዶች ጤናማ እንደማይሆን በሰፊ ቢታወቅም በአንዳንድ አገር ባሕል አመጋገብ በብዛት ይጨመራል። ከ20ኛዉ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ አሜሪካን ዉስጥ ወርቃማዉ ወይም ተዓምረኛዉ እህል የሚል ስያሜ አግኝቷል። አኩሪ አተር በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር የለም። ባለሙያ ካገኘም ለመጠጣትም ለመበላትም የሚችል የእህል ዘር ነዉ። ስለአኩሪ አተር ሲወሳ ብዙዎች የሚያስታዉሱት ለሕፃናት አካል ግንባታ ጠቃሚ መሆኑ ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአኩሪ አተር ወተት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በኢትዮጵያዉያን የምግብ ጣዕም ለዛ ተላብሶ በተለያየ ምግብነት መቅረብ እንደሚችል እየታየ ነዉ። አኩሪ አተር ወደኢትዮጵያ የገባዉ በ1950ዎቹ መሆኑን ነዉ በእህሉ ላይ ምርምር የሚያደርጉት ባለሙያዎች የሚያስረዱት። በአኩሪ አተር ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተደረገዉ ዝርያ የማዉጣት ምርምርም 22 ዓይነት ዘሮች እስካሁን ተገኝተዋል። አኩሪ አተርን በሀገር ዉስጥ በ12 የምርምር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ፤ መካከለኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ እና ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርምሩ ይካሄዳል። አኩሪ አተር ሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረተዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነዉ። አኩሪ አተርን በብዛት ከሚያመርቱ ሃገራት ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ቀዳሚዎቹ ናቸዉ። ከአኩሪ አተር ወተት ለማዘጋጀት ሲታሰብ እህሉን ከአንድ ቀን በፊት ለቅሞና አጥቦ ለ15 ደቂቃ ያህል መቀቀል ያስፈልጋል። ከዚያም አዉጥቶ ተዘፍዝፎ ያድራል። ከዚያም የራሰዉን አኩሪ አተር ልጣጩን በሚገባ በዉኃ አስለቅቆ በትንሽ በትንሹ እየቆነጠሩ ፈጭቶ እንደእህሉ መጠን ዉኃ ጨምሮ መቀቀልና መጭመቅ ነዉ። እንደባለሙያዉ ከሆነም ለአንድ ኪሎ አኩሪ አተር ስምንት ሊትር ዉኃ ያስፈልጋል። ተፈጥሮን ተከትሎ የማይበቅል እህልም ሆነ በተፈጥሮ ሥርዓት ያላደጉ እንስሳትን መመገብ ለጤና አደገኛ መሆኑን በተግባር የተረዳዉ ምዕራቡ ዓለም በአሁኑ ጊዜ ፊቱን ከእንስሳት ተዋፅኦ ወደተክሎችና ሰብሎች አዙሯል። በዚህ ምክንያትም ከአኩሪ አተር የሚገኙ የምግብ ተዋፅኦዎች ተመራጭነትን እያገኙ ነዉ። ከአኩሪ አተር ወተት እና አይቡ እንደሚገኝ ሁሉ የአኩሪ አተር ሥጋም አለዉ። \n \nጥያቄ: አኩሪ አተር በውስጡ ምን ንጥረ ነገሮችን ይዟል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣2012 (ኤፍቢሲ) ፌስቡክ ከግል መረጃ መጠበቅ ጋር ተያይዞ የአባላት የስልክ ቁጥሮች በጓደኞች ጥቆማ ሂደት ላይ መጠቀም ሊያቆም መሆኑ ተገለፀ ፡፡ የተጠቃሚዎች የፌስቡክ አድራሻ በጠላፊዎች በቀላሉ እንዳይገኝ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ኮድ እንዲላክ ምርጫ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ፌስቡክ የተጠቃሚዎችን ስልክ ቁጥር ለማስታወቂያ እና በጓደኛ ጥቆማ ሂደት ላይ ሲጠቀምበት እንደነበረ አስታውቋል፡፡ በአሁን ወቅት ከአሜሪካ አዲስ የቁጥጥር ስርዓት ጋር ተያይዞ ይሄን አሰራር ለማቆም ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: ፌስቡክ የተጠቃሚዎችን ስልክቁጥር ለምን አይነት ጥቅሞች ሲያውለው ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ለማስታወቂያ እና በጓደኛ ጥቆማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጨረቃ ላይ መውጣት ጨረቃ ላይ መውጣት የምንለው ማናቸውም ሰው ሰራሽ መንኮራኩሮች ጨረቃ ገጽ ላይ ሲያርፉ ያለውን ክንውን ነው። ይህ እንግዲህ ሰውንም ሆነ ያለሰው የተደረጉ በጨረቃ የማረፍ ክንውኖችን ይጠቀላላል። ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ሰራሽ የሆነ ነገር ጨረቃ ላይ ያረፈው በመስከረም 13፣ 1959 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውም የሶቭዬት ህብረት ሉና 2 ሚሲዮን ነበር። ለመጀመሪያ ጊዜ የሰው ልጅ እራሱ ጨረቃ ላይ የወጣው ሐምሌ 20፣ 1969 እ.ኤ.አ. ሲሆን ይኸውን በአሜሪካው የአፖሎ 11 ሚሲዮን መንኮራኩር ነበር። ባጠቃላይ 24 አሜሪካውያን ወደጨረቃ ተጉዘዋል፣ 12ቱ የጨረቃን ምድር በእግራቸው ረግጠዋል። በዚህ ወቅት ሶቪየት ህብረትም የራሷን ጠፈርተኞች ለመላክ ሞክራለች። ለዚህ እንዲረዳት ጨረቃ ላይ አራፊ LK የተሰኘ መንኮራኩር ሰራች፣ ሆኖም ግን ይህን መንኮራኩር ወደ ጨረቃ የሚወስድ ከባድ ሃይል ያለው ሮኬት ከአሜሪካ ቀድማ መስራት ስላልቻለች ተቀደመች። ዩጂን ከርናን የጨረቃን ምድር የረገጠው የመጨረሻው ሰው ነው። \n \nጥያቄ: የሰው ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃ ላይ የወጣው በምን መንኮራኩር ተጠቅሞ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በአሜሪካው የአፖሎ 11 ሚሲዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: 801.\tበዩጋንዳ በማን መሪ ጊዜ ነበር ከ300,000 በላይ ሰዎች ያለቁት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኢዲ አሚን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: የስዋሂሊ ቋንቋ የአፍ መፍቻቸው የሆኑ ምን ያህል ሕዝቦች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፭ ፡ ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ካፒቴን ስፒዲ ልዑል አለማየሁን እንዲጠብቅ የመደበው ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ጀነራል ናፔር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየባሕል ጥናት የባህል ጥናት፣ ሥነ ኅብረተሠብ ወይን ሥነ ማኅበረሰብ ሌላ ስሙ ሶሲዮሎጂ የሰው ልጆች በቡድንና በተናጥል ያላቸውን ባሕል፣ ጠባይና አደረጃጀት የሚያጠና ክፍል ነው። በዚህም ውስጥ አንትሮፖሎጂ ወይም የሰው ልጅ ጥናት (ሥነ ሰብእ) አለ። ሶሲዮሎጂ የሚለው ቃል በፈረንሳያዊው ጸሐፊ ኤማኑወል-ዦሰፍ ሲዬ በ1772 ዓ.ም. ከሮማይስጥ ሶኪውስ (ባልንጀራ፣ ጓደኛ) እና ከግሪክ ሎጎስ (ቃል ወይም ጥናት) በማጋጠም ተፈጠረ። የፈረንሳይ ፈላስፋ ኦጉስት ኮምፕት ከ1830 ዓ.ም. ጀምሮ በሰፊ ጠቀመው። የኅብረተሰብ ጥናት ሲሆን የኅብረተሰብ ጽንሰ ሀሣብ በሮማይስጥ ትርጉም ሶኪየታስ ወይም የባልንጀሮች ግንኙነት ያመልከታል። \n \nጥያቄ: ሶሲዮሎጂ የሚለው ቃል መቼ ተፈጠረ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1772 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል የሚያስችል መሳሪያ ፈጠራ ባለቤት የሆነው ቦሪስ ሮዚንግ የየት ሀገር ዜጋ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የራሻ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ በየት መጽሐፍትን ተረጎሙ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በቤተ ቀጢን (አክሱም) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nተቀማጭነቱ ካሊፎርኒያ ውስጥ ያደረገው ኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የተባለው የሶፍትዌር አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ፡፡ የኢ ኦ ኤን ኩባንያ መስራች ዳን ለጀርስካር ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት መኖሩን ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሂሩት በበኩላቸው የቴክኖሎጂውን አስፈላጊነትና ወቅታዊነትን በመገንዘብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኩባንያው ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የሶፍትዌር አምራች ድርጅት ማዕከሉን ለመክፈት የፈለገው በየት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: የጂቡቲ መንግሥት የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ቶታልን የገዛው የምን ሀገር ኩባንያ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኖክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቢል ክሊንተን ዊልያም ጄፈርሰን «ቢል» ክሊንተን (William Jefferson Bill Clinton) (የትውልድ ስም፦ ዊልያም ጄፈርስን ብላይዝ ፬ኛ፣ እንግሊዘኛ፡ William Jefferson Blythe IV) በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) በሆፕ አርካንሳው የተወለዱ ሲሆን ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ድረስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕሬዝዳንት ከመሆናቸዉ በፊት አምስት ጊዜ የአርካንሳው ስቴት አስተዳዳሪ ነበሩ። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን የአሜሪካ ፕሬዝደንት ሆነው የሰሩት ከመቼ እስከ መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየሚጠቀሙባቸው ኮምፒውተሮች ከአገልግሎት ጋር ተያይዞ ለተለያዩ ውስጣዊና ውጫዊ ጥቃቶች የመጋለጥ እድላቸው ሰፊ ነው። የኮምፒውተሮችን አጠቃላይ ባህሪ መረዳት፣ በየጊዜው ማሻሻልና መቀየር ያለባቸውን ስርዓቶች በማወቅ መረጃዎች እንዳይጠፉ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል። ከዚህ አንጻር የኮምፒውተሮችን ደህንነት ለመጠበቅ .ጠቃሚ ፋይሎችን መጠባበቂያ ወይም ባክአፕ መያዝ . የኮምፒውተር ፕሮግራሞች ሥርዓት ለደህንነት ሥጋት እንዳይጋለጡ የኦፕሬቲንግ ሲስተም ክፍተት መሙላት . ፀረ ቫይረስ ሶፍትዌሮችን መጠቀም፣ በየጊዜው መተግበሪያዎችን ማዘመን . ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ አጠቃላይ የኮምፒውተር ስርዓት ስካን ማድረግ .አጥፊ ሶፍትዌሮችን የሚከላከሉ ፀረ አጥፊ ሶፍትዌሮችን መጠቀም እና ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ስካን ማድረግ እንዲሁም . የተመጠነ የፋይል አስተዳደር መተግበር እና ዲስኮችን በየጊዜው ማፅዳት መረጃው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ነው \n \nጥያቄ: በኮምፒዩተራችን ውስጥ ያሉ መረጃዎች እንዳይጠፉብን በሌላ የፋይል ማጠራቀሚያ መያዝ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ መጠባበቂያ ወይም ባክአፕ መያዝ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: በዩጋንዳ ዋናው የንግድ ቋንቋቸው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኪስዋሂሊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአረማይክ አረማይክ ወይም አራማይስጥ፣ የሶርያ ቋንቋ ከሴማዊ ቋንቋዎች አንዱ ሲሆን በመካከለኛ ምሥራቅ ከጥንት ጀምሮ ታውቋል። መጀመርያ የአረማይክ ጽሑፎች ከ1000 ዓክልበ. ግድም በፊንቄ አልፋቤት ነበሩ፤ ይህም የአራም ሕዝብ የተናገሩት ጥንታዊ አራማይስጥ ነበር። በአንድ አስተሳሰብ ቋንቋቸው ከ1100 ዓክልበ. አስቀድሞ ሑርኛ ይሆን ነበር፤ የአሦርም መንግሥት ከገዙአቸው በኋላ እንደ አካድኛ ሴማዊ ሆነ። ከ800 ዓክልበ. አካባቢ በኋላ የራሱ አረማይክ አልፋቤት ከፊንቄ አልፋቤት ተለማ። በ740 ዓክልበ. የአሦር ንጉሥ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር አረማይስጥ ከአሦርኛ (አካድኛ) ጋር ይፋዊና መደበኛ ቋንቋ አደረገው። ከዚያ ጀምሮ የአረማይስጥ ጥቅም እየተስፋፋ የአካድኛ ጥቅም በየጊዜ ይቀነስ ነበር። ከአሦር ውድቀት (617 ዓክልበ.) በኋላ በባቢሎኒያ መንግሥት፣ ከባቢሎኒያም ውድቀት (547 ዓክልበ.) በኋላ በፋርስ አሓይመኒድ መንግሥት ውስጥ፣ አረማይክ መደበኛና ይፋዊ ቋንቋ ተደረገ፣ ስለዚህ ጥቅሙ በሰፊ ከግብጽ እስከ ባክትሪያ ድረስ ይዘረጋ ነበር። በዕብራይስጥ መጽሐፍ ቅዱስ የተገኘው አራማይክ በተለይ በትንቢተ ዳንኤል ከዚሁ ዘመን ነው። \n \nጥያቄ: አረማይክ ከምን ቋንቋ ቤተሰብ ይመደባል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከሴማዊ ቋንቋዎች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፋሽስት ቅዲስቲቱዋን ኢትዮጵያን ለማዋረድ ለመዝረፍና ለመግዛት ለሁለተኛ ጊዜ ከፍተኛ ዝግጅቱን አጠናቆ በ1928 ዓም 300, 000 ሰራዊት 160 ቦንብ ጣይ አውሮፕላኖች 450 ታንኮች 2000 የመጉዋጉዋዣ መኪናዎችን በማሰማራት ድንበር አልፎ ጦርነት በመክፈት ከገጠር እስከ ከተማ ህዝቡን ያለ እርህራሄ ጨፈጨፈ። በዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ላይ የመጀመሪያውን ህይወት ያለዉን ነገር ሁሉ የሚያጠፋውን “ማስተርድ ጋዝ” የሚባል ኬሚካል መሳሪያ በመጠቀም ታሪክ ይቅር የማይለው ወንጀል ፈጸመ። በዚያን ክፉ ቀን የነጻነትና የሀገር ትርጉም የገባቸው የቁርጥ ቀን ልጆች በየአካባቢያቸው ፋኖዎችን በመምራት የእብሪተኛዉን የፋሽ ስት ጦር መግቢያ መዉጫ በማሳጣት ኢትዮጵያ ዉስጥ በሰላም መኖር እንደማይችል ተስፋ አስቆርጠዉታል። ከነዚህ ነበልባል የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ ልጆች መካከል ጠላትን በተከታታይ ዝርክርኩን አዉጥተው ከደቡብ ያሳደዱትና በመጨረሻው ዉጊያ ላይ ኢትዮጵያዊ በሚመስሉ የትግሬ ስርጎ ገብ ባንዶች ቆሰለው የተያዙትና በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉት ዉዱ የኢትዮጵያ የክፉ ቀን ልጅ ራስ ደስታ ዳምጠው ነበሩ። ራስ ደስታ ዳምጠዉን ያስያዛቸው የባንዳ ጦር መሪ ደግሞ የትግሬው ተክሉ መሸሻ የሚባል የጣሊያን ሎሌ ሲሆን የስብሃት ነጋ አጎት የናቱ ታላቅ ወንድም መሆኑ ተረጋግጦአል ተክሉ መሸሻ በጣሊያን ደጃዝማችነት ተሰጥቶት በደቡብ ኢትዮጵያ የኢጣልያ ባንዳ ጦር አዛዥ ሆኖ በአካባቢው ኢትዮጵያ ጦር አዛዥ የነበሩት ራስ ደስታ ዳምጠው ከበርካታ አስደናቂ ጀብዱ በሁዋላ ቆስለው በጉራጌ አካባቢ መስቃ ከተባለው ሥፍራ ተኝተው በስቃይ ላይ እያሉ ተክሉ የስለላ መረቡን ዘርግቶ እግር በግር ተከታትሎ በመያዝ ከግንድ ጋር አስሮ በጭካኔ ደብድቦ ከገደላቸው በኋላ ራሳቸውን ረግጦ በመቆም ፎተግራፍ በመነሳት ለጣልያኑ ጌታው ግዳይ ካቀረቡት እርካሽ የትግሬ ከሃዲዎች አን ዱ ነበር። የፋሽስት ጣሊያን ጦር ኢትዮጵያን ወሮ መናገሻ ከተማዋን አዲስ አበባን ለመያዝ ሲገሰግስ ጀምሮ ሶስቱ ቆራጥ የኢትዮጵያ ሌጆች (የሸንቁጥ) ልጆች አበበ ሸንቁጥ ተሾመ ሸንቁጥና ጥላሁን ሸንቁጥ በመርሃቤቴ በጅሩና በዠማ ወንዝ አካባቢ በመንቀሳቀስ “ዱሩ ቤቴ” በማለት ብዙ የአካባቢውን ጀግኖች አስከትለው የጣሊያንን ሀይል በመመከትና ከአገር በማባረር ከፍተኛ ገድል ፈጽመዋል። \n \nጥያቄ: በሰርጎ ገቦች የተገደሉት ኢትዮጵያዊ ጀግና ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ራስ ደስታ ዳምጠው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nግሪክ ግሪክ ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋ አንድ ትንሽ አገር ነው። ከምሥራቅ ወደ ትንሽ እስያ፤ ከምዕራብ ወደ ኢጣሊያ አገር ከሁለቱም ወገን ርቀቱ ትክክል ነው። ግሪክ በሰሜን ወገን ከመቄዶንያ ይዋሰናል። ግሪክ ኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው። በደቡብና በምሥራቅ ወገን አያሌ ደሴቶች አሉ። ከእነርሱም በአያሌዎቹ መንደሮችና ከተሞች ተሠርተውባቸዋል። አንዱ አንቲፖሮስ ይባላል። በእዚህም ስፍራ ያለው ታላቅ ያጌጠ ዋሻ የታወቀ ስመ ጥሩ ነው። እኩሌቶቹም የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እየተወረወሩ የወጡ ይመስላሉ። እኩሌቶቹም ከጥንት ጀምረው ይታዩ የነበሩት ያሉበት አይታወቅም ጠፍተዋል። ይህ እንግዳ ነገር እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ከባሕር በታች የተነሳው እሳተ ገሞራ ነው። በደቡብ ግሪክ ወገን ባሉት ደሴቶች አየሩ በአሜሪካ እንዳለው እንደ ቨርጂኒያ ግዛት አየር ቀላል ነው። በዚህ አገር ብዙ አይነት ፍሬ ሁሉ ሞልቶዋል። በሰሜን በኩል ደግሞ አየሩ ቅዝቃዜ ያለበት ነው። በየጠረፉ የመርከብ መቋሚያዎች ወደቦች ይገኛሉ። ብዙዎቹ የአገሩ ሰዎችም መርከበኞች ናቸው። በደኑም ፓይን (ጥድ) የተባለው ጠንካራ ዛፍ ይገኛል። በላይኛው አውራጃ ኦክ የተባለው ዛፍ ይገኛል። ወደታች ባለው ክፍልም ቸስትነትና ዋልነት የሚባሉት ዕንጨቶች ይገኛሉ። በዚህ ስፍራ የሚገኘው ዋናው ነገር ደረቅ ፍራፍሬ፣ ዘቢብ፣ ጥጥ፣ ሐር ጠጉር፣ ሩዝ፣ ትንባሆና በቆሎ ነው። የእጅ ሥራ ጥቂት ነው። በቤት የተለመደ ሥራ እንደ ጥጥ እንደ ጠጉር እንደ ሐር የመሰለ ነገር ነው። ቀለም ማግባት ወይም መቀባት በጣም የተለመደ ከሆነ ብዙ ጊዜው ሆነው። ከዛፎች ፍሬ ዋነኛው ወይራ ሲሆን በብዛት ይተከላል። ወይን፣ በኽረ? ሎሚ፣ በለስ፣ አልሞንድ (ለውዝ)፣ ተምር፣ ሴትሮን፣ ፓሜግራኔት (ሮማን)፣ ኩሬንትም ይበቅላሉ። \n \nጥያቄ: በኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋች ሀገር ማን ትባላለች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ግሪክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየገቢዎች ሚኒስቴር ባለፉት ሰባት ወራት 169 ቢሊየን 501 ሚሊየን 789 ሺህ 893 ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ አፈፃጸሙ ከዕቅድም ሆነ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ የታየበት መሆኑን ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌው አስታውቀዋል፡፡ ሚኒስቴሩ 169 ቢሊየን ብር 408 ሚሊየን 889 ሺህ 4 ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የእቅዱን 100 ነጥብ 5 በመቶ ማሳካት መቻሉንም ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የገቢዎች ሚኒስቴር ሚንስትር ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አቶ ላቀ አያሌው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቴምፕላርስ ቴምፕላር ወይም በሙሉ ስማቸው የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች የሚባሉት በጣም ታላቅ እና ሃይለኛ ከነበሩት ክርስቲያናዊ ወታደራዊ ስርአቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው። ይህ ስርዓት በ1088 ዓ.ም. ከተካሄደው አንደኛው የመስቀል ጦርነት በኋላ ማለትም በ1110 ዓ.ም. አዲስ የተቋቋመውን የእየሩሳሌም መንግስት ከእስላሞች ለመከላከልና ወደ ከአውሮፓ ወደ እየሩሳሌም የሚጎርፉትን ተሳላሚዎች ደህንነት ለመጠበቅ የተመሰረተ ነው። ቴምፕላሮች የተዋቀሩት በገዳማዊ ስርዓት ሲሆን ይኸውም የሲሰተርሲያን ስርዓት መስራች የነበረው የክላርቮው በርናርድ በዘረጋላቸው ህግጋት መሰረት ነው። ቴምፕላሮች ከብዙ መሳፍንት ጋር ግንኙነት ስለነበራቸው እና ጳጳሱም እነሱ ከሚቆጣጠሩዓቸው ቦታዎች ሁሉ ግብርና አስራት እንዲሰበስቡ ስለፈቀደላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝነኛና ሃይለኛ ለመሆን ችለዋል። ቴምፕላሮቹ አራት ዋና ክፍሎች የነበሩአቸው ሲሆን እነዚሁም ዋነኞቹ ወታደሮች ወይም ናይትስ የሚባሉት ሙሉ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ከዝቅተኛ የህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡት ወይም ሰርጀንትስ በመባል የሚታወቁት፤ መለስተኛ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ገበሬዎች ዋነኛው ስራቸው የስርዓቱን ንብረት ማስተዳደር የነበረ፤ እንዲሁም ካህናት ስራቸው የስርዓቱን መንፈሳዊ ህይወት መከታተል የነበረ ናቸው። \n \nጥያቄ: ቴምፕላሮች የገዳማዊ ኑሮዋቸውን ማን በደነገገው ሕግ መሰረት ነው የሚመሩት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ክላርቮው በርናርድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፯ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፴፯ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፪ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፱ ቀናት፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፰ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፭፻ ዓ/ም - በስመ መንግሥት አንበሳ በፀር ይባሉ የነበሩት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አርፈው የ፲፪ ዓመት ልጃቸው ዓፄ ልብነ ድንግል ወናግሰገድ ተብለው ነገሡ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በኩባ ደሴት በእስፓኝ እና በአሜሪካ መኻል የነበረው የማስተዳደር ፍልሚያ ትግል አከተመ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ከፈረንሳይ ቅኝ ተገዢነት ነፃነቷን አወጀች። ዴቪድ ዳኮ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፭፻ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ናዖድ በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት አፄ ናኦድ በስንት ዓመተ ምህረት አረፉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፭፻ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዋሽ ብሔራዊ የመዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል በ፲፱፻፶፰ ዓ/ም የተመሠረተ ክልል ሲሆን ከአዲስ አበባ በስተ ምሥራቅ አቅጣጫ በ፪መቶ ፲፩ ኪሎሜትር ርቀት ፤ በአፋርና በኦሮሚያ አዋሳኝ ክልሎች ሥር ይገኛል። ይህ ክልል ሲመሠረት በ ፱፻፮ ካሬ ኪሎሜትር የቆዳ ስፋት (ቦልቶን ፲፱፻፷፰) የነበረው ቢሆንም፤ ባሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ማስረጃ እንዳስቀመጠው የክልሉ የቆዳ ስፋት ፯መቶ ፶፮ ካሬ ኪሎ-ሜትር ነው። የክልሉ ደቡባዊ ድንበር የአዋሽ ወንዝ ሲሆን፣ የተሠየመውም በዚሁ ታላቅ ወንዝ ስም ነው። ክልሉ የብዙ ዓይነት አራዊት እና አዕዋፍ መጠለያ ከመሆኑም ባሻገር ፍል-ውሓ እና የፋንታሌ ተራራ ይገኙበታል። የአገሪቱ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥልጣን ሲመሠረት ለንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በአማካሪነት የተመደበው እንግሊዛዊ ባቀረበው ኃሣብ መሠረት የመጀመሪያው ብሔራዊ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥጣን ከተመሠረተ በኋላ የቅድሚያ ሥራ የተደረገው፤ በታቀዱት ክልሎች የሚገኙትን የአገሪቱን የዱር አራዊት ኃብት መጠን ማረጋገጥ ነበር። ለዚህም ሥራ ከብሪታኒያ ተመልምሎ የተቀጠረው ባለ-ሙያ እንግሊዛዊው የሥነ-ሕይወት ባለሙያ ሜልቪን ቦልቶን ነበር። የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የበርካታ የዱር አራዊት፤ አዕዋፋት እና የውሐ አራዊት መኖሪያ ነው። በደቡብ አዋሳኙ በሆነው የአዋሽ ወንዝ አዞ እና ጉማሬ ሲገኝበት፤ በሰሜን ክፍሉ ደግሞ ጦጣና ዝንጀሮ፤ እንዲሁም ጅብ እና አጋዘን ይገኙበታል። በክልሉ ከሚገኙት የዱር አራዊት በከፊሉ፦ ጉሬዛ፤ ተራ ዝንጀሮ፤ ነጭ ዝንጀሮ፤ ጦጣ፤ ሳላ፤ የሜዳ ፍየል፤ ሚዳቋ፤ ትልቁ የቆላ አጋዘን ፤ አምባራይሌ፤ ከርከሮ፤ ቆርኪ በብዛት የሚገኙ ሲሆን አንበሣ፤ ነብር፤ ጀርባ-ጥቁር እና ተራ ቀበሮ፤ዳልጋ አንበሣ፤ አነር እና የዱር ድመት ደግም አልፎ-አልፎ ይታያሉ። ባለፉት አሥር ዓመታት ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ምዝገባ እንደተረጋገጠው፣ በክልሉ ውስጥ ፬መቶ ፷፪ ዓይነት የወፍ ዝርያዎች ተመዝግበዋል። ከነዚህም መኻል ስድስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ ናቸው። እነዚህም መንቆረ-ጥቁር ጋርደም፤ ግንደ-ቆርቁር፤ ክንፈ-ነጭ የገደል-ቻት፤ ጅራተ-ረጅም ወማይ፤ ቁራ እና ጋጋኖ ናቸው። \n \nጥያቄ: በአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የሚገኘው ተራራ ስም ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፋንታሌ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማሊ ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በቆዳ ስፋቷ ስንተኛ ናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሁለተኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሚነገሩ ቋንቋዎች በምን በምን መደብ ይከፈላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nፀሐይ ፀሓይ በምድር ሥርዐተ-ፈለክ መኻል ያለች ኮከብ ናት። ምድር ሞላላ ቀለበት በሚመስል የዑደት ምሕዋር እየተጓዘች ፀሓይን ትዞራታለች። ሌሎች ሰማያዊ አካላትም፣ ፈለኮች፣ ፈለክ-አስተኔዎች፣ ጅራታም ከዋክብት እና ኅዋዊ ብናኞች በፀሓይ ዙሪያ ይዞራሉ። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገውን አንድ ዙር ጉዞ ለመጨረስ አንድ ዓመት ይፈጅባታል፤ ይህን ጉዞ ስታደርግም በገዛ ራሷ ዘንጎ ወይም ምሽዋር ዙሪያ እየሾረች ነው። ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ወቅቶች በዓመታዊ ዑደት እንዲለዋወጡ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ሲኾን፣ በራሷ ዘንጎ ዙሪያ የምታደርገው ሹረት ደግሞ በዕለታዊ ዑደት መዓልት (ቀን) እና ሌሊት ለሚያደርጉት መፈራረቅ ምክንያት ነው። ፀሓይ ለሥርዐተ-ፈለካችን በጣም ብሩህ የኾነ ብርሃን ትሰጣለች። ያለ ፀሓይ ብርሃን ሙቀትም ኾነ ሕይወት በምድር አይኖርም ነበር። ለምሳሌ አረንጓዴ ዕፅዋት ያለ ፀሓይ ብርሃን ሊኖሩ አይችሉም፤ ለህልውናቸው የሚያስፈልጓቸውን ካርቦን ዳይኦክሳይድ እና አልሚ ምግቦች ለማስተጻመር የሚችሉት በፀሓይ ብርሃን ብቻ ነውና። ከምድር ይልቅ ለፀሓይ ይበልጥ ቅርብ የኾኑ ፈለኮች ለከፍተኛ ጨረር እና ግለት የተጋለጡ በመኾናቸው በምድር ላይ ላለው ዐይነት ሕይወት ተስማሚ አይደሉም። ከምድር ጋር ሲነጻጸር ከፀሓይ በጣም ርቀው ያሉ ፈለኮችም ለሕይወት መኖር ምቹ ኹኔታዎች የሏቸውም፤ በቂ ብርሃን እና ሙቀት ካለማግኘታቸው የተነሣ። \n \nጥያቄ: የወቅቶች መፈራረቅ ምክንያቱ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ምድር በፀሓይ ዙሪያ የምታደርገው ዙረት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በቡሩንዲ በ፲፱፻፸፱ ዓ/ም ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ በመፈንቅለ መንግሥት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከስልጣን በማስወገድ የሀገሪቱ ምን ሆነ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፕሬዚደንት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nደስታ ተክለወልድ አለቃ ደስታ ተክለወልድ የኢትዮጵያ ዕውቅ የቤተክርስቲያን ሊቅ፣ የመዝገበ ቃላት አዘጋጅና ደራሲ ነበሩ። ሐምሌ 19 ቀን 1893 ዓ.ም. በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ የተወለዱት አለቃ ደስታ፣ ያረፉት ጳጉሜን 2 ቀን 1977 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን ከአጥቢያቸው ጀምሮ እስከ ደብረ ሊባኖስ የቅኔና የዜማ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ቀለምን ፈጥኖ በመቀበልና በማስተዋል ችሎታቸው የተመሰከረላቸው አለቃ ደስታ የመጻሕፍት አንድምታ ትርጓሜን አደላድለዋል፡፡ በብርሃንና ሰላም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማተሚያ ቤት ቅዱሳት መጻሕፍትን በማረምና በማስተካከል ከ1916 እስከ 1920 ዓ.ም. ድረስ የሠሩ ሲሆን፣ በእርሳቸው አረጋጋጭነት በርካታ መጸሕፍት ለሕትመት በቅተዋል፡፡ በሀገረ ጀርመን በታተመው ኢንሳይክሎፔዲያ ኢትዮፒካ እንደተዘገበው፣ ወደ ድሬዳዋ በመሄድ በአልዓዛር ማተሚያ ቤት ሥራቸውን የቀጠሉበት አጋጣሚ የተፈጠረው ከሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መተዋወቃቸው ነበር፡፡ ከ30 ዓመት በፊት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምን እየሠሩ ዐምድ አጋጣሚውን እንዲህ ያስታውሰዋል፡፡ \n \nጥያቄ: አለቃ ደስታ የት ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ላይ ወግዳ ጎሽ ውኃ ቀበሌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር የት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አድዋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: በፕሬዝደንት ትራምፕ ትእዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ የተገደሉት የኢራኑ ጄኔራል ማን ነበሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል በሕዝብ ብዛት ትልቋ ከተማ ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዳካር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: የቢል ክሊንተን ሚስት ማናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሂለሪ ሮድሃምን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየመጀመሪያው የዓለም ጦርነት የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት በአውሮፓ አገሮች መኻል ከ ፲፱፻፮ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፲፩ ዓ/ም መግቢያ፣ ለአራት ዓመታት የተካሄደ ጦርነት ነው። ይኼ ግጭት የዘመኑ ኃያላን አገራት በሁለት ተቃራኒ ወገን ተሰልፈው ያካሄዱት ግብግብ ሲሆን እስከ ሰባ ሚሊዮን ታጣቂዎች የተካፈሉበትና እስከ አስራ አምስት ሚሊዮን አውሮፓውያን ሕይወታቸውን ያጡበት ትልቅ ጦርነት ነው። ለጦርነቱ ቅስቀሳ ብዙ ምክንያቶች በታሪክ ምሑራን ይጠቀሳሉ። ዓቢይ ከሚባሉት ነገሮች ግን የወቅቱ ኃያላን መንግሥታት የውጭ ጉዳይ ተልዕኮዎች ሲሆኑ የክብሪቱ መጫሪያ ምክንያት ግን የ አውስትሪያ እና ሁንጋሪያው ዘውድ አልጋወራሽ፣ አውስትሪያዊው አርች ዱክ ፍራንዝ ፈርዲናንድ በዩጎዝላቪያዊ ነፍሰ ገዳይ እጅ ሰኔ ፳፩ ቀን ፲፱፻፮ ዓ/ም መገደል ነው። የሳቸውን መገደል ምክንያት በማድረግ የ አውስትሪያ እና ሁንጋሪያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ለ ሰርቢያ ንጉዛት ሊያሟሉት የማይችሉትን፣ አስር ነጥብ ያዘለ የእላፊ ገደብ ማስጠንቀቂያ ይሰጡና ገደቡ ሲያልፍ ቅድሚያውን እንደወጠኑት በሰርቢያ ላይ የጦር አዋጅ አወጁ። ይሄም የታቀደ ትንኮሳ ከአስር ዓመታት በፊት ተመሥርተው የነበሩትን ብዙ የትብብር ውሎችን የሚያንቀሳቅስ ሁኔታ ስለነበረ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ሁሉንም ኃያላን መንግሥታት ጦርነቱ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ አስገደዳቸው። እያንዳንዳቸው ደግሞ በዓለም ዙሪያ የሚያስተዳድሯቸው ቅኝ ግዛቶች ስለነበሯቸው እነዚህንም ቅኝ ግዛቶች በዚሁ ግብግብ ተሳታፊ አደረጋቸው። የአለማኛ ሠራዊት በ፲፱፻፻፲ ዓ/ም የምዕራብ የጦርነቱን ግንባር ማጥቃት ከጀመሩ በኋላ የአሜሪካ ሠራዊት ከአጋሮቹ ጋር ሲሰለፍ፣ የምዕራብ አገሮች ቡድን አለማኞቹን በማጥቃት እያቸነፏቸው መጡ። መጨረሻ ላይ ተሸናፊው የአለማኛ ሠራዊት መሸነፉን አምኖ ኅዳር ፩ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ/ም የእጅ መስጫ ውል ሲፈርም፤ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፮ ዓ/ም የተለኮሰው ጦርነት አከተመ። አብሮትም የአውስትሪያ እና ሁንጋሪያ ግዛት፣ የኦቶማን ግዛት ሲጠፉ የጀርመን እና የሩሲያ ኃያልነት በፖለቲካም ሆነ በጉልበት ተደምስሰው የአራቱንም ቅኝ ግዛቶች አሸናፊዎቹ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ተከፋፈሏቸው። የቀድሞ ኃያላን መንግሥታትትን ውድመት ያስከተለ ክስተት ከመሆኑም ሌላ፤ በመካከለኛ አውሮፓ የብዙ ትናንሽ ሉዓላዊ አገሮችን መወለድ፤ የዓለም መንግሥታት ማኅበርን መቋቋሚያ መንስዔ፤ ከሁሉም በላይ ግን በአውሮፓ አኅጉር የብሔራዊነትን መንፈስ የቀሰቀሰና የጀርመን ሽንፈትን ያረጋገጠው የቬርሳይ ውል በጀርመኖች ላይ ያስከተለው የጭቆና ስሜት አገራችን ኢትዮጵያ በ፲፱፻፳፰ ዓ/ም በፋሽስት ኢጣልያ በግፍ ስትወረር የተለኮሰውን የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መነሻ ምክንያት መሆኑ ነው። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ከመቼ እስከ መቼ ተካሄደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ ፲፱፻፮ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፲፩ ዓ/ም መግቢያ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን የአውሮፓ ሀገሮችን የጎበኙት የማን ተወካይ ሆነው ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሆ ቺ ሚን ሆ ቺ ሚን ከ1890-1969 እ.ኤ.አ. የኖረ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሥራችና መሪ ነበር። ሆ ቺ ሚን ከወጣትነት ጊዜው ጀምሮ ለአብዮታዊ ተግባራት የቆመ ነበር። ሆ ቺ ሚን በሥራ ምክንያት ፈረንሳይ ውስጥ በነበረበት ወቅት የካፒታሊስት ሥርዓት ምን ያህል ሠርቶአድሩን ሕዝብ ለሥቃይና ለመከራ እንደዳረገውና የዓለም ወዛደሮች በቀለም በቋንቋና በባህል ቢለያዩም ብሶታቸው አንድ መሆኑን በቅርብ ተገነዘበ። በአፍሪካና በእስያ የኢምፔሪያሊስቶች መምጣት ምን ያህል ሥቃይና ውርደት በእነዚህ ሕዝቦች ላይ እንዳደረሰ ተረዳ። በዚህም ምክንያት ሆ ቺ ሚን የቬትናም ሕዝብ ጠላት የፈረንሳይ ኢምፔሪያሊዝም እንጂ የፈረንሳይ መላው ሕዝብ አለመሆኑን ደጋግሞ ገልጿል። ሆ ቺ ሚን በ1917 እ.ኤ.አ. በፈረንሳይ ወዝአደሮች ትግል ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊ በመሆን የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲ አባል ሆነ። ከዚህም በላይ በፈረንሳይ የቬትናም አርበኞችን ማኅበር በማቋቋም በፈረንሳይ ይኖሩ የነበሩትን ቬትናማውያን በማንቃትና በማስተማር ለሀገራቸው ነፃነትና ክብር እንዲታገሉ ያነሣሣ ነበር። የጥቅምቱ የሩሲያ አብዮት ለአያሌ ዓመታት በዓለም ሰፍኖ የነበረውን የኢምፔሪያሊዝም ብቸኛ የበላይነት ሰባብሮ አዲስ ዘመን በማብሰሩ ሆ ቺ ሚን የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ የቦልሼቪኮችን ፈለግ መከተል እንዳለበት አመነ። በሆ ቺ ሚን አስተሳሰብ የቬትናም ብቻ ሳይሆን የሌሎች ቅኝ ተገዥ የሆኑ ሀገሮች ነፃነት የሚገኘው የወዝአደሩን የአብዮት ጎዳና በመከተል ብቻ እንደሆነ አጥብቆ ያምን ነበር። የነዚህ ሀገሮች ብሔራዊ ነፃነት ከማኅበራዊ ነፃነት ጋር መያያዙንና ይህም ነፃነት ከሶሻሊዝምና ከኮሚኒዝም ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን አስገንዝቧል። ሆ ቺ ሚን ከ1924 እስከ 1930 እ.ኤ.አ. በቻይናና በቬትናም በመዘዋወር ለዚህ ውስብስብ ትግል ግንባር ቀደም አመራር ሊሰጥ የሚችለውን ማርክሳዊ ሌኒናዊ ፓርቲ ለማቋቋም ከፍተኛ ትግል አደረገ። በመጀመሪያም የቬትናም አብዮታዊ ወጣቶች ማኅበር የተባለውን በማቋቋም «ወጣት» በተባለው ጋዜጣ ወጣቱን ለትግል ቀሰቀሰ። በዚህ ዓይነት ከብዙ ጥረትና ትግል በኋላም በ1930 እ.ኤ.አ. የኢንዶቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን (ኋላ የቬትናም ሠራተኞች ፓርቲ፤ ዛሬ ደግሞ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ) መሠረተ። በ1935 እ.ኤ.አ. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደው የኮሚኒስቶች ስብሰባ አንድ ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት የሆነ ዲሞክራሲያዊ ግንባር እንዲቋቋም በወሰነው መሠረት ሆ ቺ ሚን ቬትሚን የተሰኘውን ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት ግንባር በማቋቋም መላውን ሕዝብ በትግሉ ለማሳተፍ ችሏል። ዲየን ቢየን ፉ በተባለው ታሪካዊ ስፍራ የቬትናም አርበኞች የፈረንሳይን ጦር በማሸነፋቸው ፈረንሳይ በጀኔቩ ስምምነት መሠረት የቬትናምን አንድነት በማወቅ የሰላም ውል ፈረመች። ነገር ግን ከ1955 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም በፈረንሳይ እግር በመተካት የደቡቡን ክፍል ለመቁረስ የጦር ሰፈር በመሥራትና በውስጥ አርበኞች በመጠቀም ጦርነት ከፈተ። ነገር ግን አሜሪካ ከግማሽ ሚሊዮን ወታደሮች በላይና በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ቢያፈስም ቬትናምን ሊያሸንፍ አልቻለም። \n \nጥያቄ: በቬትናም በህዝቡ ትግል ፈረንሳዮች ሲወጡ በእነርሱ እግር የመጡት እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበመረጃ መንታፊዎች የተያዘባቸዉን መረጃ ለማስለቀቀ የራንስም ክፍያ ከከፈሉ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መካከል 80 ከመቶ የሚሆኑት ድርጅቶች ለዳግም ጥቃት መጋለጣቸዉን የሳይበርሰን ጥናት ጠቁሟል ሳይበርሰን የተሰኘው የሳይበር ደህንነት ምርት አቅራቢ የሆነዉ ተቋም ባካሄደዉ አዲስ ጥናት እንዳመለከተዉ ከሆነ ተቋማቱ ብዙውን ጊዜ በተመሳሳይ የመረጃ መንታፊዎች ጥቃት እንደሚሰነዘርባቸዉ ነዉ ያመለከተዉ። ‘የራንሰም’ ክፍያ መክፈል የቅጅ ወንጀሎችን ከማበረታታት በተጨማሪ እነዚህ ኩባንያዎች በፍጥነት ወደ ተለመደው ንግድ ሥራቸዉ የመመለስ ዋስትና አለመኖሩን ነው ሳይበርሰን የገለጸው። ከዚህ ባሻገር ወደ ግማሽ የሚጠጉ የጥናቱ ተሳታፊዎች የሳይበር ጥቃት ሰለባ የሆኑ ድርጅቶች ክፍያውን ከፈጸሙ በኋላ መረጃዉን የማግኘት እድል ቢፈጠርም አንዳንዶቹ ወይም ሁሉም መረጃዎች እንደሚበላሹ ሳይበርሰን በጥናቱ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ ይህም በመረጃ መንታፊዎች የሚጠየቁ የመረጃ ማስለቀቂያ ክፍያዎችን መፈጸም ለተቋማቱ በትክክል መረጃዎቻቸዉን እንደሚያስገኝላቸው ዋስትና አለመሆኑን ማሳያ እንደሆነ እና የመረጃ መንታፊዎች በተጎጂው ድርጅት ላይ እንደገና ጥቃት ከመሰንዘር አያግዳቸውም ተብሏል። ከዚያ ይልቅ የራንሰም ክፍያ መፈጸም የመረጃ መንታፊዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እንዲያደርሱ የሚገፋፋ መሆኑን ሳይበርሰን መጠቆሙን ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ በመሆኑም የራንሰምዌር ጥቃቶችን ቀድሞ ለመለየትና ለመከላከል የቅድመ መከላከል ስትራቴጂ መኖር ኩባንያዎች ላይ የሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች እና በድርጅቶቹ ላይ ያንዣበቡ የራንሰምዌር ጥቃት እንቅስቃሴዎችን ቀድሞ ለመግታት ወሳኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: በመረጃ መንታፊዎች የተያዘባቸዉን መረጃ ለማስለቀቀ የራንስም ክፍያ የከፈሉት ስንት በመቶ የሚሆኑ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 80 ከመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ በ2006ዓ.ም የምን ማህበር መሰረተች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: አንበሳ በጥጋቡ ጊዜ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም ምን ያህል ርቀት ድረስ ማንኮራፋቱ ይሰማል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ የላከው በምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በራዲዮ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የኢያን ስሚዝ አመራር የሮዴዢያን ሪፕብሊክ በ1970 እ.ኤ.አ. ሲያውጅ እውቅና የሰጠው ብቸኛ ሀገር ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የደቡብ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል እስከ ስንት ዓመታቸው ከወላጆቻቸው ጋር ኖሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት ዓመተ ምህረት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 1768 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሂና ሂና ወይም እንሶስላ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው። የአንዳንድ አገር ሴቶች በዚህ ተክል ለቆዳቸው ምልክት ለማድረግ ቀለም ይሠራሉ። ሂና ረጅም ቊጥቋጦ ወይም ትንሽ ዛፍ ሊባል ይችላል፤ ከ1.8 እስከ 7.6 ሜትር ሊደርስ ይችላል። መላጣ፣ ብዙ ቅርንጫፍ ያለ፣ ትንንሽም ቅርንጫፎች እንደ እሾሕ ናቸው። ቅጠሎቹ በአገዳው ላይ ፊት ለፊት ይበቅላሉ፤ ቅጠሉም ዘንጋልባ፣ ሞልሟላ፣ የሥላጢን ቅርጽ ያላው (ረጅምና በመሃሉ ሰፊ)፣ የሾለ፣ እና በዘበናይ ገጽታ ረባዳ ስርወት አለው። የሂና አበባ አራት አበባቃፎች በ2 mm ቱቦ እና የተዘርጋ ግርብ 3mm አሉት። ያበባውም ቅጠል ሞላላ ነው፣ ነጭ ወይም ቀይ ወንዳካሎች በአበባቃፎች ቱቦ ጫፍ ላይ በጥንዶች ይገኛሉ። እንቁልጢው ባለ አራት ህዋስ፣ በ5 mm ዘለግ ይላል። የሂና ፍሬ ትንንሽ ቡናማ ቀለህሞች፣ 4-8 mm ባጋማሽ፣ 32-49 ዘሮች በየፍሬው፣ በአራት ኢመደበኛ ስንጥቆች ይከፈታል። የሂና ተክል ለስሜን አፍሪካ፣ ምዕራብና ደቡብ እስያ፣ እና ስሜን አውስትራልስያ በገሞጂና በከፊል ድርቅ በሆኑ ዙርያዎች ኗሪ ነው። \n \nጥያቄ: የሂና ተክል ቁመቱ ምን ያህል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ1.8 እስከ 7.6 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የዚምባቡዌ ሀገር በአፍሪካ በየትኛው ክልል ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በደቡብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \n67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ አንጋፎቹ ገጣሚያን ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ዶ/ር ሙሉአለም ተገኝወርቅ፣ መርድ ተስፋዬና ቤዛ ትዕዛዙ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ዲስኩር እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ \n \nጥያቄ: 67ኛው ግጥም በጃዝ የት ነው የሚካሄደው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በራስ ሆቴል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: በጣልያን ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን ያነገሡት በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፳፱ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኮምፒዩተር ኮምፕዩተር ማለት ማንኛውንም ኢንፎርሜሽን ፕሮሰስ የሚያደርግ ማሽን ነው። ይህንም የሚያደርገው በተርታ የተቀመጡ ትዕዛዞች በመፈጸም ነው። ለብዙ ሰዎች ኮምፒዩተር ሲባል ዐዕምሯቸው ላይ የሚመጣው የግል (ፐርሰናል) ኮምፒዩተር ነው። ነገር ግን ኮምፒዩተር ሲባል በጣም ብዙ ነገሮችን ያጠቃልላል። ላፕቶፕ ፣ ዴስክቶፕ ፣ ማይክሮ-ኮምፒዩተር ፣ ሱፐር-ኮምፒዩተር ፣ ካልኩሌተር ፣ዲጂታል ካሜራ እና ሌሎችንም ያጠቃልላል። ቀድሞ አስሊ ማለት አንድ በሒሳባዊ ትዕዛዝ የተለያዩ የጥንት መሣሪያዎችን እየተጠቀመ ቁጥሮችን የሚያሰላ ሰው ነበር። እስከ 20ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የተለያዩ ጠቃሚ መሣሪያዎች ተሰርተዋል። ከዛ በኋላ ትልልቅ ማሸኖች መሠራት ጀመሩ። እነዚህ ማሽኖች ከዛሬው ኮምፒዩተሮች(አስሊዎች) ጋር ሲወዳደሩ በጣም ትልቅና ቀርፋፋ ናቸው። የኮምፕዩተር የውስጥ ክፍሎች የሚከተሉት ናቸው፡- 1.ሞኒተር - የምንሰራውን ነገር እንዲያሳየን፤ምስል፣ጽሑፍ፣ ቪዲዮ ወይም ማንኛውም ነገር ሊሆን ይችላል፡፡ ሞኒተር 14 ኢንች፣ 15 ኢንች፣ ወዘተ. እየተባለ ይገላጻል፡፡ 2.ማዘርቦርድ - እናት ሰሌዳ ሁሉም የኮምፕዩተር ክፍሎች(ዕቃዎች)የሚቀዳጁበት 3.ሲፒዩ - የኮምፕዩተሩ አእማሮ እንደማለት ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን ሲፒዩን ከሰው አእምሮ ጋር አንድ ነው ማለት አይደለም፡፡ 4.ሜሞሪ - የምንሰራውን ስራ ወይም ፋይል በጊዚያዊነት አስቀምጠንበት የምንሰራበት፡፡ ሜሞሪበባይት (Bytes) ይለካል፡፡ ከ Bytes ፊት Kilo፣ ማለትም ኪሎባይት (kilobytes)([1,024 ባይቶች ወይም Bytes ማለት ነው፡፡ ] ፣ Mega[1,048,576 ባይቶች ወይም Bytes ] ፣ Giga [1,073,741,824 ባይቶች ወይም Bytes]፣ ወዘተ የሚሉትን ቃላት በመጠቀም ኪሎባይት(kilobyte)፣ ሜጋባይት (megabyte)፣ ጊጋባይት (gigabyte) እያልን የኮምፒዩተር ሜሞሪ መግለፅ እንገልጻለን፡፡ ለምሳሌ 10 MegaBytes ወይም ባጭሩ ሲጸፍ 10MB ይህ ማለት 10,485,760 Bytes ይሆናል ማለት ነው፡፡ 5.ኤክስፓንሽ ስሎት 6.የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረቢያ (power supply) 7.የሲዲ ማሰሪያ (cd drive) 8.ሀርድ ዲስክ (የምንሰራውን ወይም የምንጠቀምበትን ፋይል በቋሚነት ለማስቀመጥ) 9. መሎጊያ (ማውስ) 10.የፊደል ገበታ (ኪቦርድ) የመጀመሪያቹ ኮምፕዩተሮች የሚሠሩት በእንግሊዝኛ ፊደል ብቻ ነበር። ቀስ በቀስ ግን የተለያዩ ኣገሮች ሊቃውንት በየራሳቸው ፊደላት እንዲሠሩ ኣደረጉ። ኮምፕዩተር በእያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት እንዲሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኣበራ ሞላ ነው። በቅርቡም አያንዳንዱ የግዕዝ ፊደል፣ ኣኃዝና ምልክት ዩኒኮድ የሚባል የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ መግባት ቀጥሏል። \n \nጥያቄ: ኮምፒዩተር ውስጥ ያሉ የትኛውም አካላዊ ክፍሎች የሚሰኩበት ክፍል ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ማዘርቦርድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበ1913 በፕሬዝዳንት ዋረን ሃርዲንግ ዘመን ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ሆኑ። በሃርዲንግ ተከታይ በፕሬዝዳንት ካልቪን ኩሊጅ ዘመን ደግሞ እንዲህ ያለን ማዕረግ ይዘው አገለገሉ። የንግድ ሚኒስትር እየሆኑ ሃይለኛ ሰው ነበሩ። የንግድ ዘርፍና መንግሥት አንድላይ ይሠሩ የሚለውን ተስፋ በመያዛቸው በዚህ አንጻር ብዙ አደረጉ። በማዶ ባሕርና በውጭ አገር ለባለጉዳዮች ምክርና እርዳታ የሚሰጡ መሥርያ ቤቶች በማስከፈቱ የአለም አቀፍ ንግድ በጉልበት አስለሙ። በተለይም የሆሊዉድ ፊልም ማዶ ባሕር ለመግፋፋት ጉጉ ነበሩ። ዜጎችም ቤት እንዲያገነቡና የራሳቸው መሬት ባለአባት እንዲሆኑ አበረታቷቸው። ስለ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የክላርክ ሰነድ በ1920 ተጽፎ ሁቨር ፕሬዝዳንት እየሆኑ በ1922 ግልጽ ሆኖ ወጣ። በዚህ ሰነድ ዘንድ፥ አውሮጳ በላቲን አሜሪካ ላይ ዛቻ ካልጣለች በተቀር አሜሪካ በውጭ አገር ጥልቅ ለማለት ሕጋዊ መብት አልነበራትም የሚል ማስታወሻ ነበር። በዚያን ጊዜ አሜሪካ ሠራዊት በኒካራጓና በሃይቲ ነበራት። ስለዚህ ሁቨር ከነዚህ አገራት የሠራዊቱን ቁጥር ቀነሱ። በላቲን አሜሪካ ውስጥ የጦርነት መሣርያ እንዳይደርስ ማዕቀብ ለመጣል አሠቡ። በ1924 ጃፓን ማንቹርያን በወረረ ጊዜ አዲስ ፖሊሲ አወጡ። እሱም በግፍና በወረራ የሚገኝ የመሬት ለውጥ ሁሉ አናከብርም የሚል ነበር። ከታላቁ ጭፍግግ የተነሣ ብዙ ባንክ ቤቶች ስለወደቁ አንዳችም ብድር ለማግኘት ከባድ ሆነ። ብዙ ሰዎች ሥራ ፈት ሆኑ። በአውሮፓም ምጣኔ ሃብቱ ችግር ውስጥ ስለ ገባ ሁቨር ጀርመን ስለመጀመርያው ጦርነት ለፈረንሳይ ከምትከፍል ካሣ ለአንድ አመት ይቅር ትበል የሚል ዕቅድ አዋጁ። በሚከተለውም አመት የጀርመን ዕዳ በሙሉ ተሰረዘ። በ1925 ምርጫ ተቃራኒው ፍራንክሊን ሮዘቨልት በሰፊ መጠን አሸነፉና በሳቸው ፈንታ ፕሬዚዳንት ሆኑ። ሁቨር ፕሬዚዳንት ከሆኑ በኋላ ረጀም ዕድሜ ነበራቸው። እስከ 1957 ዓ.ም. ድረስ ኖሩ። ከ2ኛ አለማዊ ጦርነት ቀጥሎ በ1939 ስለ ቀድሞው ልምዳቸው ፕሬዚዳንት ሃሪ ትሩማን የአውሮፓ ምግብ ፍላጎት ለመወሰን ወደ አውሮፓ ላኳቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር በፅሁፍ ፕሬዝዳንት የሆነው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1920 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፖሎ 11 አፖሎ 11 ለመጀመሪያ ጊዜ ሰወችን ከመሬት ወደ ጨረቃ ለማጓጓዝ የተዘጋጀ የመንኮራኩር ሚስዮን ነው። ይህ ጉዞ የተቀናበረው በአሜሪካው የጠፈር አጥኝ ተቋም ናሳ ነበር። መንኮራኩሩ ሐምሌ16 1961ዓ.ም ከመሬት ሲመጥቅ፣ በውስጡ ሶስት ጠፈርተኞችን፣ ማለትም ኔል አርምስትሮንግ፣ በዝ አልድሪንና ማይክል ኮሊንስን የያዘ ነበር። መጓጓዣ መንኮራኩሩ ጨረቃ ላይ ከ4 ቀን በኋላ ሐምሌ 20 ሲደረስ፣ በዚሁ ቀን አርምስትሮንግና አልድሪን የጨረቃን ምድር በእግራቸው በመርገጥ የመጀመሪያወቹ ሰዎች ሆኑ። ኮሊንስ ባንጻሩ በጨረቃ ከባቢ በመብረር ከላይ ይጠብቃቸው ስለነበር ጨረቃን አልረገጠም። ይህ ድርጊት በፕሬዘደንት ኬኔዲ \"የሰወች ልጅን ጨረቃ ላይ አሳርፎ በሰላም መመለስ\" አላማ ያሳካ ነበር። የአፖሎ 11 ሚሲዮን ወደ ጠፈር ሲመነጠቅ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰወች በአለም ዙሪያ በቴለቪዥናቸው ተመልክተውታል። ይህን ሚሲዮን ይዞ የተጓዘው ሮኬት ሳተርን ፬ ሲባል ችቦው እየተንቀለቀለ ወደ ሰማይ ጉዞ የጀመረው ኬኔዲ ጠፈር ማዕከል፣ 1961 ዓ.ም. ነበር። መሬትን ከለቀቀ ከ2 ሰዓት በኋላ የጨረቃ ትዕዛዝ ማዕከልና ማረፊያ ሞጅሎቹ ዋናውን ሮኬት ለቀው በጠፈር ጉዞ ቀጠሉ። ከ3 ቀን በኋላ ትዕዛዝ ማዕከሉና ማረፊያው ሞዱል የጨረቃን ምህዋር ተከትለው ጨረቃን መዞር ጀመሩ። ከአንድ ቀን በኋላ ማረፊያው ሞዱል ከትዕዛዝ ማዕከሉ ተላቆ ጨረቃ ላይ አረፈ። በዚህ የማረፍ ተግባር ወቅት የኮምፒውተር ስህተት ስለገጠመ ማረፊያው ሞዱል በኔል አርምስትሮንግ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ስር ነበር። የሆኖ ሆኖ ለ25 ሰኮንዶች በቂ የሆነ ነዳጅ ሲቀር ማረፊያው መንኮራኩር ኔል አርምስትሮንግንና አልድሪንን ይዞ ጨረቃ ላይ በሰላም አረፈ። ጨረቃ ላይ ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ሁለቱ ጠፈርተኞች ወደ ማረፊያ መንኮራኩራቸው በመመለስ ለ7 ሰዓት ጨረቃ ላይ ከተኙ በኋላ ከላይ በኮሊንስ ወደ ሚበረው የትዕዛዝ ማዕከል ለመብረር ዝግጅት ጀመሩ። እነ አርምስትሮንግ በጨረቃ ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ቁሶችን ትተው ተመልሰዋል። ለምሳሌ ከ73 የአለም መሪወች የተላለፉ መልዕክቶችን፣ የሰላምታ መልክዕት በሁሉ የመሬት ላይ ቋንቋወችና የሁለት ሰው ልጆች ስዕሎችን ትተው ተመልሰዋል። የአሜሪካንንም ባንዲራ በጨረቃ ተክለዋል። ሓምሌ 24 የትዕዛዝ ማዕከሉ መሬት ላይ ሲደርስ ምናልባትም ጠፈርተኞቹ ያልታወቀ አደገኛ ቫይረስ ጨረቃ ላይ አጋጥሟቸው ሊሆን ይችላል በሚል በኳረንታይን ለ3 ሳምንት ከሰው ልጆች ተለይተው ተቀመጡ። ከኳረንታይን ሲወጡ፣ በርግጥም እንደ ታላላቅ ጀግኖች በተለያዩ የአለም ክፍሎች ስማቸው ተጠራ በዋሽንግተን ዲሲና በሜክሲኮ ሲቲ ለጠፈርተኞቹ ትልቅ ሰልፍ ሆነ። \n \nጥያቄ: የሳተርን ሮኬት አፖሎ 11 ሚሲዮንን ይዞ ከምን ያህል ጊዜ በኋላ ጨረቃ ላይ ደረሰ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከ2 ሰዓት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: ቤጂንግ የቻይና ምንድን ናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዋና ከተማዋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኋንግ ዲ ኋንግ ዲ (ቢጫው ንጉሥ) በቻይና ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ የቻይና ሕዝብ አባትና ንጉሥ ነበረ። የቤተሠቡ ስም «ጎንግሱን» የተሰጠው ስም «ሽወንዩወን» ነበር ይባላል። አባቱ ሻውድየን ተባለ። የተወለደው ሾው ጪው በተባለ ሥፍራ በጩፉ ሲሆን በኋላ ነገዱን ወደ ዥዎሉ ወሰደው፤ በዚያ ገበሬ ሆኖ ድብ፣ ነብርና ባለክንፍ አንበሣ የመሰለ ፍጡር አንዳስለመደ የሚል ትውፊት አለ። ያንጊዜ የኋንግ ዲ ወገን እና የያንዲ (ዩዋንግ) ወገን ለቢጫው ወንዝ ሸለቆ ተወዳዳሪዎች ነበሩ። ሦስተኛ ወገን - የሊ ሕዝብና ንጉሣቸው ቺ ዮው - ደግሞ ጠላቶቻቸው ሆኑ። ሦስት ውግያዎች ተከተሉ። በመጀመርያው የቺ ዮው ሥራዊት ያንዲውን አሸነፈው። ከዚያ ያንዲው ተሸንፎ ወደ ኋንግ ዲ ሸሸ። በሁለተኛው የዥዎሉ ውግያ ኋንግ ዲ እና ቺ ዮው ተጋጠሙ። በዚህ ውግያ ቺ ዮው ጉምን በጥንቆላ ፈጥሮ ኋንግ ዲ እንደገና በተነው፣ ብዙም ሌሎች ጉድ ሥራዎች እንደ ተከሠቱ የሚል ትውፊት አለ። ቺ ዮው በዚህ ውግያ ቢሸነፍም፣ የኮርያ ሕዝብና የህሞንግ ሕዝብ ዛሬውንም እንደ ቅድማያታቸው ይቆጥሩታል። በሦስተኛው የባንጯን ውግያ፣ ኋንግ ዲ በያንዲው ላይ ድል አደረገ። ከዚያ በኋላ ወገኖቻቸው ተባብረው የኋሥያ ብሔር (የቻይና ሕዝብ ቅድማያቶች) ፈጠሩ። ኋንግ ዲ በይፋ የቻይና ንጉሥነት ማዕረግ ወሰደ፤ የዘውድና ቤተ መንግሥት ሥርዓት ጀመረ። ከዚህ በተረፈ ኋንግ ዲ ጋሪና መርከብ እንደ ፈጠረ ይጻፋል። ደግሞ ምኒስትሩ ጻንግችየ መጀመርያ የቻይና ጽሕፈት ፈጠረ፤ የኋንግ ዲ ሚስት ሌዙም ልብስ ከሃር ትል እንዴት እንደሚሠራ አሳየች። የህክምና መጽሓፍ ኋንግዲ ኔጂንግ ሌሎችንም መጻሕፍት እንደ ጻፈ ይታመናል። ከዚህ በላይ የቻይና ስነ ፈለክና የቻይና ዘመን አቆጣጠር ፈጠረ። ስለ ኋንግ ዲ ብዙ ሌሎች ትውፊቶች አሉ። መጀመርያ ሚስቱ ሌዙ ተከታዩን ሻውሃውን ወለደች። 3 ሌሎች ሚስቶች እነርሱም ፋንግሌ፣ ቶንግዩ እና ሞሙ ነበሩት። በተለመደው ታሪክ ዘንድ ለ99 አመት ነገሠ። ታላቅ መቃብሩ በያንአን ከተማ ሲገኝ እስከ ዛሬ ድረስ በየአመቱ በሥነ ስርአት ይከብራል። \n \nጥያቄ: ኋንግ ዲ ከዋና ሚስቱ በተጨማሪ የነበሩት 3 ሚስቶች እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፋንግሌ፣ ቶንግዩ እና ሞሙ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኒጋል ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ስልጣን ላይ ሳሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ማማዱ ዲያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በጥር 1928 እ.ኤ.አ. የመጀመሪያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ የት ተከፈተ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኒው ዮርክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለበት ትምህርት ቤት ምን በመባል ይታወቃል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ በእሁድ ጠዋት ፕሮግራም ከ1979 ጀምሮ በመስራት ትታወቃለች፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለ 16 አመት ያገለገለችው ዝናሽ ከእነ ታደሰ ሙሉነህ ፤ ታምራት አሰፋ ጋር በትጋት የሰራች ሲሆን ከ20 አመት በፊት ከእነ ቤተሰቦችዋ ወደ ምድረ አሜሪካ አቅንታለች፡፡ እምብዛም ልደት መከበር ባልተለመደበት በዚያን ዘመን ከተወለደች ከአንድ አመቷ ጀምሮ እስከ 16 አመቷ ድረስ ቤተሰቦቿ የልደት በዐልዋን እያከበሩላት ያደገችው ዝናሽ ማሞ አብዲበአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 21 ቀን 1954 አ.ም መወለድዋን ለማስታወስ አልተቸገረችም:: ትውልዷም እድገቷም ጠብመንጃ ያዥ ወይም በቅሎ ቤትበሚባለው አካባቢ ነበርእናትና አባቷ ወ/ሮ ሽብሬ ወ/ሃናና አቶ ማሞ አብዲ ይባላሉ:: ዝናሽ ማሞ መጀመሪያ በቄስ ትምህርት ቤት ከፊደል እስከ መልእክተ ዮሀንስ ተምራ ፊደላትን ከለየች በኋላ በበቅሎ ቤት አካባቢ በነበረው አስቀድሞ ኤስ አይ ኤም የልጃገረዶች ክርስቲያን አካዳሚ ተብሎ ይታወቅ በነበረው ጂሲኤ የልጃገረዶች ት/ቤት ከ አንደኛ እስከ ስድስተኛቀጥሎም ይኸው ት/ቤት የፀጋ ክርስቲያን አካዳሚ በመባል ስሙ ተቀይሮ ወንዶችም አብረው መማር በጀመሩበት ት/ቤት ከሰባተኛ እስከ አስረኛበመጨረሻም በጊዜው የነበረው የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት ት/ቤቱን ወደ መንግስት ንብረትነት በማዘዋወር የአብዬት ቅርስ ተብሎ ከሰየመው በኋላ አስራ አንደኛና አስራ ሁለተኛ ክፍልን እዚያው ተምራለች:: \n \nጥያቄ: ዝናሽ ማሞ በኢትዮጵያ ሬድዮ ለስንት አመታት አገለገለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ለ 16 አመት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመንግሥት መንግሥት በአንድ አገር ወይም ተቋም ውስጥ ሕጎችን ለማውጣትና ለማስፈጸም ስልጣን ያለው አካል ነው። መንግሥት አንድ ሃገር ወይም ማህበረሰብ የሚስተዳደርበት ሥርዓትና ለዚህም ሲባል የተቋቋመ ኃይል ያለው አካል ነው ፡፡ ይህም ህግ አውጪውን፣ ህግ አስፈጻሚውን እና ህግ ተርጓሚውን ማለትም የዳኝነት አካላትን የያዘ ነው፡፡ ድርጅቶች ሁሉ እንደ መንግሥት ያለ አስተዳደር ሲኖራቸው ፣ መንግሥት የሚለው ቃል በተለይ በግምት 200 የሚሆኑ አገራዊ መንግስታትን በበለጠ ያመለክታል፡፡ የመንግስት አመሠራረት መቼ እንደተጀመረ በእርግጠኝነት መናገር ይቸግራል ፡፡ ሆኖም ታሪክ የጥንታዊ መንግስታትን ምስረታ ይመዘግቧል ፡፡ ከ 5,000 ዓመታት በፊት የመጀመሪያዎቹ ትናንሽ የከተማ መንግስታት ብቅ ብቅ እንዳሉ ይገመታል ፡፡ ከሶስተኛው እስከ ሁለተኛው ዓመተ ዓለም ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ወደ ትልልቅ አካባቢዎች በማደግ እንደ ሱመር ፣ የጥንቷ ግብፅ ፣ የኢንዲስ ሸለቆ ስልጣኔ እና ቢጫ ወንዝ ስልጣኔ የሚባሉትን ፈጥረዋል ። ግብርና ልማት እና የውሃ ቁጥጥር ለመንግስት ማደግና መጠናከር እንደ ዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ የአንዳንድ ነገድ አለቆች የእነሱን ጎሳ ለማስተዳደር በተለያዩ የአምልኮ ሥርዓቶች ወይም ባላቸው ጥንካሬ ተመርጠው አስተዳድረዋል፣ አንዳንዴም ከጎሣው ሽማግሌዎች ጋር በመሆን መንግሥት ሆነዋአል፡፡ በግብርና የበለጠ ውጤታማ እየሆኑ መሄድ በአንድ አካባቢ የሚኖረው ህዝብ ብዛቱ እንዲጨምር አስችሏል። ይህም በተለያዩ ቡድኖች መካከል የሚደረጉ ግንኙነቶች እየጨመሩ እንዲሄዱና የሚፈጠረውንም መሥተጋብር የሚቆጣጠር አካል (መንግሥት) እንዲኖር አድርጓል። እ.ኤ.አ. ከ 17 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ጀምሮ የሪፖብሊካዊ መንግስት ተስፋፍቷል፡፡ የእንግሊዝ፣ የአሜሪካና የፈረንሳይ አብዮቶች ለተወካይ የመንግስት ምሥረታ እድገት አስተዋጽኦ አበርክቷል ፡፡ የኮሚኒስት መንግስት የተመሠረተበት የመጀመሪያው ሠፊ ሀገር ሶቪዬት ህብረት ነው። የበርሊን ግንብ ከተደረመሰ ጊዜ ጀምሮ የሊበራል ዴሞክራሲ የተስፋፋ የመንግሥት መስተዳድር ሆኗል ። \n \nጥያቄ: በአንድ ሀገር ውስጥ ሕጎችን ለማውጣትና ለማስፈጸም ስልጣን ያለው አካል ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ መንግሥት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየሻይ ቅጠል ልማት ለማካሄድ ፈቃድ ወስዶ፣ ነገር ግን በሕገወጥ መንገድ ጣውላ ሲያመርት የተገኘው የህንዱ ኩባንያ ቬርዳንታ ሐርቨስት፣ አሁን ደግሞ በሕፃናት ጉልበት ብዝበዛ ተጠያቂ ሆነ፡፡ ቬርዳንታ ሐርቨስት ቀጥሮ ጉልበታቸውን ሲበዘብዝ ነበር የተባሉት አብዛኞቹ ሕፃናት ከሰባት ዓመት በታች እንደሆኑ፣ የተወሰኑት ደግሞ እስከ 15 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ 250 ሕፃናትን በመቅጠር ሲያሠራ መገኘቱን፣ ከጋምቤላ ክልል የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡ የጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን፣ ጉደሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዮናስ ከፑምሳ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ቬርዳንታ ሐርቨስት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የሕፃናቱን ጉልበት ሲበዘብዝ ቆይቷል፡፡ ‹‹ሕፃናቱን ሲያሠራ ቢቆይም ቃል የገባውን ክፍያ በመቀነስ ሕፃናቱ ቅሬታቸውን ይዘው ወደኛ መጥተዋል፤›› በማለት አቶ ዮናስ ገልጸው፣ ‹‹ጉዳዩ በዞን ደረጃ እየታየ ነው፤›› በማለት ገልጸዋል፡፡ ‹‹የሕፃናቱ መብት መጠበቅ አለበት፡፡ እኛ ሕፃናት እንዲህ ያለ ሥራ መሥራት የለባቸውም የሚል አቋም ነው ያለን፤›› ብለው የህንዱ ኩባንያ የፈጸመውን ተግባር ኮንነዋል፡፡ ይህንን ሕገወጥ ተግባር የፈጸመውን ይህ ኩባንያ የሚወስድበት ዕርምጃ በቀጣይ እንደሚታወቅም አቶ ዮናስ አክለው ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ያልተፈቀደለትን የጣውላ ምርት ሲሰራ የነበረው የሕንድ ኩባንያ ስያሜው ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቬርዳንታ ሐርቨስት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። ባለፉት አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ተጠናቋል። በዚህም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ለመፍጠርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ተደርሶ የነበረው ስምምነት ወደ ትግበራ ገብቷል። ባለፉት ስደስት ወራት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች የቴክኖሎጂ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መረጣ እና ተመሳሳይነት ልየታም ሲካሄድ ቆይቷል። በዚህ መሰረት 25 የህንድ የቴክኖሎጂ ባላሙያዎችና ድርጅቶች ከ57 የኢትዮጵያ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን ጥምረት መመስረታቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል። ኢትዮጵያ በቅንጅት በመስራት ታምናለች ያሉት ሚኒስትር ዴኤታ ጀማል በከር፥ የሁለቱ ሀገራት የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ጥምርታ ውጤታማ እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል። የቴክኖሎጂው ዘርፍ የእውቀት ሽግግር እንዲያመጣ፣ ሃብት እና የስራ እድል እንዲፈጥር ለማድረግ ኢትዮጵያ ምቹ የኢኖቬሽን ከባቢያዊ ሁኔታን እየፈጠረች እንደምትገኝም አብራርተዋል። በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር አኑራንግ ስትራቫስታቫ በበኩላቸው፥ኢትዮጵያ እና ህንድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የጀመሩት ስራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክረው መሆኑን ተናግረዋ። በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ፕሮግራም በሚቀጥሉት አምስት አመታት 50 ጀማሪ የቴክኖሎጂ ድርጅቶችን ለመፍጠር እቅድ መያዙ ተመላክቷል። \n \nጥያቄ: በኢትዮ-ህንድ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ገበያ ትስስር ኤክስፖ ላይ ምን ያህል የሕንድ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ተሳተፉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 25 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር እናታቸው የሚወለዱበት ጎሳ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፔውል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: የአማራ ክልል የቆዳ ስፋት ምን ያህል ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nታኅሣሥ ፳፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፫ተኛው እና የመፀው ወቅት ፹፰ተኛው ቀን ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየወሩ ፳፫ኛ ቀን የሰማዕታትን ዓለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስንን ታስታውሳለች። ፲፯፻፷፰ ዓ/ም - የእንግሊዝ ሠራዊት የክዌቤክ ከተማን ከአሜሪካ አስመለሰ። ፲፯፻፺፮ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት የፈረንሳይ ሉዐላዊነት ሲያከትም ደሴቷ በሰሜን አሜሪካ አኅጉር ከአሜሪካ ኅብረት ተከትላ ሁለተኛዋ ነፃ ሪፑብሊክ ሆነች። ፲፰፻ ዓ/ም - በባርነት የተገዙ ሰዎች ወደ አሜሪካ ኅብረት እንዳይገቡ የሚከለክል ሕግ ተደነገገ። ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የ፩ሚሊዮን ፱መቶ ሺ ኪሎ የመዳብ ሽያጭ ወደጃፓን ላከች። መዳቡ በኤርትራ ውስጥ ከሚገኘው የድባሮ መዳብ ማዕድን ቁፋሮ የተገኘ ነው። ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ። ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ የወረሰው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቱርክ በዊኪፒዲያ ላይ ላለፉት ሶስት ዓመታት ጥላው የነበረውን እገዳ በማንሳት ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት እንዲችሉ ፈቀደች። የሀገሪቱ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት እገዳው የመናገር መብትን ይጥሳል ሲል እግዱ እንዲነሳ ውሳኔ አሳልፏል። ዊኪፒዲያ በፈረንጆቹ ሚያዚያ ወር 2017 የቱርክን መንግስት የሚተች ፅሁፍ ለማንሳት ፈቃደኛ አለመሆኑን ተከትሎ የቱርክ መንግስት እገዳ ማሳላፉ ይታወሳል። በወቅቱ በዊኪፒዲያ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ የቱርክ መንግስት ከአይ ኤስ እና አል ቃይዳ ጋር ትብብር አለው የሚል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል። ይህንን ተከትሎም እገዳው ላለፉት 991 ቀናት ተግባራዊ ሆኖ መቆየቱን የኢንተርኔት ክትትል ተቋም የሆነው ኔትብሎክስ አስታውቋል። እገዳው በሂደት ቀስ በቀስ የሚነሳ በመሆኑ እና የተወሰኑ የኢንተርኔት አገልግሎት አቅራቢዎች ዊኪፒዲያን ለመመለስ እየሰሩ በመሆኑ በቱርክ የሚገኙ ሁሉም ተጠቃሚዎች ድረ ገፁን ማግኘት አይችሉም ተብሏል፡፡ ዊኪፒዲያ በበርካታ የዓለም ሀገራት ሳንሱር የሚደረግ ሲሆን በቻይና አሁንም ታግዶ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የኢንተርኔት ክትትል ተቋም ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኔትብሎክስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ ፊደላት የማንን ፊደላት ይመስላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጠልፎ በኪሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፕል ኩባንያ ተጠቃሚዎች በድምፅ ማዘዝ የሚችሉት ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ወይንም ኢርፎን ይፋ አደረገ፡፡ ይህም ተጠቃሚዎች ምንም አይነት ነገር ሳይጫኑ ሃይ ሲሪ የሚል ድምፅ በማሰማት ብቻ የድምፅ ማዳመጫውን ማዘዝ እንደሚችሉ ነው የተነገረው፡፡ ከዚህ ባለፈ ኤርፖድስ የተባለው ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ተጠቃሚዎች ባትሪ ካለቀባቸው እንዲያስተካክሉ ተጨማሪ ሰዓትን በቅድሚያ እንደሚሰጥ ነው የተነገረው፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየት የሰጡ ባለሙያዎች ኤርፖድስ የተሰኘው የድምፅ ማዳመጫ በእጅጉ እየዘመነ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ ይህ አዲሱ ድምፅ ማዳመጫ 159 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ሲሆን ገመድ አልባ ቻርጀርን የሚያካትት ከሆነ ተጨማሪ 40 ዶላር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: አፕል ኩባንያ ያቀረበው ኤርፓድስ የተባለ ገመድ አልባ ድምፅ ማዳመጫ ዋጋው ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 159 የአሜሪካ ዶላር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: የልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ እናት ማን ትባላለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን ያቋቋሙት ዩኒቨርሲቲ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዋሽ ብሔራዊ የመዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል በ፲፱፻፶፰ ዓ/ም የተመሠረተ ክልል ሲሆን ከአዲስ አበባ በስተ ምሥራቅ አቅጣጫ በ፪መቶ ፲፩ ኪሎሜትር ርቀት ፤ በአፋርና በኦሮሚያ አዋሳኝ ክልሎች ሥር ይገኛል። ይህ ክልል ሲመሠረት በ ፱፻፮ ካሬ ኪሎሜትር የቆዳ ስፋት (ቦልቶን ፲፱፻፷፰) የነበረው ቢሆንም፤ ባሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ማስረጃ እንዳስቀመጠው የክልሉ የቆዳ ስፋት ፯መቶ ፶፮ ካሬ ኪሎ-ሜትር ነው። የክልሉ ደቡባዊ ድንበር የአዋሽ ወንዝ ሲሆን፣ የተሠየመውም በዚሁ ታላቅ ወንዝ ስም ነው። ክልሉ የብዙ ዓይነት አራዊት እና አዕዋፍ መጠለያ ከመሆኑም ባሻገር ፍል-ውሓ እና የፋንታሌ ተራራ ይገኙበታል። የአገሪቱ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥልጣን ሲመሠረት ለንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በአማካሪነት የተመደበው እንግሊዛዊ ባቀረበው ኃሣብ መሠረት የመጀመሪያው ብሔራዊ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥጣን ከተመሠረተ በኋላ የቅድሚያ ሥራ የተደረገው፤ በታቀዱት ክልሎች የሚገኙትን የአገሪቱን የዱር አራዊት ኃብት መጠን ማረጋገጥ ነበር። ለዚህም ሥራ ከብሪታኒያ ተመልምሎ የተቀጠረው ባለ-ሙያ እንግሊዛዊው የሥነ-ሕይወት ባለሙያ ሜልቪን ቦልቶን ነበር። የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የበርካታ የዱር አራዊት፤ አዕዋፋት እና የውሐ አራዊት መኖሪያ ነው። በደቡብ አዋሳኙ በሆነው የአዋሽ ወንዝ አዞ እና ጉማሬ ሲገኝበት፤ በሰሜን ክፍሉ ደግሞ ጦጣና ዝንጀሮ፤ እንዲሁም ጅብ እና አጋዘን ይገኙበታል። በክልሉ ከሚገኙት የዱር አራዊት በከፊሉ፦ ጉሬዛ፤ ተራ ዝንጀሮ፤ ነጭ ዝንጀሮ፤ ጦጣ፤ ሳላ፤ የሜዳ ፍየል፤ ሚዳቋ፤ ትልቁ የቆላ አጋዘን ፤ አምባራይሌ፤ ከርከሮ፤ ቆርኪ በብዛት የሚገኙ ሲሆን አንበሣ፤ ነብር፤ ጀርባ-ጥቁር እና ተራ ቀበሮ፤ዳልጋ አንበሣ፤ አነር እና የዱር ድመት ደግም አልፎ-አልፎ ይታያሉ። ባለፉት አሥር ዓመታት ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ምዝገባ እንደተረጋገጠው፣ በክልሉ ውስጥ ፬መቶ ፷፪ ዓይነት የወፍ ዝርያዎች ተመዝግበዋል። ከነዚህም መኻል ስድስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ ናቸው። እነዚህም መንቆረ-ጥቁር ጋርደም፤ ግንደ-ቆርቁር፤ ክንፈ-ነጭ የገደል-ቻት፤ ጅራተ-ረጅም ወማይ፤ ቁራ እና ጋጋኖ ናቸው። \n \nጥያቄ: የአገሪቱን የዱር አራዊት ኃብት መጠን ለማረጋገጥ የተመረጠው ሰው የምን ሃገር ዜጋ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እንግሊዛዊው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: መባጃ ሐመር ለምን ይጠቅማል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበቶኪዮ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ በመሳተፍ በ58 ኪ.ግ ምድብ 7ኛ በመያዝ ዲፕሎማ አግኝታለች፡፡ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ የወከለው አትሌት ሰለሞን ቱፋ እየተካሄደ ባለው የቶኪዮ ኦሎምፒክ በ58 ኪ .ግ ምድብ ባደረገው ውድድር 7ኛ ደረጃ በመያዝ ዲፕሎማ መገኘቱን ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ በወርልድ ቴኳንዶ በምን ምድብ ተወዳደረች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ58 ኪ.ግ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: ብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በ ፲፱፻፶፪ ዓ/ም በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለማስማማት የውል ረቂቅ የተረከቡት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: እ.ኤ.አ ከ1888-1892 ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ የተከሰተው በማን ሴራ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበ628 ዓክልበ.፣ ድራኮ የሚባል ጸሃፊ የአቴና ከተማ ሕግጋት ጻፈ፤ ይህም ሕግ እጅግ ጨካኝ ሆኖ ይሙት በቃ ለማንኛውም ጥፋት ወሰነ። በ600 ዓክልበ.፣ የአቴና አለቃ ሶሎን አዲስ ሕገ መንግሥት ፈጠረ። የሰራተኞች ሸክም አቀለለ፣ ነገር ግን ባላባትነት በልደት ሳይሆን በንብረት ብዛት እንዲቈጠር አስደረገ። ክሊስቴኔስ እንደገና በ516 ዓክልበ. በዴሞክራሲያዊ መሠረት የተሻሸለ ለአቴና ሕገ መንግሥት አወጣ። የግሪክ ፈላስፋ አሪስጣጣሊስ በ350 ዓክልበ. ግድም የሕገ መንግሥት ሀሣብ ለይቶ ዐወቀ። በጽሑፎቹ የአቴና፣ የስፓርታና የካርታግና ሕገ መንግሥቶች ያነጻጽራል። በመደምደሚያው የተሻለው ሕገ መንግሥት ከንጉሣዊ፣ ከመኳንንታዊና ከሕዝባዊ ወገኖች የተደባለቀ መሆኑን ገመተ። በሀሣቡ በመንግሥት የሚከፋፈሉ ዜጎች ከማይከፋፈሉ ከባርዮችና ዜጎች ካልሆኑ ሰዎች ልዩነት አደረገ። ሮማውያን መጀመርያ «12ቱ ሰንተረዦች» የተባለውን ሕገ መንግሥት ያወጡ በ457 ዓክልበ. ነበር። ከዚያ በኋላ አንዳንዴ የተለያዩ ሕጎችና ትእዛዛት ይጨምሩበት ነበር እንጂ እስከ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስ ድረስ (430 ዓ.ም.) ሌላ ክምቹ ሕገ መንግሥት አልኖረም ነበር። በኋላም በምሥራቁ መንግሥት (ቢዛንታይን) በኩል መጽሐፈ ዩስጢኒያኖስ (526 ዓ.ም.) ለአውሮፓ ከፍ ያለ ተጽእኖ ነበረው። ይህም በምስራቁ ነገሥታት 3ኛ ሌዎን ኢሳውራዊ «ኤክሎጋ» (732 ዓ.ም.) እና በ1ኛ ባሲሌዎስ «ባሲሊካ» (870 ዓ.ም.) በተባሉት ሕገ ፍትሐን ተከተለ። \n \nጥያቄ: ድራኮ በ628 ዓክልበ. አቴናን በተመለከተ የጻፈው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአቴና ከተማ ሕግጋት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: አይዛክ ኒውተን በምን ነበር የፀሓይ ብርሃን የልዩ ልዩ ቀለማት ጥርቅም መሆኑን ያወቀው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በፕሪዝም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ 2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የት ተከታተሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኒጋል ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር በማማዱ ዲያ መፈንቅለ-መንግሥት ሙከራ የተደረገባቸው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከ 60 ዓመት በኋላ ወባን ለማከም የሚረዳ ኪኒን በአሜሪካ ባለስልጣናት ፈቃድ አገኘ። መድሃኒቱ በየአመቱ 8 ሚሊየን ሰዎች ላይ የሚያገረሸውን የወባ አይነት ለማከም የሚረዳ ነው። ይህ አይነት የወባ በሽታ በጉበት ውስጥ ለረጅም ዓመት ተደብቆ የመቆየት ባህሪ አለው። ተመራማሪዎች ይህንን \"ድንቅ ስኬት ሲሉ አሞካሽተውታል\"። ደጋግሞ የሚያገረሽ የወባ በሽታ ፕላስሞዲየም ቪቫክስ በሚሰኝ ጥገኛ ተዋህሲያን የሚከሰት ሲሆን በአፍሪካ በዋናነት ከሚጠቀሱ የበሽታ አይነቶች መካከል አንዱ ነው። አሁን የአሜሪካው የምግብና የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ታፌኖኪውይን ለተሰኘው መድሃኒት እውቅና ሰጥቷል። መድሃኒቱ በሽታዋ ከተደበቀበችበት ጉበት አውጥቶ በመግደል ሰዎች በህመሙ ዳግመኛ እንዳይሰቃዩ ያደርጋል። በአሁን ሰዓት ጉበት ውስጥ የተደበቀች ወባን ለማከም የሚረዳ ፕሪማኪውን የተሰኘ መድሃኒት አለ። ነገር ግን አንድ ታፌንኪውንን ወስዶ ከሚገኘው ፈውስ ጋር ሲነፃፀር ፕሪማኪውንን ለ 14 ቀን መውሰድ ይጠይቃል። \n \nጥያቄ: ጉበት ውስጥ የምትደበቀውን የወባ በሽታ ለማዳን ጥቅም ላይ ሲውል የነበረው መድሃኒት ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፕሪማኪውን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በምን ያህል ዋጋ ገዛው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ450 ሚሊዮን ብር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ young men’s Cristian association tinning school በአሁኑ መጠሪያው spring filed college ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ YMCA ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን FYBA አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ Czechoslovakia ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ lasiva፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡ \n \nጥያቄ: ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወቱት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፍራንክ ማሀን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: በጋና የሚገኘው ትልቁ ሰው ሰራሽ ሐይቅ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቮልታ ሐይቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጋሊልዮ ጋሊልዮ ጋሊሊ ታህሳስ 15, 1564 – ጥር 8, 1642 የነበረ የጣሊያን ሥነ-ፈለክ አጥኝና ተመራማሪ ነበር። ጋሊልዩ በዘመኑ የራሱን አጉሊ መነጽር በመስራት ጨረቃ ተራራ እንዳላት፣ ጁፒተር የተባለው ፈለክ ልክ እንደ መሬት የራሱ የሆኑ 4 ጨረቃወች እንዳሉት፣ ረጨቶች ከከዋክብት ስብስብ እንደተሰሩ፣ ፀሐይ ጥቁር ነጠብጣቦች እንዳሏት፣ ቬነስ ልክ እንደ ጨረቃ የተለያየ ቅርጽ በጥልቁ እንደምትይዝ የመሰከረና በኋላም መጽሃፍ ጽፎ ያሳተመ ሳይንቲስት ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጋሊልዮ የተፈጥሮ ህጎችን/ጉልበቶችን አጥንቷል። በትውፊት እንደሚነገር ጣልያን ውስጥ ባለው የተንጋደደው የፒሳ ግንብ ላይ በመውጣት፣ የተለያዩ ክብደት ያላቸውን የብረት ኳሶች ወደመሬት በመልቀቅ፣ ሁሉም በዕኩል ሰዓት መሬትን እንደሚመቱ አረጋግጧል። ከዚህ በመነሳት እስከሱ ዘመን ይሰራበት የነበረውን የአሪስቶትል አስተሳሰብ (ከባድ ነገሮች ከቀላል ነገሮች በበለጠ ፍጥነት ወደመሬት ይወድቃሉ) ፉርሽ አድርጓል። ሆኖም ግን በጊዜው የአሪስቶትል አስተሳሰብ በህብረተሰቡ ህሊና ውስጥ በጥብቅ ስለሰረጸ ቆይቶ ኢሳቅ ኒውተን የጋሊልዮን አስተሳሰብ ልክ መሆኑን በግስበት ጥናቱ እስካረጋገጠበት ድረስ የአሪስቶትል አስተሳሰብ ተቀባይነት ነበረው። ጋሊልዩ ከሱ ቀድሞ የተነሳውን የኮፐርኒከስን ሃሳብ (መሬት ሳትሆን ፀሓይ የአለም መካከለኛ ናት) በመደገፉ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለእስር ተዳርጎ ነበር። ይህም በዚያ ዘመን የነበሩ የቤ/ክርስቲያኒቱ አዋቂወች ያምኑት እንደነበረው መሬት ቆማ ሌላው አለም ሁሉ በመሬት ዙሪያ ይሽከረከራሉ የሚለውን ስለተቃወመ ነበር። ከዚህ በኋላ እስከ አረፈበት 1642 ድረስ የቤት እስረኛ ሆኖ ዘልቋል። በቅርቡ በ20ኛው ክፍለ ዘመን የሮማው ፓፓ ጆን ፓውል 2ኛ ጋሊልዮን \"የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት] አባት\" በማለት የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያ ከ400 አመት በፊት በጋሊልዮ ላይ ለፈጸመችው ግፍ ይቅርታ ጠይቀዋል። \n \nጥያቄ: ጋሊልዮ ምን ዓይነት ስራን በመስራት ታዋቂ ሊሆን ቻለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አጉሊ መነጽር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከ2010 ጀምሮ በፋይናንሱ ዘርፍ ስኬታማ ለውጦች መመዝገባቸውን ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፋይናንስ ዘርፍ ዐበይት ስኬቶች በሚል በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ እንዳስታወቁት የታክስ ገቢ በ2010 ከነበረበት 229 ቢሊየን ብር በ2012 የ36 በመቶ ጭማሪ በማሳየት 311 ቢሊየን ማድረስ ተችሏል። \n \nጥያቄ: በ2010 የነበረው የታክስ ገቢ በ2012 ምን ያህል ሆነ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 311 ቢሊየን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: የኡቶ-አዝቴካዊ ቋንቋ ቤተሠብ የሆነው ናዋትል በማን የሚነገር ቋንቋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሜክሲኮ ኗሪዎች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ በኢትዮጵያ ከመቼ እስከ መቼ በንጉሥነት ቆዩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: ሉሲ የተገኘችው በየት ክልል ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በአፋር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ በአሜሪካ ጎዳናዎች ላይ ሙከራ እንዲያደርግ ፈቃድ አገኘ። ተሽከርካሪው የአሽከርካሪ ወይም የሰው እገዛ ሳያስፈልገው አገልግሎት ይሰጣል ነው የተባለው። ኑሮ በተባለው ኩባንያ የተሰራው ተሽከርካሪ መሪን ጨምሮ ለመሽከርከር የሚያገለግሉት የነዳጅ መስጫና ፍሬን እንዲሁም የእይታ መስታወትን (ስፖኬ) ያለ አሽከርካሪ በራሱ ይጠቀማል። የአሜሪካ የትራንስፖርት ሚኒስቴርም ተሽከርካሪው በቴክሳስ ሙከራውን እንዲያደርግ ፈቃድ ሰጥቶታል። አር 2 የሚል ስያሜን ያገኘው ይህ የእቃ ማመላለሻ፥ የኩባንያው ሁለተኛው ትውልድ ተሽከርካሪ ሲሆን በሆስተን ቴክሳስ ሙከራ እንደሚያደርግ ነው የተነገረው። የእቃ ማመላለሻውን ለመሞከር ተሽከርካሪውን መቆጣጠር የሚያስችሉ ክፍሎችን ማሟላት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል። ሆኖም የእቃ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ፍጥነት በሰዓት ከ25 ኪሎ ሜትር እንዳይበልጥ የአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር አስጠንቅቋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ በአሜሪካ ሀገር በየትኛው ግዛት ላይ ሙከራውን እንዲያደረግ ነው ፍቃድ የተሰጠው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቴክሳስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nስዋሂሊ ስዋሂሊ ፡ (ወይም ፡ ኪሷሂሊ Kiswahili) ፡ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ፡ የሚናገር ፡ የባንቱ ፡ ቋንቋዎች ፡ ቤተሠብ ፡ ቋንቋ ፡ ነው። የስዋሂሊ ፡ ሕዝብ (፭ ፡ ሚሊዮን ፡ ተናጋሪዎች) ፡ ልደት ፡ ቋንቋ ፡ ከመሆኑ ፡ በላይ ፡ ለ ፴ ፡ እስከ ፡ ፶ ፡ ሚሊዮን ፡ ሌሎች ፡ ሰዎች ፡ ሁለተኛ ፡ ቋንቋ ፡ ሆኗል። የስዋሂሊ ፡ ስም ፡ መነሻ ፡ ከዓረብኛ ፡ ቃል ፡ «ሰዋሂል» ፡ ነበር ፤ ይህም ፡ የ«ሳኸል» ፡ (ማለት ፡ ዳር) ፡ ብዙ ፡ ቁጥር ፡ ነው። ስለዚህ ፡ የ«ስዋሂሊ» ፡ ትርጉም ፡ የ(ባሕር) ፡ ዳረኞች ፡ ቋንቋ ፡ ሊሆን ፡ ይችላል። የቋንቋው ፡ ቤተሰብ ፡ ባንቱ ፡ ሲሆን ፡ ተናጋሪዎቹ ፡ መርከበኞችና ፡ ነጋዴዎች ፡ በመሆናቸው ፡ መጠን ፡ ከዓረብኛ ፣ ከፋርስ ፣ ከህንዲ ፣ እና ፡ ከቻይንኛ ፡ ቢሆንም ፡ ብዙ ፡ ቃሎች ፡ ተበድረዋል። \n \nጥያቄ: ስዋሂሊ በየት አካባቢ የሚነገር ቋንቋ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በምሥራቅ ፡ አፍሪቃ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: የአጼ ዘርአ ያዕቆብ አባት ባረፉ ጊዜ ማን ነው የአባታቸውን ስልጣን የተረከበው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nግሪክ ግሪክ ወደ ሜዴቴሪኒያን ባሕር የተዘረጋ አንድ ትንሽ አገር ነው። ከምሥራቅ ወደ ትንሽ እስያ፤ ከምዕራብ ወደ ኢጣሊያ አገር ከሁለቱም ወገን ርቀቱ ትክክል ነው። ግሪክ በሰሜን ወገን ከመቄዶንያ ይዋሰናል። ግሪክ ኣብዛኛው በባሕር የታጠረ ነው። በደቡብና በምሥራቅ ወገን አያሌ ደሴቶች አሉ። ከእነርሱም በአያሌዎቹ መንደሮችና ከተሞች ተሠርተውባቸዋል። አንዱ አንቲፖሮስ ይባላል። በእዚህም ስፍራ ያለው ታላቅ ያጌጠ ዋሻ የታወቀ ስመ ጥሩ ነው። እኩሌቶቹም የግሪክ ደሴቶች ከባሕር ወደ ውጪ እየተወረወሩ የወጡ ይመስላሉ። እኩሌቶቹም ከጥንት ጀምረው ይታዩ የነበሩት ያሉበት አይታወቅም ጠፍተዋል። ይህ እንግዳ ነገር እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ከባሕር በታች የተነሳው እሳተ ገሞራ ነው። በደቡብ ግሪክ ወገን ባሉት ደሴቶች አየሩ በአሜሪካ እንዳለው እንደ ቨርጂኒያ ግዛት አየር ቀላል ነው። በዚህ አገር ብዙ አይነት ፍሬ ሁሉ ሞልቶዋል። በሰሜን በኩል ደግሞ አየሩ ቅዝቃዜ ያለበት ነው። በየጠረፉ የመርከብ መቋሚያዎች ወደቦች ይገኛሉ። ብዙዎቹ የአገሩ ሰዎችም መርከበኞች ናቸው። በደኑም ፓይን (ጥድ) የተባለው ጠንካራ ዛፍ ይገኛል። በላይኛው አውራጃ ኦክ የተባለው ዛፍ ይገኛል። ወደታች ባለው ክፍልም ቸስትነትና ዋልነት የሚባሉት ዕንጨቶች ይገኛሉ። በዚህ ስፍራ የሚገኘው ዋናው ነገር ደረቅ ፍራፍሬ፣ ዘቢብ፣ ጥጥ፣ ሐር ጠጉር፣ ሩዝ፣ ትንባሆና በቆሎ ነው። የእጅ ሥራ ጥቂት ነው። በቤት የተለመደ ሥራ እንደ ጥጥ እንደ ጠጉር እንደ ሐር የመሰለ ነገር ነው። ቀለም ማግባት ወይም መቀባት በጣም የተለመደ ከሆነ ብዙ ጊዜው ሆነው። ከዛፎች ፍሬ ዋነኛው ወይራ ሲሆን በብዛት ይተከላል። ወይን፣ በኽረ? ሎሚ፣ በለስ፣ አልሞንድ (ለውዝ)፣ ተምር፣ ሴትሮን፣ ፓሜግራኔት (ሮማን)፣ ኩሬንትም ይበቅላሉ። \n \nጥያቄ: በግሪክ ደን ውስጥ የሚገኘው ጠንካራ ዛፍ ስሙ ማን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፓይን (ጥድ) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሆ ቺ ሚን ሆ ቺ ሚን ከ1890-1969 እ.ኤ.አ. የኖረ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሥራችና መሪ ነበር። ሆ ቺ ሚን ከወጣትነት ጊዜው ጀምሮ ለአብዮታዊ ተግባራት የቆመ ነበር። ሆ ቺ ሚን በሥራ ምክንያት ፈረንሳይ ውስጥ በነበረበት ወቅት የካፒታሊስት ሥርዓት ምን ያህል ሠርቶአድሩን ሕዝብ ለሥቃይና ለመከራ እንደዳረገውና የዓለም ወዛደሮች በቀለም በቋንቋና በባህል ቢለያዩም ብሶታቸው አንድ መሆኑን በቅርብ ተገነዘበ። በአፍሪካና በእስያ የኢምፔሪያሊስቶች መምጣት ምን ያህል ሥቃይና ውርደት በእነዚህ ሕዝቦች ላይ እንዳደረሰ ተረዳ። በዚህም ምክንያት ሆ ቺ ሚን የቬትናም ሕዝብ ጠላት የፈረንሳይ ኢምፔሪያሊዝም እንጂ የፈረንሳይ መላው ሕዝብ አለመሆኑን ደጋግሞ ገልጿል። ሆ ቺ ሚን በ1917 እ.ኤ.አ. በፈረንሳይ ወዝአደሮች ትግል ውስጥ በቀጥታ ተሳታፊ በመሆን የፈረንሳይ ሶሻሊስት ፓርቲ አባል ሆነ። ከዚህም በላይ በፈረንሳይ የቬትናም አርበኞችን ማኅበር በማቋቋም በፈረንሳይ ይኖሩ የነበሩትን ቬትናማውያን በማንቃትና በማስተማር ለሀገራቸው ነፃነትና ክብር እንዲታገሉ ያነሣሣ ነበር። የጥቅምቱ የሩሲያ አብዮት ለአያሌ ዓመታት በዓለም ሰፍኖ የነበረውን የኢምፔሪያሊዝም ብቸኛ የበላይነት ሰባብሮ አዲስ ዘመን በማብሰሩ ሆ ቺ ሚን የጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ የቦልሼቪኮችን ፈለግ መከተል እንዳለበት አመነ። በሆ ቺ ሚን አስተሳሰብ የቬትናም ብቻ ሳይሆን የሌሎች ቅኝ ተገዥ የሆኑ ሀገሮች ነፃነት የሚገኘው የወዝአደሩን የአብዮት ጎዳና በመከተል ብቻ እንደሆነ አጥብቆ ያምን ነበር። የነዚህ ሀገሮች ብሔራዊ ነፃነት ከማኅበራዊ ነፃነት ጋር መያያዙንና ይህም ነፃነት ከሶሻሊዝምና ከኮሚኒዝም ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑን አስገንዝቧል። ሆ ቺ ሚን ከ1924 እስከ 1930 እ.ኤ.አ. በቻይናና በቬትናም በመዘዋወር ለዚህ ውስብስብ ትግል ግንባር ቀደም አመራር ሊሰጥ የሚችለውን ማርክሳዊ ሌኒናዊ ፓርቲ ለማቋቋም ከፍተኛ ትግል አደረገ። በመጀመሪያም የቬትናም አብዮታዊ ወጣቶች ማኅበር የተባለውን በማቋቋም «ወጣት» በተባለው ጋዜጣ ወጣቱን ለትግል ቀሰቀሰ። በዚህ ዓይነት ከብዙ ጥረትና ትግል በኋላም በ1930 እ.ኤ.አ. የኢንዶቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን (ኋላ የቬትናም ሠራተኞች ፓርቲ፤ ዛሬ ደግሞ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ) መሠረተ። በ1935 እ.ኤ.አ. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደው የኮሚኒስቶች ስብሰባ አንድ ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት የሆነ ዲሞክራሲያዊ ግንባር እንዲቋቋም በወሰነው መሠረት ሆ ቺ ሚን ቬትሚን የተሰኘውን ሰፊ ፀረ ኢምፔሪያሊስት ግንባር በማቋቋም መላውን ሕዝብ በትግሉ ለማሳተፍ ችሏል። ዲየን ቢየን ፉ በተባለው ታሪካዊ ስፍራ የቬትናም አርበኞች የፈረንሳይን ጦር በማሸነፋቸው ፈረንሳይ በጀኔቩ ስምምነት መሠረት የቬትናምን አንድነት በማወቅ የሰላም ውል ፈረመች። ነገር ግን ከ1955 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የአሜሪካ ኢምፔሪያሊዝም በፈረንሳይ እግር በመተካት የደቡቡን ክፍል ለመቁረስ የጦር ሰፈር በመሥራትና በውስጥ አርበኞች በመጠቀም ጦርነት ከፈተ። ነገር ግን አሜሪካ ከግማሽ ሚሊዮን ወታደሮች በላይና በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ቢያፈስም ቬትናምን ሊያሸንፍ አልቻለም። \n \nጥያቄ: ሆ ቺ ሚን ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከ1890-1969 እ.ኤ.አ. የኖረ የቬትናም ኮሚኒስት ፓርቲ መሥራችና መሪ ነበር። ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ ከሚኖረው ሕዝብ በመቶኛ ምን ያህሉ ነው ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖረው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 10 ከመቶ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nተክለጻድቅ መኩርያ ተክለጻድቅ መኩርያ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ አሳግርት ልዩ ስሙ ሳር አምባ በተባለ ሥፍራ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምሕርት ሲደርስ መጀመሪያ ከአባታቸውና ቀጥሎም በአጥቢያቸው ባህላዊውን ትምሕርት እስከቅኔ ያለውን ቀስመዋል። ከዚያም አዲስ አበባ መጥተው አሊያንስ ፍራንሴዝና ተፈሪ መኮንን ትምሕርት ቤት ገብተው የጊዜውን የትምሕርት ደረጃ አጠናቀዋል። ኢጣልያ አገራችንን የወረረች ጊዜም በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ፍጅት ተይዘው ወደ ሶማሌ ደናኔ ተግዘው ለሦስት ዓመታት ታስረዋል። ከነጻነትም መልስ አገራቸውን በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገልግለዋል። መጀመሪያ ተቀጥረው ያገለገሉት በትምሕርትና ሥነጥበብ ሚኒስቴር ነበር። እዚያም ሳሉ በአገራችን ሰው የተጻፈ የአገራችን ታሪክ አንድም ባለመኖሩ በቁጭትና በመቆርቆር ነበር ‘መጻፍ አለብኝ’ ብለው በደንብ ከሚታወቀው ከቅርቡ ጊዜ በቅጡ ወደማይታወቀው የሩቁ ዘመን መጻፍ የጀመሩት። የመጀመሪያውን መጽሐፍ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከዓፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ” የሚለውን በ ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. አሳተሙ። ከጫፍ እስከ ጫፍ ጽፈው የመጨረቻውን መጽሐፍ፣ የታሪካችን መጀመሪያ የሚሆነውን “የኢትዮጵያ ታሪክ ኑብያ-አክሱም-ዛጉዬ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት” የሚለውን በ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. አቅርበዋል። እኒህኑ መጻሕፍት ትምሕርት ሚኒስቴር ታሪክ ለማስተማሪያ በትምሕርት ቤት ተጠቅሞባቸዋል። ተክለጻድቅ ከታሪክ ውጭ የጻፏቸው “የሰው ጠባይና አብሮ የመኖር ዘዴ” እና በሚዮቶሎዢያ (አፈ ታሪክ) ላይ ያተኮረ “ከጣዖት አምልኮ እስከ ክርስትና” የሚሉም መጽሐፎች አሏቸው። ተክለጻድቅ በምድር ባቡር በዋና ጸሐፊነት፥ በቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ዋና ሥራ አስኪያጅነት፥ እንዲሁም በፈረንሳይ፥ በእስራኤል፥ በዩጎዝላቪያ በዲፕሎማሲ ሥራ በመጨረሻም የትምሕርትና የባህል ሚኒስቴር ሆነው አግልግለዋል። በፈቃዳቸው ጡረታም ከወጡ በኋላ በምርምር የታገዙ ሦስት ታላላቅ የታሪክ ሥራዎችን አቅርበዋል። ተክለጻድቅ ከረጅም የአገልግሎት ዘመን በኋላ በተወለዱ በ ሰማንያ ስድስት ዓመታቸው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. አርፈዋል። \n \nጥያቄ: ተክለጻድቅ መኩርያ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nናይጄሪያ ናይጄሪያ በይፋ የናይጄሪያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝ አገር ናት። በሕዝብ ብዛትም ከአፍሪቃ አንደኛ ናት። ከቤኒን ፣ ቻድ ፣ ካሜሩን ፣ ኒጄር ፣ እና ከጊኒ ባሕረ ሰላጤ ጋር ድንበር ትካለላለች። በናይጄሪያ ውስጥ ትልቁ ብሔሮች ሀውዛ ፣ ኢግቦ እና ዮሩባ ናቸው። ግማሹ ሕዝብ እስላም ሲሆን ሌላው ግማሽ ደግሞ የክርስትና እምነት ይከተላል። ትንሽ የሕዝቡ ክፍልም ባህላዊ ሃይማኖቶችን ይከተላል። የሳይንስ ጥናት እንደሚያሳየው ናይጄሪያ ከ፱ሺህ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ ነዋሪዎች እንደነበሩባት ያሳያል። በቤንዌ እና ክሮስ ወንዞች አካባቢ ያለው ሥፍራ የባንቱ ፍልሰቶች መነሻ እንደ ነበረ ይታመናል። የናይጄሪያ ስም ከኒጄር ወንዝ ነው የተወሰደው። ናይጄሪያ በአፍሪካ በሕዝብ ቁጥር አንደኛ ስትሆን ከዓለም ደግሞ ሰባተኛ ናት። የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በዓለም ላይ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። የዓለም አቀፍ ገንዘብ ፈንድ እንደሚገምተው የናይጄሪያ ኢኮኖሚ በ2011 እ.ኤ.አ. በ8% ያድጋል። \n \nጥያቄ: ናይጄሪያ በህዝብ ብዛት ከአፍሪቃ ስንተኛ ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አንደኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nብጉር ብጉር ማለት የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከቆዳ ስር በሚገኙ የወዝ እጢዎች በሚመነጭ ቅባት ወይም ወዝ እና በሞቱ የቆዳ ህዋሳት በብዛት መከማቸትና በቀዳዳው መደፈን የሚፈጠር እባጭ ነው። በርካታ ጥናቶች ጭንቀት ብጉርን ከማባባሱም በላይ የቆዳ ጤንነት ችግር ላይ እንዲወድቅ ያደርጋል ይላሉ። ብጉር በጣም ከተለመዱት የቆዳ ችግሮች ውስጥ አንዱ ነው። ዕድሜ ዘርና ጾታ ሳይገድበው ሁሉንም ያጠቃል። ቆዳችን ላይ ብዙ ጥቃቅን ቀዳዳዎች አሉ። በነዚህ ቀዳዳዎች ውስጥ ደግሞ ቅባታማ ፈሳሽ የሚያመነጩ ዕጢዎች አሉ። የቅባታማ ፈሳሽና የቀዳዳዎቹ ጥቅም የሞቱ የቆዳችን ህዋሳትን ለማስወገድ ነው፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች እነዚህ ቀዳዳዎች ሲዘጉ ቅባታማ ፈሳሹ በቆዳችን ውስጥ ስለሚጠራቀም ብጉር ይፈጠራል፡፡ የተጠራቀመው ቅባትም ለህዋሳት መራባት ዕድል ስለሚከፍት አንዳነዴ መግል ይይዛል፡፡ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከ'ስቤሸስ ግላንድ' ጋር የተያያዙ ናቸው፡ እነዚህ እጢዎች ሴበም የሚባል ንጥረነገር ሲያመነጩ ንጥረነገሩም በጸጉር መውጫ ቀዳዳ ወደላይ ወደቆዳ የሚወጣ እና ቆዳችን ላይ የሚያርፍ ነው። የብጉር መፈጠር የቆዳ ህዋሳትን ያበዛል። ይህ እባጭ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎችን ግርግዳ በመግፋት ነጫጭ የብጉር ሽፍታዎች ሲፈጥር የቀዳዳዎችን ግርግዳ በመጎተት ደግሞ ጥቋቁር የብጉር ሽፍታዎች (blackheads) ቆዳችን ላይ ሊፈጥር ይችላል። ብጉር በብዛት ሊወጣ የሚችልባቸው ቦታዎች፣ ፊት ላይ፣ በደረት፣ በኣንገት፣ በትከሻ ፣ እና በጀርባ ላይ ነው። \n \nጥያቄ: የቡጉር መፈጠር ምንን ያስከትላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የቆዳ ህዋሳትን ያበዛል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ በ1445 በተደረገው ጦርነት ላይ በማሸነፍ የትኛውን ግዛት አጠቃለው መያዝ ቻሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሶማልያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበቶኪዮ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ በመሳተፍ በ58 ኪ.ግ ምድብ 7ኛ በመያዝ ዲፕሎማ አግኝታለች፡፡ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ የወከለው አትሌት ሰለሞን ቱፋ እየተካሄደ ባለው የቶኪዮ ኦሎምፒክ በ58 ኪ .ግ ምድብ ባደረገው ውድድር 7ኛ ደረጃ በመያዝ ዲፕሎማ መገኘቱን ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: በቶኪዮ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ በወርልድ ቴኳንዶ ስንተኛ ደረጃ አገኘች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 7ኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ የትኞቹን ባህር የያዘ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ ከደቡብ አቅጣጫ በማን ትዋሰናለች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በናሚቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: የአፋር ክልል ዋና ከተማ ማናት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሰመራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጓሳ ጓሳ ወይም በደኔ ወይም ጀሞ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ዛፍ ነው። እስከ 10 ሜትር ድረስ የሚቆም ቀጭን ዛፍ ነው። ለቅርንጫፎቹ ረጅም፣ ቀጥ ያሉ ዐረንጓዴ እሾሆች በጥምዝምዝ አሉባቸው። ከእሾሆቹ መሠረት ጨለማ-አረንጓዴ ውሁድ ቅጠሎች ይበቅላሉ፣ ውሁዱም ቅጠል ከ፪ ቅጠሊቶች እየሆነ በቅርጽም ሆነ በስፋት ሊለያዩ ይችላሉ። ሽንሽን ግንዱ ግራጫማ-ቡኒ ሻካራ ልጥ አለው፤ ይህም በረገፈበት ቦታ ቢጫ-አረንጓዴ እራፊ ይኖረዋል። ህብረ አበባው የጥቂት አበቦች ዘለላ ሲሆን አበቦቹም ወይም ዘንግ-አልባ ወይም በአጭር አገዳ ላይ የሚቀመጡ ናቸው። የአበባው እንቡጥ ሞላላ እና በጉርምስና ሥሥ ጽጉር ያለበት ነው። አበቦቹ አረንጓዴ-ቢጫ ቀለም፣ ፍናፍንታም ጾታ፣ አምስት ቅጠል በክቦሽ ምጥጥን ያላቸው ናቸው፤ የአበባ ቅጠሎች 8-14 ሚሊሜትር ባጋማሽ ናቸው። የኅብራበባ ስሪት ግራጫማ ቀለም፣ ለሥላሣ ጽጉር ያለው፣ ከ10 ሚሊሜትር ያልረዘመ ነው። ሞልሟላ ፍሬው በተለምዶ ከ4 ሴንቲ ሜትር ያልረዘመ ነው፣ ያልበሰለ ሲሆን አረንጓዴ ነው፣ ሲበሰልም ቡናማ ይሆናል፣ ከሽካሽ ቆዳው ዝልግልግ ቡናማ ልጥልጥ አለበት፣ ይህም ጽኑ ፍሬ ድንጋይ አለበት። \n \nጥያቄ: የአበቦቹ ቀለም እንዴት አይነት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አረንጓዴ-ቢጫ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአንበሳ አንበሳ ጡት አጥቢ የእንስሶች መደብ ውስጥ ሲሆን ግዙፍ ድመቶች ከሚባሉት 4 አራዊት አንዱ ነው። ከነዚህም መካከል ነብር ከሚባለው ግሥላ መሳይ አውሬ ቀጥሎ በቁመቱና ክብደቱ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል። አንበሳ ዛሬ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በህንድ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በታሪክ እስያና በደቡብ አውሮፓ እንደነበርና እንደጠፋ ይታወቃል። አንበሶች በጣም ቁጡ ሊሆኑ ይችላሉ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሙጭሊትን ያህል ገራምና ተጫዋች ይሆናሉ። ሲጠግቡ በዝግታ የሚያንኮራፉ ቢሆንም እንኳ እስከ ስምንት ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሰማ በሚችል ኃይለኛ ድምፅ ሊያገሡ ይችላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰነፎችና ልፍስፍሶች ይመስሉ ይሆናል፤ ሆኖም በሚያስገርም ፍጥነት የመንቀሳቀስ ችሎታ አላቸው። የሰው ልጅ፣ አንበሳ ባለው ድፍረት ለዘላለም ሲወሳ እንዲኖር አድርጓል፤ በመሆኑም ደፋር ሰው አንበሳ ተብሎ ይጠራል። አንበሶች በማኅበር ከሚኖሩት የድመት ወገን የሆኑ እንስሶች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው። በትልልቅ መንጋ ተከፋፍለው የሚኖሩ ሲሆን እያንዳንዱ መንጋ ከጥቂት አባሎች አንስቶ ከ30 በላይ ሊደርስ ይችላል። አንድ መንጋ የጠበቀ ዝምድና ያላቸው በርከት ያሉ ሴት አንበሶች ይኖሩታል። አንድ ላይ ይኖራሉ፣ ያድናሉ እንዲሁም ይወልዳሉ። ዕድሜ ልካቸውን ሊዘልቅ የሚችለው ይህ የጠበቀ ትስስር ለመንጋው ጠንካራ መሠረት የሚጥል ከመሆኑም በላይ ለመንጋው ሕልውና ጥሩ ዋስትና ይሆናል። እያንዳንዱ መንጋ እየተዘዋወሩ የሚጠብቁና የመንጋውን የክልል ወሰን የሚያወጡ አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ለአካለ መጠን የደረሱ ወንድ አንበሶች ይኖሩታል። እነዚህ ዕጹብ ድንቅ የሆኑ አውሬዎች ከጥቁሩ የአፍንጫቸው ጫፍ አንስቶ እስከ ጭራቸው ጫፍ ድረስ ከሦስት ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ሲሆን ከ225 ኪሎ ግራም በላይ ሊመዝኑ ይችላሉ። ቤተሰቡን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ወንዶቹ ቢሆኑም አመራር የሚሰጡት ግን ሴቶቹ ናቸው። ወደ ጥላ ሥፍራ መሄድን ወይም አደን መጀመርን በመሳሰሉት ሁኔታዎች ብዙውን ጊዜ መንጋውን ለአንድ ዓይነት እንቅስቃሴ የሚያነሳሱት ሴቶቹ አንበሶች ናቸው። ሴት አንበሶች በአብዛኛው በየሁለት ዓመቱ ይወልዳሉ። ግልገሎቹ በሚወለዱበት ጊዜ ምንም ዓይነት አቅም አይኖራቸውም። ግልገሎችን ማሳደግ የሁሉም የጋራ ሥራ ነው፤ በመሆኑም ሴቶቹ አንበሶች በሙሉ በመንጋው ውስጥ ያሉትን ግልገሎች ይጠብቃሉ እንዲሁም ያጠባሉ። የግልገሎቹ ዕድገት ፈጣን ሲሆን በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ መሮጥና መቦረቅ ይጀምራሉ። ልክ እንደ ሙጭሊቶች እየተንደባለሉ ይጫወታሉ፤ ከሚያጫውቷቸው ጋር ይታገላሉ፤ እንዲሁም በረጃጅሙ ሣር ውስጥ ወዲያና ወዲህ ይዘላሉ። እያንዳንዱ የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ ስሜታቸውን ይማርከዋል፤ ቢራቢሮዎችን ለመያዝ ይዘላሉ፣ ትናንሽ ነፍሳትን ያሳድዳሉ፣ ከየጭራሮና ከየሐረጉ ጋር ይታገላሉ። ይበልጥ ስሜታቸውን የሚማርከው ግን እነርሱን ለማጫወት እናታቸው ወዲያና ወዲህ የምታወናጭፈው ጭራዋ ነው። እያንዳንዱ መንጋ የሚኖርበት በደንብ የተከለለ ቦታ ያለው ሲሆን ይህ መኖሪያ ብዙ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ሊኖረው ይችላል። አንበሶች ውኃ እንደ ልብ ባለበትና ከቀትር ሐሩር የሚከላከል ጥላ በሚያገኙበት ከፍ ያለ ቦታ ላይ መኖር ይመርጣሉ። በእንዲህ ዓይነቱ ሥፍራ ከዝሆኖች፣ ከቀጭኔዎች፣ ከጎሽና ከሌሎች ሜዳማ በሆኑ ሥፍራዎች ከሚኖሩ እንስሶች ጋር በአንድነት ይኖራሉ። አንበሳ አብዛኛውን ጊዜውን በእንቅልፍ ጥቂቱን ጊዜ ደግሞ በአደንና በተዋስቦ ያሳልፋል። እንዲያውም አንበሶች በቀን ውስጥ ወደ 20 የሚጠጋውን ሰዓት የሚያሳልፉት በዕረፍት፣ በመተኛት ወይም በመቀመጥ ነው። ከባድ እንቅልፍ ተኝተው ሲታዩ ሰላማዊና ለማዳ ይመስላሉ። ይሁን እንጂ በዚህ መታለል የለብህም፤ አንበሳ እጅግ ቁጡ ከሆኑት አራዊት መካከል አንዱ ነው! \n \nጥያቄ: የአንበሳ እንስሶች መደብ ውስጥ ከየትኛው መደብ ነው የሚመደበው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጡት አጥቢ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: የሞሪታንያ ዋና ከተማ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኑዋክሾት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: በ1996 በሜሪላንድ ስቴት ከሚኖሩ ነዋሪዎች ምን ያህሎቹ የሌላ ስቴት ወይም ሀገር ተወላጆች ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 583,900ቹ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመንግስቱ ለማ መንግሥቱ ለማ (1924-1988) በጣሊያን ወረራ ዋዜማ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ተወልዶ ከቆሎ ተማሪነት ተነስቶ የለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ ደቀመዝሙርነት እስከመሆን በቅቶ የቅኔ ቤት ሊቅነት ሳይበቃው የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ቀደምቶች መሃከል ለመደብለቅ የበቃ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ድንቅ ገጣምያን/ፀሃፌ ተውኔቶች አንዱ ነው። አባቱ አለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ-ታሪክ (ታሪክ የእናታቸው ስም ነው - ምናልባት በኢትዮጵያ ታሪክ የእናታቸውን ስም ከስማቸው አስተባብረው በመጻፍ የመጀመሪያው ሳይሆኑ አይቀሩም) ታዋቂ የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩ ሲሆን በመጀመሪያ ላይ የመንግስቱን የአስኳላ (በወቅቱ ዘመናዊ ትምህርት የሚጠራው እንዲህ ነበር) ትምህርት ባይወዱለትም ጣሊያኖቹ ልጁን የማያስተምር ሰው ሁሉ ይቀጡ ስለነበር ለማስተማር ተገደዋል። ሁዋላ ላይ ግን እሳቸው አዲስ አበባ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ ተቀይረው መጥተው እሱ የኮተቤ ተማሪ ከሆነና የትምህርት ውጤቱም እስደሳች ሲሆን የቀድሞ ቅዋሜያቸውን ሳያላሉት አልቀሩም። መንግስቱ በእንግሊዝ አገር ወደ ስድስት አመት ቢቆይም ትምህርቱን ሳያጠናቅቅ ነው በ1956 ዓ.ም ወደ አገሩ ለመመለስ የበቃው። ይሁን እና በቆይታው ከብዙ የእንግሊዝ ደራስያን ጋር ለመተዋወቅ በቅቷል። በተለይም ከጆርጅ በርናርድ ሾው ጋር ወዳጆች እንደነበሩ ይነገራል። መንግሥቱ ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በሁዋላ የተሰማራው ወደ መንግስት ሥራ ሲሆን በህንድ አገር ዲፕሎማት ሆኖ ከሄደ በሁዋላ ምናልባትም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ዘመናዊ ኮሜድ ተውኔት «ጠልፎ በኪሴ\"ን ደርሷል ከዚያ በሁዋላ የደረሳቸው እነ «ያላቻ ጋብቻ»፣ «ጸረ-ኮሎኒያሊስት»፣ «ባለካባና ባለዳባ» የመንግስቱን ስም በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ውስጥ ቀዳሚ ተጠቃሽ ካደረጉት ስራዎቹ መካከል ናቸው። በተጨማሪም «The bear» የተሰኘውን እና የታዋቂው የሩሲያ ደራሲ አንቷን ቼኾቭ ተውኔት የሆነውን «ዳንዴዎ ጨቡዴ» በሚል የተረጎመ ሲሆን የጄ.ቢ. ፕሪስትሊን «The Inspector Calls»ን ተርጉሞ ለመድረክ አብቅቷል። መንግስቱ ከተውኔቱ በተጨማሪም በስነ-ግጥም የተዋጣለት እንደነበር ስራዎቹ ይመሰክራሉ። «የግጥም ጉባኤ» የተሰኘው ስብስብ መንግስቱ የግጥም መክሊት የተቸረው ደራሲ እንደነበር ይመሰክራል። መንግሥቱ ደራሲም ብቻ አልነበረም፤ በተማሪዎቹ የተወደደ መምህር በሳል ተመራማሪ ለባህሉ እና ለቋንቋው ሙት የነበረ ከኢትዮጵያ ብርቅዬዎች አንዱ ነው። \n \nጥያቄ: በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ", "targets": "ለጥያቄው መልስ በሀረር ሀደሬ ጢቆ መካነ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአኩሪ አተር አኩሪ አተር የአባዝርት አትክልት ዝርያ ነው። በየጊዜው አኩሪ አተርን መመገብ ለሴቶች ጉዳት ባያደርግም፣ ለወንዶች ጤናማ እንደማይሆን በሰፊ ቢታወቅም በአንዳንድ አገር ባሕል አመጋገብ በብዛት ይጨመራል። ከ20ኛዉ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ አሜሪካን ዉስጥ ወርቃማዉ ወይም ተዓምረኛዉ እህል የሚል ስያሜ አግኝቷል። አኩሪ አተር በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር የለም። ባለሙያ ካገኘም ለመጠጣትም ለመበላትም የሚችል የእህል ዘር ነዉ። ስለአኩሪ አተር ሲወሳ ብዙዎች የሚያስታዉሱት ለሕፃናት አካል ግንባታ ጠቃሚ መሆኑ ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአኩሪ አተር ወተት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በኢትዮጵያዉያን የምግብ ጣዕም ለዛ ተላብሶ በተለያየ ምግብነት መቅረብ እንደሚችል እየታየ ነዉ። አኩሪ አተር ወደኢትዮጵያ የገባዉ በ1950ዎቹ መሆኑን ነዉ በእህሉ ላይ ምርምር የሚያደርጉት ባለሙያዎች የሚያስረዱት። በአኩሪ አተር ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተደረገዉ ዝርያ የማዉጣት ምርምርም 22 ዓይነት ዘሮች እስካሁን ተገኝተዋል። አኩሪ አተርን በሀገር ዉስጥ በ12 የምርምር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ፤ መካከለኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ እና ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርምሩ ይካሄዳል። አኩሪ አተር ሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረተዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነዉ። አኩሪ አተርን በብዛት ከሚያመርቱ ሃገራት ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ቀዳሚዎቹ ናቸዉ። ከአኩሪ አተር ወተት ለማዘጋጀት ሲታሰብ እህሉን ከአንድ ቀን በፊት ለቅሞና አጥቦ ለ15 ደቂቃ ያህል መቀቀል ያስፈልጋል። ከዚያም አዉጥቶ ተዘፍዝፎ ያድራል። ከዚያም የራሰዉን አኩሪ አተር ልጣጩን በሚገባ በዉኃ አስለቅቆ በትንሽ በትንሹ እየቆነጠሩ ፈጭቶ እንደእህሉ መጠን ዉኃ ጨምሮ መቀቀልና መጭመቅ ነዉ። እንደባለሙያዉ ከሆነም ለአንድ ኪሎ አኩሪ አተር ስምንት ሊትር ዉኃ ያስፈልጋል። ተፈጥሮን ተከትሎ የማይበቅል እህልም ሆነ በተፈጥሮ ሥርዓት ያላደጉ እንስሳትን መመገብ ለጤና አደገኛ መሆኑን በተግባር የተረዳዉ ምዕራቡ ዓለም በአሁኑ ጊዜ ፊቱን ከእንስሳት ተዋፅኦ ወደተክሎችና ሰብሎች አዙሯል። በዚህ ምክንያትም ከአኩሪ አተር የሚገኙ የምግብ ተዋፅኦዎች ተመራጭነትን እያገኙ ነዉ። ከአኩሪ አተር ወተት እና አይቡ እንደሚገኝ ሁሉ የአኩሪ አተር ሥጋም አለዉ። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ስንት አይነት የአኩሪ አተር ዝርያ አለ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 22 ዓይነት ዘሮች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ ኢትዮጵያዊው ሊቅና ጻድቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ የተወለዱት በ፲፫፻፶፯ ዓ.ም. በወሎ ክፍለ ሀገር በቦረና ወረዳ ሸግላ/ሰግላ በተሰኘች ቦታ ነው። አባታቸው ሕዝበ ጽዮን ከተከበሩ መምህራን ወገን የሆኑ የቤተ መንግሥት ባለሟል ፤ መጽሐፍትን የሚያውቁ ጥበብ የተሞሉ ሲሆን የሰግላ አገረ ገዢም ነበሩ ። እናታቸው እምነጽዮንም ከወለቃ ሹማምንት ወገን የሆኑ ደግ ሰው ነበሩ። ሲጀመር እናታቸው ፈሪሃ እግዚአብሔርን እያስተማሩ በጥበብና በዕውቀት አሳደጓቸው ። አባ ጊዮርጊስ የተመረጠ የሆነ ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በመማፀን የተወለዱ ልጃቸው ስለሆኑ እንደሰማዕቱ የእውነት ምስክር እንዲሆኑላቸው በመመኘት ስማቸውን ጊዮርጊስ ብለው ጠርተዋቸዋል ። ከተወለዱበትም ሀገር በመነሳት ጊዮርጊስ ሰግላዊ ተብለው ሲጠሩ በጊዮርጊስ ዘጋስጭና በጊዮርጊስ ሰግላዊ መካከል ምንም ልዩነት የለም። ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ እንደ ሰማዕት ግርፋትንና እሥራትን የተቀበሉ ፣ እንደ ሊቃውንት የመናፍቃንና የከሀድያንን ክርክር የረቱ ፣ እንደ መሐንዲስ ሐናጺ ፣ የሕግና የሥርዐት የሚስጥራትና የትርጉዋሜያት መምህር ፣ የጸሎትና የትምህርት መጻሐፍት ደራሲ ፣ የሥርዓተ ገዳምና ማኅበረ መነኰሳት አባት እንዲሁም ቢያንስ የአንድ ትምህርት መሥራች ሲሆኑ በግዞት በሄዱባቸውና በታሰሩባቸው ቦታዎችም ሆነ በተሾሙባቸው እንደ ደብረዳሞ ገዳም በመሰሉ ቦታዎች ሁሉ ሲያስተምሩና ሲገስጹ ኖረዋል ። በድርሰቱም እስካሁን በሃገራችን ተወዳዳሪ የላቸውም ። እጃቸው ከብዕር ተጨማሪ ከጠንካራ ሥራ ሳይቦዝኑ ዋሻ ሲፈለፍሉ የውሃ ጉድጉዋድ ሲቆፍሩ ድልድይ ሲሠሩ ኖረዋል ። አንደበታቸውና ሕሊናቸው ከምስጋና ሳያቁዋርጡ ለቤተክርስቲያን ጸሎትና ምስጋና ሥርዓት ሲተጉ ኖረው በፅድቅና በቅድስና ሕይወት እንዳጌጡ ለተዋህዶ ኮከብ ሆነው በተወለዱ በ፷ ዓመታቸው በ፲፬፻፲፯ ዓ.ም. ሐምሌ ፯ ቀን አርፈዋል ። ተማሪዎቻቸውም በመረረ ሐዘን ሆነው አፅማቸውን በጋስጫ ራሳቸው ፈልፍለው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በሠሩት ገዳም ውስጥ አስቀምጠውታል። \n \nጥያቄ: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጭ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲፫፻፶፯ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሱዳን ሱዳን በይፋ የሱዳን ሪፑብሊክ (አረብኛ السودان) ከአፍሪካ በስፋት ሦስተኛ ስትሆን በአህጉሪቱ ሰሜናዊ ምስራቅ ክልል ትገኛለች። ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው። ከግብፅ ፣ ከቀይ ባሕር ፣ ከኤርትራ ፣ ከኢትዮጵያ ፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከመካከለኛው የአፍሪካ ሪፑብሊክ ፣ ከቻድ ፣ እና ከሊቢያ ጋር ድንበር ትካለላለች። የአባይ ወንዝ (ናይል) ሀገሪቱዋን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ ይከፍላል። የአረብ ባህል ደንበኛ ሲሆን አብዛኛው ሕብዝ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ነው። ሱዳን ከግብፅ የተጣመረ ረዥም ታሪክ አላት። የመጀመሪያው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1955 እስከ 1972 እ.ኤ.አ. ከዚያም ሁለተኛው የሱዳን እርስ በርስ ጦርነት ከ1983 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ተከስቷል። በ1989 እ.ኤ.አ. በሰላማዊ መፈንቅለ መንግሥት ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር ሥልጣን ላይ የወጡ ሲሆን እራሳቸውን የሱዳን ፕሬዝዳንት ብለው ሾመዋል። የእርስ በርስ ጦርነቱ በሰላም ውል የቆመ ሲሆን ይህ ውል ያኔ የሀገሪቱዋ ደቡባዊ ክፍል ለነበረው ቦታ ራስን የመምራት መብት ሰጥቷል። በጃኑዋሪ 2011 እ.ኤ.አ. በተካሄደው ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት በሱዳን ፈቃድ ደቡብ ሱዳን ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፫ ዓ.ም. ሉዓላዊ ሀገር ሆነች። ዋና ከተማዋ ካርቱም የሱዳን የፖለቲካ፣ ባህል እና ንግድ ማዕከል ናት። የሀገሪቱዋ መንግሥት በይፋ ፌዴራላዊ ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ቢሆንም ስልጣን ላይ ያለው ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ (National Congress Party) በሁሉም የመንግሥት አካላት ላይ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር ምክንያት በብዙ የዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ ዘንድ መንግሥቱ አምባገነናዊ ተብሎ ይቆጠራል። \n \nጥያቄ: የሱዳን ዋና መዲና ማናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ካርቱም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየኒያ ፋውንዴሽን እና የጆይ ኦውቲዝም ማዕከል መሥራች ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በኮሮና ቫይረስ ፅኑ ህክምና ማዕከል ውስጥ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዘሚ የኑስ በአሁኑ ሰአት ከ200 በላይ ለሚሆኑ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች እንክብካቤ እያደረጉ እንደሚገኙ ከቅርብ ቤተሰቦቻቸው ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል። \n \nጥያቄ: ወይዘሮ ዘሚ የኑስ በምን ቫይረስ ተጠቁ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በኮሮና ቫይረስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: አጼ ዘርአ ያዕቆብ ከደቀ እስጢፎ እምነት ተከታዮች ከነበሩት ጋር የተከራከሩት በምን ጉዳይ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጨኖ ጨኖ ግራጫ ቢጤ የሆነ፣ ፈርጠም ያለ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ አፍሪቃ፣ በተጨማሪም በኮንጎ ደኖች የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው ዓይነት ጨኖ የፀጉሩ ቀለም ግራጫና ጥቁር የሆነ፣ ፊቱ የጠቆረ ሰማያዊ የሆነ፣ አገጭና አንገቱ ነጭ ነው። የወንዶቹ ክብደት እስከ 12 ኪ.ግ. ሲሆን፤ አማካዩ 4.5 ኪ.ግ ይመዝናሉ። ጨኖ የደን ዝንጀሮ ነው። የደን ዝንጀሮች ብዙ ጊዜ ከዝናባማ ሥፍራዎች ደኖች ውጪ አይገኙም። ጨኖ ግን ከነዚህ ደኖች ውጪም በሚገኙ ደኖች ውስጥ ይኖራል። በኢትዮጵያ፣ በጎደሬ ደን ውስጥ፣ ቴፒ አጠገብ ሜጢ አካባቢ ይገኛሉ። በተራራማ ሥፍራዎች ደኖችም እስከ 3000 ሜትር ከፍታ ድረስ ይገኛሉ። እጅጉን በዛፍ ላይ የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። የሚገኘው በደን ዛፎች ግማሽ ላይ ነው። በተለያዩ ዓይነት ተግባሮች መገለጫ የሚሆኑ ሰባት ዓይነት ድምፆች አሏቸው። በቡድናቸው ውስጥ የሚታየው አብዛኛው ፀብ፣ በዋናው ወንድና ለአካለ መጠን ባልደረሱና ጎረምሳ ወንዶች መሃል የሚታየው ነው። በሴቶቹና ሕፃናትን በሚገድሉ ወንዶች መኻከል ከባድ ግጭት ያድጋል። በቡድኖች መኻከል የሚደረግ ግጭት የሚሆነው አልፎ አልፎ ነው። እንዲህ ያለ ግጭት የሚነሳው በድንበር አካባቢ በምግብ ሽኩቻ የተነሳ ነው። የእርግዝና ጊዜአቸውን 140 ቀን ነው። የልጆቻቸውን እድገትም ቀስ ያለ ነው። ከወለዱ ወዲያ ለሚቀጥለው እርግዝና 15 ወራት መቆየት አለባቸው። \n \nጥያቄ: የደን ዝንጀሮች በአብዛኛው በየት አካባቢ ይኖራሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከዝናባማ ሥፍራዎች ደኖች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው የደም ቧንቧ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጀጉላር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሥነ ቁጥር ሥነ ቁጥር ወይንም በእንግሊዝኛ \"አርቲሜቲክስ\" ከሁሉ የሒሳብ ዘርፎች አንጋፋውና በሁሉም ሰው ጥቅም ላይ የሚውል ክፍል ነው። ሥነ ቁጥር የቁጥሮችን ቅልቅል ውጤት የሚያጠና ሲሆን ብዙ ጊዜ ቁጥሮች ሲደመሩ፣ ሲቀነሱ፣ ሲባዙና ሲካፈሉ የሚያሳዩትን ባህርይ ይመረምራል። ሒሳብ ተማሪዎች የቁጥር ኅልዮት ውጤቶችን ከፍተኛ ሥነ ቁጥር በማለት ከለተ ተለት መደመርና መቀነስ ጥናቶች ይለዩዋቸዋል። የሰው ልጆች ከጥንት ጀምሮ ሥነ ቁጥርን ተጠቅመዋል። ለምሳሌ አፍሪቃ ውስጥ የተገኘ 22፣000 ዓመት እንዳለው የሚቆጠር የአጥንቶች ቁርጥራጭ ለመቁጠርና ለመደመር ያገለግል እንደነበር ይጠቀሳል። በኋላም የግብጽ እና ባቢሎን ሰወች ቁጥርን መጻፍ እንደጀመሩና ይህን ፈጠራቸውን ለመደመርና ለመቀነስ እንደተገለገሉበት አሁን የተገኙ ቅርሶች ያስገነዝባሉ። የግብጽን የአጻጻፍ ስልት የተከተሉ ግሪኮችም በዩክሊድ እና ሌሎች የግሪክ ተማሪዎች አማካይነት ጥናቱን ለማሳደግ ችለዋል። ሆኖም እስከዚህ ዘመን የነበረው የቁጥር አጻጻፍ ስልት አቀማመጣዊ አልነበረም። ስለሆነም ለመደመርና ለመቀነስ፣ በተለይ ደግሞ ለማባዛትና ለማካፈል እጅግ የተወሳሰበና አሰልቺ ነበር። የሒሳብና የሥነ ቁጥር እድገት ከፍተኛ እመርታ ያሳየው ሕንዳውያን ተማሪዎች ዜሮና አቀማመጣዊ አጻጻፍ ስልትን በ4ኛው ክፍለዘመን ሲፈለስፉ ነበር። ይህም አሁን በመላው አለም የሚሰራበት ህንዲ-አረብ ቁጥር (ማለቱ፡ 0 1 2 3 4 5 6 7 8 9 ) እንዲፈጠር አደረገ። ፊቦናቺ የተሰኘው የጣሊያን ነጋዴ የዚህን ድንቅ ቁጥር ቀመርና ጥቅም በመጽሐፉ በ1202 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) በመጻፍና በአውሮጳ አገራት ሁሉ በማሰራጨት ታዋቂነቱ እንዲገን ሆነ። የህንዲ-አረብ ቁጥር ስርዓት በጣም ቀላል ከመሆኑ የተነሳ የሒሳብ ትምህርት በአውሮጳ እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አደረገ። ይሄው አዲሱ ስልት ለሒሳብ ጥናት መሰረት በመሆን የጥንቶቹን ሒሳብ ተማሪዎች ድንቅ ውጤቶች ከአዲሱ ስርዓት ጋር ሲነጻጻሩ እምብዛም ሆነው እንዲታዩ አደረጉ። የሂንዲ አረብ ቁጥር ስርዓት ለዘመናዊው የሒሳብ ትምህርት መነሳት ምክንያት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። \n \nጥያቄ: ቁጥርን መጻፍ የጀመሩት እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ግብጽ እና ባቢሎን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ ዜማና ቅኔ የት ተማረ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኮረማሽ ኮረማሽ በአማራ ክልል ውስጥ፤ በሰሜን ሸዋ የምትገኝ ወረዳ ናት። ከአዲስ አበባ በምሥራቅ በኩል ሰማንያ አምሥት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ሥፍራ ስትሆን፣ በስምጥ ሸለቆ ምሥራቃዊ ፍንጭ አናት ላይ ያላት ገዥ ይዞታ ከአፋር (የቀድሞው አዳል) እና ከሶማሌ በኩል በታሪክ ዘገባ ይመነጩ የነበረቱን እስላማዊ አጥቂዎች ለመከላከል የተመቸች ቦታ በመሆኗ የተመሠረተች ጥንታዊ ምሽግ ናት። ከፊት ለፊትዋ የመገዘዝ ተራራ፤ እንኮይ፤ ሰንበሌጥ፤ ቡልጋ እና ወደ ምሥራቅ የደረቂት እና አማሪት ወንዞች ከከሰም ወንዝ ጋር ሲቀላቀሉ እንዲሁም የመስኖ ዘንባባ ተራራ እና የመስኖ ማርያም ቤተ ክርስቲያን፤ ሜዳማው የሾላ ገበያ ወደደቡብ ምሥራቅ ደግሞ ከማዶ የክርስቶስ ሰምራ ትውልድ አገር እና ምንጃር ቁልጭ ብለው ይታያሉ። የአካባቢው ቃለ ታሪክ ሥፍራዋ በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አያት ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እንደተመሠረተች ሲያረጋግጥ፤ የልጅ ልጃቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ደግሞ የሸዋ ንጉሥ በነበሩ ጊዜ እስካሁን ድረስ ያለውን ታላቅ የመሣሪያ ምሽግ እና በግቢው ውስጥ ያሉትን አሥራ አንድ ቤቶች እንዳሠሩ ብዙ የጽሑፍና የቃል ታሪኮች እንዲሁም ሕንጻዎቹ እራሳቸው ምስክር ናቸው። ከነኚህ አሥራ አንድ ሕንጻዎች ሁለቱ በ ፲፱፻፸፯ ዓ/ም በሉተራን ኃይማኖታዊ ተልዕኮ ልገሣ ታድሰው የ ጥራ ጥሬ እና የ እህል ምርት ማከማቻ ጎተራ ሆነዋል። ሌሎቹ ቤቶች የወረዳው ፍርድ ቤት፤ የቤተ ክህነት ጽ/ቤት ፤ የወረዳው የፖሊስ ጽ/ቤት እና የመሳሰሰሉ መንግሥታዊ ቢሮዎችን ይዘዋል። በጥቅምት ወር ፲፱፻፱ ዓ/ም አዲስ በተመሠረተው የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እና የራስ ተፈሪ መኮንን መንግሥት ላይ ጦርነት አውጀው ከወሎ የዘመቱትን የልጅ እያሱ አባት ንጉሥ ሚካኤልን ሊከላከል የተሰለፈው የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠራዊት ጥቃቱን ያደራጀው እዚሁ ኮረማሽ ላይ ሲሆን፡ ኋላም ዓርብ ጥቅምት ፲፯ ቀን ራስ ተፈሪና ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሰገሌ ሜዳ ላይ ንጉሥ ሚካኤልን ድል ያደረጉት ከዚሁ ደጀን ቦታ ነው። በ፳፻፩ ዓ/ም ከ ዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የኤሌክትሪክ መሥመር ተዘርግቶ ለዚች መንደርና ለአካባቢው የቡልጋ ሕዝብ የልማት መስፋፊያ ጮራ ተገልጾለታል። በዘመናዊ መልክ የተገነባው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በተመረቀበት ዋዜማ፣ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ባለው የአሥራ ሦስት ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ ላይ በሳምንት ሁለት ጊዜ፤ ማለትም ሐሙስ እና ቅዳሜ ለገበያ የሚያመች የሕዝብ መመላለሻ የአውቶቡስ መሥመር አገልግሎቱን ጀምሮ፣ በተለይም ቆለኞቹ ምርታቸውን ወደ ገበያ በማቅረብ ላይ የነበረባቸውን የእግር ጉዞ እንግልት ቀንሶላቸዋል። ወደፊትም ገብያቸውን ሐሙስ ገበያ ድረስ ከመሄድ እዚችው ኰረማሽ ላይ ለመመሥረት ተስፋ ሰጥቷቸዋል። ለ የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምረቃ ሥነ ስርዐት የተጓዙ እንግዶች በዚሁ የአውቶቡስ አገልግሎት ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ቢያንስ የሦስት ሰዐት የእግር ጉዞ ቀርቶላቸዋል። \n \nጥያቄ: ኮረማሽን የመሰረቷት ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: የፀሀይ የመጠነ ቁስ ጥንቅር ነገሮች መካከል 74% ያህሉ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሃይድሮጂን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስን ለክስ የዳረጉት ምክንያቶች ስንት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ስለፀሀይ ሳይንሳዊ መግለጫ ከሰጡ ጥንታዊ የግሪክ ፈላስፎች ቀዳሚው ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አናክሳጎራስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን ሁለተኛውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ መቼ አሸንፉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲፰፻፶፮ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመዓዛ ብሩ መዓዛ የተወለደችው እዚህ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን ዘመኑም 1951 ዓ.ም ነበር፡፡ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ክፍል በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሒርና ከተማ ተምራ፣ ከአራተኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርቷን ደግሞ በቅድስት ማርያም ትምህርት ቤት ተከታትላ ፈጽማለች፡፡ መዓዛ በትምህርት ቤቷ በክፍል ውስጥ አጫጭር ታሪኮችን ለተማሪዎች በማንበብ ከመታወቋም ሌላ ከፍ ያለ የሥነ - ጽሑፍ ዝንባሌ እንደነበራት የሚያስታውሱት መምህራኗ “አንድ ቀን ታላቅ የጥበብ ሰው እንደሚወጣት እናውቅ ነበር” ይላሉ፡፡ መዓዛ በ1971 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ - ቋንቋ ጥናት ተቋም ውስጥ በሥነ-ልሣን ትምህርት ክፍል ተመደበች፡፡ ሥነ-ልሣን መዓዛ የምትፈልገው ጥናት ባለመሆኑ በምደባው ቅር ብትሰኝም፤ በንዑስ ትምህርት ደረጃ የምትወስደው የውጭ ቋንቋና ሥነ - ጽሑፍ በመሆኑ ለነበራት ቅሬታ እንደማካካሻ ሆኖላታል፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለች የተፈጠረ አንድ አጋጣሚ ደግሞ መዓዛንና ሬዲዮንን የሚያስተሳስር ይሆናል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሬዲዮ የፕሮግራሞች ኃላፊ የነበረው አቶ ታደሰ ሙሉነህ ለሚያዘጋጀው የእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም ድራማ የሚጫወቱ ሸጋ ድምጽ ያላቸው ወጣቶችን ሲያፈላልግ ከመዓዛ ጋር ይተዋወቃል፡፡ ድራማው አስታጥቃቸው ይሁን ያሰናዳው ሲሆን የመዓዛ ድምጽ ለሙከራ በስቱዲዮ ተቀርጾ ሲሰማው፣ ታደሰ ሙሉነህ የሚፈልገውና የሚወደው ድምጽ ሆኖ ስላገኘው ይደሰታል፡፡ ከዚህ በኋላም ለእሁድ ፕሮግራም የሚሆኑ ጽሑፎችን በየሳምንቱ እንድታነብለት ያግባባትና የመዓዛና የሬዲዮ ፍቅር በኢትዮጵያ ሬዲዮ ይወለዳል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የመዓዛ ድምጽ በእሁድ የሬዲዮ ፕሮግራም አድማጮች ዘንድ የተለመደና የተወደደ ሆነ፡፡ መዓዛም የሌሎችን ጽሑፎች በማንበብ ብቻ ሳትወሰን የራሷን ጽሁፎች እያዘጋጀች የምታቀርብ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ከሬዲዮ ፕሮግራሙ ቤተሰቦች እንደ አንዱ ሆነች፡፡ በ1974 ዓ.ም ከዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ትምህርቷ ፍጻሜውን እስካገኘ ድረስም መዓዛ ሬዲዮና ትምህርትን ጎን ለጎን ስታስኬድ ቆይታለች፡፡ የመዓዛ የሥራ ዓለም የተጀመረው ግን በምትወደውና በምትፈልገው በኢትዮጵያ ሬዲዮ ውስጥ ሳይሆን መንግስት በመደባት በባህል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ ነበር፡፡ ስራዋም ባህልና ስፖርት የተባለው የመስሪያ ቤቱ መምሪያ በሚያሳትመው “መርሐ ስፖርት” የተሰኘ ወርሃዊ የስፖርት መጽሔት (በኋላ ጋዜጣ) ላይ ሆነ፡፡ ምንም እንኳ አዲሱ ስራዋ ከራዲዮ የሚያርቃት ቢሆንም መዓዛ ግን ሳትሸነፍ ሬዲዮን በትርፍ ጊዜ ሥራነት ተያያዘችው፡፡ ሬዲዮ ጣቢያው የሚሠጣትን አነስተኛ ክፍያ እየተቀበለችም ልዩ ልዩ ጭውውቶችን እና መጣጥፎችን በግልና በጋራ በማቅረብ ተወዳጅ ሥራዎቿን ለሕዝብ አበርክታለች፡፡ \n \nጥያቄ: መዓዛ ብሩ የት ተወለደች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አዲስ አበባ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ በአዲስ አበባ ከተማ በደቡብ-ምሥራቅ አቅጣጫ ከአራዳ በስምንት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ የአገሪቱ ዋና አድማሳዊ የንግድና የግንኙነት በር ነው። አውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መግባት የጀመሩት በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ሲሆን በአዲስ አበባ ዙሪያ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ያርፉ እንደነበር በታሪክ ተዘግቧል። የመጀመሪያው ቋሚ የአውሮፕላን ጣቢያ ግን የተሠራው በአምሥቱ የፋሺስት ዘመናት ሲሆን የካቲት ፳፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም አክሱም አካባቢ ላይ ከነጥያራው ተከስክሶ በሞተው አብራሪያቸው፣ “ኢቮ ኦሊቬቲ” ስም ሠይመውት የነበረው የልደታ የጥያራ ጣቢያ ነው። በዚሁ በፋሺስት ወረራ ዘመን ‘አላ ሊቶሪያ’ የተሰኘው ኩባንያ በአገር ውስጥ ከአዲስ አበባ ተነስቶ ነገሌን፤ ሞቃዲሾን፤ ድሬ ዳዋን፤ ጎራኄን፤ ጂቡቲን፤ አሰብን፤ ጂማን፣ ጋምቤላን ደምቢ ዶሎን፤ ጎንደርን አስመራን፤ ደሴን፤ ለቀምትን እና አሶሳን የሚያገለግሉ የበረራ መሥመሮች ሲኖረው ከአድማስ ባሻገር ደግሞ ከተማዋን በካርቱም፣ ዋዲ ሃይፋ፤ ካይሮ፣ ቤንጋዚ እና ሲራኩሳ አድርጎ ከሮማ ጋር የሚያገናኝ የበረራ መሥመርም ነበረው። ከድል ወዲህ ልደታ አውሮፕላን ጣቢያ፤ የብሪታኒያ ጦር ኃይሎች ሲገለገሉበት ከቆየ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታኅሣሥ ፳፩ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሲመሠረት ዋና ጣቢያው እዚያው ነበር። ዳሩ ግን የአየር መንገዱ አገልግሎት እየተስፋፋ ሲመጣና ትላልቅ ጄት አውሮፕላኖች እንደሚያስፈልጉት ግልጽ ሲሆን፣ የልደታ አየር ጣቢያ ብቃት እንደሌለው እና ለጄት አየር ዠበቦችም ማሳረፊያ የማይስማማ መሆኑ ታምኖበት የአማራጭ ሥፍራ ፍለጋ ተጀመረ። የአዲሱንም አየር ጣቢያ ዝርዝር ጥናት እንዲያዘጋጅ ውሉ ለአሜሪካዊው ‘አማን እና ዊትኒ’ ኩባንያ ተሰጥቶ፤ ጥናቱ በ፲፱፻፶ ዓ/ም ተገባዶ አማራጩ ሥፍራ ቦሌ እንዲሆን ተወሰነ። የአየር ጣቢያውን የግንባታ ወጪ ከአሜሪካዊው ‘ኤክስፖርት-ኢምፖርት’ ባንክ በተገኘ ብድር ተሸፍኖ ሥራው ተጀመረ። ጠቅላላ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ ኅዳር ፲፩ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ተመርቆ ተከፈተ። \n \nጥያቄ: የቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ የቀድሞ ስም ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ፕሬዝዳንት አብዱ ዲዮፍ መቼ በተደረገው ምርጫ ነበረ የተሸነፈው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ2000 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: 31ኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ማን ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሄርበርት ሁቨር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት በተከታታይ በማሸነፍ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ ለመጨረሻጊዜ ያሸነፉት ምርጫ በስንት ዓመተ ምህረት የተደረገውን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1933 ምርጫ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአብዱልራዛቅ እ.ኤ.አ. በ1994 ላይ ያሳተሙት ‹ፓራዳይዝ› የተሰኘው ልብ ወለድ ታንዛኒያ ውስጥ በ20ኛው ምዕት ዓመት የልጅ አስተዳደግ ምን እንደሚመስል ፍንትው አድርገው ያሳዩበት ነው። በዚህ ልብ ወለድም ዓለም አቀፉን የ‹ቡከር› ሽልማት ለማግኘት መቻላቸውን ቢቢሲ ዘግቦታል፡፡ እንደ የኖቤል ኮሚቴ የሥነ ጽሑፍ ክፍል አገላለጽም፣ ‹‹[የእሳቸው] ገጸ ባህርያት ሁሌም ቢሆን በባህልና አኅጉራት መካከል የሚሽከረከሩ፣ በአሁን ሕይወትና በመጪው ሕይወት መካከል የሚመላለሱ ናቸው። በቀላሉ ሊያልፉት የማይችሉት ከባድ እውነታ ውስጥ ናቸው፡፡›› እ.ኤ.አ. በ1948 በዛንዚባር የተወለዱት አብዱልራዛቅ፣ እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መገባደጃ አገረ እንግሊዝ የገቡት ስደተኛ ሆነው ነው። በቅርቡ ጡረታ እስከወጡበት ዕለት ድረስ በካንተርበሪው የኬንት ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛና የድኅረ ቅኝ ግዛት ሥነ ጽሑፎች ፕሮፌሰር ነበሩ። ሽልማቱ፣ ደራሲው ያለፉበትን የስደተኞች ቀውስንና ቅኝ አገዛዝን በመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ውይይት እንዲደረግባቸው ያስችላል ብለዋል፡፡ ‹‹እነዚህ በየዕለቱ ከእኛ ዘንድ ያሉ ነገሮች ናቸው። ሰዎች እየሞቱ ነው፣ ሰዎች በዓለም ዙርያ አሁንም እየተጎዱ ነው፡፡ በእነዚህን ጉዳዮች ላይ በፍፁም ቀናነትና አስተውሎት መንገድ መነጋገር መላ መምታት አለብን፤›› ብለዋል የኖቤል ተሸላሚው አብዱልራዛቅ። ዓምና በሥነ ጽሑፍ ያሸነፉት አሜሪካዊው ገጣሚ ሊዊስ ግሉክ መሆናቸው ይታወሳል። የስዊድኑ አካዴሚ በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት ከሸለማቸው ታላላቅ ደራስያን መካከል ከአፍሪካ አኅጉር ስድስት ደራስያን ይገኙበታል፡፡ እነርሱም ዎሌ ሾንካ (ናይጀሪያ)፣ ነጂብ ማኅፉዝ (ግብፅ)፣ ናዲን ጎርዲመር (ደቡብ አፍሪካ)፣ ጄ.ኤም ኮትዚ (ደቡብ አፍሪካ)፣ እና ዶሪስ ሌሲንግ (ዚምባቡዌ -እንግሊዝ) ይገኙበታል፡፡ \n \nጥያቄ: በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሽልማት ያሸነፉት ሊዊስ ግሉክ ምናዊ ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አሜሪካዊው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ young men’s Cristian association tinning school በአሁኑ መጠሪያው spring filed college ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ YMCA ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን FYBA አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ Czechoslovakia ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ lasiva፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡ \n \nጥያቄ: FYBA መቼ ተቋቋመ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ እኤአ በ1932 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሊንጋላ ሊንጋላ (Lingala) ከባንቱ ቋንቋዎች ቤተሠብ አንድ ነው። የሚናገርበት በተለይ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ስሜን-ምዕራብ ክፍል፣ በኮንጎ ሪፑብሊክም፣ እንዲሁም በአንጎላና በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ነው። ተናጋሪዎቹ 10 ሚልዮን ናቸው። የሊንጋላ መነሻ ቦባንጊ በተባለ ቋንቋ ነበር። ከኮንጎ ነጻ መንግሥት አስቀድሞ ቦባንጊ የአከባቢው መደበኛ ቋንቋ ይሆን ነበር። የቤልጅክ ንጉስ አገሩን ከያዙ በኋላ የቀኝ አገሩ መንግሥት ለማስተዳደርና ለመሰበክ ቋንቋውን ጠቃሚ ሆኖ አገኙት። ካለፈው ቦባንጊ እንዲለይ የአዲሱን ቋንቋ ስም ባንጋላ ብለው ጠሩት። ሚስዮናዊዎቹ ወዲያ (1900 አ.ም.) ባንጋላን ዳግመኛ ሲያሻሽሉ \"ሊንጋላ\" እንዲህ ተፈጠረ። ሊንጋላ ከፈረንሳይኛ ብዙ ቃሎች ተበድሮ ደግሞ ከፖርቱጊዝ ተጽእኖ አለ (ለምሳሌ \"ማንቴካ\" = ቅቤ፤ \"ሜሳ\" = ጠረጴዛ፤ \"ሳፓቱ\" = ጫማ) ከእንግሊዝኛም ተጽእኖ አለ (\"ሚሊኪ\" = ወተት፤ \"ቡኩ\" = መጽሐፍ)። \n \nጥያቄ: የሊንጋላ ቋንቋ ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 10 ሚልዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: ሶቅራጥስ ከዛንቲፕ ስንት ልጆች ወለደ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሶስት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የከተማዋ የሙቀት መጠን ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 240c ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሮማንሽ ሮማንሽ ወይም ሩማንች (Rumantsch) ከስዊስ አገር 4 ብሔራዊ ቋንቋዎች 1ዱ ሆኖ ሌሎቹ 3 ጀርመንኛ ጣልኛና ፈረንሳይኛ ናቸው። ከሮማይስጥ የታደገ ቋንቋ በመሆኑ የሮማንስ ቋንቋ ቤተሠብ አባል ነውና በተለይ የሚመስለው ፈረንሳይኛ ወይም እጣልኛ ነው። የሚናገረው በግራውብውንደን (ግሪዞን) ካንቶን ስዊስ በሚኖሩ 60,000 ሰዎች ነው። ይህ ከስዊስ አገር ሕዝብ ብዛት 1% ብቻ ሲሆን ከስዊስ አገር ብሔራዊ ቋንቋዎች ሁሉ ትንሹ ነው። እንኳን በስዊስ አገር ከሚኖሩት ስርቦ-ክሮዌሽኛ ተናጋሪዎች ቁጥር ብዛት (111,000) በግማሽ ያንሳል። በስሜን እጣልያ አገር ዛሬ ለሚናገሩ ቋንቋዎች ለፍሪዩልያንና ለላዲን ቅርብ ዘመድ ነው። \n \nጥያቄ: የሮማንሽ ቋንቋ በሰሜን ጣልያን ከሚነገሩት ቋንቋዎች ለየትኞቹ ቅርብ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለፍሪዩልያንና ለላዲን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2014 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፳ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከሰኔ ፭ እስከ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በብራዚል ይካሄዳል። ብራዚል ይህን ውድድር ስታዘጋጅ ይሄ ሁለተኛ ጊዜዋ ነው። ፊፋ የ2014 እ.ኤ.አ. ውድድር በደቡብ አሜሪካ እንደሚካሄድ በ2007 እ.ኤ.አ. ካወጀ በኋላ ብራዚል ያለማንም ተቀናቃኝ አዘጋጅ አገር ሆና ተመርጣለች። የ፴፩ አገራት ብሔራዊ ቡድኖች ከጁን 2011 እ.ኤ.አ. ጀምሮ የተካሄዱ የማጣሪያ ውድድሮችን በማለፍ ከብራዚል ጋር በመጨረሻው ውድድር ላይ ለመሳተፍ በቅተዋል። በጠቅላላው ፷፬ ጨዋታዎች በ፲፪ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አዲስ የተገነቡ ወይም የተሻሻሉ ስታዲየሞች ይከናወናሉ። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎል ላይን ቴክኖሎጂ በጥቅም ላይ ውሏል። በ1930 እ.ኤ.አ. ከተካሄደው የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ጀምሮ ሁሉም የዓለም ዋንጫ ሻምፕዮን አገራት (ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ፣ ጀርመን፣ ኢጣልያ፣ እስፓንያ እና ኡራጓይ) በዚህ ውድድር ውስጥ ተሳታፊ ናቸው። ከዚህ በፊት በደቡብ አሜሪካ የተዘጋጁትን ዋንጫዎች እንዳለ የወሰዱት የደቡብ አሜሪካ ቡድኖች ናቸው። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $576 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2010 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የ፴፯ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $70 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1.5 ሚሊዮን የተረከበ ሲሆን ቀሪው ገንዘብ እንደሚመለከተው ተከፋፍሏል፦ $8 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በምድብ ደረጃ የወደቀ ቡድን (፲፮ ቡድኖች) $9 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በየ፲፮ ዙር የወደቀ ቡድን (፰ ቡድኖች) $14 ሚሊዮን - ለያንዳንዱ በሩብ ፍፃሜ የወደቀ ቡድን (፬ ቡድኖች) $20 ሚሊዮን - በአራተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $22 ሚሊዮን - በሶስተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $25 ሚሊዮን - በሁለተኛ ደረጃ ለጨረሰው ቡድን $35 ሚሊዮን - ለአሸናፊው ቡድን በአስራ ሁለት ከተማዎች የሚገኙ አስራ ሁለት ስታዲየሞች ለውድድሩ ተዘጋጅተዋል። ሰባቱ አዲስ የተገነቡ ሲሆን አምስቱ ደግሞ የተሻሻሉ ስታዲየሞች ናቸው። \n \nጥያቄ: ብራዚል በ2014 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ስታዘጋጅ ስንተኛዋ ነበር", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለተኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ የየት አካባቢ ነዋሪዎች ብሔራዊ ቋንቋ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የጉጃራት ክፍላገር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nጉጃራቲ ጉጃራቲ (ગુજરાતી) በህንዳዊ-አውሮፓዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ የሚገኝ ቋንቋ ነው። በዓለሙ ውስጥ በ46 ሚልዮን ሰዎች ይናገራል፤ ከነዚህም 45.5 ሚልዮን በህንደኬ፣ 250,000 በታንዛኒያ፣ 150,000 በዩጋንዳ፣ 100,000 በፓኪስታንና 50,000 በኬንያ አሉ። በሕዝብ ብዛት የዓለሙ 23ኛ ቋንቋ ነው። በምእራብ ህንደኬ ያለው የጉጃራት ክፍላገር ይፋዊ ቋንቋ ነው። የጉጃር ሕዝብ ወደ ህንደኬ የደረሱ በ5ኛው መቶ ዘመን ሲሆን በ6ኛው መቶ ዘመን ዛሬ ጉጃራት በሚባለው አገር ሰፈሩ። የራሳቸውን ቋንቋ ቶሎ ትተው እንደ አገሩ ሰዎች ሳንስክሪት ለመናገር ጀመሩ። በ12ኛው ክፍለ ዘመን ግን ሳንስክሪት ተለውጦ ብዙ አዲስ ቋንቋዎች ተወለዱ። ከነዚሁም አንድ ጉጃራቲ ነበር። አብዛኛው ተናጋሪዎቹ የህንድ ሃይማኖት ተከታዮች ቢሆኑም ለረጅም ዘመን የእስላም ገዢዎች ስለነበሩባቸው ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከፋርስ ሆኗል። ከዚያ በላይ በንግድ ምክንያት ብዙ ቃሎች ከፖርቱጊዝ ወይም ከእንግሊዝኛ ተበደሩ። የሚጻፍበት በራሱ ጉጃራቲ ፊደል ነው፤ ይህም ከላይኛ መስመር በማጣቱ በስተቀር የህንዲ ደቫናጋሪ ፊደል ይመስላል። \n \nጥያቄ: ጉጃራቲ ቋንቋ በምድር በምን ያህል ተናጋሪዎች ለመግባቢያነት ያገለግላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ46 ሚልዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nገብረሃና ገብረማሪያም አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም (፲፯፻፺፯ - ፲፰፻፺፬ ዓ.ም.) ዕውቅ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። አባታቸው መምህር ገብረ ማርያም ምጥኑ ሲባሉ እናታቸው ወይዘሮ ሳህሊቱ ተክሌ ይባሉ ነበር። ገብረሃና ገብረማሪያም በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ በ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ተወለዱ። ገብረሃና እቴጌ መነንን መዝሙርን፣ ውዳሴ ማርያምንና ሌሎችንም አስተምረው ከጨረሱ በኋላ ለከፍተኛ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በእቴጌይቱ ትዕዛዝ ወደ ጎንደር ተላኩ። ትምህርታቸውን ከጨረሱ በኋላም በእቴጌይቱ ትዕዛዝ የአለቃነት ማዕረግ ተሰጣቸው። ከዚያም ገብረሃና በጎንደር አካባቢ የሚገኙትን ቤተ ክርስቲያናት ብቃት በተሞላበት ሁኔታ ያስተዳድሩ ጀመር። እንደ ትልቅ ምሁር ይታዩ ጀመር። በተለይ ፍትሐ ነገስትን በመተርጎም የሚወዳደራቸው ወይም የሚስተካከላቸው አልነበረም። አለቃ ገብረሃና አቶ ሙንሮዝ በተባለ አውሮጳዊ በ1890 ዓ.ም. ፎት እንደተነሱ ሞላቨር ይገልጻል። ዓፄ ቴዎድሮስ ስልጣን ከያዙና እራሳቸውንም ዳግማዊ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ብለው ዙፋናቸውን በጫኑበት ጊዜ በሀገሪቱ ከፍትሐ ነገስት ሌላ የተፃፈ ሕግ ባለመኖሩ አለቃ ገብረሃና በተለይ ፍትሐ ነገስትን መሠረት በማድረግ ንጉሡ ሀገርን እንዲያስተዳድሩ ይረዱዋቸው ነበር። በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ቤተክርስቲያን ብሉይ ኪዳንንና አዲስ ኪዳንን በመተርጎም ትልቅ አገልግሉት ቢያደርጉም ትልቁን አስተዋጽዖ ያደረጉት በሕግና በቤተ ክርስቲያን ዜማና አቋቋም ነበር። እንደዚሁም የፈጠሩት አዲስ ዓይነት የቤተክርስቲያን አቋቋም ከደብረታቦር ወደ ሸዋ እና ትግራይ ተሰራጭቷል። ይህንንም አቋቋም ከብቸኛው ልጃቸው በኋላ ተክለ ብለው ሰየሙት። ይህም አቋቋም አስደሳችና ማራኪ የአቋቋም ዘዴ ነው። \n \nጥያቄ: አለቃ ገብረሃና ገብረማሪያም የት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በደብረታቦር አውራጃ በፎገራ ወረዳ ልዩ ስሟ ናበጋ ጊዮርጊስ በምትባል ቦታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአፈወርቅ ተክሌ የዓለም ሊቀ ሊቃውንት፣ የኪነ ጥበብ ምሑር የተከበሩ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በዓለም የታወቁና የተከበሩት ኢትዮጵያዊ ሰዓሊ አፈወርቅ ተክሌ በሰሜን ሸዋ በምትገኘው የሸዋ ነገሥታት ከተማ አንኮበር ላይ ጥቅምት ፲፫ ቀን ፲፱፻፳፭ ዓ/ም ከአባታቸው አቶ ተክሌ ማሞ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ፈለቀች የማታወርቅ ተወለዱ። ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በግፍ ሲወራት፣ የልጅነት ትዝታቸውም ይሄው የግፍ ወረራ እና ጦርነት የሚያስከትለው የሰው፣ የንብረት እና የባህል ጥፋት ፤ ከነጻነትም በኋላ ዐቢዩ ሥራ በወረራ የተበላሸችውን ሀገራቸውን እንደገና መገንባት እንደሆነ ነው። ለዚህም የሀገር ግንባታ አስፈላጊውን እውቀት መሸመት የፈለጉት በ ማዕድን ምሕንድስና ዘርፍ ነበር። ወላጆቻቸውና ዘመድ አዝማዶች ግን የኪነ ጥበብ ስጦታቸውን በቤታቸውና በከተማው ዙሪያ በሚስሏቸው ስዕሎች ተገንዝበውት ነበር። ገና በአሥራ አምስት ዓመታቸው በ፲፱፻፵ ዓ/ም ለከፍተኛ ትምህርት ተመርጠው የምሕንድስና ትምህርታቸውን ለመከታተል ወደ እንግሊዝ አገር ይላካሉ። አፈወርቅ ተክሌ በእንግሊዝ አገር የአዳሪ ተማሪ ቤትን ኑሮ ሲያስታውሱ የባዕድ ባህላት፣ የአየር ለውጥ እና የተለመደው የተማሪ ቤት ዝንጠላ እንዳስቸገራቸው ያወሳሉ። ቢሆንም ትምሕርታቸውን በትጋት ሲከታተሉ ቆዩ። በተለይም በሒሣብ፣ በኬሚስትሪ እና በታሪክ ትምሕርቶች ጥሩ ውጤት በማምጣት ሰለጠኑ። ነገር ግን አስተማሪዎቻቸው የተፈጥሮ ስጦታቸው ኪነ ጥበብ እንደሆነ ለመገንዘብ ብዙ ጊዜም አልወሰደባቸውም። በነሱም አበረታችነት በእዚህ ስጦታቸው ላይ የበለጠ ለማተኮር ወስነው በሎንዶን የኪነ ጥበብ ማእከላዊ ትምሕርት ቤት ተመዝግበው ገቡ እዚህ ትምህርት ቤት ጥምሕርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለከፍተኛ ጥናት በስመ ጥሩው የሎንዶን ዩኒቨርሲቲ የስሌድ ኪነ ጥበብ ማዕከል የመጀመሪያው አፍሪቃዊ ተማሪ (ከተከተሏቸው አፍሪቃውያን አንዱ የሱዳን ተወላጁ ኢብራሂም ኤል ሳላሂ ናቸው) በመሆን ገቡ። እዚህ በስዕል፣ ቅርጽ እና በአርክቴክቸር ጥናቶች ላይ አተኩረው ተመረቁ። ትምሕርታቸውን አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ፣ በየጥቅላይ ግዛቶቹ እየተዘዋወሩ፣ በየቦታው እስከ ሦስት ወራት በመቀመጥ የኢትዮጵያን ታሪክ እና የብሔረሰቦቿን ባህልና ወግ በሚገባ አጥንተዋል። \n \nጥያቄ: አፈወርቅ ተክሌ በስንት ዓመተ ምህረት ነበር ለከፍተኛ ት/ት ተመርጠው ወደ እንግሊዝ ሀገር የተላኩት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲፱፻፵ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁን እንዲጠብቀው የተመደበው ሰው ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ካፕቴን ስፒዲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012(ኤፍቢሲ) ኡበር የተሰኘው የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት ተባባሪ መስራች ትራቪስ ካላኒክ በዓመቱ መጨረሻ ከቦርድ አባልነታቸው ሊለቁ መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡ ይሁን እንጂ የ43 ዓመቱ ትራቪስ በድርጅቱ ውስጥ ካሉ ዘጠኙ ዳይሬክተሮች ውስጥ አንዱ ሆነው የሚቀጥሉ መሆኑን ነው የተናገሩት። ትራቪስ ካላኒክ እንደ አውሮፓውያ ኑ አቆጣጠር 2017 ላይ በድርጅቱ በተስተዋሉ የተለያዩ የሙስና ቅሌቶች ምክንያት ስራ ለማቆም ጫፍ ደርሰው ነበር ። ይህን ተከትሎም በኡበር ድርጅት ውስጥ ያላቸውን አብዛኛውን የአክሲዮን ድርሻ መሸጣቸው ነው የተነገረው። ትራቪስ ካላኒክ በአስር ዓመቱ መገባደጃ ኩባንያው ያለው የሕዝብ ግንኙነት እና በጎ አድራጎት ላይ ለማተኮር ለእኔ ትክክለኛ ጊዜ ይመስለኛል፤ በዚህም ደስተኛ ነኝ ተናግረዋል ፡፡ ካናኒክ በጣም ዝነኛ የሆነው የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት በመመስረት በዓለም ዙሪያ የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ምንጭ፣ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: ኡበር በተሰኘው የታክሲ አገልግሎት ሰጪ ድርጅት ውስጥ የቦርድ አባል የነበሩ አሁን ሊለቁ የወሰኑት የቦርድ አባል ስማቸው ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ትራቪስ ካላኒክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: የአጼ ኃይለሥላሴ ወላጅ እናት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወይዘሮ የሺ እመቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ የሙዚቃን ትምህርትን ያስተማራቸው ማነው ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበቶኪዮ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ በመሳተፍ በ58 ኪ.ግ ምድብ 7ኛ በመያዝ ዲፕሎማ አግኝታለች፡፡ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ጊዜ በወርልድ ቴኳንዶ የወከለው አትሌት ሰለሞን ቱፋ እየተካሄደ ባለው የቶኪዮ ኦሎምፒክ በ58 ኪ .ግ ምድብ ባደረገው ውድድር 7ኛ ደረጃ በመያዝ ዲፕሎማ መገኘቱን ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ በወርልድ ቴኳንዶ የተሳተፈችው ለስንተኛ ጊዜ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጮቄ ተራራ ጠቅላላ ስፋቱ ስንት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 53558 ሄክታር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል። ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማራያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል። ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ ይኖራል። አልፎም በግራኝ አህመድ ዘመን በእሳት ጋይቶ የነበረችውን አክሱም ፂዮን በአዲስ መሰረት እንደገና ማሰራት ችሎአል። ፋሲለደስ በዘመኑ እጅግ ተወዳጅ ንጉስ ቢሆንም አመጽ መነሳቱ አልቀረም። በላስታ ለምሳሌ በ1637 መልክዓ ክርስቶስ በተባለ ሰው መሪነት ጦርነት ተነስቶ አፄ ፋሲልን ስጋት ላይ ቢጥልም በሚቀጥለው አመት በተደረገው ጦርነት አመፁ ሊገታ ችሎአል። ፋሲለደስ ፖርቱጋሎችን ቢያባርርም ከውጭው አለም ጋር ብዙ ግንኙነት ያደርግ ነበር። ለምሳሌ በ1664-5 የህንድ ንጉስ አውራንግዘብ ሲነግስ መልካም ምኞትን በመልክተኞቹ ለሙግሃሉ መሪ ልኮ ነበር። በ1666 ልጁ ዳዊት ሲያምጽ፣ ወህኒ ተብሎ ወደሚታወቀው አገር በግዞት ልኮት ነበር። ይህም ከጥንቶቹ የኢትዮጵያውን ነገሥት ተፎካካሪያቸውን ወደ አምባ ግሽን በግዞት እንደሚልኩት ስርዓት ነበር። \n \nጥያቄ: መልክዓ ክርስቶስ በአፄ ፋሲል ላይ ያመፁት መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1637 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን ከመቼ እስከ መቼ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነው ሰሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nለአጽዋማትና በዓላት ማውጫ ወሳኝ የሆነው ነጥብ መባጃ ሐመር ነው፡፡ መባጃ ሐመር መባጊያ ሐመር እየተባለም ይጠራል፡፡ መባጊያ ሐመር ሲሆን የበጋ መመላለሻ የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በሌላ በኩል መባጃ በራሱ ማቆያ፣ ማክረሚያ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ሐመር መርከብ፣ መጓጓዣ የሚለውን ትርጉም ያስገኛል፡፡ መባጃ ሐመር የመጥቅዕና የዕለታት ተውሳክ ድምር ሆኖ አጽዋማትና በዓላት የሚውሉበትን ቀን ያመለክታል፡፡ በሐመር የተመሰለውም አጽዋማትና በዓላት ወደ ላይና ወደታች የሚመላለሱበት ሥርዓት /መርከብ/ ስለሆነ ነው፡፡ በአጠቃላይ መባጃ ሐመር ማለት የአጽዋማትንና የበዓላትን መዋያ ወይም መግቢያ ቀን ለማወቅ የሚያገለግል ልዩ ቁጥር ማለት ነው፡፡ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አራቱ በመባጃ ሐመር መሠረት በየዓመቱ እየተቀያየሩ ወይም ቀመር እየተሠራላቸው የሚወጡ ሲሆን፣ ሦስቱ ግን ያለ መባጃ ሐመር በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ይባጃሉ፡፡ በመባጃ ሐመር የሚባጁት አራት አጽዋማት ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌና ጾመ ሐዋርያት ሲሆኑ፣ ያለ ማባጃ ሐመር በየዓመቱ ቋሚ ጊዜ ይዘው የሚብቱት ሦስቱ አጽዋማት ደግሞ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድና ጾመ ማርያም /ፍልሰታ/ ናቸው፡፡ ከላይ በተመለከትነው መሠረት መባጃ ሐመር የአጽዋማትና የበዓላት ማስገኛ ልዩ ቁጥር ነው ካልን ቁጥሩ እንዴት እንደሚገኝ ማወቅ ያስፈልገናል፡፡ መባጃ ሐመርን ለማግኘት መጥቅዕንና በዓለ መጥቅዕ የዋለበትን ዕለት ተውሳክ እንደምራለን፡፡ \n \nጥያቄ: በኦርቶዶክስ እምነት ስንት የአዋጅ አጽዋማት አሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከሰባቱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: አይቮሪኮሰስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ውጤቶች በመቶኛ ምን ያህሉን የመማሪያ ክፍሎች ለመስራት ተጠቀችበት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 5 በመቶውን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: የአፍሮ-ኤስያዊ ቋንቋ ቤተሰብ ንዑስ መደቦች እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቴምፕላርስ ቴምፕላር ወይም በሙሉ ስማቸው የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች የሚባሉት በጣም ታላቅ እና ሃይለኛ ከነበሩት ክርስቲያናዊ ወታደራዊ ስርአቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው። ይህ ስርዓት በ1088 ዓ.ም. ከተካሄደው አንደኛው የመስቀል ጦርነት በኋላ ማለትም በ1110 ዓ.ም. አዲስ የተቋቋመውን የእየሩሳሌም መንግስት ከእስላሞች ለመከላከልና ወደ ከአውሮፓ ወደ እየሩሳሌም የሚጎርፉትን ተሳላሚዎች ደህንነት ለመጠበቅ የተመሰረተ ነው። ቴምፕላሮች የተዋቀሩት በገዳማዊ ስርዓት ሲሆን ይኸውም የሲሰተርሲያን ስርዓት መስራች የነበረው የክላርቮው በርናርድ በዘረጋላቸው ህግጋት መሰረት ነው። ቴምፕላሮች ከብዙ መሳፍንት ጋር ግንኙነት ስለነበራቸው እና ጳጳሱም እነሱ ከሚቆጣጠሩዓቸው ቦታዎች ሁሉ ግብርና አስራት እንዲሰበስቡ ስለፈቀደላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝነኛና ሃይለኛ ለመሆን ችለዋል። ቴምፕላሮቹ አራት ዋና ክፍሎች የነበሩአቸው ሲሆን እነዚሁም ዋነኞቹ ወታደሮች ወይም ናይትስ የሚባሉት ሙሉ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ከዝቅተኛ የህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡት ወይም ሰርጀንትስ በመባል የሚታወቁት፤ መለስተኛ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ገበሬዎች ዋነኛው ስራቸው የስርዓቱን ንብረት ማስተዳደር የነበረ፤ እንዲሁም ካህናት ስራቸው የስርዓቱን መንፈሳዊ ህይወት መከታተል የነበረ ናቸው። \n \nጥያቄ: አንደኛው የመስቀል ጦርነት የተካሄደው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1088 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየቴክኖሎጂ ኩባንያው አፕል 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ተቀጣ። ኩባንያው በፈረንሳይ የንግድ ውድድርና ሸማች ባለስልጣን ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል በሚል ነው ለቅጣት የተዳረገው። ቅጣቱ የተጣለበት መስሪያ ቤቱ በኩባንያው ላይ ለ10 ዓመት ምርመራ ካደረገ በኋላ ነው ተብሏል። አፕል ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ዋጋዎችን በመወሰንና በሌሎች የገበያ ተወዳዳሪነት ላይ ተፅዕኖ አሳርፏል በሚል ቅጣቱ እንደተወሰነበትም ታውቋል። ከዚህ ባለፈም ሁለት የአፕል አከፋፋዮች ላይ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል። አካፋፋዮቹ አፕል ገበያውን ብቻውን እንዲቆጣጠር በማሴር ነው ማዕቀብ የተጣለባቸው። ኩባንያው በፈረንሳይ የ40 ዓመት አገልግሎት በመስጠት ለ240 ሺህ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን መረጃዎች ያመላክታሉ። \n \nጥያቄ: አፕል ኩባንያ በፈረንሳይ በምን ምክንያት ነው የተቀጣው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከንግድ ውድድር ህጉ ውጭ ተንቀሳቅሷል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ በርካታ ስራዎችን አበርክቶ በስንት ዓመተ ምህረት አረፈ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1910 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የኢያን ስሚዝ አመራር በዚምባቡዌ ከስንት መሪዎች ጋር ነበር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት የተፈራረመው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሶስት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: የራስ መኮንን በታመሙ ጊዜ ሕክምና የተደረገላቸው የት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቁልቢ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: እቴጌ ጣይቱ በየት ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ደብረ ታቦር ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሞሪታኒያ ሞሪታኒያ (አረብኛ፡ موريتانيا‎) በይፋ የሞሪታኒያ እስላማዊ ሪፐብሊክ፣ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በምዕራብ ከአትላንቲክ ውቂያኖስ፣ በደቡብ-ምዕራብ ከሴኔጋል፣ በምሥራቅና ደቡብ-ምሥራቅ ከማሊ፣ በሰሜን-ምሥራቅ ከአልጄሪያ፣ እና በሰሜን-ምዕራብ ከምዕራባዊ ሣህራ ጋር ትዋሰናለች። የአገሩዋ ስም የመጣው ከጥንቱ የሞሪታኒያ መንግሥት ነው። ዋና እና ትልቁዋ ከተማዋ ኑዋክሾት ናት። በዛሬው ሞሪታንኒያ በመጀመሪያ የሠፈሩት የባፎር ሰዎች ነበሩ። እነዚህ ስዎች ከዘላን ሕይወት ወደ ግብርና ከተቀየሩት የመጀመሪያ የሰሃራ ሕዝቦች አንዱ ናቸው። ከ5ኛው እስከ 7ኛው ምዕተ ዓመት፣ ባፎሮች በበርበር ህዝቦች ፍልሰት ምክኒያት ተፈናቀሉ። ብዙዎቹ የሞሪታኒያ ሕዝብ በመቆያ ግብርና ቢኖሩም ይሄ ወደ ውጭ አገር ለመላክ አይደለም። በተለይ ወደ ውጭ የሚላከው ብረት፣ ፔትሮሊየም፣ እና ዓሣ ናቸው። ሞሪታኒያ በ12 ዊላያ በሚባሉ ክልሎችና በአንድ የአስተዳደር አካባቢ ተከፍላልች። እነዚህም ክልሎች በ44 ሙጋታ በሚባሉ ክፍሎች ተከፍለዋል። \n \nጥያቄ: ሞሪታንያ በደቡብ-ምእራብ አቅጣጫ የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከሴኔጋል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: ኩሻዊ ቋንቋ በምን መደብ ይካተታል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: ደቡብ አፍሪካ የፊፋ ዓለም ዋንጫን ያዘጋጀችው በስንት ዓመተ ምህረት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፳፻፪ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመልከአ-ምድር አንጎላ፣ በ1,246,620 ካሬ ኪ.ሜ. ከኒጄር ቀጥላ ከዓለም 23ኛው ትልቅ አገር ናት። በስፋት ከማሊ ጋር ትነጻጸራለች። የአሜሪካ የቴክሳስ ክፍላገርን ሁለት ዕጥፍ ታክላለች። አንጎላ ከደቡብ በናሚቢያ፣ ከምሥራቅ በዛምቢያ፣ ከሰሜን-ምሥራቅ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ከምዕራብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። የአንጎላ አማካይ የባህድ ዳር የአየር ሁኔታ በክረምት 16° ሴንቲግሬድና በበጋ 21° ሴንቲግሬድ ነው። አንጎላ ሁለት ወቅቶች አሏት። እነዚህም ደረቅና ዝናባማ ናቸው። መጓጓዣ በአንድ ላይ ርዝመታቸው 2,761 ኪ.ሜ. የሆኑ ሦስት የባቡር መንገዶች፤ 76,626 ኪ.ሜ. አውራ ጎዳና ከዚህም ውስጥ 19,156 ኪ.ሜ. አስፋልት፤ 1,295 ኪ.ሜ. የውሃ መንገድስምንት ትልቅ ወደቦች፤ 243 የአውሮፕላን ማረፊያዎች ከነዚህም 32ቱ የአስፋልት መንደርደሪያ ያላቸው፤ አንጎላ የሰፋ የመጓጓዛ አውታር ቢኖራትም በጊዜ ማለፍና ጦርነት ምክንያት መንገዶች አስፈላጊ ጥገኛ አልተደረገባቸውም። በአንዳንድ ቦታዎች አሽከርካሪዎች መጥፎ ቦታዎችን ለማለፍ ሲሉ ከመንገድ ውጭ ይነዳሉ። እንደዚህ ከማድረግ በፊት ግን በመንገድ ዳር ያሉ በመሬት ውስጥ ስለተቀበሩ ፈንጂዎች የሚያስጠነቅቁ ምልክቶችን ማስተዋል ያስፈልጋል። ኢኮኖሚ የአንጎላ ኢኮኖሚ ትልቅ ለውጥ አሳይቷል። የሩብ ምእተ ዓመት ጦርነት ያሳደረበት ተጽእኖን አልፎ ዛሬ በዓለም ውስጥ በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉት ኢኮኖሚዎች ይመደባል። በ2004 እ.ኤ.አ. የቻይና ኤክሲምባንክ ፪ ቢሊዮን ብር ለአንጎላ አበድሯል። ይህ ገንዘብ እንደ መንገዶች ያሉትን የአንጎላ መሠረታዊ ተቋሞች ለማሻሻል የሚውል ነው። ዘ ኢኮኖሚስት መጽሄት በ2008 እ.ኤ.አ. እንደዘገበው ነዳጅና ዕንቁ የአንጎላ ዋና ኤክስፖርቶችና የገቢ ምንጮች ናቸው። \n \nጥያቄ: አንጎላ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ከየት አቅጣጫ ትዋሰናለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ በ2021 የሥነ ጽሑፍ ኖቤል የሚሸልማቸው ድርጅት ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የስዊድን አካዴሚ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nክቡር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ ከተጫወታቸው ሙዚቃዎች ውስጥ “ስቆ መኖር”፣ “እውነት ማሪኝ”፣ የሚሉትን ግጥሞች፣ “ዋይ ዋይ ሲሉ”፣ “ውሸት ለመናገር”፣ “ልብሽን ለአፈርሰው”፣ “ኮቱሜ”፣ የሚሉትን ዘፈኖች ግጥምና ዜማዎች የደረሰው ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ እንደሆነ ይታወቃል። ከዚህም ሌላ ለድምፃዊት ብዙነሽ በቀለ “አይወጣኝም ክፉ ነገር” በሚል የዘፈነችውና በብዙኀን ዘንድ ተወዳጅነት ያለውን (“ወደመጣሁበት ምድር፣ እስክመለስባት በክብር፣ ሰውን ከማስደሰት በቀር፣ አይወጣኝም ክፉ ነገር፣ ...” ) ሙዚቃውን ያቀናበረው ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ነው። ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ “ፍላጎቴ”፣ “ምን ነበር”፣ “ምንድነው ትዝታህ”፣ ... የተሰኙትን የብዙነሽ በቀለን ዘፈኖች ያቀናበረ ሲሆን፣ “ከንቱ ሥጋ” የሚለውንና ሌሎችንም ዘፈኖችዋን ግጥም ደርሶላታል። “አታሳየኝ ጭንቁን”፣ “የፍቅር ወጋገን”፣ “ቃልኪዳን”፣ “በብር አይጋዛም”፣ “ፍቅርህ ቀሰቀሰኝ”፣ … የተሰኙትን ዜማና ግጥሞች ያዘጋጀው ሣህሌ ደጋጎ እንደነበረ ይታወቃል። “ሰው ከተሰማራ” በተሰኘው ዘፈኗ ለምትታወቀው ለድምፃዊት መንበረ በየነ ደግሞ “እንዴት ከረማችሁ” የሚለውን ዘፈን ግጥም የደረሰው ሌ /ኮ /ል ሣህሌ ነበር። “የቆራጡ መሪ ፍሬው ጎመራ” የተሰኘውንና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለማርያም ላቀነቀነችው ለድምፃዊት ውብሻው ስለሺ ደግሞ “ይህ ነው ጌትነት”፣ “የምድር ፈተና” የተሰኙትንና በ 1966 ዓ /ም የታተሙትን ዘፈኖችዋን ያቀናበረላት ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ነበር። በዕድሜ ዘመን የኪነ ጥበብ አገልግሎት የክብር ሜዳሊያ እና የ 20 ሺህ ብር ተሸላሚ የሆነው ሣህሌ ደጋጎ፤ የ 30፣ የ 20 እና የ 10 ዓመት የረዥም ዘመን አገልግሎት የወርቅ፣ የብርና የነኀስ እንደዚሁም የተዋጊ ወታደርነት የደረት ዓርማ ኒሻን ተሸለሚም ነበር። ሙዚቃ ቀማሪው ሣህሌ ደጋጎ ከባለቤታቸው ከወ /ሮ ወይንሸት ተክሉ 4 ሴት እና 3 ወንድ ልጆችን አፍርቶ የ 10 ልጆች አያት ለመሆን በቅቷል። በቀብር ሥነ ሥርዓቱም ላይ ከቤተሰቡ ውጪ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ወዳጅ ዘመዶቹ፣ የቀድሞ የሥራ ባልደረቦቹ እና አድናቂዎቹ፣ የመኖሪያ አካባቢያው ሰዎች ተገኝተው በዕንባ ሸኝተውታል። የአበባ ጉንጉንም አኑረዋል። ኢህአዲግ ግንቦት 20 ቀን 1983 ዓ .ም . ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረ በኋላ ሌ /ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ለሰባት ወራት በጦላይ የጦር ማሠልጠኛ ማዕከል ታስሮ እንደነበር ይታወቃል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ባለቤታቸው ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ወ /ሮ ወይንሸት ተክሉ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ የተካሄደው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፳፱ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: የሶቅራጥስ እናት ፌርናት ምን ሙያ ነበራት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አዋላጅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበኢትዮጵያ ካሉ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ውስጥ 59 ነጥብ 5 ከመቶ የሚሆኑት ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል /password/ እንደሚጠቀሙ ጥናት አመለከተ። ተጠቃሚዎች የስልክ ቁጥርን መጠቀማቸው ጠንካራ የይለፍ-ቃል እንደተጠቀሙ እንደሚሰማቸውም በጥናቱ ተመላክቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ መጠን እያደገ መምጣቱም ነው የተነገረው። በኢትዮጵያ ያለው በሳይበር ደህንነት የግንዛቤ መጠንም ዝቅተኛ እንደሆነ የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ ጥናት ያመለክታለል። ኤጀንሲው በ2011 ዓ.ም 1 ሺህ 635 የሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ሀገር-አቀፍ የሳይበር ደህንነት ምዘና ጥናት አከናውኗል። በጥናቱ ከተሳተፉት መካከል 975 (59 ነጥብ 5 በመቶ) ያክሉ ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል/password/ በመጠቀም ጠንካራ የይለፍ-ቃል እንደተጠቀሙ እንደሚሰማቸው ጥናቱ ያመለክታል። በተጨማሪም 59 ነጥብ 1 በመቶ ያክሉ የጥናቱ ተሳታፊዎች የይለፍ ቃሎቻቸውን የሚታይ ቦታ ላይ ጽፈው ማስቀመጥን እንደ ማስታወሻ መንገድ እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል። 67 ነጥብ 6 ከመቶ የሚሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጩ መረጃዎች ትክክለኛ ናቸው ብለው እንደሚያምኑም ነው የተነገረው። በመሆኑም የሳይበር ደህንነት ጉዳይ በቸልታ ሊታለፍ የማይገባውና የለት ተለት የህይወታችን አካል እየሆነ በመምጣቱ ተገቢውን ትኩረትና ጥናቃቄ ልናደርግ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ የሰራውን ጥናት አስመልክቶ ያወጣው መረጃ ያመለክታል። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ካሉ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ውስጥ ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል የሚጠቀሙት ምን ያህል ፐርሰንት ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 59 ነጥብ 5 ከመቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ በ1870 ዓ.ም በትዳር የተጣመራት እንስት ማን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኦሊቭያ ላንግዶንን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: የነጭ ወራሪ ጦርን በማሸነፍ ታሪክ የሰራችው ብቸኛ አፍሪካዊት ሀገር ማን ናት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ኢትዮጵያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለስንት ዓመት በተከታታይ ተጫወተ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ለ10 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ሬይን ሜከርስ እንጦጦ አካባቢ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለደራ ጋር አንድ ላይ በመሆን ችግኝ የተከሉት መች ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1995 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዮወሪ ሙሴቪኒ የየት ሀገር ፕሬዝዳንት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የዩጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበጀት በጀት ማለት ለወደፊቱ የሚመጣን ገቢና ወጪ የሚተነብይ የንዋይ/ገንዘብ እቅድ ነው። በዚህ እቅድ ውስጥ ቁጠባ፣ ብድር እና ወጪ ይካተታሉ ። ግለሰቦች ወይንም ቢዝነሶች ገቢና ወጪያቸው ሲመረመር ከሞላ ጎደል ቋሚ ሆኖ ስለሚገኝ የበጀት ጥቅም ከዚህ ይመነጫል። ማለት፣ ቋሚ ገቢ ወጪ፣ ለወደፊት ይሚሆነን ለመተንበይ አመቺ ነው። ተንብዮ በበጀት መመራት ግለሰቦብ በገንዘባቸው/ንዋያቸው ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖራቸው ያደርጋል። አላስፈላጊ ወጭወችን ለመለየት እና በአቅም መኖርን ለማወቅ ይረዳል። የበጀት ዋናው ጥቅም አንድ ግለሰብ በራሱ ገቢና ወጪ ላይ ሙሉ ቁጥጥር እንዲኖረው ማስቻሉ ነው። ስለሆነም ግለሰቦች ዕዳ ውስጥ መግባት ሲጀምሩ በቶሎ እንዲያውቁ ይሆናሉ። ስለሆነም ችግሩ ከመባባሱ በፊት አስቀድመው እርምጃ ለመውሰድ ይችላሉ። አንድ ግለሰብ ዕዳ ውስጥ እየገባ መሆኑን መረዳት ሲጀመር መጀመሪያውኑ የዕዳውን አይነት መለየት አስፈላጊ ነው። ቅድሚያ ትኩረት አግኝተው መከፈል ያለባቸው እማይለወጡ ዕዳወች (ምሳሌ ሞርጌጅ፣ የቤት ኪራይ ..) እና ቀስ ብለው ሊከፍሉ የሚችሉ ተለዋዋጭ ዕዳዎች (ምግብ፣ የኤሌክትሪክ፣ ውሃ ና ሌሎች በጥንቃቄ ሊቀነሱ የሚችሉ ቢሎች) ተለየተው ሊታወቁ ይገባል። ዕዳዎቹ ከተለዩ በሗላ፣ ዕዳዎቹን ለማስወገድ መንገድ ማበጀት ተገቢ ነው። ለዚህ ተግባር እንዲረዳ «በደህና ጊዜ» በትንሽ በትንሹ ማጠራቀም ጥሩ ነው። ነገር ግን ይህ ተደርጎ ካልሆነ፣ ቀሪ እዳን ቀስ በቀስ ለመክፍል የሚያስችል ስምምነት ከዕዳ-ሰጪው ጋር መግባት ጥሩ ነው። ባንኮች የአንድ ግለሰብ ዕዳ ባለቤት ከሆኑ፣ ግለሰቡን ለመርዳት ፍላጎት ይኖራቸዋል፣ ምክንያቱም ከርሱ ነውና ገንዘብ የሚያገኙት። ለዚህ ተግባር እንዲረዳ ኮንሶሊዴሽን (ሁሉን ዕዳን በአንድ ላይ መሰብሰብ) እና ሪፋይናንሲንግ (ብድርን፣ በተራዘመ ጊዜ እንዲከፍሉ ማስቻል) የሚባሉ ሁለት መሳሪያወችን ባንኮች ይጠቀማሉ። እኒህን ማግኘት እዳ ከቁጥጥር ውጭ እንዳይወጣ ይረዳሉ። ሆኖም እኒህ እድሎች ካልተገኙ ዴቢት ስፔሻሊስት የተሰኙ መካሪዎችን ማነጋገር ይቻላል። \n \nጥያቄ: ለወደፊቱ የሚመጣን ገቢና ወጪ የሚተነብይ የንዋይ ወይም የገንዘብ እቅድ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በጀት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የፈለሰፉት ለእንስሳት የሚሆን ክትባት የምን በሽታ መድኃኒተ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የደስታ በሽታ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአይቮሪኮስት በትምህርት ቤቶች የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን እየተጠቀመች ነው። በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሃገር አይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል። በዚህ ሳቢያም 1 ነጥብ 6 ሚሊየን ያህል ህፃናት ወደ ትምህር ቤት እንደማይሄዱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህን የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍም አንድ የኮሎምቢያ ኩባንያ ከተባበሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር በመተባበር በቆሻሻ መጣያ ስፍራ የተከማቹ የፕላስቲክ ውጤቶችን በመጠቀም የመማሪያ ክፍሎችን መስራት ጀምሯል። ከፈረንጆቹ 2018 ጀምሮም ከተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶች 26 የመማሪያ ክፍሎች ተሰርተዋል ነው የተባለው። በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም 528 የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት እቅድ የተያዘ ሲሆን፥ በፕላስቲክ የሚሰሩት መማሪያ ክፍሎች በመደበኛነት ከሚሰሩት ክፍሎች ከወጪ አንጻር በግማሽ ይቀንሳሉም ተብሏል። የመማሪያ ክፍሎቹ የወዳደቁ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ብቻ የሚሰሩና ምንም አይነት ብሎኬትም ሆነ አሸዋን የማይጠቀሙ ናቸው። አሁን የተጀመረው ይህ የፈጠራ ስራ ታዲያ በቀጣዮቹ ሁለት አመታት ትምህርትን ለ25 ሺህ ህጻናት ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያስችልም ዩኒሴፍ ገልጿል። በተጨማሪም ዩኒሴፍ በአይቮሪኮስት የፕላስቲክ ጡብ ማምረቻ ፋብሪካ አስገንብቷል። ፋብሪካው ያለውን የመማሪያ ክፍል እጥረት ከመቅረፉም ባሻገር የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ለፋብሪካው የሚያቀርቡ ሴቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። አይቮሪኮስት ከምታስወግደው የፕላስቲክ ተረፈ ምርት ውስጥ 5 በመቶውን ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏ ለፕሮጀክቱ መሳካት ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበታል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በአይቮሪኮስት ከፍተኛ የመማሪያ ክፍል እጥረት እንዳለ ይነገራል ይህን እጥረት ለመቀነስ መንግስት ትምህርት ቤቶችን በምን እየገነባ ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የተጣሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዝግመተ ለውጥ የአንድ ሕይወት ያለው ማህብረሰብ የዘር ውርስ ባህሪይ ከትውልድ ወደትውልድ እየተቀየረ መሄዱ ዝግመተ ለውጥ ይባላል። ቻርለስ ዳርዊን ይህን ኩነት በማስተዋልና በሳይንሳዊ አመክንዮ አሰደግፎ በመተንተኑ የመጀመሪያው ሰው ነው። ዳርዊን በተጨማሪ የተፈጥሮ ምርጫ ባለው ኅልዮቱ ሕይወት ያላቸው ማህበረሰቦች ዝግመተ ለውጥ እሚያካሂዱት ምንም እንኳ በዘፈቀደ ስህተት እየፈጸሙ ቢሆንም፣ ተፈጥሮ እራሷ በምትፈጥረው መሰናክሎች እኒህን መሰናክሎች አልፈው የሚሄዱትን በመምረጧ ነው። ዳርዊን የተፈጥሮ ምርጫን አስተሳሰብ ከ፫ የሚታዩ ነገሮች አንጥሮ ነበር ያወጣው፦ ፩) እንስሳትም ሆነ እጽዋት ወደፊት ሊኖር ከሚችሉ ዘሮች በላይ አተረፍርፈው ነው እሚራቡት ፪) ሕይወት ያላቸው እያንዳንዳቸው ነገሮች ሁልጊዜ የተለያየ ጸባይ ነው ያላቸው፣ ስለሆነም እያንዳንዳንቸው በቀጣይ የመኖር ዕድላቸው የተለያየ ነው ፫) ስለሆነም የአንድ ማህበረሰብ አባላት ሲሞቱ፣ የሚገላቸውን ነገር ጠንክረው እሚቋቋሙት ግለሰቦች ብቻ በሕይወት ቆይተው ወደፊት መራባች ይችላሉ። ስለሆነም ቀስ በቀስ እነዚህ በህይወት ያሉ፣ በህይወት የሌሉትን አይነቶች እየተኩ ይሄዳሉ። በ፳ኛው ክፍለ ዘመን ጄኔቲክስ (ሥነ በራሂ) እና ዝግመተ ለውጥ ተዋህደው ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ እሚባለውን ጥናት ለመፍጠር ችለዋል። አንድ ማህበርሰብ ለየት ያለ ግለሰቦችን ለመፍጠር ከሚያስችሉት መንገዶች አንዱ ሙቴሽን የተባለው ሂደት ሲሆን፣ ሙቴሽን እሚፈጠረው የዚያ ግለሰብ ዲ ኤን ኤ ከወላጆች ሲወረስ በሚደረግ ስህተት (ወይም እቅድ) ነው። \n \nጥያቄ: ማህበረሰባዊ ጄኔትክስ እሚባለው የምን ጥናት ውህድ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጄኔቲክስ (ሥነ በራሂ) እና ዝግመተ ለውጥ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: በአንበሶች ዘንድ 90 በመቶ የማደኑን ተግባር የሚያከናውኑት የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሴቶቹ አንበሶች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማሊ ከፈረንሳይ በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ነጻነቷን ስታገኝ የሀገሪቱ መሪ ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሞዲቦ ኪየታ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nከ 60 ዓመት በኋላ ወባን ለማከም የሚረዳ ኪኒን በአሜሪካ ባለስልጣናት ፈቃድ አገኘ። መድሃኒቱ በየአመቱ 8 ሚሊየን ሰዎች ላይ የሚያገረሸውን የወባ አይነት ለማከም የሚረዳ ነው። ይህ አይነት የወባ በሽታ በጉበት ውስጥ ለረጅም ዓመት ተደብቆ የመቆየት ባህሪ አለው። ተመራማሪዎች ይህንን \"ድንቅ ስኬት ሲሉ አሞካሽተውታል\"። ደጋግሞ የሚያገረሽ የወባ በሽታ ፕላስሞዲየም ቪቫክስ በሚሰኝ ጥገኛ ተዋህሲያን የሚከሰት ሲሆን በአፍሪካ በዋናነት ከሚጠቀሱ የበሽታ አይነቶች መካከል አንዱ ነው። አሁን የአሜሪካው የምግብና የመድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ታፌኖኪውይን ለተሰኘው መድሃኒት እውቅና ሰጥቷል። መድሃኒቱ በሽታዋ ከተደበቀበችበት ጉበት አውጥቶ በመግደል ሰዎች በህመሙ ዳግመኛ እንዳይሰቃዩ ያደርጋል። በአሁን ሰዓት ጉበት ውስጥ የተደበቀች ወባን ለማከም የሚረዳ ፕሪማኪውን የተሰኘ መድሃኒት አለ። ነገር ግን አንድ ታፌንኪውንን ወስዶ ከሚገኘው ፈውስ ጋር ሲነፃፀር ፕሪማኪውንን ለ 14 ቀን መውሰድ ይጠይቃል። \n \nጥያቄ: የአሜሪካው መድኃኒት ፈቃድ ሰጪ መስሪያ ቤት ጥቅም ላይ እንዲውል የፈቀደው የወባ በሽታ መድኃኒት ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ታፌኖኪውይን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰቆጣ መቼ ነዉ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የነበረችው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከአክሱም መዳከም በኋላ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፌስቡክ የሰዎችን ምስል ለማጣራት እና ለመለየት የሚጠቀምበት መሳሪያ ጋር ተያይዞ ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የህግ ክርክር እልባት መስጠቱ ተገልጿል። ፌስቡክ በፈረንጆቹ 2010 የሰዎችን የፊት ገጽታ መለያዎች መሣሪያን መጠቀም በፈረንጆቹ 2010 ላይ የጀመረ ሲሆን፥ መሣሪያው የተጠቃሚውን ፊት ገጽታ በመቃኘት ስለ ደንበኛው ማንነት ሃሳቦችን የሚያቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ምንም እንኳን ተጠቃሚዎች እሱን የማጥፋት አማራጭ ቢኖራቸውም፣ በወቅቱ ቴክኖሎጂው አወዛጋቢ ሆኖ መገኘቱ ተጠቁሟል። ተቃዋሚዎቹ የፊት ገጽታ መለያ መሣሪያው በኢሊኖስ ግዛትከወጣው የግላዊነት ህጎችን ይጥሳል ብለው የተከራከሩ ሲሆን ÷በግዛቱ ለሚገኙ ቡድኖችም 550 ሚሊየን ዶላር ይከፍላልም ተብሏል። ጉዳዩ በፈረንጆቹ ከ2015 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን ፥ስምምነቱም በየሩብ ዓመቱ ከሚገኝ ገቢ መሆኑም ተመላክቷል። ይህ የፊት ገጽታ እውቅናው በፖሊስ እና በአደባባይ ቦታዎችጥቅም ላይ ሲውል በጥልቀት ክትትል እንደሚደረግበትም ተገልጿል። በፈረንጆቹ ታህሳስ ወር 2017ተጠቃሚዎች ይበልጥ በቀላሉ ማብራት ወይም ማጥፋት ይችላሉ እንዲችሉ ተደርጎ የተሰራ ሲሆን ÷በ 2019 ፌስቡክ ይበልጥ በግላዊነት ላይ ያተኮረ እንዲሆን አድርጎ አዲሱ የመቆጣጠሪያ አካል አድርጎ መስራቱም ነው የተገለጸው። የማህበራዊ አውታር መረቡ ይህንን ጉዳይ ለማህበረሰባችን እና ለባለአክሲዮኖቻችን ጥቅም ስንል ለመፍታት ወስነናል ሲል አስታውቋል፡፡ ይህ ማስተካከያ የሰዎችን መረጃ እና ግላዊነትን ለመጠበቅ በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ሁለተኛውን ትልቁ መሆኑን የኢንቨስትመንት ባንክ ጃንስትር የሆኑት ክርስቶፎር ሮዝባች ተናግረዋል። ምንጭ፡-ቢ.ቢ.ሲ \n \nጥያቄ: ፌስቡክ የሰዎችን ምስል ለማጣራት እና ለመለየት የሚጠቀምበት መሳሪያ ምክንያት በነበረው የህግ ክርክር ስንት እንዲከፍል ተወሰነበት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 550 ሚሊየን ዶላር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር። ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች ኮሞዲቲ ገንዘብ መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ ከብትና እህል (ገብስ) መደበኛ ነበሩ። በተለይ ዛጎል በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። መዳብ፣ ብረት፣ ብርና ወርቅ በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረታብረት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ። በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ የፈተና ደንጊያ ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሳንቲም እና የብር ሳንቲም መጠቀም የጀመሩት ልድያውያን ነበር።. በኢትዮጵያም በአክሱም ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል። ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው ተወካይ ገንዘብ የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው ደረሰኝ በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በሶንግ ስርወ መንግስት (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በቻይና አገር ነበር፣ ብሮቹም ያወዚ ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የደረሰኝ ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። አውሮጳ ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ ስዊድን አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው። ሆኖም ስዊድን የወረቀት ብር ያወጣው ምክንያት ጦርነት ለማድረግ ፈልጎ በቂ ወርቅ ወይም ሌላ ገንዘብ በአገሩ ስላልነበረው ነው። አሁን ወዲያው የስዊድን መንግሥት ፈቃዱን እንዲፈጽሙ ሥራተኖች መክፈል ቻለ። በጥቂት ዓመት ውስት የስዎድን ወረቀት ገንዘብ ወደቀ። ነገር ግን ከትንሽ በኋላ የእንግላንድ መንግሥት በፈረንሣይ ላይ በጦርነት ተይዞ ለጦርነትም ያህል በቂ ሀብት ባለመኖሩ እንዲህ አይነት መፍትሄ መረጡ፤ የኢንግላንድ ፓውንድ ድፍን ጀመሩ። ስለዚህ ከዚህ በኋላ አገራት ፈቃዳቸውን ለመፈጽም አዲስ የወርቅ ወይም የብር ማዕድን ማግነት አስፈላጊ አልነበረም። በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ይህ በወርቅ የተደገፈ የተሰኘው የገንዘብ ስርዓት በይፋ በመላው ዓለም ተንሰራፋ። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በብሬቶን ውድስ ስብሰባ፣ አብዛኞቹ የአለማችን አገሮች ፊያት ገንዘብን በማጽደቅ ገንዘባቸውን በቀጥታ በወርቅ ከመደገፍ ይልቅ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር እንዲተረጎም አደረጉ። የአሜሪካን ዶላር በተራው በወርቅ የተደገፈ ነበር። በ1971 የአሜሪካን መንግስት ዶላሩን በወርቅ መደገፍ/መተርጎም አቆመ። ከዚህ በኋላ ሌሎቹም አገሮች የየራሳቸውን ገንዘብ ከአሜሪካን ዶላር አንጻር መተርጎም አቆሙ። በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን ገንዘቦች በወርቅም ሆነ በሌላ ቋሚ ነገር የሚደገፉ ሳይሆን በየአገሩ ባሉ መንግስታት እንደ ህጋዊ መገበባያ በወጡ አዋጆች ምክንያት ነው። \n \nጥያቄ: የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በየት ሀገር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በቻይና ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየቻይና ስነ ፈለክ ተመራማሪዎች የመጀመሪዋን ከፀሀይ ስርዓት ውጪ የሆች ኤክሶፕላኔት ማግኘታቸው ተገለፀ። በቻይና የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች የተገኘችው ይህች ፕላኔት “ወንግሹ” እና “ዢሂ” የሚል ስያሜ ተሰቷታል። ይህም ማለት የጨረቃ አምላክ ወይም የጸሃይ አምላክ የሚል ትርጉም አለው። ሁለቱ ስሞች የሚያሳዩት የኮኮብ እና ፕላኔትን ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ዩንቨርስን የማሳስ ሂደት የሚወክል ወይም ምሳሌ የሚሆን ነው ተብሏል። የፕላኔትዋ መጠን ከፀሐይ ሁለት እጥፍ የሚበልጥ ሲሆን፥ ከጁፒተርም በ2 ነጥብ 7 እጥፍ ትበልጣለች፤ በዚህም ከጸሃይ ስርዓት ውስጥ ትልቋ ነው የተባለችው በብሔራዊ የሥነ ፈለክ ምርምር ተቋም። የቻይና የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች በአውሮፓውያኑ በ2008 ከቻይና 10 ምርጥ የሥነ ፈለክ እድገቶች መካከል አንዱ ሆነው የተመረጡት ትልቁን ኤክስፕላኔት HD173416b’ን አገኝታለች። ምንጭ፡-ሲጂቲኤን በፌቨን ቢሻው \n \nጥያቄ: የቻይና ስነ ፈለክ ተመራማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ከፀሀይ ስርዓት ውጪ የሆች ኤክሶፕላኔት የተሰጣት ስያሜ ምን ትርጉም አለው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የጨረቃ አምላክ ወይም የጸሃይ አምላክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከ1936 ጀምሮ ኤርትራ የኢኮኖሚ እድገት ማሳየት ችሏል። በ30ዎቹ መጨረሻ 2፣198 የኢንደስትሪ ተቋሞች በአገሪቱ ተመስርተዋል። ይሁንና ጣሊያኖች አገሪቱ እራሷን እንድትችል ሳይሆን የነርሱ ጥገኛ እንድትሆን ነበር ያደረጉት፣ ለዚህ ሲሉ አብዛኛው ምርት ከውጭ ያስመጡ ነበር። ከ10-15% የሚሆነው የአገሬው ወንድ ሃይል በኢንደስትሪ፣ በእርሻና በጥቃቅን የተላላኪ ስራወች ተቀጥርው ይሰሩ ነበር። ከ1936-41 ድረስ አብዛኛውን የአግሬውን ወንድ ቀጥሮ ያሰራ የነበረው የቅኝ ገዥው ውትድርና ተቋም ነበር (40% ወይም 60፣000 ለአቅመ አዳም የደርሱ ወንዶችን)። እኒህ ወታደሮች ኢትዮጵያን ለመውረር ያገለገሉ ሲሆን ለዚህ ታማኝነታቸው ምክንያቱ ቅኝ ገዥወች በኤርትራ ላይ ያሰፈኑት ፖለቲካዊ መረጋጋት እንደምክንያት ይጠቀሳል። የጤና፣ የገበያ ኢኮኖሚ እንዲሁም ቁሳዊ ፍጆታ መስፋፋት በ1905ዓ.ም. 250 ሺህ ብቻ የነበረው የኤርትራ ህዝብ ወደ 614 ሺሕ በ1935 ዓ.ም. እንዲያድግ አድርጓል። ትግርኛ ተናጋሪው ክፍል በዚህ ጊዜ 54% የአገሪቱ ክፍል ነበር። እኒህ ለውጦች በአገሬው ላይ የስነ ልቦና ለውጥን አስከተሉ፣ ስለሆነም ከኢትዮጵያውያን ጐረቤቶቻቸው የተለዩ ህዝቦች የመሆን ማንነትን ፈጠረ። ሁለተኛው የአለም ጦርነትን ተከትሎ እንግሊዞች ከአንግሎ ግብጻዊ ሱዳን በመነሳት ጥር 1941 በኤርትራ ላይ ጥቃት አደረሱ። ከሶስት ወር በኋላ የከረን ጦርነትን በማሸነፍ ሚያዝያ 1941 ሙሉ ኤርትራን ተቆጣጠሩ። የእንግሊዝ ወታደራዊ አገዛዝ(BMA) በጣሊያኖች ምትክ አገሪቱን ማስተዳደር ጀመረ። 1947 ጣሊያን በፈረመችው የሰላም ውል መሰረት ኤርትራ ለአራቱ ሃይላት ተሰጠች። ከዚህ በኋላ ኤርትራ የጣሊያን ቅኝ መሆኗ አበቃላት። \n \nጥያቄ: በ1935 በኤርትራ የትግረኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ምን ያህል ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 54% ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: የእቴጌ ምንትዋብ የቀብር ስነስርዓት የተፈፀመበት ቤተክርስቲያ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኒኑስ ኒኑስ በጥንታዊ የግሪክ ታሪክ ጸሃፊዎች ዘንድ የነነዌ መስራችና የአሦር ንጉስ ነበረ። ለዘመናዊ ሥነ ቅርስ የታወቀ አንድ ግለሰብ አይመስልም፤ ዳሩ ግን የአያሌ ታሪካዊ ወይም አፈ ታሪካዊ ግለሰቦች ትዝታ በአንድ ስም በግሪኮች በኋለኛ ዘመን እንደ ተዘከረ አሁን ይታስባል። የንጉሥ ኒኑስና ሚስቱ ንግሥት ሴሚራሚስ ስሞች በጽሁፍ መጀመርያ የተገኘው ክቴስያስ ዘክኒዱስ (400 ዓክልበ. ገዳማ) በጻፈው በፋርስ አገር ታሪክ ነው። ክቴስያስ ለ2 አርጤክስስ (2 አርታሕሻጽታ) የመንግሥት ሀኪም ሆኖ የፋርስ ነገሥታት ታሪካዊ መዝገቦች አንብቤያለሁ ብሎ አሳመነ። ከዚህ በኋላ የግሪክ ታሪክ ጸሐፊ ዲዮዶሮስ ሲኩሉስ የክቴስያስን ወሬ አስፋፋ። የአለም ታሪክ ሊቃውንት እስከ 1880ዎቹ ድረስ የኒኑስ ታሪክ ዕውነት መሆኑን ይቈጠሩት ነበር። በዚያን ጊዜ የኩኔይፎርም ጽሕፈት ፍች ስለ ተፈታ፣ በሜስፖጦምያና በነነዌ ብዙ ቅርሶችም በመገኘታቸው፣ የአሦር ትክክለኛ ታሪክ ዕውቀት ተጨመረልን። ኒኑስ የቤሉስ ወይም ቤል ልጅ ተባለ፤ ይህም ምናልባት በሴማዊ ቋንቋ ሥር «ባል» (ጌታ) የመሰለ ማዕረግ ሊሆን ይችላል። በካስቶር ዘሮድስ ዘንድ ኒኑስ ለ52 ዓመታት ነገሰ፤ ክቴስያስም እንዳለው መጀመርያው ዓመተ መንግሥቱ 2198 ዓክልበ. ነበረ። በ17 አመታት ውስጥ ኒኑስ በአረቢያ ንጉስ አርያዎስ እርዳታ ምዕራብ እስያን በሙሉ እንዳሸነፈ ተብሏል። ከዚህ ቀጥሎ የአርመን ንጉስ ባርዛኔስን (ይቅርታ የሰጠውን) እና የሜዶን ንጉስ ፋርኖስን (በስቅለት ይሙት በቃ የሰጠውን) ድል በማድረግ የአለም መጀመርያ ንጉሠ ነገስት እንደ ሆነ ተብሏል። \n \nጥያቄ: የኑኒስ ሚስት ማን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ንግሥት ሴሚራሚስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሰርጌይ ብሪን ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ተወለደ ሩሲያዊ-አሜሪካዊ ሲሆን ጉግልን በመፍጠሩ ይታወቃል። በሩሲያ የተወለደ ሲሆን፥ ብሪን ከላሪ ፔጅ ጋር ጉግልን ከመጀመሩ በፊት ኮምፒዩተር ሳይንስና ሒሳብ አጥንቷል። ብሪን ባሁኑ ጊዜ የጉግል ቴክኖሎጂ ፕሬዝዳንት በመሆኑ ወደ 14.1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ገንዘብ አለው። ይህም ከዓለም 26ኛ እና ከአሜሪካ 12ኛው ሀብታም ሰው ያደርገዋል። ሰርጌይ በሞስኮ፣ ሩሲያ ለየይሁዳ ቤተሰብ ተወለደ። 6 ዓመቱ ሲሆን ሰርጌይና ቤተሰቡ ወደ አሜሪካ መጡ። አባቱ ሚካኤል በሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ ማቲማቲሻን ሆኖ እስክ ዛሬ ድረስ ያስተምራል። የስርጂ እናት ዩጂኒያ ብሪን ማቲማቲሻንና ሲቭል ኢንጅነር ሆና ለናሳ ትሰራለች። ሳሙኤል የሚባል ታናሽ ወንድምም አለው። ሰርጌይ በኮምፒዩተር ዕድገት ጊዜ በማደጉ የኮምፒዩተር ፍላጎቱ ከልጅነቱ ነው የጀመረው። መጀመሪያው ያገኘው ኮምፒዩተር አንድ ኮሞዶር 64 ሲሆን ይህንንም ከአባቱ ዘጠነኛው ልደት በዓሉ ላይ ነው ያገኘው። በሒሳብና ኮምፒዩተር ያለውን ተስዕጦም ገና ትንሸ እያለ ነው ያሳየው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በፔንት ብራንች ሞንቴሶሪ ትምህርት ቤት የወሰደ ሲሆን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በኤላኖር ሩዝቬልት ትምህርት ቤት አጠናቋል። ቤተስቡም የሒሳብ ዕውቀቱንና ሩሲያኛው በማዳበር ረድተውቷል። በሴፕቴምብር 1990 እ.ኤ.አ.፣ ሰርጌይ ሒሳብና ኮምፒዩተር ሳይንስ ለማጥናት ሜሪላንድ ዩኒቨርስቲ፣ ኮሌጅ ፓርክ ገባ። በሜይ 1993 እ.ኤ.አ. የባችለር ሳይንስ ካማግኘቱ በኅላ በስኮላርሺፕ ኮምፒዩተር ሳይንስን ለማጥናት ወደ ስታንፎርድ ዩኒቨርስቲ ሄደ። ከዛም ከታሰበው ጊዜ በፊት በኦገስት 1995 እ.ኤ.አ. የማስተርስ ዲግሪውን ተቀበለ። ባሁኑ ጊዜ ግን የፒ.ኤች.ዲ. ጥናቱን ላልተወስነ ጊዜ አቋርጦ ጉግል ውስጥ እየሰራ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ሰርጌይ ሚካይሎቪች ብሪን መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ኦገስት 21, 1973 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበ ፰፻ (800) ዓመተ-ዓለም አካባቢ ደአማት የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው የሀ የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በየመን የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር። የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በፋርስ ፣ ሮማ እና ቻይና ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ ክርስትና ተለወጠ። በ፮ኛው ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን የመን ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮ኛው እና በ ፰ኛው አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በእስልምና መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ ይኵኖ አምላክ ሥልጣን በ ፲፪፻፷፪ (1262) ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥትን መለሱ። ከዚያም ለብዙ ዘመናት የሰለሞናዊው መንግስት ከጠለ። \n \nጥያቄ: በደአማት መንግስት ላይ ተጽእኖ የነበራቸው እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በየመን የሚኖሩት ሳባውያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፋሲለደስ ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው አፄ ሱሰኒዮስ እና እናታቸው ልዕልት ስልጣነ ምገሴ በመገዛዝ፣ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው። አፄ ፋሲል አዘዞ ተብላ በምትታወቀው ከጎንደር ከተማ 5 ማይል ርቃ በምትገኘው ከተማ ጥቅምት18፣1667 እ.ኤ.አ. (ጥቅምት 10፣ 1660) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አስከሬናቸውም የአገሪቱ መላ ህዝብ ባዘነበት ሁኔታ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ተብላ በምትታወቀው ደሴት የዘላለም እረፍት አገኘ። \n \nጥያቄ: የአፄ ፋሲል የሲመት ንግስና መቼ ተካሄደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1632 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአክሱም አክሱም በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ ክ/ሃገር ከአድዋ ተራራዎች አጠገብ የምትገኝ ከተማ ነች። በክርስቶስ ልደት በፊት ተመስርቶ የነበረው የአክሱም ስርወ መንግስት ማእከል ነበረች የአክሱም ስርወ መንግስት በ12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አካባቢ እየተዳከመ ሲመጣ የማእከላዊው መንግስት ወደ ደቡብ ተንቀሳቀሰ። ሰባ አምስት በመቶ የሚሆነው የከተማው ነዋሪ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ነው። የተቀሩት ነዋሪዎች የሱኒ እስልምና ተከታዮች ናቸው። ባላቸው ታሪካዊ ተፈላጊነት ከተማ ውስጥ የሚገኙት የአክሱም ስርወ መንግስት ቅሪቶች UNESCO በ1980 የአለም ቅርስ ቦታ ተብለው ተሰይመዋል ። አክሱም በኢትዮጵያ የ ትግራይ ክልል ከተማ ሲሆን በማዕከላዊ ዞንና በላዕላይ ማይጨው ወረዳ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አክሱም በኢትዮጵያ በየት አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሰሜን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ የመጀመሪያው አልበሙ ምን ይሰኝ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ወፌ ላላ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጨኖ ጨኖ ግራጫ ቢጤ የሆነ፣ ፈርጠም ያለ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ አፍሪቃ፣ በተጨማሪም በኮንጎ ደኖች የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው ዓይነት ጨኖ የፀጉሩ ቀለም ግራጫና ጥቁር የሆነ፣ ፊቱ የጠቆረ ሰማያዊ የሆነ፣ አገጭና አንገቱ ነጭ ነው። የወንዶቹ ክብደት እስከ 12 ኪ.ግ. ሲሆን፤ አማካዩ 4.5 ኪ.ግ ይመዝናሉ። ጨኖ የደን ዝንጀሮ ነው። የደን ዝንጀሮች ብዙ ጊዜ ከዝናባማ ሥፍራዎች ደኖች ውጪ አይገኙም። ጨኖ ግን ከነዚህ ደኖች ውጪም በሚገኙ ደኖች ውስጥ ይኖራል። በኢትዮጵያ፣ በጎደሬ ደን ውስጥ፣ ቴፒ አጠገብ ሜጢ አካባቢ ይገኛሉ። በተራራማ ሥፍራዎች ደኖችም እስከ 3000 ሜትር ከፍታ ድረስ ይገኛሉ። እጅጉን በዛፍ ላይ የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። የሚገኘው በደን ዛፎች ግማሽ ላይ ነው። በተለያዩ ዓይነት ተግባሮች መገለጫ የሚሆኑ ሰባት ዓይነት ድምፆች አሏቸው። በቡድናቸው ውስጥ የሚታየው አብዛኛው ፀብ፣ በዋናው ወንድና ለአካለ መጠን ባልደረሱና ጎረምሳ ወንዶች መሃል የሚታየው ነው። በሴቶቹና ሕፃናትን በሚገድሉ ወንዶች መኻከል ከባድ ግጭት ያድጋል። በቡድኖች መኻከል የሚደረግ ግጭት የሚሆነው አልፎ አልፎ ነው። እንዲህ ያለ ግጭት የሚነሳው በድንበር አካባቢ በምግብ ሽኩቻ የተነሳ ነው። የእርግዝና ጊዜአቸውን 140 ቀን ነው። የልጆቻቸውን እድገትም ቀስ ያለ ነው። ከወለዱ ወዲያ ለሚቀጥለው እርግዝና 15 ወራት መቆየት አለባቸው። \n \nጥያቄ: የጨኖ አማካይ ክብደት ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 4.5 ኪ.ግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012(ኤፍቢሲ) ኡበር የተሰኘው የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት ተባባሪ መስራች ትራቪስ ካላኒክ በዓመቱ መጨረሻ ከቦርድ አባልነታቸው ሊለቁ መሆኑን አስታውቀዋል ፡፡ ይሁን እንጂ የ43 ዓመቱ ትራቪስ በድርጅቱ ውስጥ ካሉ ዘጠኙ ዳይሬክተሮች ውስጥ አንዱ ሆነው የሚቀጥሉ መሆኑን ነው የተናገሩት። ትራቪስ ካላኒክ እንደ አውሮፓውያ ኑ አቆጣጠር 2017 ላይ በድርጅቱ በተስተዋሉ የተለያዩ የሙስና ቅሌቶች ምክንያት ስራ ለማቆም ጫፍ ደርሰው ነበር ። ይህን ተከትሎም በኡበር ድርጅት ውስጥ ያላቸውን አብዛኛውን የአክሲዮን ድርሻ መሸጣቸው ነው የተነገረው። ትራቪስ ካላኒክ በአስር ዓመቱ መገባደጃ ኩባንያው ያለው የሕዝብ ግንኙነት እና በጎ አድራጎት ላይ ለማተኮር ለእኔ ትክክለኛ ጊዜ ይመስለኛል፤ በዚህም ደስተኛ ነኝ ተናግረዋል ፡፡ ካናኒክ በጣም ዝነኛ የሆነው የታክሲ አገልግሎት ሰጭ ድርጅት በመመስረት በዓለም ዙሪያ የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ምንጭ፣ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: በኡበር የታክሲ አገልግሎት ውስጥ ለረጅም ጊዜ በቦርድ አባልነት ያገለገሉት ትራቪስ ካላኒክ በምን ምክንያት ነው ከቦርድ አባልነታቸው የሚለቁት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሙስና ቅሌቶች ምክንያት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋናን ካለሃሪ በርሃ ምን ያህል ሸፍኗታል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከሰባ ከመቶ በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ኃይሌ ገብረሥላሴ ዜግነቱ ምናዊ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኢትዮጵያዊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ ላይ ምን ያህል ወጥ ልብ-ወለዶች ለዓለም አበርክቷል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያዊቷ ዶ/ር ውለታ ለማ ባሸነፉበት አዲስ የሥራ ፈጠራ ውድድር በመጀመሪያው ዙር ምን ያህል ተወዳዳሪዎች ነበሩ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 2500 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: ሜሪላንድ በየት ሀገር የምትገኝ ስቴት ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በአሜሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢንስታግራም እና ፌስቡክ በአሜሪካ የተገደሉትን የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱለይማኒን ሃሳብ የሚደግፉ መረጃዎችን ከገጻቸው እያስወገዱ ነው። የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ መተግበሪያዎቹ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ደንበኞች የጀኔራል ሱለይማኒን ሃሳብ ደግፈው በመተግበሪያዎቹ የሚያሰራጯቸውን መረጃዎች እያስወገዱ መሆኑ ተመላክቷል። በተለይም በኢራን የሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ጄኔራሉን ደግፈው የሚያሰራጩትን መረጃ ከገጻቸው እያስወገዱ መሆኑንም አስታውቀዋል። ይህን ተከትሎም ኢራናውያን ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክ በፈፀሙት ህገ ወጥ ተግባር እርምጃ ሊወሰድባቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል። የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ አሊ ሬቤይ በበኩላቸው፥ ድርጊቱን ዴሞክራሲያዊ አሰራርን ያልተከተለ እና ሃላፊነት የጎደለው ሲሉ ኮንነውታል። የኢራኑ ጀኔራል ቃሲም ሱለይማኒ በፕሬዚዳንት ትራምፕ ትዕዛዝ በኢራቅ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንዲገደሉ ከተደረገ በኋላ በሀገራቱ መካከል ውጥረት መንገሱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎም አሜሪካ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ባለቻቸው በተለያዩ ኢራናያውያን ግለሰቦች እና ድርጅቶች ላይ ማዕቀብ ጥላለች። ኢንስታግራም እና ፌስ ቡክም አሜሪካ ማዕቀብ በጣለችባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ሲተዳደሩ የነበሩ ገጾችን ከመተግበሪያቸው ማስወገዳቸውን አስታውቀዋል። ምንጭ ፥ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: ኢንስታግራም እና ፌስቡክ የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፅ በኢራን ጀነራል አሟሟት ጋር በተየያዘ መረጃዎቹን ከገጸቸው የሚያስወገዱት በምን ምክንያት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ተከትሎ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ. ሴኔጋል ከማን ጋር ነው ኮንፌደሬሽን የመሰረተችው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከጋምቢያ ጋር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ዶክተር ተሾመ አብዶ ያላቸው ኃላፊነት ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: የናይጄሪያ የቆዳ ስፋት ስንት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ ዘመን (ጋዜጣ) አዲስ ዘመን ጋዜጣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥር የምተዳደር ነዉ ፣ በየዕለቱ የሚታተም ብሔራዊ ጋዜጣ ነው። አዲስ ዘመን በአሁኑ ጊዜ ከ ፵ በላይ ጋዜጠኞች ያሉት ሲሆን የጋዜጣው መጠን ‘መካከለኛ’ /በርሊነር/ (31.5 cm × 47 cm (12.4 in × 18.5 in) ) ሆኖ የፊትና ጀርባ ገፆችን በሙሉ ቀለም ያቀርባል። ይህ ጋዜጣ የአገሪቱ ብቸኛው ዕለታዊ ጋዜጣ ሲሆን የመንግሥትን አቋም የሚያንፀባርቅ እና በየዕለቱ የተለያዩ ልማታዊ ዜናዎችን ይዞ ይወጣል። ከአምሥት ዓመት የኢጣልያ ወረራ በኋላ የኢትዮጵያ ነፃነት መመለሱን ተከትሎ ንጉሠ ነገሥቱ ዙፋናቸው እንደ ተረከቡ ካከናወኗቸው ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ተግባራት አንዱ የመገናኛ ብዙኀን በማደራጀትና በማቋቋም ላይ ያተኮረ ነበር። በዚህም መሠረት አዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅዳሜ፣ ግንቦት ፴ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በይፋ ሥራ ጀመረ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከጠላት ወረራ በኋላ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ/ም በድል አድራጊነት አዲስ አበባ ሲገቡ ባደረጉት ንግግር የመግቢያው አንቀጽ፦ «የሰማይ መላእክት የምድር ሠራዊት ሊያስቡትና ሊያውቁት ይቻላቸው ባልነበረ በዚህ በዛሬው ቀን ቸር እግዚአብሔር በመካከላችሁ ለመገኘት ስላበቃኝ በሰው አፍ የሚነገር ምስጋና የሚበቃ አይደለም። ከማናቸውም አስቀድሞ ለሁላችሁ ልነግራችሁና ልትረዱት የምፈልገው፣ ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ መሆኑን ነው። በዚሁ በአዲሱ ዘመን ሁላችንም መፈጸም ያለብን አዲስ ሥራ ይጀመራል።» የሚል ነበር የጋዜጣውም ሥያሜ «ይህ ቀን ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የአዲስ ታሪክ ዘመን መክፈቻ ነው» ማለታቸውን መሠረት ያደርጋል። የጋዜጣው ድረ-ገጽ ስለጋዜጣው ታሪክ ሲዘግብ፤«የመጀመሪያ ዕትም ባለሁለት ገፅ፣ አርበ ጠባብ /ታብሎይድ/» (43.2 cm X 27.9 cm (17 in X 11 in)) እንደነበረና ስርጭቱም ፲ሺ ቅጂ እንደነበር ይገልጽና፤በዚሁ የመጀመሪያ ዕትም ርዕሰ አንቀጽ «\"የአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጀመር\" በሚል ርዕስ ባስነበበው ጽሑፍ ‹ይህ አዲስ ዘመን ተብሎ የተሰየመው ጋዜጣ ከዛሬ ጀምሮ ወደፊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የነፃነቱን ሥራ ይሠራ ዘንድ ተመሠረተ› በማለት የተቋቋመበትን ዓላማ ያስረዳል» ይለናል። ቀጥሎም ያንኑ የመጀመሪያውን ርዕሰ አንቀጽ በመጥቀስ፤ «‹ይህ ጋዜጣ የፕሮፖጋንዳ ጋዜጣ ሳይሆን እውነትን፣ አገልግሎትን፣ ረዳትነትን መሰረት አድርጐ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ በአዲስ ሥራ ተመርቶ እንዲረዳ የቆመ ነው› ቢልም ‹አገልግሎት ስንል የኢትዮጵያን ነፃነት ሲመሰስ ራሳቸውን መስዋዕት አድርገው፤ የነበራቸውን ጥቅም ሁሉ አስወግደው፤ ለሕዝባቸውና ለአገራቸው ሲሉ የሰው አቅም ሊሸከመው የማይችለውን ድካም ተቀብለው፤ ማናቸውም ሰው ሊያደርገው ያልቻለውን በኢትዮጵያ ሕይወት ውስጥ እስከ ዛሬ ያልታየውን ሥራ ከፍፃሜ ላደረሱ ለንጉሠ ነገሥታችንና ላቆሙት መንግሥት የሚያገለግል እንዲሆነ ነው።› በማለትም በዋነኝነት የተቋቋመበትን ዓላማ በግልፅ ይተነትናል።» የሚል ዘገባ እንደነበር የጋዜጣው ድረ-ገጽ አስቀምጦታል። አዲስ ዘመን ከተጀመረበት ጊዜ እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፱፻፶፩ ዓ/ም ድረስ በየሳምንቱ፤በአርበ-ጠባብ፣ በመካከለኛና በአርበ-ሰፊ /ብሮድሺት/ (74.9cm X 59.7cm (291⁄2 in X 231⁄2 in)) መጠን ሲታተም ከቆየ በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ፲፱፻፶ ዓ/ም ያቋቋመው የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን፣ ጽሕፈት ቤቱን አዲስ አበባ ላይ ማድረጉን ምክንያት በማድረግ የጋዜጣው ዕትመት በሳምንት ወደ ስድስት ቀን ተሸጋግሯል። ከመስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ጋዜጣው ከሰኞ እስከ እሑድ በሳምንት ሰባት ቀናት ወደመታተምከተሸጋገር በኋላ የጋዜጣው መጠን ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ጀምሮ ወደ መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ዝቅ ብሏል። \n \nጥያቄ: አዲስ ዘመን የተለያዩ ቅርፆች የነበሩት ሲሆን ጋዜጣው መካከለኛ ጋዜጣነት /በርሊነር/ ቅርፅ የያዘው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ በማን እርዳታ ወደ አዲስ አበባ መጣ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ትራምፕ በኮሌጅ እያለ የት ድርጅት ይሰራ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: ተማሪዎቹ ለተቃውሞ ሰልፍ በመውጣት የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን ምን አቃጠሉ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የአሻንጉልት ምስል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የአውሮፓን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው ኢጣሊያን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የውጫሌ ውልን በተመለከተ፤ «...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የጀርመን ንጉሠ ነገሥት ከኢትዮጵያ የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል...» እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን ፲፭ ሺህ እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል። በ፲፰፻፺፰ ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ጥር ፬ ቀን ከከተማቸው ከሐረር ተነሱ። ጥር ፱ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የጥምቀትን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ መጋቢት ፲፫ ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው አዲስ አበባ እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ ሰኞ ሚያዝያ ፳፪ ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የክርስቲያን የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም ማክሰኞ የጊዮርጊስ ዕለት ሚያዝያ ፳፫ቀን ፲፰፻፺፰ ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን በዳግማዊ ምኒልክ ተወክለው ወዴት ነበር የተላኩት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አውሮፓ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በደረሰ የመከስከስ አደጋ አደጋ የሟቹች ቁጥር ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፻፩ ሰዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ናጊብ ማህፉዝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአፄ ምኒልክ አዲስ አበባ የመንግሥታቸው መቀመጫ እንድትሆን መወሰን የቻሉት ከአውስትራሊያ የመጣው ባህር ዛፍ ለማገዶ ችግር አፋጣኝ ምላሽ የሚሰጥ ሆኖ በመገኘቱ ነበር፡፡ ባህር ዛፍን ጨምሮ የደን ልማት ለአገርና ለሕዝብ ያለውን ጠቀሜታ የተረዳው የአፄ ኃይለሥላሴም መንግሥት ከሐምሌ 9 ቀን 1948 ዓ.ም ጀምሮ በየዓመቱ የደን በዓል ቀን ሆኖ እንዲከበር ወስኖ እንደነበር “ፍሬ ከናፍር 3ኛ መፅሐፍ” በሚል ርእስ በ1957 ዓ.ም የታተመው ጥራዝ ውስጥ ታሪኩ ተዘግቧል፡፡ በዘመኑ በሆለታ ከተማ በተከበረው የደን በዓል ቀን ላይ ንግግር ያደረጉት የእርሻ ሚኒስትሩ ባላምባራስ ማህተመሥላሴ ወልደመስቀል ለበዓሉ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ችግኝ መዘጋጀቱን፣ ችግኞቹን መትከያ 120,000 ሜትር ካሬ መሬት መሰናዳቱን፣ ከሚተከሉትም ችግኞች የሚበዙት ከውጭ አገር የመጡ መሆናቸውን፣ ለፕሮጀክቱ መሳካት የተባበሩት መንግሥታት የእርሻና የምግብ ድርጅት እገዛ ማድረጉን ገልፀዋል፡፡ የደን በዓል ቀን ተቆርጦለት መከበር ከመጀመሩ በፊት በተሰራው ሥራም ወደ አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ እፅዋት መተከላቸውን ያመለከቱት አፄ ኃይለሥላሴ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር “አስፈላጊውን ችግኝ ምንም እንኳን የእርሻ ሚኒስቴር እንዲሰጥ ቢታዘዝ ከእርሻ ሚኒስቴር እየተወሰዱ የሚተከሉት ዛፎች ሁሉ የባለርስቱ ንብረት ናቸውና ይህን ሥራ ያለማቋረጥ በትጋት መፈፀም ግዴታ ነው፡፡” ዛፍ እንደ ቅርስ፣ እንደ ሐውልት ታሪክ ማስተላለፊያ ሆኖም አገልግሏል፡፡ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሕንፃ ፊት ለፊት በ”አፍሪካ ፓርክ” ውስጥ ያሉት እፅዋት በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት ለአፍሪካ አንድነት ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ የመጡ የአህጉሪቱ መሪዎች የተከሏቸው ናቸው፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይሆን በክልል ከተሞችም በታዋቂ ሰዎች የተተከሉ እፅዋት እንዳሉ መረጃ ከሚሰጡን መፃሕፍት አንዱ የሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው “ዐፈር ያነሳ ሥጋ” የግጥም ስብስብ መድብል ነው፡፡ በ1964 ዓ.ም የታተመው ይህ መፅሐፍ ጥር 24 ቀን 1961 ዓ.ም የተፃፈና “አንድ ያልታደለ ዛፍ” የሚል ርእስ ያለው ግጥምን ይዟል፡፡ በዘመኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ሆነው ያገለግሉ የነበሩት ኡ፡ታንት በኢትዮጵያ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት በደብረዘይት ከተማ የዛፍ ተከላ ሥነ ሥርዓት አከናውነዋል የቅጠሉ ተናኝ ዘይት ለጉንፋን ይረዳል። ትንኞችንም ለማባረር ይረዳል። ቅጠሎቹ በወለሎች ላይ የሚዘረጉ ናቸው። የቅጠሉም ውጥ ለማጅራት ገትር ተጉመጠመጠ። በአውስትራሊያ ለቅጠሉ ሱስነት ያለ ኪሴ እንስሳ ወይም «ኮዋላ» ይገኛል። \n \nጥያቄ: የደን በዓል ቀን መቼ ተጀመረ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከሐምሌ 9 ቀን 1948 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል በሕዝብ ብዛት ሁለተኛ የሆነች ከተማ ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቱባ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመጋቢት ፪ ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በልሚ ወቼ ሞሹ የኢትዮጵያ አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ወገኖች ጦር ውጊያ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ከኮንጎ የመጣ የቤልጅግ ሠራዊት የጣልያንን ሠራዊት አሸንፎ ፩ሺ፭፻ ወታደሮች በመማረክ አሶሳን ያዘ። ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት (በኋላ ፕሬዚዳንት) ሪቻርድ ኒክሰን ኢትዮጵያን ጎበኙ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን አስታወቁ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል። ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ሊትዌኒያ እራሷን ከሶቭየት ኅብረት አስተዳደር ውጭ ነጻ መሆኗን አወጀች። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - ፔኒሲሊንን ያገኘው የብሪታኒያ ተወላጁ አሌክሳንደር ፍሌሚንግ በልብ ምታት አረፈ። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበራቸውን የሚወስን የጋራ ጉባዔ ለመመሥረት መወሰናቸውን ያሳወቁት መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየፌስቡክ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ10 የአፍሪካ ሀገራት ሀሰተኛ መረጃዎችን መቀነስ የሚያስችለውን የሶስተኛ ወገን የትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም (Third-Party Fact-Checking Program) መጀመሩን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው ፕሮግራሙን ካስጀመረባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ዛምቢያ፣ ሶማሊያ፣ ቡሪኪና ፋሶ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኮትዲቯር፣ ጊኔ ኮናክሪ እና ጋና ይገኙበታል፡፡ ሶስተኛ ወገን የመረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት የሚያስችል እንደሆነ ተነግሯል፡፡ በዚህም የፌስቡክ ተጠቃሚዎች በማህበራዊ ሚዲያው ጥራት ያለው መረጃ የሚያገኙበትን አሰራር የሚያሻሽል እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ \n \nጥያቄ: ሶስተኛ ወገን የመረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጫ ፕሮግራም ለምን ይጠቅማል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ላይ የሚሰራውን የተ.መ.ድ አካል (UNAIDS) ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ እና የዩኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን በኢትዮጵያ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተያዙ ዕቅዶች ላይ መምከራቸውን ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: የተ.መ.ድ አካል ዩኤን ኤድስ በምን ላይ ትኩረት አድርጎ ይሠራል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ቪክቶሪያ ሐይቅ የሚገኘው የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዩጋንዳ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጎግል ስለኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ለማቅረብ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ። ኩባንያው በትናንትናው ዕለት ወደ ስራ ያስገባው ማንቂያ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ አስፈላጊ መረጃዎችን ለማድረስ ያግዛል ተብሏል። ስለኮሮና ቫይረስ እና ተያያዥ ጉዳዮች ሰዎች መረጃዎችን በሚፈልጉበት ወቅት ጎግል “በነጭ ካርድ መደብ” ላይ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያውን በማሳየት ተፈላጊውን መረጃ ለተጠቃሚዎቹ በቀጥታ ያጋራልም ነው የተባለው። ጎግል ለዓለም አቀፍ መረጃ ፈላጊዎች በማንቂያው ላይ የዓለም ጤና ድርጅት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራሎችን አድራሻ ማካተቱንም አስታውቋል። አስፈላጊ ከሆነም በሂደት ማንቂያውን ለአካባቢያዊ መረጃ ፈላጊዎች በሚሆን መልኩ እንደሚያካትትም ገልጿል። በቀጣይም ስለ ኮሮና ቫይረስ ጠቃሚ መረጃ፣ ያለበትን ሁኔታ እና ጥያቄና መልሶችን ያካተቱ አንቀጾች ያሉበት “የእርዳታ እና መረጃ” ማፈላለጊያን ከዓለም ጤና ድርጅት አድራሻ ጋር በማያያዝ አቀርባለሁ ብሏል። ኩባንያው በአስፈላጊ እና ወሳኝ ወቅት ላይ ተጨማሪ የመረጃ ማሻሻያ እንደሚያደርግ በመግለፅ የማንቂያ ስርዓቱ ለኮሮና ቫይረስ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲገኙ ያስችላል ነው ያለው። በሞባይሎች እና ድረ ገፆች ላይ የሚገኘው ኤስ ኦ ኤስ ማንቂያ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች በሚፈጠሩበት ወቅት እንዲሁም በአጠቃላይ የሰዎች ደህንነት አደጋ ላይ በሚሆንበት ወቅት ጥቅም ላይ የሚውል ነው። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው ለቻይና የቀይ መስቀል ማህበር የ250 ሺህ ዶላር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፥ በመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በተከፈተ ዘመቻ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ምንጭ፦ ጎግል \n \nጥያቄ: ጉግል ከኮሮና ቫይረስ ለመከላከል በተደረገ ዘመቻ ምን ያህል ዶላር አሰባሰበ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎግል ስለኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ለማቅረብ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያን ወደ ስራ ማስገባቱን አስታወቀ። ኩባንያው በትናንትናው ዕለት ወደ ስራ ያስገባው ማንቂያ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ አስፈላጊ መረጃዎችን ለማድረስ ያግዛል ተብሏል። ስለኮሮና ቫይረስ እና ተያያዥ ጉዳዮች ሰዎች መረጃዎችን በሚፈልጉበት ወቅት ጎግል “በነጭ ካርድ መደብ” ላይ የኤስ ኦ ኤስ ማንቂያውን በማሳየት ተፈላጊውን መረጃ ለተጠቃሚዎቹ በቀጥታ ያጋራልም ነው የተባለው። ጎግል ለዓለም አቀፍ መረጃ ፈላጊዎች በማንቂያው ላይ የዓለም ጤና ድርጅት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዳይሬክተር ጄኔራሎችን አድራሻ ማካተቱንም አስታውቋል። አስፈላጊ ከሆነም በሂደት ማንቂያውን ለአካባቢያዊ መረጃ ፈላጊዎች በሚሆን መልኩ እንደሚያካትትም ገልጿል። በቀጣይም ስለ ኮሮና ቫይረስ ጠቃሚ መረጃ፣ ያለበትን ሁኔታ እና ጥያቄና መልሶችን ያካተቱ አንቀጾች ያሉበት “የእርዳታ እና መረጃ” ማፈላለጊያን ከዓለም ጤና ድርጅት አድራሻ ጋር በማያያዝ አቀርባለሁ ብሏል። ኩባንያው በአስፈላጊ እና ወሳኝ ወቅት ላይ ተጨማሪ የመረጃ ማሻሻያ እንደሚያደርግ በመግለፅ የማንቂያ ስርዓቱ ለኮሮና ቫይረስ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን በቀላሉ እንዲገኙ ያስችላል ነው ያለው። በሞባይሎች እና ድረ ገፆች ላይ የሚገኘው ኤስ ኦ ኤስ ማንቂያ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች በሚፈጠሩበት ወቅት እንዲሁም በአጠቃላይ የሰዎች ደህንነት አደጋ ላይ በሚሆንበት ወቅት ጥቅም ላይ የሚውል ነው። ከዚህ ባለፈም ኩባንያው ለቻይና የቀይ መስቀል ማህበር የ250 ሺህ ዶላር ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፥ በመረጃ ማፈላለጊያ ገጹ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በተከፈተ ዘመቻ ከ800 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ምንጭ፦ ጎግል \n \nጥያቄ: ጎግል ስለኮሮና ቫይረስ መረጃዎችን ለማቅረብ ወደ ስራ ያስገባው ማንቂያ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የኤስ ኦ ኤስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ዊሊያም ኸርሽል በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ያገኘው ግኝት ምን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኢንፍራሬድ ጨረር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ ከብቶች በማለቃቸው ከመቼ እስከ መቼ ረሀብ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ እ.አ.አ ከ1888-1892 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: ቤርድ ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ. ምን ያደረገበት ቀን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ እንዴት ሞተ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ‌ተደብድቦ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጎግል የሶስተኛ ወገን አጠቃቀምን የሚገድብ አዲስ የግላዊነት ማስጠበቂያ ፖሊሲ የሚተገበርበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ። ተቋማት በበይነ መረብ ላይ እየጨመረ የመጣውን ጥቃት ተከትሎ የግላዊነት ጥበቃ ደህንነታቸውን እንዲያጠናክሩ የሚያደርግ ግፊት እየጨመረ ነው። ለዚህ ደግሞ በሶስተኛ ወገን የተጠቃሚዎችን የበይነ መረብ እንቅስቃሴ መከታተል የሚያስችሉት መሳሪያዎች (ኩኪዎች) ጋር በተያያዘ ያለው አጠቃቀም አናሳ መሆኑ ይነገራል። ጎግልም በሶስተኛ ወገን አጠቃቀምን የሚገድብ አዲስ የግላዊነት ማስጠበቂያ ፖሊሲ የሚተገበርበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። አዲሱ ፖሊሲ ፕራይቬሲ ሳንድቦክስ የሚል መጠሪያ ያለው ሲሆን፥ የሶስተኛ ወገን ማስታወቂያ አሰራጮች የተጠቃሚዎችን መረጃ በፈለጉት ጊዜ ሳይሆን በጎግል አማካኝነት እንዲያገኙ የሚያደርጋቸው ነው። ይህ መሆኑ ደግሞ ጎግል በዲጂታል ማስታወቂያ ገበያው ያለውን ተደራሽነት የበለጠ ያሰፋለታል እየተባለ ነው። ኩኪዎች የዲጂታል ማስታወቂያ ባለሙያዎች የተጠቃሚዎችን እንቅስቃሴ ማዕከል ተንተርሰው ማስታወቂያ እንዲሰሩ ይረዷቸዋል። ኩባንያዎች በበይነ መረብ ላይ የግለሰቦችን እንቅስቃሴ ለማወቅ የመረጃ ማፈላለጊያዎች ላይ የተከማቹ መረጃዎችን ይጠቀማሉ። በዚህም የጎበኟቸውን ድረ ገጾች ጨምሮ በዲጅታል ማስታወቂያ የተደረጉ የግብይት እንቅስቃሴዎችን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን፥ ማስታወቂያ ሰሪዎችም ተጠቃሚወችን መሰረት ያደረገ መረጃ እንዲለቁ ያግዛቸዋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ \n \nጥያቄ: ጎግል ያስተዋወቀው የሶስተኛ ወገን አጠቃቀምን የሚገድብ አዲስ የግላዊነት ማስጠበቂያ ፖሊሲ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፕራይቬሲ ሳንድቦክስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ምድር ጦር የሙዚቃ ቡድን መቼ ተመሰረተ መቼስ ፈረሰ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዩጋንዳ በስንት ወረዳዎች የተከፈለች ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ70 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በህፃናት ልብ ህክምን ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ዶክተር በላይ አበጋዝ እና 30ኛ አመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል ያላቸውን አስተዋፅኦ በማድነቅ ሽልማት አበረከቱ። \n \nጥያቄ: ዶ/ር በላይ አበጋዝ በህፃናት ልብ ህክምና ላበረከቱት አስተዋፅኦ በማዕከሉ 30ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ማን ሸለማቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የሆነው በስንተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 19ኛው ምእት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዳኝ አንበሶች በጣም ቀልጣፋና ፈጣን ቢሆኑም እንኳ በአደን ጊዜ የሚሳካላቸው 30 በመቶ ብቻ ነው። በመሆኑም አንበሶች ከተደቀኑባቸው ትልልቅ አደጋዎች አንዱ ረኃብ ነው። ለአካለ መጠን የደረሰ አንድ አንበሳ ያለው ጥንካሬ እጅግ የሚያስገርም ነው። በቤተሰብ ደረጃ የሚያድኑ እንደ መሆናቸው መጠን ከ1,300 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያላቸውን እንስሳት የመጣልና የመግደል አቅም እንዳላቸው ይነገራል። አንበሶች በመጀመሪያ ላይ በሰዓት እስከ 59 ኪሎ ሜትር ድረስ ሊሮጡ ይችላሉ፤ ሆኖም ይህ ፍጥነታቸው እስከ መጨረሻ አይዘልቅም። በዚህ ምክንያት ቀለባቸውን ለማግኘት አድብቶ የመያዝ ዘዴ ይጠቀማሉ። የማደኑን ተግባር 90 በመቶ የሚያከናውኑት ሴቶቹ አንበሶች ቢሆኑም በሚበሉበት ጊዜ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ናቸው። አደን በሚጠፋበት ጊዜ አንዳንዴ አንበሶች በጣም ስለሚርባቸው ያገኙትን መብል ለራሳቸው ግልገሎች እንኳ ለማካፈል ፈቃደኛ አይሆኑም። ታዳኝ ከብዙ ዓመታት በፊት ባለ ግርማ ሞገሱ አንበሳ በመላው የአፍሪካ አህጉር እንዲሁም በእስያ፣ በአውሮፓ፣ በህንድና በፍልስጤም አንዳንድ ቦታዎች ይገኝ ነበር። አዳኝ እንደመሆኑ መጠን ሰውን እየተቀናቀነ የሚኖር እንስሳ ነው። በከብቶች ላይ አደጋ የሚጥልና በሰዎች ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ አንበሳ ገና እንደታየ በጥይት የሚገደል ፍጡር ሆነ። የሕዝብ ቁጥር ፍንዳታ የአንበሳን መኖሪያ በእጅጉ አመናምኖታል። ዛሬ ከአፍሪካ ውጪ ባለው የዓለም ክፍል በዱር የሚኖሩት አንበሶች በጥቂት መቶዎች ብቻ የሚቆጠሩ ሆነዋል። በአሁኑ ጊዜ አንበሶች ሰው ከሚያደርስባቸው ጥቃት ሙሉ በሙሉ ተጠብቀው መኖር የሚችሉት ጥበቃ በሚደረግባቸው ክልሎች ውስጥና በዱር አራዊት መጠበቂያ ቦታዎች ብቻ ሆኗል። አንበሳ ሲያገሣ አንበሶች በሚያገሡበት ጊዜ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ሊሰማ የሚችል ከፍተኛ ድምፅ የማውጣት ልዩ ችሎታ አላቸው። አንበሳ ሲያገሣ የሚያሰማው ድምፅ “እጅግ ማራኪ ከሆኑት የተፈጥሮ ድምፆች” አንዱ እንደሆነ ይነገራል። ብዙውን ጊዜ አንበሶች በጨለማ ሰዓትና ንጋት ላይ ያገሣሉ። ወንዶቹም ሆኑ ሴቶቹ አንበሶች የሚያገሡ ሲሆን አንዳንዴም የመንጋው አባላት በአንድነት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ያገሣሉ። በአንበሶች ላይ ጥናት የሚያካሂዱ ሳይንቲስቶች አንበሶች የሚያገሡባቸው የተወሰኑ ምክንያቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ወንዶቹ አንበሶች የሚኖሩበትን ክልል ድንበር ለማሳወቅ እንዲሁም ሌሎች ወንድ አንበሶች ወደ ክልላቸው እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ ሲሉ ያገሣሉ። በርቀት ወይም በጨለማ ተነጣጥለው ያሉ የአንድ መንጋ አባላት ያሉበትን ቦታ ለመጠቆም ያገሣሉ። በተጨማሪም አንድ እንስሳ ከገደሉ በኋላ ለሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ምግቡ ያለበትን ቦታ ለማሳወቅ ያገሣሉ። አንበሶች በሚያድኑበት ጊዜ የሚያድኗቸውን እንስሳት ለማስደንበር ብለው አያገሡም። ሪቻርድ ኤስቲዝ ዘ ቢሄቭየር ጋይድ ቱ አፍሪካን ማማልስ በተባለው መጽሐፋቸው ላይ “አንበሶች የሚያድኑትን እንስሳ ለማጥመድ ሲሉ ሆን ብለው እንደሚያገሡ የሚጠቁም ምንም ነገር የለም (በተሞክሮዬ እንዳየሁት በአንበሳ የሚታደኑ እንስሳት አንበሳ ለሚያሰማው የግሣት ድምፅ ብዙም ትኩረት አይሰጡም)። \n \nጥያቄ: አንበሶች አድነው ካመጡት ውስጥ በመመገብ ትልቁን ድርሻ የሚያገኙት የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ትልልቆቹ ወንድ አንበሶች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በዚምባቡዌ በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከስንት ዓመታት በፊት ፍልሰት ጀመሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ2 ሺህ ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዕዝራ ዕዝራ ወይም ሱቱኤል በብሉይ ኪዳን ዘንድ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ የአይሁድ ካህን ነበረ። የሠራያ ልጅ ሲሆን በፋርስ ንጉስ አርጤክስስ 7ኛው አመት (464 ክ.በ.) ከ5000 ከወገኖቹ ጋራ ወደ ኢየሩሳሌም ለመመለስ ፈቃድ ተቀበለ። ከዚህ 13 አመት በኋላ ነህምያ የከተማውን ቅጥር ሲጠግነው ዕዝራ ኦሪት በሙሉ ለሕዝብ አነበበ (መጽሐፈ ነህምያ ምዕ. 8)። በአይሁዳዊው ታሪክ ጸሐፊ በዮሴፉስ ዘንድ ይህ የፋርስ ንጉስ አርጤክስስ ሳይሆን አሕሻዊሮስ ነበረ። አርጤክስስ የአሕሻዊሮስ ልጅ ሲሆን እነዚህ 2 ነገስታት ስሞች ብዙ ጊዜ በተለያዩ ቅጂዎች ተደናገሩ። ዮሴፉስ ደግሞ ዕዝራ የሞተበት ወራት ኤልያሴብ ታላቁ ካህን በሆኑበት ወቅት ገደማ እንደ ነበር ይመሰክራል። የአሕሻዊሮስ ዘመን ከሆነ 7ኛው አመት 486 ክ.በ. ነበር። ዕዝራ መጽሐፈ ዕዝራንና መጽሐፈ ነህምያ ከመጻፉ በላይ በዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ክፍል የሚገኙት መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤልና መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ እንደ ጻፈ ይባላል። መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ ለመጽሐፈ ዕዝራ በጣም ተመሳሳይ በመሆኑ በዕዝራ ካልዕ 81 ግን ሠራያ ሳይል በግድፈት የአዛርያስ ልጅ ይለዋል። ዕዝራ ሱቱኤል በሚባለው ትንቢት ደግሞ በ11 የጻፈው ኢየሩሳሌም ከጠፋች 30 አመት በባቢሎን መሆኑን ይላል። ይህም 565 ክ.በ. ማለት ነው። በዚህ መጽሐፍ 1344 መሠረት 24 መጻሕፍት በ40 ቀን ውስጥ ጻፈ ቢለን፥ በሌሎች ልሣናት ሕትመት ግን ስለ 94 መጻሕፍት እየተናገረ ከነዚህ መሀል ተጨማሪው 70 መጻሕፍት በምስጢር እንዲቆዩ ነበረባቸው ይላል። \n \nጥያቄ: የሠራያው ልጅ በፋርስ ንጉስ አርጤክስስ ከ5000 ከወገኖቹ ጋራ ወደ ኢየሩሳሌም ለመመለስ ፈቃድ የተቀበለው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 7ኛው አመት (464 ክ.በ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ የፊፋ ዓለም ዋንጫን ያዘጋጀች ሀገር ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ደቡብ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: በጤና ቴክኖሎጂ አዲስ የሥራ ፈጠራ አሸናፊ የሆኑት ዶ/ር ውለታ ለማ ዜግነታቸው ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኢትዮጵያዊ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ምንድን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዋና ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል። ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ። \n \nጥያቄ: ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፫፻፳ ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበኢትዮጵያ ካሉ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ተጠቃሚዎች ውስጥ 59 ነጥብ 5 ከመቶ የሚሆኑት ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል /password/ እንደሚጠቀሙ ጥናት አመለከተ። ተጠቃሚዎች የስልክ ቁጥርን መጠቀማቸው ጠንካራ የይለፍ-ቃል እንደተጠቀሙ እንደሚሰማቸውም በጥናቱ ተመላክቷል። በዓለም አቀፍ ደረጃ የሳይበር ጥቃት በከፍተኛ መጠን እያደገ መምጣቱም ነው የተነገረው። በኢትዮጵያ ያለው በሳይበር ደህንነት የግንዛቤ መጠንም ዝቅተኛ እንደሆነ የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ ጥናት ያመለክታለል። ኤጀንሲው በ2011 ዓ.ም 1 ሺህ 635 የሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ሀገር-አቀፍ የሳይበር ደህንነት ምዘና ጥናት አከናውኗል። በጥናቱ ከተሳተፉት መካከል 975 (59 ነጥብ 5 በመቶ) ያክሉ ስልክ ቁጥርን እንደ ይለፍ-ቃል/password/ በመጠቀም ጠንካራ የይለፍ-ቃል እንደተጠቀሙ እንደሚሰማቸው ጥናቱ ያመለክታል። በተጨማሪም 59 ነጥብ 1 በመቶ ያክሉ የጥናቱ ተሳታፊዎች የይለፍ ቃሎቻቸውን የሚታይ ቦታ ላይ ጽፈው ማስቀመጥን እንደ ማስታወሻ መንገድ እንደሚጠቀሙበት ገልጸዋል። 67 ነጥብ 6 ከመቶ የሚሆኑት የጥናቱ ተሳታፊዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጩ መረጃዎች ትክክለኛ ናቸው ብለው እንደሚያምኑም ነው የተነገረው። በመሆኑም የሳይበር ደህንነት ጉዳይ በቸልታ ሊታለፍ የማይገባውና የለት ተለት የህይወታችን አካል እየሆነ በመምጣቱ ተገቢውን ትኩረትና ጥናቃቄ ልናደርግ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብና ደህንነት ኤጀንሲ የሰራውን ጥናት አስመልክቶ ያወጣው መረጃ ያመለክታል። \n \nጥያቄ: በ2011 ዓ.ም ከተፈጸመ የሳይበር ጥቃት ውስጥ ምን ያህል ግለሰቦችን ተጎጂ አድርጓል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 1 ሺህ 635 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ እድሜያቸው ስንት ሲሆን ወደ ብሔረ ህያዋን ሄዱ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ዘጠና ዘጠኝ አመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኤዎስጣጤዎስ በግዕዝ ኤዎስጣቴዎስ ወይም ዮስጣቴዎስ፣ ከሐምሌ ፭ ቀን ሺ፪፻፷፭ – ሺ፪፫፵፬ በኢትዮጵያ ሰለሞናዊ መንግሥት አገዛዝ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ታላቅ መሪ የነበሩ አባት ናቸው። በጣም አጥብቀው ከሚያስተምሩት ትምህርት ስለ ሰንበት መከበር ነበረ። ተከታዮቻቸው የኤዎስጣጤዎስ ቤት ወይም በግል ሲጠሩ ኤዎስጣጤዎሳውያን ይባሉ ነበር ለተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ናቸው። የኤዎስጣጤዎስ መጀመሪያ ስማቸው ማዕቀበ እግዚእ ሲሆን ከእናታቸው ከስነሕይወትና ከአባታቸው ከክርስቶስ ሞዐ ሐምሌ ፳፩ ቀን ፩ሺ፪፷፭ ተወለዱ። እኒህም ደጋግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ነበሩ ። ኤዎስጣጤዎስ የታወቀውን ደብራቸውን (ደብረ ፀራቢን) የመሠረቱት የተወለዱበት ቦታ እዛው (እንድርታ) እንደሆነ ገድላቸው ይገልፃል። በወጣትነታቸው ዘመን በሺ፪፸፪ አካባቢ ከአጎታቸው አባ ዳንኤል (የደብር ስማቸው አባ ዘካርያስ) ቆርቆር (ደብረ ማርያም) አስተዳዳሪ ጋር እንዲኖሩ ወደ ገራልታ ይላካሉ። አባ ዳንኤልም ኤዎስጣጤዎስን ተቀብለው ተገቢውን የሃይማኖት ትምህርትና የደብር ሕይወትን ካስተማሩ በኋላ ማዕቀበእግዚእ በ፲፭ ዓመቱ ቅስና ሥራዬ መሆን አለበት ብሎ በወሰደው ውሳኔ መሠረት ስሙ ኤዎስጣጤዎስ ተብሎ ተሰየመ። ኤዎስጣጤዎስ ከአባ ዳንኤል የቅስና መዐረጋቸውን ካገኙ በኋላ የራሳቸውን ደብር በ(ሰራይ) መሠረተው በዚያም በማስተማር ብዙ ተማሪዎችን አፈሩ ። በሰንበት ላይ ያተኮረ አመለካከታቸውን ለይተው ያስተምሩ ነበር ፣ የሚቃወማቸው አቡነ ያእቆብ ፫ኛው አስኪመጣ ድረስ። ከዛ ግን ከተከታዮቻቸው ከባካርሞስ ፣ መርቆርዮስ ፣ ገብረእያሱ ጋር ኢትዮጵያን ለቀው ወደ ግብፅ (ካይሮ) ገብተው በአሌክሳንድሪያው ጳጳስ ቢንያም ፪ኛው ፊት በሰንበት ባላቸው አመለካከት ፀንተው ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም አምርተው በመጨረሻም የሕይወታቸው ማብቂያ ወደ ሆነችው አርሜኒያ ገብተው ኖሩ። \n \nጥያቄ: የኤዎስጣጤዎስ የመጀመሪያ ስማቸው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ማዕቀበ እግዚእ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. መሠረቱ። ከምዕራቡ ሮማ መንግሥት ውድቀት ደግሞ ወደ ተረፈው ሕዋእ ውስጥ ከፈለሱት ጀርመናውያን ወገኖች አብዛኛው የራሳቸውን ሕጎች ዝርዝር በጽሑፍ አወጡ። በተለይ የሚታወቁም የቪዚጎቶች አለቃ ዩሪክ ሕግ (463 ዓ.ም.)፣ የቡርጎንዳውያን ሕግጋት (እኚህ ለጀርመናውያንና ለሮማውያን የተለያየ ፍትሕ ነበራቸው)፣ የአላማናውያን ሕግጋትና፣ የፍራንኮች ሕግጋት ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ የተጻፉት ከ492 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በ498 ዓ.ም. የቪዚጎቶች አለቃ 2ኛ አላሪክ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስና አንዳንድ የተለያዩ የቀድሞ ሮማ ሐገጋት አከማችተው አዋጁአቸው። ከዚህም በኋላ የታዩ ሕጎች የሎምባርዶች ሕግጋት (635 ዓ.ም.)፣ የቪዚጎቶች አዳዲስ ሕግጋት (646 ዓ.ም.)፣ የአላማናውያን አዳዲስ ሕግጋት (722 ዓ.ም.) እና የፍሪዝያውያን ሕግጋት (777 ዓ.ም.) አሉ። በአውሮፓ አኅጉር ላይ የተጻፉት እነኚህ ፍትሖች ሁሉ በሮማይስጥ ቢጻፉም፣ በእንግሊዝ አገር ግን የተጠቀሙት ሕጎች ከኬንት ንጉሥ ኤጠልቤርት ሕጎች (594 ዓ.ም.) ጀምሮ በጥንታዊ እንግሊዝኛ የተቀነባበሩ ነበሩ። በ885 ዓ.ም. ታላቁ አልፍሬድ ይህንንና ሁለት የድሮ ፍትሖች ከሕገ ሙሴና ከሕገ ወንጌል ጋራ አጋጥመው የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ዶም ቦክ ሠርተዋል። \n \nጥያቄ: ታላቁ አልፍሬድ የድሮ ሕጎችን፣ የኦሪትና የወንጌል ሕግጋትን በመጠቀም አዲስ የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ885 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: መስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. ራስ ተፈሪ መኮንን ከእንደራሴነት ስልጣን በተጨማሪ ያገኙት ኃላፊነት ምን ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የንጉሥነት ማዕረግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አሁን ምን በመባል ይጠራል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሴኔጋል ሴኔጋል ወይም የሴኔጋል ሪፐብሊክ በምዕራብ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። ሴኔጋል ከምዕራብ በሴኔጋል ወንዝ፣ ከሰሜን በሞሪታንያ፣ ክምሥራቅ በማሊ እና ክደቡብ በጊኒና ጊኒ-ቢሳው ይዋሰናል። የጋምቢያ ግዛት እንዳለ በሴኔጋል ውስጥ ነው የሚገኘው። የሴኔጋል የቆዳ ስፋት 197,000 ካሬ ኪ.ሜ. የሚጠጋ ሲሆን የሕዝብ ብዛቱ ደግሞ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሆነ ይገመታል። የሴኔጋል የአየር ሁኔታ የየምድር ወገብ ሲሆን ደረቅና ዝናባማ ወራት ተብሎ ወደ ሁለት ይከፈላል። የሴኔጋል ርዕሰ ከተማ ዳካር በሀገሩ የምዕራብ ጫፍ በካፕ-ቨርት ልሳነ ምድር ላይ ይገኛል። ከባህር ጠረፍ ወደ ፭፻ ኪ.ሜ. ገደማ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የኬፕ ቨርድ ደሴቶች ይገኛሉ። በ፲፯ኛው ና ፲፰ኛው ክፍለ ዘመናት በቅኝ ገዢ መንግሥታት የተሠሩ የንግድ ተቋማት ከባህር ዳር ይገኛሉ። በአካባቢው ያሉ ግኝቶች ሴኔጋል ከጥንት ጀምሮ የሚኖርበት እንደነበረ ያሳያሉ። እስልምና የአካባቢው ዋና ሀይማኖት ሲሆን ወደ ሴኔጋል የተዋወቀውም በ11ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን እንደሆነ ይታመናል። በ13ኛውና 14ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የማንዲንጎ ግዛት በአካባቢው ላይ ተጽኖ ያደርግ ነበር። በዚሁም ጊዜ ነው የጆሎፍ ግዛት የተመሠረተው። በ15ኛው ክፍለ-ዘመን ፖርቱጋል፣ ኔዘርላንድስ እና ኢንግላንድ በአካባቢው ለመነገድ ይወዳደሩ ነበር። በ1677 እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ጎሪ የሚባለውን ዋና የባሪያ ንግድ ደሴት ተቆጣጠረች። ከዛም በ1850ዎቹ እ.ኤ.አ. ፈረንሣይ ቁጥጥሩዋን ወደ መላው ሴኔጋል ማስፋፋት ጀመረች። \n \nጥያቄ: ጊኒና ጊኒ-ቢሳው ሴኔጋልን ከየት አቅጣጫ ያዋስኑዋታል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ክደቡብ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: በቀጭኔ ርዝመት ላይ እስከ አሁን በሪከርድነት የተያዘው ከፍተኛው ርዝማኔ ስንት ሜትር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 5.87ሜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአቡነ ባስልዮስ ቀዳማዊ አቡነ ባስልዮስ (፲፰፻፹፬ዓ/ም (ሚዳ ሚካኤል) - ፲፱፻፷፫ ዓ/ም (አዲስ አበባ)) የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመጀመሪያው ፓትርያርክ ነበሩ። አቡነ ባስልዮስ ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም ገብረ ጊዮርጊስ ሲሆን መጋቢት ፲፬ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ/ም ከደብተራ ወልደጻድቅ ሰሎሞንና ከወይዘሮ (በኋላ እማሆይ) ወለተማርያም ባዩ በሸዋ አውራጃ ሚዳ ሚካኤል ተወለዱ። ደብተራ ወልደጻድቅ የይፋት ቀውትጌስ ማርያም ተወላጅ ሲሆኑ፣ እማሆይ ወለተማርያም ደግሞ በመንዝ ላሎ ምድር የተወለዱ ነበር። በሕጻንነታቸው ዘመን መንፈሳዊ ትምህርትን እየተማሩና የኮሶ ማርያምን ቤተ ክርስቲያን እያገለገሉ አድገዋል። አቡነ ባስልዮስ የአሥራ-አራት ታዳጊ ወጣት እያሉ በ፲፰፻፺፱ ዓ/ም ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገብተው ትምህርታቸውን ከመምህር ገብረ ኢየሱስ ሲከታተሉ ቆይተው በዚያው ገዳም መዓርገ-ምንኩስናቸውን እስከተቀበሉበት ድረስ ለሦስት ዓመታት በእርድና አገልግለዋል። በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመን በ፲፱፻፱ ዓ/ም በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ትዕዛዝ በመናገሻ ግርጌ ለሚሠራው የማርያም ቤተ ክርስቲያን ለሚጠጉ መነኮሳትና ባሕታውያን የሚሠሩትን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳደር ረዳት እንዲሆኑ በተጠየቁት መሠረት፣ እያገለገሉና ቅዳሴ እያስተማሩ ለሦስት ዓመታት በመናገሻ ማርያም ደብር ቆዩ። እዚሁም ገዳም መምህር (አበ ምኔት) ሆነው ሲኖሩ ወደሐዋርያዊነት ሥራ በመሠማራት ቆዩ። \n \nጥያቄ: አቡነ ባስልዮስ የህይወት ዘመናቸው ከስንት አስከ ስንት ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፰፻፹፬ዓ/ም (ሚዳ ሚካኤል) - ፲፱፻፷፫ ዓ/ም (አዲስ አበባ) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በ198 ሺህ ደንበኞች የሞባይል ስልኮች ላይ በተጫነ መተግበሪያ ዘመናዊ የቆጣሪ ንባብን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ። አሰራሩ በመኖሪያ ቤቶች፣ የንግድ እና የመንግስት ተቋማት እና በሌሎች የውሃ አገልግሎቶች ላይ ተግባራዊ በመደረጉ ደንበኞች የሞባይል ስልኮች ላይ በተጫነ መተግበሪያ አማካኝነት ቆጣሪ ማንበብ ይችላሉ ተብሏል፡፡ ይህም ግምታዊ አሞላልን ከማስቀረት ባለፈ ደንበኞች የውሃ ፍጆታቸውን በተጠቀሙበት ወር ለመክፈል የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል። ከዚህ ወር ጀምሮም በአራት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በሚስተናዱ 198 ሺህ 428 ደንበኞች ዘመናዊ የቆጣሪ ንባብ ስርዓት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ የክፍያ ስርዓቱ ደንበኞች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል በተዘረጉ የተለያዩ የክፍያ አማራጮች በመጠቀም የታህሳስ እና የጥር ወር የውሃ አገልግሎት ክፍያ መፈጸም የሚችሉ መሆኑንም ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። \n \nጥያቄ: የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በምን ያህል ደንበኞች የሞባይል ስልኮች ላይ በተጫነ መተግበሪያ ዘመናዊ የቆጣሪ ንባብን ተግባራዊ እያደረገ ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ198 ሺህ ደንበኞች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዓለማየሁ ቴዎድሮስ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የወይዘሮ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ነበር። በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብረ ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ በኋላ ከእድሜው ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና አጫዋቾች ተመረጡለት፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ከሶስት ወራት የመርከብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሀገር ደረሰ፡፡ \n \nጥያቄ: ልዑል አለማየሁ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሩሲያ ለአለም አቀፍ በይነመረብ አማራጭ የሚሆን አር ዩ ኔት የተሰኘ ኢንተርኔት በተሳካ ሁኔታ መሞከሯን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል ፡፡ ይሁን እንጂ የተከናወነውን ሙከራ በተመለከተ ዝርዝር መረጃ አለመሰጠቱ በዘገባው ተመላክቷል። እንደ ሀገሪቱ ኮሙኒኬሽን ሚኒስቴር መረጃ ፥ማንኛውም ተጠቃሚ በተደረገው ሙከራ ወቅት ምንም አይነት ለውጥ ማስተዋል አለመቻሉን አስታውቋል፡፡ የሙከራ ውጤቱም ለሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ይቀርባል ነው የተባለው ፡፡ ምሁራኖችበ አንዳንድ ሀገሮች በበይነ መረብ የሚደርስ ጥፋትን እንዳለ ይጠቅሳሉ። በጥናቱ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒተር ሳይንቲስት የሆኑት ፕሮፌሰር አላን ውድዋርድ እንዳሉት፥ በሚያሳዝን ሁኔታ የበይነመረብ ሰርጎ ገቦች መበራከት የሩሲያ የጉዞ አቅጣጫ ሌላ ደረጃ እያደረሰ ነው። ቁጥራቸው እየጨመረ ያሉ ሃያላን መንግስታት ዜጎች የሚያዩትን መቆጣጠር የሚፈልጉ ስለመሆናቸው ከኢራን እና ከቻይና መመልከት ይቻላል። ይህ ማለት ሰዎች ሀገራቸው ውስጥ ስለሚሆነው ነገር የመነጋገር እድል አይኖራቸውም፡፡ የተገኘው ውጤት እንደሚያሳየው ባለስልጣኖች እና የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ውጤታማ ምላሽ በመስጠት አደጋዎች እና ስጋቶችን ማስወገድ እንዲሁም በሁለቱም በይነመረብ እና ቴሌኮሙዩኒኬሽን አውታር መረብ ውስጥ የተስተካከለ አሠራር በሩሲያ ፌዴሬሽን እንዲኖር ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸው ተነግሯል። \n \nጥያቄ: ሩስያ ለዓለም አቀፍ በይነ መረብ አማራጭ የሚሆን ኢንተርኔት በተሳካ ሁኔታ መሞከሯ ታውቋል ይህ ኢንተርኔት ስሙ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አር ዩ ኔት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nረጅሙ የቦይንግ አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን በስኬት አጠናቋል። ቦይንግ 777- 9 ኤክስ የተሰኘው ይህ አውሮፕላን ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ርዝመት እንዳለው ተገልጿል። አዲሱ አውሮፕላን በኩባንያው ምርቶች ላይ በሚፈጠሩ እክሎች ምክንያት የሚደርሱ አደጋዎችን ለመቀነስ ያስችላል ነው የተባለው። የአውሮፕላኑ የተሳካ የበረራ ሙከራ ሲያትል ከተማ አካባቢ የተከናወነ ሲሆን፥ ይህ ሙከራ ከመካሄዱ በፊት በአየር ፀባይ ችግር ምክንያት ሊካሄዱ የነበሩ ሁለት የሙከራ በረራዎች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ኩባንያው እስካሁን 309 የሚሆኑ 777 ኤክስ አውሮፕላኖችን የሸጠ ሲሆን፥ የአንዱ ዋጋም 442 ሚሊየን ዶላር ነው ተብሏል። ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖቹ ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዢያ የሆኑ ሁለት አውሮፕላኖች ተከስክሰው የ346 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው የሚያመርታቸው አውሮፕላኖች ደህንነት አስተማማኝ አይደለም በሚል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና በባለሙያዎች ከፍተኛ ወቀሳ ሲቀርብበት ቆይቷል። ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን   \n \nጥያቄ: ባለ ሁለት ሞተር እና 76 ሜትር ርዝመት እንዳለው የተገለጸው የቦይንግ አውሮፕላን ምን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ቦይንግ 777- 9 ኤክስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nታሊየም የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ መረጃ መዝባሪዎች ቡድን ሚስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር እንደተቆጣጠረው ማይክሮ ሶፍት አስታወቀ፡፡ መቀመጫው ሰሜን ኮሪያ እንደሆነ የታመነው ይህ መረጃ መዝባሪ ቡድን የመንግስት ሰራተኞችን ፣ የዩኒቨርሲቲ ሰራተኞችን ፣ የኒውክሌር ሙያተኞችን እና የጥናት ተቋማንን ኢላማ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡ የመረጃ መዝባሪ ቡድኑ በዋነኝነት ኢላማ ያደረገው በአሜሪካ የሚገኙ ተቋማትን ሲሆን በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ የሚገኙ ተቋማንንም ኢላማ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡ ታሊየም በመጀመሪያ እይታ ትክክለኛ ሆነው የሚታዩ የኢሜል አድራሻዎችን በመጠቀም መረጃ ሲመዘብር ነበር ተብሏል፡፡ ማይክሮሶፍትም በአሁን ወቅት መረጃ መዝባሪ ቡድኑ የሚጠቀምባቸውን 50 የድር ጎራዎች መቆጣጠሩን የገለፀ ሲሆን በምሥራቃዊ ቨርጂኒያ አውራጃ በሚገኝ ፍርድ ቤት በጠለፋ ቡድን ላይ ክስ መመስረቱን ገልጿል፡፡ ምንጭ፡-ሮይተርስ \n \nጥያቄ: ማይክሮሶፍት ምስጢራዊ መረጃዎችን ሲመዘብር የያዘው የሰሜን ኮሪያ ቡድን ማን ተብሎ ይጠራል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ታሊየም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል የሚገኙ በርካታ ወንዞችን በስንት ዋና ዋና ተፋሰሶች መክፈል ይቻላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በሦስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአማርኛ ውክፔዲያ የአማርኛው ውክፔዲያ ጥር 18፣ 1996 ዓ.ም. (27 January 2004 እ.ኤ.አ.) ተጀመረ። አሁን ገጽ ስራዎች በውስጡ ይገኛሉ። ውክፔዲያ ዓለም-ዓቀፍ የዕውቀት ማከማቻ ድረ-ገጽ ነው። ውክፔዲያ የጋራ ነው። ሁሉም ሰው በመዝገበ ዕውቀቱ እንዲሳተፍ ተፈቅዷል። አዳዲስ ተሳታፊዎች፣ የጀማሪዎች ማያያዣን በመጫን በፍጥነት ስለ ድረ-ገጹ መረጃ ማግኘት ይችላሉ። አዲስ ጽሑፍ ለመጻፍ ወይንም ነባር ጽሑፍ ለማስተካከል ደፍሮ መሞከር ጥሩ ልምድ ነው። ከሌሎች ውክፔዲያዎች የተተረጎሙ ጽሑፎች እንዲያቀርቡ ይበረታታሉ። ለዚህ ተግባር እነዚህን መዝገበ ቃላት ማማከር ይችላሉ ። የሚያቀርቡት ጽሑፍ ያልተሟላ ወይንም ያልተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳ መጨነቅ አያስፈልግም። ጅምር ጽሑፍ በተፈለገ ጊዜ ሊሻሻል ይችላልና። \n \nጥያቄ: ውክፔዲያ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የዕውቀት ማከማቻ ድረ-ገጽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: የፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ እናት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአንድ ወጣት ተማሪ ከወዳደቁ ቁሳቁሶች በውሃ ላይ የሚነዳ የብስክሌት ጀልባ መስራቱ ተገለጸ፡፡ ጌታባለው መኩሪያው የተባለው ወጣት በባህርዳር ዩኒቨርስቲ 3ኛ ዓመት የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሲሆን ወጣቱ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች እንዲሁም አገልግሎት መስጠት ያቆሙ የብስክሌት አካላትን ተጠቅሞ ነው የብስክሌት ጀልባ (Pedal-Boat) መስራት የቻለው፡፡ ጌታባለው መኩሪያው ከወዳደቁ ቁሳቁሶች የሰራውን የብስክሌት ጀልባ በውሃ ላይ በመንዳት ሙከራ ማድረጉም ተገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: ጌታባለው መኩሪያ የፈጠራ ስራውን ከምን ከምን ሊሰራው ቻለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የወዳደቁ ፒፒሲ ትቦዎች፣ የላሜራ ብረቶችና ፌሮዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየኮምፒዩተር አውታር የኮምፒዩተር አውታር (ኔትወርክ) ማለት ሁለት ወይም ከሁለት በላይ የሆኑ ኮምፒዩተሮችን ማገናኘት ነው። እነዚህ ኮምፒዩተሮች ሲገናኙ መረጃ መለዋወጥ ይቻላል። አውታሩ ውስጥ ያሉት ኮምፒዩተሮች በአንደ ክፍል ውስጥ ወይም በጣም በተራራቁ ሕንጻዎች ውስጥ ሊገኙ ይችላሉ። ኮምፒዩተሮቹ በኤሌትሪክ ገመድ ፣ በገመድ የለሽ ግንኙነት ወይም በሞደም ሊገናኙ ይችላሉ። አውታሩ ላይ ሌሎች የኮምፒዩተር መሣሪያዎችንም መግጠም ይቻላል። ለምሳሌ አንድ ፕሪንተር አውታር ውስጥ አገናኝቶ አውታሩ ውስጥ ከሚገኝ ማንኘውም ኮምፒዩተር ወደዛ ፕሪንተር ማተም ይቻላል። የአውታሩን ኮምፒዩተሮች ሁሉንም እኩል ሥልጣን መስጠት ይቻላል ወይም ለአንዳንድ ኮምፒዩተሮች የተለዩ ሥራዎች መሥራት እንዲችሉ ማድረግ ይቻላል። ሁለተኛው ዘዴ ክላየንት-ሰርቨር ይባላል። አብዛኛው ጊዜ ሰርቨሮቹ ሀይለኛና ትልቅ ሲሆኑ ክላየንቶቹ ደግሞ አነስተኛ ናቸው። \n \nጥያቄ: የኮምፒዩተሮች አውታር ስንፈጥር ኮምፒዩተሮቹን በምን በምን መንገድ ልናገናኛቸው እንችላለን?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በኤሌትሪክ ገመድ ፣ በገመድ የለሽ ግንኙነት ወይም በሞደም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ወይም በብእር ስሙ ማርክ ትዌይን አሜሪካ ካፈራቻቸው ድንቅ ጸሃፍት መካካል የሚመደብ ደራሲ ነው። ትዌይን በኖቬምበር 1835 ዓ.ም. ሚዙሪ በተባለችው የአሜሪካ ግዛት ተወለደ። 18 ዓመት እስኪሞላው ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር የኖረው ሃኒባል በተባለች እና ሚሲሲፒ ላይ በተቆረቆረች ትንሽ ከተማ-አከል ቦታ ነው። አባቱ በ1847 ሲሞት ትዌይን ትምህርቱን በማቋረጥ በማተሚያ ቤት ውስጥ በሰልጣኝነት ተቀጠረ። ይህን ስራውን በ1857 በመተው የእንፋሎት ጀልባ ነጂ በመሆን መስራት ጀመረ። በዚሁ ስራ በቆየባቸው አመታት ነው ኋላ ላይ አድናቆትን ላተረፉለት የስነ-ጽሁፍ ስራዎቹ የሚሆኑትን እውቀቶች ለማሰባሰብ የበቃው። እሱ ራሱም እንዳለው በዚሁ ስራ ላይ ነው \"ማንኛውንም በልብ-ወለድ፣ በግለ-ታሪክም ሆነ በታሪክ ላይ ሊገኙ የሚችሉ የሰው ባህርያትን\" ሊያጠና የበቃው። በ1861 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የእርስ-በርስ ጦርነት በመቀስቀሱ ምክንያት ማንኛውም አይነት የመርከብ ላይ ጉዞ ሲስተጓጎል ትዌይንም ስራውን ለመልቀቅ ተገዷል። ከዚህ በኋላም በውትድርና ወዶ-ገብነት፣ በወርቅ ማእድን ፈላጊነት፣ በጋዜጠኝነት ወዘተ ስረቷል። በ1869 ዓ.ም የመጀመሪያ ዋነኛ ስራው የሆነውን \"The Innocents Abroad\" ለማሳተም በቃ። ይኽ ድርሰት ክሌመንስ ራሱ በአውሮፓ እና በእየሩሳሌም ባካሄዳቸው ጉብኝቶች ላይ የተመሰረተ ነው። በ1870 ዓ.ም ኦሊቭያ ላንግዶንን በማግባት ኑሮውን ኮኔቲከት በተባለችው ግዛት አድርጓ በዛው ለ17 ዓመታት ኖሯል። በነዚህ 17 ዓመታት ነው አድናቆት ያተረፉለት ስራዎቹን ማለትም \"Roughing It\"፣ \"The Adventures of Tom Sawyer\"፣ Life on the Mississippi\"፣ እና ከሁኡ የላቀ የተባለለት ድርሰቱን \"The Adventures of Huckleberry Finn\"ን ያሳተመው። ትዌይን በ1910 ዓ.ም አርፎ ሬዲንግ፣ ኮኔቲከት ውስጥ በድኑ አርፏል። \n \nጥያቄ: ማርክ ትዌይን ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ ብዙ አድናቆትን ያገኙ ድርሰቶችን ጽፏል ይበልጥ አድናቆትን ያገኘለት የመጽሀፍ ርዕስ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ The Adventures of Huckleberry Finn ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዳም ረታ አዳም ረታ ልቦለድና ግጥም በአማርኛ የሚጽፍ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነው። አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተመው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ”፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። ይህ የአጻጻፍ ስልቱ ሕጽናዊነት የሚባል ሲሆን ደራሲው በሌሎቹ መጻሕፍቱም ውስጥ በስፋት ተጠቅሞበታል፡፡ በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየዓመቱ አንዳንድ መፅሐፍ ለአንባቢያ ያደረሰ ሲሆን በ2002 ዓ.ም “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ በ2003 ዓ.ም “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” እና በ2004 ዓ.ም “ሕማማት እና በገና” ታትመው ለንባብ በቅተዋል። “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” በተሰኘው መፅሀፉ ድንቅ የፋንታሲ (“ፈንጠዚያ”) ሥራዎች የተካተቱ ሲሆን በ”ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” ለመጀመሪያ ጊዜ መቼቱን ከሀገር ውጭ በማድረግ የውጭውን ሕይወት በስሱ የዳሰሰ ሲሆን ከሌሎቹ ስራዎቹ በተለየ መልኩ ስለሀገራችን ፖለቲካ ወጣ-ገባ መንገድ በታዛቢ አይን ምልከታው፣ ትውስታውን … አስፍሯል፡፡ ሕማማትና በገና የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ሲሆን ለየት ያለ ቅርፅ ያላቸው አንዳንድ ልቦለዶች ተካተውበታል። ፍልስፍናውና ስልቱ ሕፅናዊነት በሚል ስያሜው ይፋ ሆኗል። \n \nጥያቄ: አዳም ረታ የመጀመሪያ ዲግሪውን በምን ዘርፍ ነበር ያገኘው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በጂኦግራፊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: ነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ማን ላይ ፈረደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጃን ፖል አካዬሱ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ ከሌሎቹ አረብ አገራት ብቸኛዋ የምን አባል ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ G-2ዐ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዩጋንዳ ዩጋንዳ ሪፐብሊክ (ወይም ዑጋንዳ) በምስራቅ አፍሪካ የሚገኝ ሀገር ነው። በኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ፣ ሩዋንዳ እና ታንዛኒያ ይዋሰናል። የዩጋንዳ ሰም የመጣው ከቡጋንዳ መንግሥት ነው። ከአረቦችና አውሮፓውያን በ1800ቹ ከመድረሳቸው በፊት ብዙ የሚታወቅ ነገር አልነበረም። በ15ተኛ መቶ ክፍለ-ዘመን ችዌዚ የተባለውን መንግስት በአፈ ታሪክ ይገኛል። አረቦችና አውሮፓውያን በ19ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ሲደርሱ ብዙ መንግሥቶች በቦታው ነበሩ። እነዚህም በንዮሮ ፣ ቡሶጋ ፣ ቡጋንዳ ፣ ቶሮ እና አንኮልን ያጠቃልላሉ። ከ1894 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በታላቁ ብሪታን ስትመራ ነበር። የተለያዩ ቦታዎች ከተዋሃዱ በኋላ ዩጋንዳ በ1914 እ.ኤ.አ. ቅርጿን ያዘች። በ1966 እ.ኤ.አ. ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ ሕገ-መንግሥቱን አፍርሰው እራሳቸውን ፕሬዝዳንት አደረጉ። በ1971 እ.ኤ.አ. ኢዲ አሚን ሀገሩን መምራት ጀመሩ። የኢዲ አሚን አመራር 300,000 የሚገመቱ ዩጋንዳውያንን አስጨርሷል። በ1979 እ.ኤ.አ. የታንዛንያ ኃይሎች ኢዲ አሚንን ከሥልጣን ያስወግዳሉ። ሚልተን ኦቦቴ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ግን በ1985 እ.ኤ.አ. እንደገና ይወርዳሉ። ያሁኑ ፕሬዝዳንት ዮወሪ ሙሴቪኒ ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ናቸው። ፕሬዝዳነንቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይመርጣሉ። ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አፖሎ ሲባምቢ ናቸው። ዩጋንዳ በመሬት የተቆለፈች ብትሆንም ታላላቅ የውሃ አካላት አሉ። ከነዚህ ውስጥም ቪክቶሪያ ሐይቅ፣ አልበርት ሐይቅ፣ ክዮጋ ሐይቅ እና ኤድዋርድ ሐይቅ ይዘረዘራሉ። ታላላቅ ከተማዎች በቪክቶሪያ ሐይቅ አቅራቢያ ይገኛሉ። እነዚህም ካምፓላንና እንትቤን ያጠቃልላል። ዩጋንዳ በ70 ወረዳዎች የተከፋፈለች ስትሆን እነዚህም በአራት አመራር ክልሎች ውስጥ ናቸው። አራቱ አመራር ክልሎች ሰሜናዊ ፣ ምሥራቃዊ ፣ ማዕከላዊ እና ምዕራባዊ ይባላሉ። ወረዳዎቹ በዋና ከተማዎቻቸው ነው የሚሰየሙት። በዩጋንዳ ውስጥ የመዳብ እና ነጭ ብረት ክምችቶት አሉ። ግብርና ዋናው የኤኮኖሚ ሴክተር ነው። ከ80 በመቶ በላዩ የስራ ኃይል በግብርና ነው የተሰማራው። ቡና ዋናው የኤክስፖርት ትርፍ ምንጭ ነው። ከ1986 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መንግሥቱ ከሌሎች ሀገሮችና ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን በኢዲ አሚን ጊዜ የወደቀውን ኤኮኖሚ ለማንሳት ተጣጥሯል። ዩጋንዳ ለብዙ ብሔረሰቦች ቤት ነው። ከነዚህ ውስጥ ግን አንድ ትልቁን ሕዝብ ብዛት የሚወክል የለም። 40 አካባቢ የሚሆኑ ቋንቋዎች ባሁኑ ጊዜ ይነገራሉ። ከነጻነት በኋላ እንግሊዝኛ ብሔራዊ ቋንቋ ተደርጓል። ብዙ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ ሉጋንዳ ሲሆን የአቴሶ ቋንቋ በሁለተኛነት ይከተላል። ኪስዋሂሊ ዋናው የንግድ ቋንቋ ነው። የዩጋንዳ የትምህርት ስርዐት የሰባት ዓመት መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፣ ስድስት ዓመት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት እና ከ3 እስከ 5 ዓመት ከሁለተኛ ደረጃ በኃላ ትምህርት ያጠቃልላል። \n \nጥያቄ: ዮወሪ ሙሴቪኒ አሁን የዩጋንዳ ምንድን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፕሬዝዳንት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: ቱርክመንኛ በየትኛው የቋንቋ መደብ ውስጥ ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በቱርኪክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ። ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት ETRSS-1 የተባለች የመጀመሪያዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ታኅሣሥ ወር 2012 ዓ.ም ማምጠቋ ይታወሳል። ባለፈው አመት የመጠቀችው “ETRSS-1” የሚል ስያሜ የተሰጣት ምድርን እየቃኘች ፎቶ እየመዘገበች መረጃ የምትሰበስበው ሳተላይት በሀገራችን የዕድገት ጉዞ ላይ ቁልፍ ሚና እንደሚኖራት መነገሩ አይዘነጋም። መረጃ መላክ የጀመረችው ይች ሳተላይት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር፣ ከግብርና ጋር የተያያዙ ጥናት እና ምርምሮችን ለመሥራት እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ የመሠረተ ልማት ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። ኢትዮጵያ አሁን ደግሞ ET-Smart-RSS የተባለች ሳተላይት ማምጠቋን ነው ኢንስቲትዩቱ ያስታወቀው። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በ2013 \"ET-Smart RR\" የተሰኘችውን ሳተላይት ማምጠቋን ማን አስታወቀ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቢል ክሊንተን ዊልያም ጄፈርሰን «ቢል» ክሊንተን (William Jefferson Bill Clinton) (የትውልድ ስም፦ ዊልያም ጄፈርስን ብላይዝ ፬ኛ፣ እንግሊዘኛ፡ William Jefferson Blythe IV) በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) በሆፕ አርካንሳው የተወለዱ ሲሆን ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ድረስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕሬዝዳንት ከመሆናቸዉ በፊት አምስት ጊዜ የአርካንሳው ስቴት አስተዳዳሪ ነበሩ። \n \nጥያቄ: በአሜሪካ እ.ኤ.ኣ ከ1993 – 2001 ፕሬዝደንት የነበረው ማነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ቢል ክሊንተን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: በናይጄሪያ ከፍተኛው ቦታ በምን ያህል ከፍታ ላይ ይገኛል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 2,419 ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ወ/ሮ ስምረት ግርማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: በአዶልፍ ሂትለር መንግሥት በ1926 ዓም የማን ሕዝቦች ናቸው የአርያኖች ዘር የተደረጉት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የሀንጋሪ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀጭኔ ከዝሆን በስተቀር ማንኛውም ሌላ እንስሳ ሊደርስ በማይችልበት ከፍታ ላይ የሚገኙ ረዣዥም ቀንበጠቦችን ለመብላት የሚያስችል አስደናቂ አፈጣጠር አላት። ልዩ የሆነ የመቆንጠጥ ችሎታ ያለው የላይኛው ከንፈሯና እንደተፈገለው የሚተጣጠፍ ችሎታ ያለው ምላሷ ሹል በሆኑ እሾሆች የታጠሩ ቅጠሎችን ለመቀንጠብ ያስችሏታል። ቀጭኔዎች በቀን እስከ 34 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕፅዋት መመገብ ይችላሉ። የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ቢሆኑም ይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን እሾሃማ ግራሮች ነው። አንድ ወንድ ቀጭኔ ምግብ ለመፈለግ ምላሱን እስከ 42 ሳንቲ ሜትር መዘርጋት ይችላል። የቀጭኔ አንገት በጣም አስደናቂ የሆነ የመተጣጠፍ ችሎታ አለው። ይህም ላይኛዎቹን የዛፍ ቅርንጫፎች ለመቀንጠብ በምታደርገው እንቅስቃሴ ረዥሙን ራሷን እንደ ልቧ ለማዘንበልና ለማዟዟር ያስችላታል። ለቀጭኔ ወደ ላይ መንጠራራት በጣም ቀላል ነገር ሲሆን ተጎንብሶ ውኃ መጠጣት ግን ይከብዳታል። ወደ ውኃ ጉድጓድ በምትቀርብበት ጊዜ የፊት እግሮቿን ቀስ በቀስ ከፍታ ካራራቀቻቸው በኋላ ወደ ውኃው ለመድረስ እንድትችል ሁለት ጉልበቶቿን አጠፍ ታደርጋለች። ቀጭኔዋ እንዲህ ባለው አመቺ ባልሆነ ሁኔታ እያለች ረዥም አንገቷን እስከ መጨረሻ ትዘረጋለች። ደግነቱ ግን ከምትመገባቸው ቅጠላ ቅጠሎች በቂ እርጥበት ስለምታገኝ ቶሎ ቶሎ መጠጣት አያስፈልጋትም። የቀጭኔ አንገትና ትከሻ የቅጠል ቅርፅ ባላቸውና ቀጫጭን በሆኑ ነጭ መስመሮች ያጌጠ ነው። ቀለማቸው የተለያየ ሲሆን ከወርቃማ ዳለቻ አንስቶ እስከ ቡናማ እንዲያውም ጠቆር እስካለ ቀለም ይደርሳል። የቀጭኔ ዕድሜ እየገፋ በሄደ መጠን ቀለሟም እየጠቆረ ይሄዳል። ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው። አንዲት ነፍሰ ጡር ቀጭኔ ልጅዋን ከ420 እስከ 468 ለሚደርሱ እርግዝና ቀናት ከተሸከመች በኋላ ሁለት ሜትር ቁመት ያለው ግልገል ትወልዳለች። ግልገሏ በምትወለድበት ጊዜ ራስዋን ታስቀድምና ከሁለት ሜትር ከፍታ ላይ ወደ መሬት ትወረወራለች። ይሁን እንጂ በ15 ደቂቃ ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባት እየተውተረተረች ትነሳና ጡት ለመጥባት ዝግጁ ትሆናለች። ከሁለት ወይም ከሦስት ሳምንት በኋላ በደመ ነፍስ ተመርታ የግራር ቀንበጦችን መለቃቀም ስለምትጀምር ብዙም ሳትቆይ ረዥም እርምጃ ያላትን እናትዋን ተከትላ ለመሄድ የሚያስችል ጉልበት ታገኛለች። አንዲት የቀጭኔ ግልገል በጣም ውብ መልክ ሲኖራት የወላጆችዋ አነስተኛ ግልባጭ ነች። ቁመቷ ከቀጭኔ ርዝመት ጋር ሲወዳደር አጭር ብትሆንም ከብዙ ሰዎች ቁመት ግን ትበልጣለች። በእናቷ ጥንቃቄ የተሞላበት ጥበቃ ተማምና አላንዳች መሸበር አካባቢዋን የምትማትረው ግልገል ላያት ሁሉ ልዩ መስህብ አላት። ግልገል ቀጭኔዎች በተወለዱበት ወራት በግልገል መዋያ ተሰባስበው ሙሉውን ቀን ዕረፍት በማድረግ፣ በመጫወትና በአካባቢያቸው የሚሆነውን ነገር በመመልከት ጊዜያቸውን ያሳልፋሉ። የቀጭኔ ግልገል ለማመን በሚያዳግት ፍጥነት ያድ⁠ጋል። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ አንድ ሜትር የሚያክል ቁመት ሲጨምር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በእጥፍ ያድጋል። በአንድ ሳምንት ብቻ 23 ሳንቲ ሜትር ያህል ሊያድግ ይችላል! እናትዬው ለልጅዋ ከፍተኛ ጥበቃ የምታደርግ ሲሆን ልጅዋ የተወሰነ ርቀት እንድትዘዋወር ብትፈቅድላትም ሩቅ የማየት ችሎታ ስላላት በዓይኗ ትከታተላታለች። ቀጭኔ ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ስላላት ከአንበሳ በቀር የሚያጠቃት ጠላት የለም። ቢሆንም ይህችን የምታምር ፍጥረት የሰውን ያህል በብዛት አድኖ የገደለ የለም። ቀጭኔ በሚያምር ቆዳዋ፣ በሚጣፍጥ ሥጋዋና አንዳንዶች ምትሐታዊ ኃይል አለው በሚሉት ረዥምና ጥቁር ጭራዋ ምክንያት እጅግ ተፈላጊ ስለሆነች በአሁኑ ጊዜ የዚህች ሰላማዊ ፍጡር የወደፊት ሕልውና ስጋት ላይ ወድቋል። በአንድ ወቅት በብዙ የአፍሪካ አካባቢዎች እንደ ልብ ትታይ የነበረችው ቀጭኔ በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው በቂ ጥበቃ በሚደረግላት ፓርኮች ብቻ ሆኗል። የቀጭኔ አካላዊ ቅርጽና ግዝፈት ችግሮች ማስከተሉ አይቀርም ብሎ የሚያስብ ይኖር ይሆናል። በጣም ትልቅ ቁመትና ረዥም አንገት ስላላት የተስተካከለ የደም ዝውውር እንዲኖራትና ወደ ሁሉም የአካሏ ክፍሎች ደም እንዲደርስ ማድረግ የማይቻል ነገር ሊመስል ይችላል። ለምሳሌ ያህል ቀጭኔ አንገቷን ወደ መሬት ስታጎነብስ በስበት ኃይል ምክንያት ብዙ ደም ወደ ጭንቅላቷ ፈስሶ አንጎሏን ማጥለቅለቅ ነበረበት። ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ደሟ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ልቧ ተመልሶ ራሷን እስከ መሳት ሊያደርሳት ይገባ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ነገር አይደርስም። ለምን? የቀጭኔ የደም ዝውውር ሥርዓት በዓይነቱ ልዩ ለሆነው ለዚህች እንስሳ ቅርጽና መጠን እንዲያገለግል ሆኖ በታላቅ ጥበብ የተሠራ ነው። ልቧ ራሱ በጣም ትልቅ ሲሆን ደሙን ሦስት ሜትር ተኩል ገደማ ርቆ እስከሚገኘው እስከ አንጎላ ለመግፋት የሚያስችል አቅም አለው። በደቂቃ እስከ 170 ጊዜ የሚመታውና 7 ሳንቲ ሜትር ያህል ውፍረት ባለው ጡንቻ የተገነባው የቀጭኔ ልብ ከሰው የደም ግፊት በሦስት እጥፍ የሚበልጥ ግፊት ያመነጫል። ወደ አንጎል የሚሄደውን ደም የሚሸከመው ካሮቲድ የተባለው የደም ቧንቧና ከአንጎል ወደ ልብ የሚመለሰውን ደም የሚሸከመው ጀጉላር የተባለው የደም ቧንቧ እንዲህ ያለውን ከፍተኛ ግፊት መቋቋም የሚያስችል መጠን ሊኖራቸው ይገባል። በእርግጥም እነዚህ የደም ቧንቧዎች ከ2.5 ሳንቲ ሜትር በላይ ስፋት ያላቸው ከመሆኑም በላይ ጠንካራና የመለጠጥ ችሎታ ባላቸው ሕዋሳት የተገነቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ጥንካሬና የመለመጥ ችሎታ አላቸው። ቀጭኔ ከጭንቅላቷ ጎንበስ በምትልበት ጊዜ ወደ አንጎሏ የሚሄደውን የደም ፍሰት የሚቆጣጠሩ ልዩ መቆጣጠሪያዎች አሏት። አንጎልና አንገት በሚገናኙበት ቦታ ላይ ትልቁ ካሮቲድ የደም ቧንቧ ሬቴ ሚራቢሌ ተብሎ ከሚጠራ አስደናቂ የሆነ መረብ መሰል አካል ይገናኛል። በከፍተኛ ኃይል ተገፍትሮ የመጣው ደም እዚህ ጋር ሲደርስ በጣም በርካታ ወደሆኑ ትናንሽ የደም ሥሮች እንዲገባ ስለሚደረግ የደሙ ግፊት ተስተካክሎ በአንጎል ላይ ጉዳት የማያስከትል ይሆናል። ቀጭኔዋ ራስዋን ጎንበስ በምታደርግበት ጊዜ ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው መረብ ይለጠጣል፤ ራሷን ቀና በምታደርግበት ጊዜ ደግሞ ይኮማተራል። ይህም የስበት ኃይል የሚያሳድረው ተጽዕኖ ሚዛኑን የጠበቀ እንዲሆን ማድረግና የደም ግፊቷ በእጅጉ ቀንሶ ራሷን የምትስትበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ለመከላከል ይረዳታል። የሳይንስ ሊቃውንት በጣም አስደናቂ ርዝመት ያለው የቀጭኔ አንገት ያሉት አከርካሪዎች ቁጥር ከአይጥ ወይም ከብዙዎቹ አጥቢ እንስሳ ጋር እኩል መሆኑን ሲያውቁ በጣም ተደንቀዋል! ይሁን እንጂ የቀጭኔ አከርካሪዎች በጣም ረዣዥሞችና እርስ በርሳቸው ልዩ በሆነ ሁኔታ የተሰካኩ በመሆናቸው እንደ ልብ ሊተጣጠፉ ይችላሉ። ቀጭኔ አንገቷን መጠምዘዝና ማጠፍ ስለምትችል ሁሉንም የአካሏን ክፍሎች ለመላስም ሆነ ረዣዥም የዛፍ ቅርንጫፎች ላይ ለመድረስ ትችላለች። \n \nጥያቄ: ቀጭኔዎች የተለያዩ ዕፅዋትን የሚበሉ ሲሆን ከሁሉም በይበልጥ የሚመርጡት በአፍሪካ ሜዳዎች የሚገኙትን ምግባቸው ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ እሾሃማ ግራሮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተው መች ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1862 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመስከረም 23/12 ዓ ም ሽሬ ኢዜአ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን ለተጠቃሚዎች በማቅረብ ይሁንታ ያገኘው የ35 ዓመት ወጣት ሔሊኮፕተር ሰርቶ ለሙከራ እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ ። ወጣት ዕበ ለገሰ ይባላል ። በመደበኛ ትምህርት ብዙ ገፍቶ ባይሔድም በፈጣራ ብቃቱ ግን በርካታ ስራዎች ለህዝብ እንዲያደርስ አድርጎታል ። የ10ኛ ክፍል ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሰራ ምጣድ ጥገና ሥራ የጀመረው ወጣት አሁን ላይ ትልቅ ራእይ አንግቦ የራሱ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን በማቅረብ ውጤታማነቱን በተጠቃሚዎች ዘንድ እየተመሰከረለት መጥቷል ። የምጣድ ጥገና ስራው ለታናሽ ወንድሙ በመልቀቅ የወርቅ መአድን መፈለጊያ መሳሪያ ወደ ማሻሻል መሸጋገሩን ይገልፃል ። በራሱ ፈጠራ ያሻሻለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ በባህላዊ መንገድ ወርቅ ለሚያመርቱ ሰዎች በሽያጭ በማቅረብ የፍለጋ ሥራቸውን እንዲቃለል እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ ። ቀደም ሲል የነበረው ‘’ጂ አር ዜድ’’ የተባለው የወርቅ መፈለጊያ መሳሪያ ከ70 እስከ 80 ሳንቲ ሜትር ጥልቀት ባለው መሬት ውስጥ የሚገኝ የደለል ወርቅ የሚጠቁም ነበር ። ወጣቱ ያሻሸለው ግን በአንድ ሜትር ጥልቀት የሚገኘውን የደለል ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል መሳርያ ሆኖ ተገኝቷል ። እንዲሁም ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ በቀላሉ መለየት የሚያስችል የድንጋይ ወፍጮ በመፍጠር ለተጠቃሚዎቹ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝም ወጣት ለገሰ ይናገራል ። ባለፉት አምስት ዓመታት አምስት የድንጋይ ወፍጮዎችን በመስራት ለተጣቀሚዎቹ በተመጣጣኝ ዋጋ አቅርቧል ። በተጠናቀቀው ዓመት በራሱ ፈጠራ ሶስት ሰዎች የማሳፈር አቅም ያለት ሔሊኮፕተር ሰርቶ በሙከራ ደረጃ ለህዝብ እይታ አቅርቦ የነበረው ወጣቱ ዘንድሮ ለማብረር እየተዘጋጀ መሆኑንም ተናግሯል ። የፈጠራ ሥራዬ ስኬትና ሚስጥር “ይቻላል” የሚል ጽኑ እምነት ስላለኝ ነው የሚለው ወጣቱ ከኢንተርኔት የሚያገኛቸው የፈጠራ ሥራዎችም እገዛ እንዳደረጉለት ጠቁሟል። ሥራ ፈጣሪ ወጣቱ ወደ ገበያ በሚያቀርባቸው የፈጠራ ውጤቱ ጥሩ ገቢ ከማግኘቱም ባሻገር ለሌሎች 10 ወጣቶች የስራ እድል መፍጠሩን ተናግሯል። የወጣቱ የፈጠራ ወጤት ተጠቃሚ ከሆኑትና በባህላዊ መንገድ በደለል ወርቅ ምርት ፍለጋ ከተሰማሩ ማህበራት መካከል የ“ስምረት” ማህበር አንዱ ነው። የማህበሩ አባል የሆነው ወጣት በላይ ተክለሃይማኖት በሰጠው አስተያየት ” ከወጣቱ የገዛነው የደለል ወርቅ ጠቋሚ መሳርያ ሥራችንን ከማቃለል በተጨማሪ በወርቅ ፍለጋው ስኬታማ እንድንሆን አግዞናል” ብሏል። ሌላው የማህበሩ አባል ወጣት ተስፋይ በላይ በበኩሉ ” ከድንጋይ ጋር ተደባልቆ የሚገኝ ወርቅ ለመለየት እጅግ አድካሚ የነበረው ሥራ ወጣቱ ባቀረበልን አነስተኛ የድንጋይ ወፍጮ በመጠቀም የድካማችንን ዋጋ ማግኘት አስችሎናል ” በማለት አድናቆቱን ገልፆለታል ። የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ ጎይቶኦም ይሰማ እንዳሉትም ደግሞ የወጣቱን የፈጠራ ክህሎት እንዲሰፋና ሄሊኮፕተሯ ለህዝብ እይታ እንድትበቃ አስፈላጊውን ድጋፍ ይደረግለታል ። የሽሬ እንደስላሴ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ ዲን አቶ ፀጋይ ገብረሚካኤል በበኩላቸው የፈጠራ ባለቤት የሆነው ወጣት እበ ለገሰ የፈጠራ ስራዎች የሚያተኩሩት በአካባቢው ህብረተሰብ ላይ በሚታዩ መሰረታዊ ችግሮች ዙሪያ በመሆናቸው ተቀባይነታቸው የጎላ ነው ብለዋል ። ወጣቱ የሚያሳየው ትጋት የተሞላበት የፈጠራ ስራ ለሌሎች ወጣቶችም አርአያ በመሆን መነቃቃት መፍጠሩን የኮሌጁ ዲን መስክረውለታል ። \n \nጥያቄ: ወጣት እበ ለገሰ ከድንጋይ ጋር የተቀላለን ወርቅ ለመለየት ምን ዓይነት ነገር ፈጠረ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የድንጋይ ወፍጮ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኤሮስፔስና ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ ዘርፎች ዙሪያ ከኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ጋር በቅንጅት ለመስራት እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታውቋል። በዚህ መሰረት ሚኒስቴሩ በሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ እና ኤሮስፔስ ላይ ለመስራት ከተሰማራው ፋሪስ ከተሰኘ ኢንስቲቲዩት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጅ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ እና የፋሪስ ቴክኖሎጅ ኢንስቲቲዩት መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ይርዳው ተፈራርመውታል። ስምምነቱ ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ፣ ኤሮስፔስና ሌሎች የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መስኮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል መሆኑ ነው የተገለጸው። ፋሪስ በወጣት ኢትዮጵያውያን ኢንጅነሮች እና የፈጠራ ባለሙያዎች የተቋቋመ ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ፣ ኤሮስፔስና መሰል ዘርፎች ላይ የሚሰራ ኢንስቲቲዩት መሆኑን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኤሮስፔስና ሰው ሰራሽ ቴክኖሎጅ ዘርፎች ምን ከሚባል ኢንስቲቲዩት ጋር አብሮ ለመስራት ስምምነት አደረገ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የፋሪስ ቴክኖሎጅ ኢንስቲቲዩት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል የፕሬዝደንትነት ምርጫ ውድድር በየሰባት ዓመት የነበረው በየአምስት ዓመቱ እንዲሆን የተደረገው ከመቼ ጀምሮ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከ2001 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵ ሁለተኛ የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበበው ባህላዊ ቅርስ የትኛው ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማሊ ከፈረንሳይ ነጻነቷን ያገኘችው መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: ዋና ከተማዋ ካይሮ የሆነችው ሀገር ማን ናት?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ግብፅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየፌዴራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል ዲቼቶ አካባቢ የተገነባውን የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሽከርካሪዎች መቆያ ተርሚናል ዛሬ ተመረቀ። ተርሚናሉ በ12 ሂክታር ላይ ያረፈ ሲሆን በአንድ ጊዜ 800 ከባድ ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል መሆኑ ተገልጿል። የዲቾቶ የከባድ ተሽከርካሪ ተርሚናል 99 ሚሊየን 279 ሺህ 944 ብር ወጭ ተደረጎበት መገንባቱ ተነግሯል። \n \nጥያቄ: የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን በአፋር ክልል የት አካባቢ የጭነት መኪናዎች መቆያ ተርሚናል አስገነባ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዲቼቶ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ የመጀመሪያው አልበሙ መቼ ተለቀቀ ምንስ ይሰኝ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1963 አ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበእንግሊዝ የተሰራውና የመንገድ ላይ ምልክት ማድረጊያው ሮቦት ሙከራውን አድርጓል። ሮቦቱ የተለያዩ የመንገድ ምልክቶችን በማስመር ወጪና ጊዜን ይቆጥባል ተብሏል። የሙከራ ስራውን ባደረገበት ወቅት ውጤታማነት ታይቶበታል የተባለውቅ ሮቦት፥ በአራት ሰዓት በ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር መንገድ ላይ ምልክቶችን ማድረጉ ተነግሯል። ይህ ቴክኖሎጂ ጊዜን በመቆጠብ ስራውን የሚሰሩ ሰራተኞች ያጋጥማቸው የነበረውን ድካም፣ የሚደርሰውን የወገብ ጉዳት እና ምልክት በሚያደርጉበት ወቅት የሚከሰተውን የመኪና አደጋ ይቀንሳል ነው የተባለው። ይህን ቴክኖሎጂ የተቀበሉት ዋይ ጂ የመንገድ ተቋራጭ ቡድን ሥራ አስኪያጅ ዌን ጆንስተን፥ ቴክኖሎጂው መጨናነቅን ለመቀነስ፣ ጊዜን እና ገንዘብን ለመቆጠብ እንዲሁም ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው ነው ያሉት። እንዲሁም ለተሻለ እና ጥራት ላለው የመንገድ ላይ ምልክት ያገለግላልም ብለዋል። ምንጭ፡- traffictechnologytoday.com ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመንገድ ላይ ምልክት ማድረጊያው ሮቦት የሙከራ ስራውን ባደረገበት ወቅት በሰዓት ምን ያህል ኪሎ ሜትሮችን ሰራ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአራት ሰዓት በ12 ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ ሁለተኛ ዲግሪዋን በምን የትምህርት ዘርፍ ተመረቀች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በማኅበራዊ ሥራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ ሀገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ባሕርን አቋርጦ መጣ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገር በመጣ ወራሪ ቀጥተኛ ተጠቂናትና ሊቃውንቷ፣ ገዳማትና አድባራቷ እንዲሁም ንዋያተ ቅድሳቷ በወራሪው የኢጣልያ ኃይል ይጨፈጨፉና ይቃጠሉ ገቡ ፡፡ ይህ ግፍ በዕውቀት ኮትኩታ ባሳደገቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈጸም ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ወሰኑ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላ ከተማዋ ባሰማራቸው በርካታ ባንዳዎች መካከል ብፁዕነታቸው እንዳሰቡት ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ እዚሁ ከተማ ተሰውሬ መኖር አልፈልግም፤ ወደ ገጠር ፊቴን አልመልስም በማለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በወቅቱ የኢጣሊያ እንደራሴ ለነበሩት ራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፡፡ እራስ ኃይሉም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ ፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀት በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲያዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ከድል በኋላ የብፁዕነታቸ ሐውልት ተመርቆ የቤተ መንግሥቱም ሆኑ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት አበባ ጉንጉን ከሐውልቱ ሥር ሲያስቀምጡ ከቤተ ክህነት ካስቀመጡት አባቶች አንዱ በ1921 ዓ.ም አብረዋቸው የተሾሙት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ነበሩ፡፡ ትውልድ ሁሉ ለሀገር ክብርና ለነጻነት በተከፈለው፡፡ የብዕፁነታቸው ሕይወት እንዲማርበትና ሕያው ምስክር ሆኖ እንዲኖር የቆመላቸውን ሐውልት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በክብር ይጠብቁታል ፡፡ የእኝህን ታላቅና ቅዱስ ሰማዕት አባት ክብርና ተጋድሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ዓመት በፊት ቅዱስ /ሰማዕት/ ብሎ በማጽደቅ በስማቸው በቅድስና ማዕረግን ሰጥቶ በስማቸው ታቦት ተቀርጾ ቤተክርስቲያን እንዲሰራላቸው ወስኗል ፡፡ ይህም በተወለዱበት በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረሰብከት በፍቼ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ አርበኛ፣ ጀግና፣ ጳጳስ፣ ሰማዕት ቅዱስም የሆኑ አባት ናቸው ፡፡ \n \nጥያቄ: ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አልሸሽም ብለው መቼ ለኢጣሊው እንደራሴ ለራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ዘ ኢትዮጵያ ካረፉ በኋላ ተከታዩን ፓትርያርክ ለመሾም በተደረገው ምርጫ በዕለቱ ተገኝተው የመረጡት ፻፵፮ አባላት ሲሆኑ ሦስቱ ዕጩዎች፦ ፩) አቡነ ቴዎፍሎስ (የሐረርጌ ሊቀ ጳጳስ) - ፻፳፫ ድምጽ ፪) አቡነ ያዕቆብ (የወለጋ ሊቀ ጳጳስ) - ፰ ድምጽ ፫) አቡነ ጢሞቲዎስ (የሲዳሞ ሊቀ ጳጳስ - ፲፫ ደምጽ አግኝተዋል። በዚህም መሠረት የፓትርያርኩ ስርዓተ ሲመት ግንቦት ፩ ቀን ፲፱፻፷፫ ዓ/ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናውኗል። በ፲፱፻፷፮ ዓ/ም በኢትዮጵያ ወታደራዊው አብዮት ተለኩሶ ንጉሠ ነገሥቱ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም ከሥልጣን ሲወርዱ ወዲያው የቤተ ክርስቲያኗም ንብረት ተወረሰ። ፓትርያርኩንም ከሥልጣን ከማውረዱ በፊት ደርግ “የተሐድሶ ጉባዔ” የሚል ኮሚቴ አቋቁሞ በተለያየ ክፍል በሳቸው ላይ የማይገታ አመጽና አድማ መነሳሳት ጀመረ። በዚህ ሁኔታ ለአንድ ዓመት ያኡል በትዕግስት ከቆዩ በኋላ በየካቲት ወር ፲፱፻፷፰ ዓ/ም የደርግ መንግሥት “ሲጠበቅ የቆየ ፍርድ” በሚል አዋጅ ከሥልጣን አውርዶ እሳቸውንና በመጨረሻ በእሳቸው የተሾሙትን ሦስት ጳጳሳት (ያሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ አንዱ ናቸው) አሰራቸው። በኋላም ሐምሌ ፯ ቀን ፲፱፻፸፩ ዓ/ም እኒህ የቤተ ክርስቲያን መሪ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ርዕሰ ሊቃና ጳጳሳት ወፓትርያርክ ዘ ኢትዮጵያ በደርግ እጅ ተገደሉ። ቀደም ሲል “የተቀባ ፓትርያርክን ሞት ብቻ ነው የሚሽረው” የሚለውን እምነት በሚቃረን ሁኔታ ከሥልጣን አውርደው “የተቀባ ፓትርያርክ ሳይሞት በላዩ ላይ ሌላ ፓትርያርክ አይሾምም” የሚለውን ሁለተኛውን እምነት ጥሰው ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ሦስተኛው ፓትርያርክ እንዲሾሙ አደረጉ። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ማናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ ለዓለም በርካታ ስራዎችን አበርክቶ ከዚህ ዓለም ያረፈው መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቦትስዋና ቦትስዋና ወይም በይፋ የቦትስዋና ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ Republic of Botswana ሰጿና፡ Lefatshe la Botswana) በደቡባዊ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ አገር ናት። ቦትስዋና የቀድሞ የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ስትሆን ነፃነቷን በመስከረም ፳ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ከተቀዳጀች በኋላ መሪዎቿ በነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫዎች ተመርጠዋል። ቦትስዋና ሜዳማ ስትሆን ከሰባ ከመቶ በላይ በካለሃሪ በርሃ የተሸፈነች ናት። በደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ከደቡብ አፍሪካ፣ በምዕራብና ሰሜን ከናሚቢያ እና በሰሜን ምሥራቅ ከዚምባብዌ ጋር ትዋሰናለች። ከዛምቢያም ጋር በደንብ ያልተወሰነ ቢበዛ በመቶ ሜትር የሚቆጠር ወሰን አላት። \n \nጥያቄ: ቦትስዋና በምዕራብና ሰሜን ምሥራቅ የምትዋሰነው ከማን ጋር ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከናሚቢያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: የፀሓይ ክብደት ከጁፒተር ጋር ሲነጻጸር ስንት እጥፍ ይበልጣል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 1000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ከቅኝ ግዛት ነጻነት በኋላ የመጀመሪያ ፕሬዘዳንት የሆነው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሊዎፖልድ ሴንግሆርም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ትራምፕ የፕሬዝደንትነት ስልጣን ላይ መቼ ወጣ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: በውሃ ላይ የሚሄደው የኤሌክትሪክ ብስክሌት በሰአት እስከ ስንት ኪሎ ሜትር ድረስ ይጓዛል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን ያሻሻለው ውድድሩን በምን ያህል ሰዓት በመሮጥ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል የፕሬዘንዳቶች ምርጫ ከ2001 ዓ.ም. በኋላ በየስንት ዓመቱ ማድረግ ጀመረች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በየአምስት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር መንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር በቢትወደድ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ተጽፎ በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. የታተመ መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ ከመስራት የተነሳ የሰው ልጅ እንዴት ከተፈጥሮ ጥገኝነት ተላቅቆ ከኋላ ቀር አኗኗር ወደ ተሻለ ሕይወት እንደሚለወጥ የሚያስረዳ ሲሆን የዓለም ሕዝቦች የዕውቀታቸውና የሀብታቸው ደረጃ ከፍና ዝቅ ያለ መሆኑ ምክንያቱ ከጦርነት የተነሳ ነው ይላል። ጦርነቱንም የሚነሱ ነገሥታትና አለቆቹ ሁሉ ልባቸው ሀብት እንደፈለጉ አይገልፅም። ነገር ግን ስም ለመፈለግና ለማግኘት ወይም ሀይማኖቱን ለማስፋፋት ወይም የተጠቃውን ለመርዳት አስመስለው ይነሳሉ። የጦርነት ሁሉ ፍፃሜ ምኞት ግን መዝረፍና ማስገበር ነው። ይህንንም ሲሉ ዕውቀታቸው የሰፋ ነገሥታትም ቢሆኑ መዝረፍን አይተዉም። አዘራረፋቸው ግን የዕውቀት አዘራረፍ ነው እያለ በሰፊው ያወሳል። በአክሱም ዘመነ መንግሥት የእስራኤልና የአህዛብ ወገን ተብሎ የሁለት ዓመት ጦርነት በመፍጀቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፍ ወዳለው ደረጃ እንዳይደርስ ዋና መሰናክል ሆኗል። ዋጋ ማለት የስራ መለኪያ ነው። ዕውቀት ከጉልበት ይከበራል። ዕውቀት የሌለው ሕዝብ ሁሉ ለብቻው መንግሥት ቢኖረውም ባይኖረውም ዕውቀት ያላቸው ሕዝቦች ይገዙታል። ሰው ሲፈጠር ጌታና ድሀ ሆኖ አልተፈጠረም። ድህነትና ጌትነት የተለየው በሰው ዕውቀት ነው። የሀብት መለኪያ ሥራ ነው። ስለዚህ ሀብት ማለት የተከማቸ ሥራ ማለት ነው። \n \nጥያቄ: መንግስት እና የህዝብ አስተዳደር የተሰኘው መጽሐፍ በማን ተጻፈ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በቢትወደድ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: ብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር የሰላምታ መልዕክት በመለዋወጥ የመረቁት እነማን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ በደቡብ ምስራቅ የሚያዋስናት ሀገር የትኛው ነው ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ኦማን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ ፈጥራው የነበረው ኮንፌደሬሽን ከስንት ዓመት በኋላ ፈረሰ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ከስምንት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: ሯጭ ኃይሌ የአሥር ሺህ ሜትር ርቀት ሩጫ የወርቅ ሜዳልያ ያገኘው የት በተካሄደው ኦሎምፒክ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በሲድኒ እና በአትላንታ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በአፍሪካ የመጀመሪያው የቴሌቪዥን ስርጭት የተደረገው መች ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1952 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nውትድርና የናይጄሪያ ጦር ሠራዊት ሀገሯን የመከላከል፣ የሀገሯን ፍላጎት የማስጠበቅ እና ፀጥታ አስጠባቂ ጥረቶችን የመደገፍ ግዴታ አለበት። ሠራዊቱ የምድር፣ የባህርና የአየር ኃይል አለው። ሠራዊቱ ከነፃነት ጀምሮ በሀገሯ ታሪክ ላይ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በተለያዩ ጊዜያት የውትድርና ጁንታዎች ሥልጣን በመያዝ አገሯን አስተዳድረዋል። የናይጄራያ ሠራዊት በፀጥታ ጠባቂነት ደረጃ ከ1995 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በላይቤሪያ (1997 እ.ኤ.አ.)፣ አይቮሪ ኮስት (ከ1997 እስከ 1999 እ.ኤ.አ. ) እና ሲየራ ሊዮን (ከ1997 እ.ኤ.አ. 1999 እ.ኤ.አ.) ተሰማርቷል። ምጣኔ ሀብት በግብርና ናይጄሪያ በዋናነት ለአለም የምታቀርበው ምርቶች በተለይ ካካውና ጎማ ናቸው። እንዲሁም ፔትሮሊየም ከሚያቀርቡት አገራት 12ኛ ነች። በተጨማሪ፣ የመኪና ሥራ ድርጅት (ኢኖሶን ተሽከርካሪ መፈብረክ) ይኖራል። መልከዓ ምድር ናይጄሪያ በምዕራብ አፍሪካ በጊኒ ባሕረ ሰላጤ ላይ ትገኛለች። የቆዳ ስፋቷ 923,768 ካሬ ኪ.ሚ. ሲሆን ከዓለም ፴፪ኛዋ ትልቅ ሀገር ናት። ድንበሯ 4,047 ኪ.ሜ. ርዝመት ሲኖረው ከቤኒን 773 ኪ.ሜ.፣ ኒጄር 1,497 ኪ.ሜ.፣ ቻድ 87 ኪ.ሜ.፣ ካሜሩን 1,690 ኪ.ሜ. ትዋሰናለች። በተጨማሪም 853 ኪ.ሜ. ርዝመት ያለው ጠረፍ አላት። በናይጄሪያ ውስጥ ከፍተኛው ቦታ ቻፓል ዋዲ ተራራ ሲሆን ከፍታው 2,419 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ነው። የአገሯ ዋና ወንዞች ኒጄር እና ቤንዌ ሲሆን ወደ ኒጄር ደለል ይፈሳሉ። \n \nጥያቄ: የናይጄሪያ ሰራዊት ሰላም ለማስከበር ወደ ላይቤሪያ የገባው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1997 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nከ1881 እስከ 1905 ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ በአፍሪካ ይዞታቸውን እያሰፉ የነበሩትን የአውሮፖ ሀይሎችን ጥቃት በመከላከል ኢትዮጵያን በስርዓት አስተዳድረዋል፡፡ በዚያን ጊዜ ጣልያን ኤርትራን በከፊል ቅኝ ገዝታ የነበረችበትና በ1880ዎቹ አጋማሽ ላይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ቅኝ ገዝታት የነበረችበት ጊዜ ስለነበር ከሌሎች አውሮፖ አገራት በበለጠ ለኢትዮጵያ አስጊ ነበረች፡፡ በ1880 ግን እስከዛሬ ድረስ ዝነኛ በሆነው የአድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ጣልያንን ድል በማድረግ በአፍሪካ የባእዳን ገዥ ሀይሎችን ያሸነፈች ብቸኛዋ ሀገር ሆናለች፡፡ ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ የቅኝ ገዥዎችን ወረራና መስፋፋት በመመከትና ድልን በመቀዳጀት ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን በባርነት ቀንበር ተጠምደዉ ለሚማቅቁ የመላዉ ዓለም ህዝቦች ከፍተኛ ክብርና ተስፋን አጎናጥፈዋል በ1908 የዳግማዊ ሚኒሊክ ልጅ የሆኑትን እቴጌ ዘውዲቱ ስልጣን ያዙ ፡፡ የሳቸው የቅርብ የስጋ ዘመድ የነበሩት ራስ ተፈሪ መኮንንም ሞግዚት አስተዳደርና ወራሽ ሆነው ተሹመዋል፡፡ እቴጌ ዘውዲቱ በ1922 ሲሞቱ ተተኪያቸው ዐጼ ሀይለስላሴ ስልጣን ያዙ ፡፡ ነገር ግን በ1928 ዓ.ም የጣልያን ሀይሎች ኢትዮጵያን ለአጭር ጊዜ ወረው ሲቆጣጠሩ ግዛታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ \n \nጥያቄ: በንጉሥ ዳግማዊ ሚኒሊክ ዘመን ለኢትዮጵያ አስጊ የነበረችው የኤርትራ ገዢ ሀገር ማን ነበረች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጣልያን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በስንት ዓመታቸው አረፉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፳፫ ዓመታቸው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ፓርላማ ውስጥ ካሉት ሁለት ምክር ቤቶች ፻፳ መቀመጫዎች ያለው የቱ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የብሔራዊ ስብሰባ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ከሚገኙት አምስቱ ነጋድራሶች መካከል በሰቆጣ የነበረው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዋልተር ፕላውዴን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nተቀማጭነቱ ካሊፎርኒያ ውስጥ ያደረገው ኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የተባለው የሶፍትዌር አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ፡፡ የኢ ኦ ኤን ኩባንያ መስራች ዳን ለጀርስካር ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት መኖሩን ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሂሩት በበኩላቸው የቴክኖሎጂውን አስፈላጊነትና ወቅታዊነትን በመገንዘብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኩባንያው ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የሶፍትዌር አምራች ድርጅት ተቀማጭነቱ የት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ካሊፎርኒያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዐምደ ጽዮን ቀዳማዊ አጼ ዐምደ ጽዮን (የዙፋን ስም ገብረ መስቀል) ከ1314 እስከ 1344 ዓ.ም. የነገሡ ሲሆን በጥንቱ ዘመን ከተነሱ ነገሥታት ውስጥ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ሰፋ ያለ አሻራ ትተው ካለፉት (ለምሳሌ፦ ዘርአ ያዕቆብ) ጎን ወይም በላይ ስማቸው ይጠቀሳል። አጼ ዐምደ ጽዮን የአጼ ይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅና የአጼ ወድም አራድ ልጅ እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ይኩኖ አምላክ አዲሱን የሰሎሞን ስርወ መንግስት ቢመሰርቱም፣ በልጅ ልጆቻቸው የነበረው ፉክክርና አዲስ ከሚስፋፋው የእስልምና ሃይማኖት የሚሰነዘረው ጥቃት ስርዓቱን ስጋት ላይ የጣለ ነበር። አጼ አምደ ጽዮን ይህን ፉክክር በማስቆምና በዘመናት በማይደበዝዘው ጀግንነታቸው የኢትዮጵያን ድንበር ከሞላ ጎደል አሁን በሚታወቀው መልኩ በማስቀመጥ፣ የአዲሱን ስርወ መንግስት መሰረት በማጽናት እንዲሁም በማረጋጋት ዝናቸው በጥንቱ አለም ክአፍሪቃ ቀንድ እስከ አውሮጳ የተንሰራፋ ነበር። \n \nጥያቄ: የአጼ ዐምደ ጽዮን የዙፋን ስም ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ገብረ መስቀል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአልጄሪያ አልጄሪያ (አረብኛ፦ الجزائر‎ አል ጃዝኤር; በርበርኛ፦ ድዜየር) በይፋ የአልጄሪያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በሰሜን አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። ከቆሳ ስፋት አኳያ በሜዲቴራንያን ባህር ዙሪያ ትልቋ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ ከሱዳን በኋላ ሁለተኛ ናት። አልጄሪያ ከሰሜን ምሥራቅ በቱኒዚያ፣ ከምሥራቅ በሊቢያ፣ ከምዕራብ በሞሮኮ፣ ከደቡብ ምዕራብ በምዕራባዊ ሣህራ፣ ሞሪታኒያና ማሊ፣ ከደቡብ ምሥራቅ በኒጄር፣ ከሰሜን በሜዲቴራንያን ባህር ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ አልጂርዝ ሲሆን የ፳፻፫ ዓ.ም. ሕዝብ ብዛቷ ወደ 35.7 ሚሊዮን ይገመታል። አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት፣ የአፍሪካ ሕብረት፣ ኦፔክ እና ሌሎችም ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አባል ሀገር ናት። የሀገሯ ስም የመጣው ከአልጂርዝ ከተማ ሲሆን በድሮ ጊዜ ከዛሬዎቹ ምዕራብ ቱኒዚያና ምሥራቅ ሞርኮ አብራ ኑሚዲያ ትባል ነበር። በጥንት ጊዜ አልጄሪያ የኑሚዲያ መንግሥት ትባል የነበረ ሲሆን ነዋሪዎቿ ደግሞ ኑሚዲያውያን ይባሉ ነበር። የኑሚዲያ መንግሥት ከካርታጎ፣ ሮማና ጥንታዊ ግሪክ ጋር ግንኙነት ነበራት። አካባቢው ለምለም እንደነበረ ሲነገር ኑሚዲያውያን ደግሞ ለኃይለኛ ፈረሰኛ ጦራቸው ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የአልጄርያ የጥንት መንግሥት ስያሜ ምን ይባል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የኑሚዲያ መንግሥት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ታሊዝ የፀሐይ ግርዶሽ እንደሚኖር የተናገረው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ593 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሌሎች የፍልስፍና ባህሎች ከምዕራባውያን ፍልስፍና በተለየ በነዚህ ጉዳዮች ላይ በዙም አላተኮሩም። ምንም እንኳን የሂንዱ ፍልስፍና በዚህ አንፃር ከምዕራባውያኑ ቢመሳሰለም እስከ 19ኛው ምዕት-አመት ድረስ በኮሪይኛ፣ በጃፓንኛ፣ እና በቻይንኛ ውስጥ \"ፍልስፍና\" የሚል ቃል ይገኝ አልነበረም። በተለይ የቻይና ፈላስፎች ከግሪኮቹ ለየት ያለ የምደባ ስርዓት ይከተሉ ነበር። የምዕራቡ አለም ፍልስፍና የሚጀምረው ከግሪኮች ሲሆን የመጀመሪያው ፈላስፋ ተብሎ የሚታወቀው ታሊዝ ነው። ይህ ሰው የኖረበትን ጊዜ ለማወቅ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም። ይኸውም በ593 ዓክልበ. (ዓም) የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚኖር በመተንበዩ ከዚህ ጊዜ የተወሰነ አመት ቀደመ ብሎ ማይሌጠስ በተባለችው የትንሹ እስያ (የአሁኑ ቱርክ) ክፍል እንደተወለደ የታወቀ ነው። ታሊዝ ዓለም እና በውስጡ ያሉ ነገሮች ሁሉ ከውሃ እንደተፈጠሩ ያምን ነበረ። ከሱ በኋላ የተነሱ የግሪክ ፈላስፎች የሱኑ መንገድ በመከተል ዓለም ከአንድ ወይም ከሌላ ነገረ እንደተፈጠረች አስተምረዋል። ለምሳሌ አናክሲሜነስ የዓለም ጥንተመሰረቷ አየር ነው ሲል፣ ሄራቅሊጠስ እሳት ነው ብሏል። አናክሲማንደር ከነዚህ ሁሉ ለየት በማለት የዓለም መሰረቷ ይህ ነው የማይባል «apeiron» ወይም የትየለሌ የሆነ ነገር ነው ይላል። የምእራቡን ዓለም ፍልስፍና እስክ 1900 ድረስ ቅርጽ እንዳስያዙ የሚነግርላቸው ፈላስፋዎች የሚከተሉት ናቸው፡ ሶቅራጥስ፣ አሪስጣጣሪስ፣ ፕላጦ፣ አክዊናስ፣ ኤራስመስ፣ ማኪአቬሌ፣ ቶማስ ሞር፣ ሞንታጝ፣ ግሮቲየስ፣ ዴካርት፣ ሆበስ፣ ስፒኖዛ፣ ሎክ፣ ሌብኒሽት፣ በርክሌ፣ ሑሜ፣ ቮልቴይ፣ ሩሶ፣ ካንት፣ ሺለር፣ ሄግል፣ ሾፐናዎር፣ ጆን ኦስቲን፣ ጄ.ኤስ. ሚል፣ ኮምቴ፣ ዳርዊን፣ ማርክስ፣ እንግልስ፣ ፍሬደሪሕ ኚሼ፣ ዱርካሂም የምስራቁ አለም ፍልስፍና መነሻ ኢትዮጲያ ናት፡፡እንደውም የመላው አለም፡፡ በተለይ ኮከባቸው ጀምኒ የሆኑት የሐበሻ ተወላጆች የኮከባቸውን ሀያልነት በመጠቀም ወደ አረቡ አለም በመገስገስ የምድራችንን የፍልስፍና መንገድ ቀይሠዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በአናክሲሜነስ አመለካከት የዚህ ዓለም ጥንተ መሰረት ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አየር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየኢትዮጵያ ሙዚቃ የመጀመሪያውን ግራማፎን ወይም የሸክላ ማጫወቻ በ፲፰፻፹፱ ዓ.ም. ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ሊዋንቲቭ ለዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አመጡላቸው። ይኸውም ማጫወት ብቻ እንጂ ድምጽ አይቀዳም ነበር። በኋላ ግን በዓመቱ በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ከንግሥት ቪክቶሪያ የተላኩ የእንግሊዝ መልዕክተኞች በመጡ ጊዜ ግራማፎኑንና ድምፅ መቅጃውን ይዘውላቸው መጡ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸው በዲስክ የተቀረፁት ዓፄ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ናቸው። ዛሬ በእንግሊዝ አገር በለንደን ከተማ ብሪቲሽ ኢንስቲቲውት ኦፍ ሪኮርድ ሳውንድ በተባለው ሙዚየም ውስጥ ይገኛል። በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ በሸክላ የተቀረፀው የመጀመሪያው ዜማ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ስራዎች ሲሆኑ ዘመኑም በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ነበር። ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በጀርመን ቆይታቸው ወቅት የጀርመን የሙዚቃ ድርጅት ጠይቋቸው የኢትዮጵያ መዲናና ዘለሰኛ ዜማዎች በ፲፯ አይነት ስልት እየተጫወቱ ተቀርፀዋል። ኩባንያው የተሰማ እሸቴን ዜማዎች በ፲፯ ሸክላዎች የቀረፀው ሲሆን ለዜማው ባለቤት የድካም ዋጋ እንዲሆን በወቅቱ ፲፯ ሺህ የጀርመን ማርክ ከፍሏቸዋል። በዘመኑ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያም አሁንም እነዚህ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ብርቅዬ ሸክላዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ውስጥ ተሰብስበው ይገኛሉ። እነዚህ በተቋሙ እጅ ያሉት ፲፮ ሸክላዎች እያንዳንዳቸው ሁለት ዜማዎችን የያዙ ሲሆኑ ባጠቃላይ ፴፪ ዜማዎች ተቀርፀውባቸዋል። እያንዳንዱ የሸክላው ገፅ ላይ A ወይም B ተብሎ ተሰይሟል፣ የዜማው ስም ተፅፎበታል፣ የዜማው ባለቤት ተሰማ እሸቴ ስም አለ፣ ሸክላው ጀርመን ሀገር መሰራቱ እንዲሁም የሸክላው ቁጥር ተጠቅሷል። በ፲፱፻፳፭-፳፮ ዓ.ም. አካባቢ የእነ ፈረደ ጎላ፣ ንጋቷ ከልካይና ተሻለ መንግሥቱ የዜማ ሸክላዎች ብቅ እስከሚሉ ድረስ የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ሸክላዎች ከ፳ ዓመታት በላይ አቅም ባላቸው ቤተሰቦች ዘንድ በብቸኝነት በግራማፎን ሲደመጡ ቆይተዋል። \n \nጥያቄ: የመጀመሪያውን የሸክላ ማጫዋች ለአፄ ሚኒልክ ያመጡላቸው እነማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሄንሪ ደ አርሊንስ እና ኒኮላስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nነሐሴ ፳፰ ነሐሴ ፳፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፰ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፰ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፯ ዕለታት ይቀራሉ። 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ። 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳንን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት። 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቿ ሃያላት (በጀርመን ኃይል) ተወረረች። 1946 - የቻይና ኃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ። ፲፱፻፸፱ ዓ/ም በቡሩንዲ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ የአገሪቱን ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን ከሥልጣን አስወረዱ። \n \nጥያቄ: በቡሩንዲ በ፲፱፻፸፱ ዓ/ም ፕሬዚደንት ዣን ባፕቲስት ባጋዛን በመፈንቅለ መንግሥት ከስልጣናቸው የሻራቸው ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሻለቃ ፒዬር ቡዮያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ በመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ላስመዘገበችው ውጤት ሩዋንዳ በተዘጋጀው የአፍሪካ የጤና ኮንፍራስ ላይ እውቅናን አግኝታለች :: በሀገር አቀፍ ደረጃ ሞዴል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያ የሆነችው ወ/ሮ ሰናይት 40,000 የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን በመወከል ሽልማቱን ተቀብላለች:: \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ ሩዋንዳ በተዘጋጀው የአፍሪካ የጤና ኮንፈረንስ ላይ እውቅና ያገኘችው በምን ምክንያት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በመሰረታዊ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ላስመዘገበችው ውጤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአዋሽ ብሔራዊ የመዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል በ፲፱፻፶፰ ዓ/ም የተመሠረተ ክልል ሲሆን ከአዲስ አበባ በስተ ምሥራቅ አቅጣጫ በ፪መቶ ፲፩ ኪሎሜትር ርቀት ፤ በአፋርና በኦሮሚያ አዋሳኝ ክልሎች ሥር ይገኛል። ይህ ክልል ሲመሠረት በ ፱፻፮ ካሬ ኪሎሜትር የቆዳ ስፋት (ቦልቶን ፲፱፻፷፰) የነበረው ቢሆንም፤ ባሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ማስረጃ እንዳስቀመጠው የክልሉ የቆዳ ስፋት ፯መቶ ፶፮ ካሬ ኪሎ-ሜትር ነው። የክልሉ ደቡባዊ ድንበር የአዋሽ ወንዝ ሲሆን፣ የተሠየመውም በዚሁ ታላቅ ወንዝ ስም ነው። ክልሉ የብዙ ዓይነት አራዊት እና አዕዋፍ መጠለያ ከመሆኑም ባሻገር ፍል-ውሓ እና የፋንታሌ ተራራ ይገኙበታል። የአገሪቱ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥልጣን ሲመሠረት ለንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በአማካሪነት የተመደበው እንግሊዛዊ ባቀረበው ኃሣብ መሠረት የመጀመሪያው ብሔራዊ የዱር አራዊት ጥበቃ ባለ-ሥጣን ከተመሠረተ በኋላ የቅድሚያ ሥራ የተደረገው፤ በታቀዱት ክልሎች የሚገኙትን የአገሪቱን የዱር አራዊት ኃብት መጠን ማረጋገጥ ነበር። ለዚህም ሥራ ከብሪታኒያ ተመልምሎ የተቀጠረው ባለ-ሙያ እንግሊዛዊው የሥነ-ሕይወት ባለሙያ ሜልቪን ቦልቶን ነበር። የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል የበርካታ የዱር አራዊት፤ አዕዋፋት እና የውሐ አራዊት መኖሪያ ነው። በደቡብ አዋሳኙ በሆነው የአዋሽ ወንዝ አዞ እና ጉማሬ ሲገኝበት፤ በሰሜን ክፍሉ ደግሞ ጦጣና ዝንጀሮ፤ እንዲሁም ጅብ እና አጋዘን ይገኙበታል። በክልሉ ከሚገኙት የዱር አራዊት በከፊሉ፦ ጉሬዛ፤ ተራ ዝንጀሮ፤ ነጭ ዝንጀሮ፤ ጦጣ፤ ሳላ፤ የሜዳ ፍየል፤ ሚዳቋ፤ ትልቁ የቆላ አጋዘን ፤ አምባራይሌ፤ ከርከሮ፤ ቆርኪ በብዛት የሚገኙ ሲሆን አንበሣ፤ ነብር፤ ጀርባ-ጥቁር እና ተራ ቀበሮ፤ዳልጋ አንበሣ፤ አነር እና የዱር ድመት ደግም አልፎ-አልፎ ይታያሉ። ባለፉት አሥር ዓመታት ጊዜ ውስጥ በተካሄደ ምዝገባ እንደተረጋገጠው፣ በክልሉ ውስጥ ፬መቶ ፷፪ ዓይነት የወፍ ዝርያዎች ተመዝግበዋል። ከነዚህም መኻል ስድስቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ ናቸው። እነዚህም መንቆረ-ጥቁር ጋርደም፤ ግንደ-ቆርቁር፤ ክንፈ-ነጭ የገደል-ቻት፤ ጅራተ-ረጅም ወማይ፤ ቁራ እና ጋጋኖ ናቸው። \n \nጥያቄ: የአዋሽ ብሔራዊ መዝናኛ እና የዱር አራዊት ጥበቃ ክልል አሁን ያለው የቆዳ ስፋት ስንት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፯መቶ ፶፮ ካሬ ኪሎ-ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የምን ክትባት ፈለሰፉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የደስታ በሽታ ክትባት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ዳምጠው አየለ የመጀመሪያው ወፌ ላላ የተሰኘ አልበሙ የምን ሥራ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የሸክላ ስራ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ የመጀመሪያውን ዲግሪ ከየት ዩኒቨርሲቲ አገኘ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከለንደን ዩኒቨርስቲ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nከተጠመቀ በኋላ ባስሊዮስ በ፫፻፵፱ ዓ ም ወደ ፍልስጤም ፣ ግብፅ ፣ ሶርያ እንዲሁም ሜዞፖታሚያ የመመንኮስንና የገዳማዊነት ትምህርት ለማጥናት ሄደ ። ያለውን ሐብት በሙሉ ለድሆች አድሎ እንደጨረሰ ወደ ምነና በፖንተስ ኒዎሢዛርያ (በዘመኑ አጠራር ኒክሳር ቱርክ) ቤተክርስቲያን ገባ ። ባስልዮስ ይህን የገዳማዊ ኑሮ ቢያከብረውም ለሱ እንዳልተጠራ ተረዳ ። የሴባስቴው እዩስታቴየስ እጅግ የታወቀ መኖክሴ በፖንተስ አካባቢ ባስሊዮስን ያስተምረው ነበር ። በዶግማ ላይ ግን ይለያዩ ነበር ። ይልቁን ባስሊዮስ በመንፈሳዊ ማኅበራዊ ኑሮ ተሳበና በ፫፻፶ በአስተሳሰብ ከእሱ ጋር የሚመሳሰሉትን የክርስትና ደቀመዝሙሮች ወንድሙን ጴጥሮስን ጨምሮ ማሰባሰብ ጀመረ ። አንድላይ ሆነው በቤተሰቡ ርስት ላይ አኔዚ አጠገብ ገዳም መሠረቱ ። በጣም ግልፅ ለማረግ (በዘመኑ አጠራር ሶኑዛ ወይም ኡሉኮይ የዬሲሊርማክ ባሕርና የኬልኪት ባሕር የሚገናኙበት ቦታ ላይ ማለት ነው ።). ባልተቤትዋ እናቱ ኤሚልያ ፣ እህቱ ማክሪናና ሌሎች ሴቶችም ራሳቸውን ለቅዱስ ተግባር መጽዋት በማድረግ ከባስሊዮስ ጋር ተባበሩ ። (ይህን ማኅበረሰብ የመሠረተችው እህቱ ማክሪና ናት የሚሉም አሉ) ። ቅዱስ ባስሊዮስ እዚህ ባታ ላይ ስለ ገዳማዊ ማኅበራዊ ኑሮ ጽፎ ነበር ። ጽሁፉ ግን ለምሥራቃዊ ክርስትና ዕድገት ከፍተኛ ምክኒያት ሆንዋል. በ፫፻፶ዓ ም ባስሊዮስ ጉዋደኛውን ጎርጎሪ (ግሬጎሪ) የናዚያነስን በአኔዚ እዲቀላቀል ጋበዘው። ጎርጎሪዮም (ግሬጎሪ) እንደመጣ በኦሪጄን ፊሎካሊያ የኦሪጄን ሥራዎች ስብስብ ላይ ጥናት ማድረግ ጀመሩ ። ከዚህም በኋላ ግሬጎሪ ወደ ናዚያነስ ወደ ቤተሰቦቹ ለመመለስ ወሰነ ። ባስሊዮስ የቁንስጥጢናውን የሊቃውንት ጉባዔን ፫፻፶፪ ዓ ም ተሳተፈ ። በመጀመሪ ከኤዩስታቲየስና ከሆሞወሲያንስ ወገነ ፣ ግማሽ አራዊያን የሆነ የመናፍቅ ቡድን ፣ ወልድ ከአብ ጋር ተመሳሳይ እንጂ አንድ ባሕርዪ ወይም አካል አይደለም ብለው ከሚያስተምሩ ጋር ማለት ነው። ሆሞወሲየንስ የአውኖሚየስን አርያኒዝም ይቃወማሉ ግን ደግሞ ከኒቂያ ጉባዔ ተከታዮች ጋር የሥላሴን አንድነት \"ሆሞወሲዮስ\" ከሚያስተምሩት ጋር መተባበር አይፈቅዱም ። በዚህም ቢሆን በዚያ የባስሊዮስ ጳጳስ ዲያኒየስ የቄሣሪያው የሚከተሉት የቀድሞውን ንቂያ ስምምነት ነበረ ። ባስሊዮስም ወዲያውኑ ሆሞወሲያንስን ጥሎ እንዲየውም ጠንካራ የኒቂያ ጉባዔ ውሳኔን ተከታይ ሆነ። \n \nጥያቄ: ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ የቁንስጥጢናውን የሊቃውንት ጉባኤ መቼ ተሳተፉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፫፻፶፪ ዓ ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nመጋቢት ፳፮ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት የመጀመሪያው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፱ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል። ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅት መሠረቱ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (የዓለም የንግድ ማዕከል) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል። ፲፱፻፷ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በሜምፊስ ከተማ በነፍሰ-ገዳይ እጅ ተገደለ። \n \nጥያቄ: አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በየትኛው ከተማ ተገደለ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሜምፊስ ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ የ2010 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፲፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የነበረ ሲሆን ከሰኔ ፬ እስከ ሐምሌ ፬ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ተካሄዷል። ውድድሩን ለማቅረብ የተካሄደው ዕጣ ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ብቻ እንዲሳተፉ ነበር የተፈቀደው። ደቡብ አፍሪካ ግብፅና ሞሮኮን በማሸነፍ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫን ያቀረበች አፍሪካዊ ሀገር ሆናለች። ፊፋ ለውድድሩ ያቀረበው ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ $420 ሚሊዮን ነው። ይህም ከ2006 እ.ኤ.አ. ውድድር ሽልማት ገንዘብ የስልሳ ከመቶ ዕድገት አለው። ከዚህ ውስጥ $40 ሚሊዮን የሚሆነው ተጫዋቾቹ ለሚጫወቱበት ክለቦች ተጫዋቾቹ ለሚደርስባቸው ጉዳት መካካሻ እንዲሆን ተሰጥቷል። ከውድድሩ በፊት እያንዳንዱ ቡድን ለዝግጅት ወጪው $1 ሚሊዮን ተረከበ። ግጥሚያዎቹ በዘጠኝ ከተማዎች ውስጥ በሚገኙ አስር ስታዲየሞች ውስጥ ነው የተካሄዱት። የዋንጫ ጨዋታው በጆሃንስበርግ ከተማ በሚገኘው ሶከር ሲቲ ስታዲየም ነው የተከናወነው። የምድብ ድልድል ሥነ ስርዓቱ በኬፕ ታውን፣ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል በኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፪ ዓ.ም. ተከናወነ። ሥነ ስርዓቱ የቀረበው በደቡብ አፍሪካዊቷ ተዋናይ ሻርሊዝ ቴሮን እና የፊፋ ዋና ጸሐፊ ዠሮም ቫልክ ነው። የዕጣ ኳሶቹን ያወጡት ዴቪድ ቤክሃም፣ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ፣ ጆን ስሚት፣ መካያ ንቲኒ፣ ማቲው ቡዝ እና ሲምፊዌ ድሉድሉ ናቸው። የፊፋ ዳኛዎች ኮሚቴ ፳፱ ዳኛዎችን ለዓለም ዋንጫ መርጧል። እነዚህም ከኤ.ኤፍ.ሲ. አራት፣ ከካፍ አስር፣ ከኮንሜቦል ስድስት፣ ከኮንካካፍ አራት፣ ከኦ.ኤፍ.ሲ. ሁለት እና ከዩኤፋ አስር ዳኛዎችን ያጠቃልላል። እንግሊዛዊው ዳኛ ሀዋርድ ዌብ የዋንጫ ጨዋታውን እንዲዳኝ ተመርጧል። \n \nጥያቄ: የ2010 ዓ.ም. የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ማን ናት?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ደቡብ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: ግብጽ የምትገኝበት አህጉር የት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ኣፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ ሴት አሜሪካዊት ማን ትባላለች?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፐርል በክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአዲስ አበባ መስከረም 23/2012 ዕውቁና አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ በውጭ አገራት የሚሰሩ ኢትዮጵያዊያን ሳይንቲስቶች ወጣቶችን በሳይንስ በማነጽ ተግባር እንዲሰማሩ፤ መንግስትም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰር ጥላሁን በቻይና ከሚገኙ የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ ውስጥ የአፍሪካ ሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ሊያቋቁሙ መሆኑን ይፋ አድርገዋል። የአሜሪካው ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ቤት ዕውቁ ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በሚዘጋጀው ወርኃዊ የሳይንስ ገለጻ መድረክ ወጣቱን ትውልድ ማስተማርና ማነጽ ለኢትዮጵያ ተስፋ፤ የቻይና ተምሳሌትነት በሚል ትናንት ምሽት ገለጻ አድርገዋል። በአውሮጳዊያኑ ዘመን አቆጣጠር 1943 በኢትዮጵያ የተወለዱት ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ጥላሁን ይልማ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በናዝሬት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ የግብርና ቴክኒካል ትምህርት ቤቶች አጠናቀው በቀድሞው የአለማያ እርሻ ኮሌጅ ለሁለት ዓመት ተከታትለዋል። ከዛሬ 55 ዓመታት በፊት በኮሌጅ ቆይታቸው ባሳዩት የላቀ ውጤትም አሜሪካን አገር በሚገኘው የካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና ትምህር ቤት ተልከው ትምህርታቸውን በማጥናት ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በቢሾፍቱ የእንስሳት ህክምና ትምህርት ቤት አስተምረዋል። ከሁለት ዓመታት በኋላም ወደ ካሊፎርኒያ ዳቪስ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የ3ኛ ዲግሪያቸውን በደቂቀ ሥነ ሕይወት መስክ በማጥናት በአውሮጳዊያኑ አቆጣጠር ከ1980-2006 በተማሩበት ካሊፎርኒያ በዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ከረዳት እስከ ሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አስተምረዋል፤ ተመራምረዋል። እ.አ.አ ከ2017 ጀምሮ ደግሞ የዲስቲንጉሽድ ፕሮፌሰር ኤሜሪተስ ማዕረግ ያገኙ ሲሆን እ.አ.አ ከ1990 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዓለም አቀፍ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል በማቋቋም በዳይሬክተርነት እየመሩ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ በዳይሬክተርነት እየመሩት ያለው ተቋም ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሞሌኪዩራል ባዮሎጂ ላብራቶሪ ማዕከል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nበውሃ ላይ የሚሰራ የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ መዋሉ ተነገረ። ማንታ 5 የተባለው የኒውዝላንድ ኩባንያ ኤክስ ኢ 1 የተሰኘችውን እና በውሃ ላይ የምትሰራውን የኤሌክትሪክ ብስክሌት በላስ ቬጋስ አስተዋውቋል። ብስክሌቱ በፔዳል የሚሰራ ሲሆን፥ አንድ ጊዜ ባትሪ ከተሞላ በኋላ ለአንድ ሰዓት ያክል መጠቀም ይቻላል። በሰዓትም እስከ 20 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ድረስ መጓዝ ይችላልም ነው የተባለው። አዲሱ ብስክሌት የ6 ሺህ ፓውንድ ዋጋ ተቆርጦለታል። ብስክሌቱን ለዕይታ ለማብቃት እስከ 10 አመት ጊዜ እንደፈጀ ኩባንያው ምርቱን ባስተዋወቀበት ወቅት ገልጿል። አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 29፣ 2012 (ኤፍቢሲ) \n \nጥያቄ: በውሃ ላይ የሚሰራ ኤክስ ኢ 1 የኤሌክትሪክ ብስክሌት በገበያ ላይ ያዋለው ድርጅት ማነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ማንታ 5 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ በማን ተመሰረተች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በኢብን ሣኡድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ምርምሮች በቫይረስ ጥቃት በእንስሳትና በሰው ላይ ለሚከሰቱ በሽታዎች በዘረመል ምህንድስና ጥበብ ክትባት ወይም መከላከያ መድሃኒት ግኝቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው። በዚህም የበርካታ በሽታዎች ክትባትና መድሃኒት ግኝቶች ባለቤት ሲሆኑ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ያደረጋቸው ደስታ በተሰኘውና ከ100 ዓመት በፊት በአውሮጳና በአፍሪካ ከፍተኛ ዕልቂት ላደረሰው የከብቶች መቅሰፍት በሽታ ክትባት መፈልሰፋቸው ነው። ይህን ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በርካታ የምርምር ተቋማት ደክመው ያላሳኩትን የደስታ በሽታ ክትባት ማግኘታቸው በህክምና ግኝቶች መስፈርት አንቱ አስብሏቸዋል፤ ዓለምንም በደስታ በሽታ ከሚደርሰው እልቂት ታድገዋል። በእንግሊዝና በጣሊያን ወታደሮች ሴራ ወደ ኢትዮጵያ በገቡ ከብቶች በተዛመተው የደስታ በሽታ እ.አ.አ ከ1888-1892 ለአራት ዓመታት በኢትዮጵያ በደረሰው እልቂት ከፍተኛ ረሀብ መከሰቱን ያስታወሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን የምርምራቸው መነሻ ከወላጆቻቸው ስለ ከብት መቅሰፍት ሲሰሙ ማደጋቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሰውና በእንስሳት ህክምና ዕውቀት በሁለቱም ሰይፍ የተካኑት አንጋፋው ሳይንቲስት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ክትባት ለማግኘትም ደክመዋል። ከ124 በላይ የሚሆኑ የምርምር ግኝቶች በስመ ጥር ዓለም አቀፍ የምርምር መጽሔቶች የታተሙላቸው ሲሆን በአሜሪካና በቻይና በሚገኙ በርካታ ተቋማትም የአካዳሚ አባልነት ተመርጠዋል፤ በአማካሪነትም እየሰሩ ይገኛል። በተማሩበት ብሎም ባስተማሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ጨምሮ በአሜሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ዕውቅናና ሽልማቶችን ያገኙ ሲሆን ለአብነትም የዩኒቨርሲቲዎች የምርጥ አስተማሪነትና ተመራማሪነት ሽልማት፣ የእንስሳት ህክምና ዘርፍ ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ ሽልማት፣ የልዩ አገልግሎት ሽልማቶች ተበርክተውላቸዋል። እርሳቸው ባቋቋሙትና በዳይሬክተርነት በሚመሩት የዓለም አቀፉ የሃሩራማ አካባቢ በሽታዎች የምርምር ማዕከል ከተለያዩ ታዳጊ አገራት በርካታ ሳይንቲስቶችንም አፍርተዋል። በትምህርትና ምርምር ዘመናቸው የነጮችን የዘረኝነት ጫና በመቋቋም ከስኬት ማማ ላይ የደረሱት ፕሮፌሰር ጥላሁን፤ አሁን ላይ በማደግ ላይ በሚገኙ አገራት ወጣት ሳይንቲስቶችን በማስተማርና በማበረታት ላይ ትኩረት አድርገው በመስራት ላይ ይገኛሉ። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ ሌላ ለምን በሽታ ክትባት ለማግኘት ጥረዋል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ለኤች አይ ቪ/ኤዲስ ቫይረስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nደቡብ አፍሪካ በደቡብ አፍሪቃ ሕገ መንግሥት መሠረት 11 ልሳናት በእኩልነት ይፋዊ ኹኔታ አላቸው። ከነዚህ መካከል ኳዙሉ ከሁሉ ብዙዎች ተናጋሪዎቹ በአገሩ ውስጥ አሉት፤ ቆሣ በቁጥር ብዛት 2ኛው ነው። ከነዚያ በኋላ በተናጋሪዎች ብዛት አፍሪካንስ 3ኛው፣ ስሜን ሶጦ 4ኛው፣ እንግሊዝኛም 5ኛው፣ ጿና 6ኛው፣ ደቡብ ሶጦ 7ኛው፣ ጾንጋ 8ኛው፣ ሷቲ 9ኛው፣ ቬንዳ 10ኛው፣ ንዴቤሌም 11ኛው ነው። ብዙ ሰዎች እስከ 6 ቋንቋዎች ድረስ የመናገር ዕውቀት አላቸው፤ ከነጭም ዜጋዎች አብዛኛው አፍሪካንስና እንግሊዝኛ ሁለቱን ይችላሉ። ትልቁ ከተማ ጆሃንስበርግ ሲሆን ዋና ከተሞቹ ሦስት ናቸው፤ እነርሱም ኬፕ ታውን፣ ብሉምፎንቴንና ፕሪቶሪያ ናቸው። ይህ ፓርላሜንቱ በኬፕ ታውን፣ ላዕላይ ችሎቱ በብሉምፎንቴን፣ ቤተ መንግሥቱ በፕሪቶሪያ ስለ ሆነ ነው። ስመ ጥሩ የሆኑት የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች ሂው ማሴኬላ እና ሌዲስሚስ ብላክ ማምባዞ ናቸው። የደቡብ አፍሪካ ሙዚቀኞች አሁን የራሳቸውን ዘመናዊ ሙዚቃ ዓይነት «ኳይቶ» አላቸው። የአገሩ አበሳሰል የተለያየ ነው። ብዙ ኗሪዎች የተቀመመ በሬ ቋሊማ ጥብስ (ቡረቮርስ)፣ የበቆሎ አጥሚት (ኡምጝቁሾ)፣ የተቀመመ ዶሮ፣ እና የተቀመመ ወጥ (ካሪ) ይወድዳሉ። የተወደዱ እስፖርቶች እግር ኳስ፣ ክሪኬት እና ራግቢ ናቸው። \n \nጥያቄ: በደቡብ አፍሪካ ስንት ቋንቋዎች በሕገ መንግሥቱ እኩል ተቀባይነት እንዳላቸው ተደንግጓል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 11 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nመንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር መንግሥትና የሕዝብ አስተዳደር በቢትወደድ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ ተጽፎ በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. የታተመ መጽሐፍ ነው። ይህ መጽሐፍ ከመስራት የተነሳ የሰው ልጅ እንዴት ከተፈጥሮ ጥገኝነት ተላቅቆ ከኋላ ቀር አኗኗር ወደ ተሻለ ሕይወት እንደሚለወጥ የሚያስረዳ ሲሆን የዓለም ሕዝቦች የዕውቀታቸውና የሀብታቸው ደረጃ ከፍና ዝቅ ያለ መሆኑ ምክንያቱ ከጦርነት የተነሳ ነው ይላል። ጦርነቱንም የሚነሱ ነገሥታትና አለቆቹ ሁሉ ልባቸው ሀብት እንደፈለጉ አይገልፅም። ነገር ግን ስም ለመፈለግና ለማግኘት ወይም ሀይማኖቱን ለማስፋፋት ወይም የተጠቃውን ለመርዳት አስመስለው ይነሳሉ። የጦርነት ሁሉ ፍፃሜ ምኞት ግን መዝረፍና ማስገበር ነው። ይህንንም ሲሉ ዕውቀታቸው የሰፋ ነገሥታትም ቢሆኑ መዝረፍን አይተዉም። አዘራረፋቸው ግን የዕውቀት አዘራረፍ ነው እያለ በሰፊው ያወሳል። በአክሱም ዘመነ መንግሥት የእስራኤልና የአህዛብ ወገን ተብሎ የሁለት ዓመት ጦርነት በመፍጀቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፍ ወዳለው ደረጃ እንዳይደርስ ዋና መሰናክል ሆኗል። ዋጋ ማለት የስራ መለኪያ ነው። ዕውቀት ከጉልበት ይከበራል። ዕውቀት የሌለው ሕዝብ ሁሉ ለብቻው መንግሥት ቢኖረውም ባይኖረውም ዕውቀት ያላቸው ሕዝቦች ይገዙታል። ሰው ሲፈጠር ጌታና ድሀ ሆኖ አልተፈጠረም። ድህነትና ጌትነት የተለየው በሰው ዕውቀት ነው። የሀብት መለኪያ ሥራ ነው። ስለዚህ ሀብት ማለት የተከማቸ ሥራ ማለት ነው። \n \nጥያቄ: መንግስት እና የህዝብ አስተዳደር የተሰኘው መጽሐፍ መቼ ተጻፈ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ዚምባቡዌ የትኛው አህጉር ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አፍሪካ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት እምባቦ በተባለው ቦታ ላይ ውጊያ ገጠሙት በስንት ዓመተ ምህረት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን እ.ኤ.ኣ. በ1978 የያዙት ኃላፊነት ምን ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የአርካንሳው አስተዳዳሪ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቲቪ በ1950ዎቹ እንደ ብርቅ በሚታይበት ዘመን በ1957 አ.ም ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተከፈተ፡፡ ታዲያ የመጀመሪያዋ የቲቪ ሴት አንባቢ የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ነበሩ፡፡ ይህ ለወይዘሮ እሌኒ ትልቅ የታሪክ አጋጣሚ ነበር፡፡ በወቅቱ ሳሙኤል ፈረንጅ አንዱ ወንድ ተናጋሪ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ሬድዮ በጋዜጠኝነቱና በህዝብ ግንኙነት ሙያ ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ ከሰው ጋር በቀላሉ የሚግባቡ ተወዳጅ ደግ እናት ነበሩ፡፡ በበጎ አድራጎት ምግባራቸው በስፋት የሚታወቁት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ የወጣት ሴቶች ክርስቲያናዊ ማህበር ውስጥ በንቃት በመሳተፍ ማህበሩን ረድተዋል፡፡ በተጨማሪም በአንሚ ሬድዮ ከ20 አመት በፊት ያገለገሉት ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ወልደስላሴ ከአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ነበራቸው፡፡ ከዚህም ባሻገር አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ወደ ሀገራችን በሚመጡበት ጊዜ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ስራ ላይ ትልቅ ሚና አበርክተዋል፡፡ ቤታቸው ሲኬድ ሁልጊዜም ከአረንጓዴ ተክል ጋር የማይታጡት ወይዘሮ እሌኒ ነፋሻማ ቦታ ልዩ ትርጉም ይሰጣቸዋል፡፡ አንድ ከዛፍ ጋር በተያያዘ በፎቶግራፍ የታገዘ መጽሀፍም ለህትመት አብቅተዋል፡፡ በዚህም መጽሀፍ አማካይነት ስለ ሀገራችን ዛፎች በቂ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ቴምብሮችን ያሰባስባሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ለታሪክ ልዩ ፍቅር ያላቸው ወይዘሮ እሌኒ የጡረታ ጊዜያቸውን በማንበብ እና በምርምር ያሳልፉ ነበር፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በ1959 አመተ ምህረት ከኢንጂነር ሰይፉ ለማ ጋር ጋብቻን መስርተው 3 ሴት ልጆችን ወልደው አንድ ልጅ ደግሞ አሳድገዋል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ በተወለዱ በ79 አመታቸው ሮብ ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነስርአታቸውም ሀሙስ ሀምሌ 15 2013 ከቀኑ በ6 ሰአት በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡ \n \nጥያቄ: የወ/ሮ እሌኒ ስርአተ ቀብርራቸው በየት ተፈፀመ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንጉሠ ነገሥት አጼ ኃይለሥላሴ ወደዚህ ዓለም የመጡበት ዕለት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአቡነ ጴጥሮስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራነት የሰጠቻቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ በትምህርታቸው እያበረቱ በማስተዳደር ላይ እንዳሉ በ፲፱፳፰ ዓ.ም. አረመኔው የኢጣልያ ፋሺስት በግፍ ሀገራችንን ለመውረር ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት በማለት ባሕርን አቋርጦ መጣ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀገር በመጣ ወራሪ ቀጥተኛ ተጠቂናትና ሊቃውንቷ፣ ገዳማትና አድባራቷ እንዲሁም ንዋያተ ቅድሳቷ በወራሪው የኢጣልያ ኃይል ይጨፈጨፉና ይቃጠሉ ገቡ ፡፡ ይህ ግፍ በዕውቀት ኮትኩታ ባሳደገቻቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ሲፈጸም ያዩት ብፁዕነታቸው ወራሪውን ኃይል ከኢትዮጵያውያኑ አርበኞች ጋር በመሆን በጸሎት ሊዋጉት ወሰኑ፡፡ ይሁን እንጂ ጠላት በመላ ከተማዋ ባሰማራቸው በርካታ ባንዳዎች መካከል ብፁዕነታቸው እንዳሰቡት ሊንቀሳቀሱ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ እዚሁ ከተማ ተሰውሬ መኖር አልፈልግም፤ ወደ ገጠር ፊቴን አልመልስም በማለት ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በወቅቱ የኢጣሊያ እንደራሴ ለነበሩት ራስ ኃይሉ እጃቸውን ሰጡ፡፡ እራስ ኃይሉም ወዲያውኑ ለግራዚያኒ አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ ተይዘው ወደ ግራዚያኒ ቀረቡ ፡፡ ጠላት ድል ተደርጎ ሀገራችን ነፃነቷን ከተቀዳጀት በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲያዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ከድል በኋላ የብፁዕነታቸ ሐውልት ተመርቆ የቤተ መንግሥቱም ሆኑ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት አበባ ጉንጉን ከሐውልቱ ሥር ሲያስቀምጡ ከቤተ ክህነት ካስቀመጡት አባቶች አንዱ በ1921 ዓ.ም አብረዋቸው የተሾሙት ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ነበሩ፡፡ ትውልድ ሁሉ ለሀገር ክብርና ለነጻነት በተከፈለው፡፡ የብዕፁነታቸው ሕይወት እንዲማርበትና ሕያው ምስክር ሆኖ እንዲኖር የቆመላቸውን ሐውልት ኢትዮጵያዊያን ሁሉ በክብር ይጠብቁታል ፡፡ የእኝህን ታላቅና ቅዱስ ሰማዕት አባት ክብርና ተጋድሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከአምስት ዓመት በፊት ቅዱስ /ሰማዕት/ ብሎ በማጽደቅ በስማቸው በቅድስና ማዕረግን ሰጥቶ በስማቸው ታቦት ተቀርጾ ቤተክርስቲያን እንዲሰራላቸው ወስኗል ፡፡ ይህም በተወለዱበት በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሃገረሰብከት በፍቼ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ አርበኛ፣ ጀግና፣ ጳጳስ፣ ሰማዕት ቅዱስም የሆኑ አባት ናቸው ፡፡ \n \nጥያቄ: የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት በማን አሳሳቢነት ተሰራ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቶክ ፒሲን ቶክ ፒሲን (Tok Pisin) በስሜን ፓፑዋ ኒው ግኒ የሚናገር የእንግሊዝኛ ቋንቋ ዲቃላ ነው። ከእንግሊዝኛ ስዋሰው በጣም ተለውጧልና ዛሬ እንደ ራሱ ቋንቋ ይቆጠራል። የፓፑዋ ኒው ግኒ መደበኛ ቋንቋ ሆኖ በ120,000 ያሕል ተናጋሪዎችና በ4 ሚሊዮን እንደ 2ኛ ቋንቋ ይነገራል። የቶክ ፒሲን አጀማመር በፓሲፊክ ውቅያኖስ ደሴቶች ላይ የሚኖሩ የተላያዩም ልሣናት የሚችሉ ሰራተኞች አንድላይ ለአትክልት ስፍራዎች ሲሰሩ ነበር። ብዙ ጊዜ የእነዚህ ሰራተኞች የጋራ ቋንቋ ጥቂት ቀላል እንግሊዝኛ ቃሎች ብቻ ነበር። ስለዚህ አዲስ \"የቋንቋ ዲቃላ\" ተወለደ። ከእንግሊዝኛ ብቻ ሳይሆን ብዙ ቃላት የተወሰዱ ከደሴተኞቹ ቋንቋዎች፣ ከጀርመንኛ፣ ወይም ከፖርቱጊዝ ነበር። ይህ ቋንቋ \"ፕጅን\" ተብሎ አሁን ሶስት ተወላጆች አሉት፣ እነሱም ቢስላማ (በቫኑዋቱ) ፒጂን (በሰሎሞን ደሴቶች) እና ቶክ ፒሲን ይባላሉ። ቶክ ፒሲን በአንዳንድ ትምህርት ቤት የትምህርት ቋንቋ ነው። \n \nጥያቄ: ቶክ ፒሲን በሁለተኛ ቋንቋነት በምን ያህል ሰዎች ይነገራል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ4 ሚሊዮን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ተወዳጅ የሆነው የሙዚቃ ስልት ምን ይባለል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ምባላክስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: የአጼ ዘርአ ያዕቆብ አባትና እናት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ስብሐት (ስብሐት ለአብ) ገብረ እግዚአብሔር (ሚያዝያ 27 [1928]ዓ.ም. - ሰኞ፣ ቀን ትግራይ ጠቅላይ ግዛት፣ አድዋ አውራጃ፣ እርባ ገረድ በተባለች መንደር ከአባቱ ከቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከወይዘሮ መአዛ ወልደ መድኅን ተወለደ። ትምህርቱን በስዊድን ሚሲዮን፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተከታትሎ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀብሏል። በአስፋ ወሰን ትምህርት ቤት በእንግሊዝኛ መምህርነት ለ2 ዓመት አገልግሏል። በመቀጠልም ከየተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፤ ሳየንስ እና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) ባገኘው የትምህርት እድል አማካይነት ወደ ፈረንሳይ (ኤክስ አን ፕሮቫንስ) በመሄድ ከ1962-1964 ቆይቷል። የሄደበትን ትምህርት አጠናቆ ምስክር ወረቀት ባይቀበልም ቆይታው ከአውሮፓ ባህል እና ስነ-ጽሁፍ እንዲተዋወቅ በጣም እንደረዳው ይናገራል። ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመውን የልብ-ወለድ ድርስቱን «ሌቱም አይነጋልኝ»ን ብዙውን ለመጻፍ የበቃው እዚያው በፈረንሳይ እንደሆነም ይናገራል። ይኸው ድርሰቱም ወደ ፈረንሳይኛ ቋንቋ የተተረጎመ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ልብ-ወለድ ነው። ስብሐት ወደ አዲስ አበባ ከተመለሰ በኋላ በመነን መጽሄት የዝግጅት ክፍል ውስጥ ሰርቷል። በ1966 ዓ.ም. ወታደራዊው ደርግ ስልጣን ከያዘ በኋላ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ሲቋቋም በአርታኢነት ተቀጥሮ ሰርቷል። በመንግሥት ትእዛዝም ከሌሎች ሰዎች ጋር በመሆን የካርል ማርክስ ሥራ የሆነውን ካፒታልን ከእንግሊዝኛ ወደ አማርኛ በመመለስ ሥራ ላይ ተሳትፏል። ብዙዎቹ የስብሐት ሥራዎች በተጻፉበት ጊዜ ለመታተም ባይታደሉም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን የህትመትን ብርሃን ለማየት በቅተዋል። ጽሁፎቹ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይታተሙ ለመቆየታቸው ዋነኛው ምክንያቱ ስብሐት በመጽሐፉ የሚጠቀማቸው ቃላት ብዙዎቹ በኢትዮጵያ ባህል ያደገ አንባቢን አይን የሚያስፈጥጡ፣ ጆሮ የሚያስይዙ በመሆናቸው ነው። በገበያ ላይ በቅርብ የወጡት ድርሰቶቹ ከመጀመሪያ ቅጂያቸው ብዙ ለውጥ እና የአርትኦት ሥራ የተደረገባቸው እንደሆኑ ይነገራል። ስለዚሁ ጉዳይ ለአዲስ ላይቭ በሰጠው ቃለመጠይቅ ላይ ሲናገር «በጨለማ ያልተደረገውን ነገር አንድም የጻፍኩት የለም... ያለውን እንዳለ ነው የምጽፈው» ብሏል። ይህንኑም ከኤሚል ዞላ የአጻጻፍ ዘይቤ የወሰደው እንደሆነ ይናገራል። ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ደራሲ፣ አርታኢ፣ ጋዜጠኛ ብቻ አይደለም - የልብ-ወለድ ድርሰት ገጸባህርይም ነው። ደራሲው የተሰኘው የበአሉ ግርማ ልብ-ወለድ በስብሐት ህይወት ላይ ተመስርቶ የተጻፈ ነው። ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር የ2 ወንዶች እና የ3 ሴቶች አባት ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ ነው። \n \nጥያቄ: ስብሐት ገብረ እግዚአብሔር ወደ ፈረንሳይኛ «Les Nuits d'Addis-Abeba» ተብሎ በፍራንሲስ ፋልሴቶ የተተረጎመው የልብ-ወለድ ድርስቱ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሌቱም አይነጋልኝ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢትዮ ሬይን ሜከርስ ኢትዮ ሬይን ሜከርስ (Ethio Rain Maker) በኢትዮጵያ ውስጥ ዛፎች በመትከል ረሃብን ለመከልከል የተቋቋመ ቡድን ነው። አሁን ወደ ምድረ በዳ መጥተው በወንድማማችነት ገነት ይሠራሉ። በድርቅ አፈር ውስጥ የሚተክሉት ዘር ታላቅ ደን ይሆናል፤ ምድሪቱ እንደገና በሙሉ እስክትሸፈን ድረስ ረጀም ዛፎች በዝተው አረንጓዴ ክንፎቻቸውን ይዘረጋሉ። ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም መገናኛ ብዙሃን በረሃብ ስትጠራ፣ ህዝቦችዋ በጠኔ ሲሰቃዩ ዘመናት ተቆጥረዋል። የወገኖቻችን ስቃይ፣ የሀገራችን ኋላ ቀርነት በኢትዮጲያዊነታችን እያንዳንዳችንን ይመለከተናል። ላለፉት ሰላሳ አመታት በጎ አድራጊ ድርጅቶች በአይነትም ሆነ በጥሬ ገንዘብ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንደረዱን መረጃ አውጥተዋል። የኛ ስቃይ ግን አላበቃም። መከር ሲመጣ ሰብል ከማጨድና ምርት ከመሰብሰብ ይልቅ ለልመና እጁን የሚዘረጋ ኢትዮጲያዊ ቁጥር በሶስት እጥፍ ጨመረ። ይህ ሂደት መቆም አለበት። እንዴት? አበው “ነገርን ከስሩ …” እንደሚሉት የሁሉም ችግር መፍትሔው ያለው ከመነሻው ላይ ነው። የኛ ረሐብ መንስዔው ምንድነው? በአጭሩ ለመግለጽ ያህል ለረሐባችን መንስዔ የዝናብ አለመኖር (ድርቅ) መሆኑን ከረሐባችን ታሪክም ሆነ ጥናቱን ካካሄዱት ምሁራን መረዳት ይቻላል። ዛሬም ቢሆን ገበሬው ዝናብ በማጣቱ ሰብሉ መበላሸቱን ከአንደበቱ እየሰማን ነው። ጦርነትን ለማቆም የጦርነት መነሻ ሃሳቦችን ማስወገድ እንጂ ጦርነትን ከጦር ሜዳ ማስቆም እንደማይቻል ሁሉ የሃገራችንንም ረሃብ ከመንስዔው እንንቀለው። ኢትዮ ሬይን ሜከርስ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ደን ማደነን (አፎረስቴሽን) ችግራችንን ከመቅረፊያ መንገዶች አንዱ እንደሆነ በማመን የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ችግኞችን መትከል ጀምሯል። በ1995 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለ አደራ ጋር በመተባበር በእንጦጦ የተፈጥሮ መናፈሻ አስር ሺህ ችግኞችን ተክሎ ሰባ ሁለት ከመቶው (7167) ፀድቋል። በ1996 ክረምት ደግሞ ሀምሳ ሺህ ችግኞችን ለመትከል አቅዶ ሀያ ከመቶው ተጠናቋል። በአሰላ፣ በመቀሌና በባህር ዳር አንድ ሺህ ዛፎችን የሚይዙ የተፈጥሮ መናፈሻዎችንን በመስራት ላይ ነን። በ1997 ለሀገራችን የሺህ አመት ስጦታ እንስጥ በሚል መነሻ ሀሳብ እያንዳንዱ ኢትዮጲያዊ አንድ ዛፍ ተክሎ የሚንከባከብበትን እቅድ አውጥተናል። ከነዚህም አንዱ አንድ ዛፍ ለአንድ ተማሪ ነው። የሃገራችን የዘመናት ችግር በአንድ አመትና በጥቂት ሰዎች ጥረት አይፈታም። ለዚህ አላማ መሳካት የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥረትና እገዛ ያስፈልጋልና ሃገራችንን ከረሐብ ለመታደግ አብረን ዛፍ እንትከል። እንንከባከብም። \n \nጥያቄ: ኢትዮ ሬይን ሜከርስ እንጦጦ አካባቢ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለደራ ጋር አንድ ላይ በመሆን ምን ያህል ችግኝ ተከሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ አስር ሺህ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበኢትዮጵያ የሚገኙ በርካታ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች መንግሥት ተገቢውን ክትትል እያደረገ ባለመሆኑና ኩባንያዎች በክህሎት የበቁ ኢትዮጵያዊያን በሥልጠና ዕገዛ ባለማድረጋቸው ምክንያት፣ አብዛኛዎቹ በሲሚንቶ ፋብሪካዎች ተቀጥረው የሚሠሩት ሠራተኞች የውጭ ዜጎች መሆናቸው ተገለጸ፡፡ በኢትዮጵያ ምርት በማምረትና በግንባታ ላይ የሚገኙትን ጨምሮ 17 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 12ቱ በተለያየ የማምረት መጠን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይሁን እንጂ በበርካታ ፋብሪካዎች በተለይም ግዙፍ በሚባሉት ዳንጎት፣ ሙገርና ደርባ ኩባንያዎች ውስጥ የውጭ ዜጎች የማኔጅመንቱንና ቴክኒካል ሥራውን በበላይነት እንደሚይዙ የኬሚካልና ኮንስትራክሽን ግብዓቶች ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ስምረት ግርማ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም በሥራ ላይ በሚገኙት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የውጭ ዜጎች እንዳሉ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሯ፣ ኢትዮጵያውያን እየሠሩባቸው ያሉ ዘርፎችም ቢሆን በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ላይ የሚገኙ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡ \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ በሚገኙ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ኢትዮጵያውያን ሠራተኞች በብዛት የሚሳተፉት በምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በዝቅተኛ ዕርከንና በጉልበት ሥራ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nፍቅር እስከ መቃብር ፍቅር እስከ መቃብር በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. በደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የቀረበ ልብ ወለድ ሲሆን ሰብለ ወንጌል እና በዛብህ የሚባሉ የሁለት ገፀ ባህሪያትን ፍቅር ይተርካል። ይህ ድርሰት ከሌሎች ልብወለድ ሥራዎች ለየት የሚያደርገው ደራሲው ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ በፊደል አጠቃቀም ላይ ለውጥ አድርገው በማቅረባቸው ነው። ይኸውም ለምሳሌ ያህል ሦስት «ሀ»ዎች፣ ሁለት «ሰ»ዎች፣ ሁለት «ኣ»ዎች የመሳሰሉትን እንደ አንድ ወይም የመጀመሪያውን ብቻ በመያዝ ነው። በተጨማሪም ጠብቀው በሚነገሩ ቃላት ላይ ከላይ አንድ ነጥብ በማስቀመጥ ይታወቃሉ።ሀዲስ ኣለማየሁ በኢትዮጵያ ስነ-ፅሑፍ የራሳቸው ትልቅ አሻራ አኑረው ያለፉ አንጋፋ ደራሲ ናቸው። የታሪኩ ማጠቃለያ በዛብህ‌ ‌ጎጃም‌ ‌ማንኩሳ‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከእናቱ‌ ‌ከውድነሽ‌ ‌በጣሙና‌ ‌ከአባቱን‌ ‌ከቦጋለ‌ ‌መብራት‌ ‌ይወለዳል።‌ ‌በሽታ‌ ‌ይበዛበትና‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይባላል።‌ ‌እናቱ‌ ‌ከበሽታው‌ ‌እንዲድን‌ ‌ስእለት‌ ‌ይሳላሉ።‌ ‌ዕድል‌ ‌ሆኖ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይተርፋል፤‌ ‌አድጎ‌ ‌ጎበዝ‌ ‌ልጅ‌ ‌ይሆናል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌በሽታ፣‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ዕውቀትና‌ ‌ፍቅር‌ ‌(የሰው‌ ‌መውደድ)‌ ‌ይበዛበታል።‌ ‌በወጣትነቱ‌ ‌ይቀድስና‌ ‌ለቤተሰቡ‌ ‌ገንዘብ‌ ‌ማምጣት‌ ‌ይጀምራል።‌ ‌ቀድሞ‌ ‌የስእለት‌ ‌ልጅ‌ ‌መባልን‌ ‌አይጠላም‌ ‌ነበር።‌ ‌ሲያድግ‌ ‌ግን‌ ‌ትርጉሙን‌ ‌በመረዳቱ‌ ‌ነጻነቱን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌ዲማን‌ ‌ጥሎ‌ ‌ወደደብረ‌ ‌ወርቅ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌እዚያም‌ ‌ከእመት‌ ‌ጠጂቱ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይጠጋል።‌ ‌ትንሽ‌ ‌ዜማና‌ ‌ቅኔም‌ ‌ይማራል።‌ ‌ደብተራ‌ ‌በየነ‌ ‌መጥቶ‌ ‌የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ‌ሲያረዳው‌ ‌ወደዲማ‌ ‌ይወርዳል።‌ ‌በተክለ‌ ‌አልፍአው‌ ‌በዓል‌ ‌በመልካም‌ ‌ድምጹ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻንና‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትን‌ ‌ያወድሳል።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻም‌ ‌የሰብለ‌ ‌መምህር‌ ‌አድርገው‌ ‌ይቀጥሩታል።‌ ‌ሰብለና‌ ‌በዛብህ‌ ‌የሕይወት‌ ‌ገጠመኞቻቸው‌ ‌በመጠኑ‌ ‌ስለሚመሳሰል‌ ‌ይግባባሉ።‌ ‌በመሃል‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌አሰጋኸኝ‌ ‌ሰብለን‌ ‌በፈት‌ ‌ወግ‌ ‌አገባለሁ‌ ‌በማለቱ‌ ‌በርሱና‌ ‌በፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌መካከል‌ ‌ጥል‌ ‌ተፈጠረ፤‌ ‌ሆኖም‌ ‌በሃይማኖት‌ ‌ጣልቃገብነት‌ ‌ሳይዋጉ‌ ‌ቀሩ።‌ ‌ከዚያም‌ ‌ደግሞ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከባላገሮች‌ ‌ጋራ‌ ‌በግብር‌ ‌ጉዳይ‌ ‌ተጣሉ።‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ተማርከው‌ ‌ሳለ‌ ‌የበዛብህንና‌ ‌የሰብለወንጌልን‌ ‌የፍቅር‌ ‌ዜና‌ ‌ይሰማሉ።‌ ‌ወዲያውም‌ ‌መጥተው‌ ‌ሰብለን‌ ‌በሌሊት‌ ‌ያስሯታል።‌ ‌የሰብለ‌‌አጎት‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ሁለቱን‌ ‌ለማስመለጥ‌ ‌ወጣ፣‌ ‌ወረደ።‌ ‌የዕጣ‌ ‌ነገር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ግን‌ ‌ሳይሳካ‌ ‌ቀረ።‌ ‌በዛብህ‌ ‌ግን‌ ‌በግራጌታ‌ ‌ቀለመወርቅና‌ ‌በጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጥረት‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ይሄዳል።‌ ‌በራጉኤል‌ ‌ቤተክርስቲያንም‌ ‌የቅኔ‌ ‌መምህር‌ ‌ሆኖ‌ ‌ይቀጠራል።‌ ‌ባደረጉላቸው‌ ‌ውለታ‌ ‌ምክንያት‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌መሸሻ‌ ‌ሰብለን‌ ‌ለፊታውራሪ‌ ‌ታፈሰ‌ ‌ሊድሯት‌ ‌ይሞክራሉ።‌ ‌የሰብለን‌ ‌አቋም‌ ‌አውቀው‌ ‌አባ‌ ‌ተክለሃይማኖት‌ ‌በተባሉ‌ ‌መነኩሴ‌ ‌ያስጠብቋቷል።‌ ‌መነኩሴው‌ ‌ግን‌ ‌ሰክረው‌ ‌ሰብለ‌ ‌ታመልጣለች።‌ ‌ፍለጋ‌ ‌ሲሄዱ‌ ‌ፊታውራሪ‌ ‌ከፈረስ‌ ‌ላይ‌ ‌ተወርውረው፣‌ ‌ተንኮታክተው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ወይዘሮ‌ ‌ጥሩአይነትም‌ ‌ቤተክርስቲያን‌ ‌ውስጥ‌ ‌ከደረጃ‌ ‌ላይ‌ ‌ተንሸራትተው‌ ‌ወድቀው‌ ‌ይሞታሉ።‌ ‌ሰብለ‌ ‌ደግሞ‌ ‌በዛብህን‌ ‌ለማግኘት‌ ‌መነኩሴ‌ ‌መስላ‌ ‌ወደአዲስ‌ ‌አበባ‌ ‌ትሄዳለች።‌ ‌ደርሳም‌ ‌በዛብህ‌ ‌አለመኖሩን‌ ‌ትሰማና‌ ‌ጎሃጽዮን‌ ‌ትወርዳለች።‌ ‌በዚያም‌ ‌በዛብህ‌ ‌ተደብድቦ፣‌ ‌ነፍስ‌ ‌ውጪ‌ ነፍስ‌ ‌ግቢ‌ ‌አይነት‌ ‌ሁኔታ‌ ‌ላይ‌ ‌ሳለ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌እንደምንም‌ ‌ብለው‌ ‌ሥጋ‌ ‌ወደሙን‌ ‌ይቀበላሉ።‌ ‌ጥቂት‌ ‌ቆይቶ‌ ‌በዛብህ‌ ‌ይሞታል።‌ ‌ሰብለም‌ ‌መንኩሳ፣‌ ‌የበዛብህን‌ ‌አስከሬን‌ ‌ባጠገቧ‌ ‌አድርጋ‌ ‌ስትኖር‌ ‌ከጉዱ‌ ‌ካሳ‌ ‌ጋራ‌ ‌ይገናኛሉ።‌ ‌ጉዱ‌ ‌የተሰኘው‌ ‌ካሳ‌ ‌ዳምጤም‌ ‌እርሷ‌ ‌ዘንድ‌ ‌ይቀመጣል።‌ ‌አስራ‌ ‌አምስት‌ ‌ቀናት‌ ‌አንድ‌ ‌ላይ‌ ‌ይኖሩና‌ ‌ሰብለ‌ ‌የልብ‌ ‌በሽታዋ‌ ‌ተነሥቶባት‌ ‌ትሞታለች፣‌ ‌ጉዱ‌ ‌ካሳም‌ ‌ከበዛብህ‌ ‌አጠገብ‌ ‌ያስተኛታል።‌ ‌በሦስተኛው‌ ‌አመት‌ ‌ጉዱም‌ ‌አረፍተ‌ ‌ዘመን‌ ‌ይገታዋል።‌ \n \nጥያቄ: በዛብህ ለምን ወደ ዲማ ተመለሰ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የወላጆቹን‌ ‌ሞት‌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: በቱርክምኒስታን ምን ያህል የቱርክመንኛ ቋንቋ ተናጋሪ አለ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 3,430,000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጓሳ ጓሳ ወይም በደኔ ወይም ጀሞ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ዛፍ ነው። እስከ 10 ሜትር ድረስ የሚቆም ቀጭን ዛፍ ነው። ለቅርንጫፎቹ ረጅም፣ ቀጥ ያሉ ዐረንጓዴ እሾሆች በጥምዝምዝ አሉባቸው። ከእሾሆቹ መሠረት ጨለማ-አረንጓዴ ውሁድ ቅጠሎች ይበቅላሉ፣ ውሁዱም ቅጠል ከ፪ ቅጠሊቶች እየሆነ በቅርጽም ሆነ በስፋት ሊለያዩ ይችላሉ። ሽንሽን ግንዱ ግራጫማ-ቡኒ ሻካራ ልጥ አለው፤ ይህም በረገፈበት ቦታ ቢጫ-አረንጓዴ እራፊ ይኖረዋል። ህብረ አበባው የጥቂት አበቦች ዘለላ ሲሆን አበቦቹም ወይም ዘንግ-አልባ ወይም በአጭር አገዳ ላይ የሚቀመጡ ናቸው። የአበባው እንቡጥ ሞላላ እና በጉርምስና ሥሥ ጽጉር ያለበት ነው። አበቦቹ አረንጓዴ-ቢጫ ቀለም፣ ፍናፍንታም ጾታ፣ አምስት ቅጠል በክቦሽ ምጥጥን ያላቸው ናቸው፤ የአበባ ቅጠሎች 8-14 ሚሊሜትር ባጋማሽ ናቸው። የኅብራበባ ስሪት ግራጫማ ቀለም፣ ለሥላሣ ጽጉር ያለው፣ ከ10 ሚሊሜትር ያልረዘመ ነው። ሞልሟላ ፍሬው በተለምዶ ከ4 ሴንቲ ሜትር ያልረዘመ ነው፣ ያልበሰለ ሲሆን አረንጓዴ ነው፣ ሲበሰልም ቡናማ ይሆናል፣ ከሽካሽ ቆዳው ዝልግልግ ቡናማ ልጥልጥ አለበት፣ ይህም ጽኑ ፍሬ ድንጋይ አለበት። \n \nጥያቄ: የአበባ ቅጠሎች ርዝመት ምን ያህል ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 8-14 ሚሊሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዐምደ ጽዮን ቀዳማዊ አጼ ዐምደ ጽዮን (የዙፋን ስም ገብረ መስቀል) ከ1314 እስከ 1344 ዓ.ም. የነገሡ ሲሆን በጥንቱ ዘመን ከተነሱ ነገሥታት ውስጥ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ሰፋ ያለ አሻራ ትተው ካለፉት (ለምሳሌ፦ ዘርአ ያዕቆብ) ጎን ወይም በላይ ስማቸው ይጠቀሳል። አጼ ዐምደ ጽዮን የአጼ ይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅና የአጼ ወድም አራድ ልጅ እንደሆኑ ይታመናል፡፡ ይኩኖ አምላክ አዲሱን የሰሎሞን ስርወ መንግስት ቢመሰርቱም፣ በልጅ ልጆቻቸው የነበረው ፉክክርና አዲስ ከሚስፋፋው የእስልምና ሃይማኖት የሚሰነዘረው ጥቃት ስርዓቱን ስጋት ላይ የጣለ ነበር። አጼ አምደ ጽዮን ይህን ፉክክር በማስቆምና በዘመናት በማይደበዝዘው ጀግንነታቸው የኢትዮጵያን ድንበር ከሞላ ጎደል አሁን በሚታወቀው መልኩ በማስቀመጥ፣ የአዲሱን ስርወ መንግስት መሰረት በማጽናት እንዲሁም በማረጋጋት ዝናቸው በጥንቱ አለም ክአፍሪቃ ቀንድ እስከ አውሮጳ የተንሰራፋ ነበር። \n \nጥያቄ: የአጼ ዐምደ ጽዮን አያት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአጼ ወድም አራድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቴምፕላርስ ቴምፕላር ወይም በሙሉ ስማቸው የክርሰቶስ እና የሰለሞን መቅደስ ምስኪን ወታደሮች የሚባሉት በጣም ታላቅ እና ሃይለኛ ከነበሩት ክርስቲያናዊ ወታደራዊ ስርአቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው። ይህ ስርዓት በ1088 ዓ.ም. ከተካሄደው አንደኛው የመስቀል ጦርነት በኋላ ማለትም በ1110 ዓ.ም. አዲስ የተቋቋመውን የእየሩሳሌም መንግስት ከእስላሞች ለመከላከልና ወደ ከአውሮፓ ወደ እየሩሳሌም የሚጎርፉትን ተሳላሚዎች ደህንነት ለመጠበቅ የተመሰረተ ነው። ቴምፕላሮች የተዋቀሩት በገዳማዊ ስርዓት ሲሆን ይኸውም የሲሰተርሲያን ስርዓት መስራች የነበረው የክላርቮው በርናርድ በዘረጋላቸው ህግጋት መሰረት ነው። ቴምፕላሮች ከብዙ መሳፍንት ጋር ግንኙነት ስለነበራቸው እና ጳጳሱም እነሱ ከሚቆጣጠሩዓቸው ቦታዎች ሁሉ ግብርና አስራት እንዲሰበስቡ ስለፈቀደላቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝነኛና ሃይለኛ ለመሆን ችለዋል። ቴምፕላሮቹ አራት ዋና ክፍሎች የነበሩአቸው ሲሆን እነዚሁም ዋነኞቹ ወታደሮች ወይም ናይትስ የሚባሉት ሙሉ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ከዝቅተኛ የህብረተሰቡ ክፍል የተውጣጡት ወይም ሰርጀንትስ በመባል የሚታወቁት፤ መለስተኛ የፈረሰኛ ትጥቅ የታጠቁ ገበሬዎች ዋነኛው ስራቸው የስርዓቱን ንብረት ማስተዳደር የነበረ፤ እንዲሁም ካህናት ስራቸው የስርዓቱን መንፈሳዊ ህይወት መከታተል የነበረ ናቸው። \n \nጥያቄ: ቴምፕላርስ የተባለው ስርዓት መቼ ተመሰረተ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ1110 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየሠውነት ማጎልመሻ ትምህርተ ፕሮፌሽናል በ young men’s Cristian association tinning school በአሁኑ መጠሪያው spring filed college ውስጥ አሰልጣኝ የነበሩት ካናዳዊ ጀምስ ኒስዝ እኤአ ከዲሴምበር 1891 ቀደም ብሎ የጂም ትምህር ቤት ክፍልን በዝናባማ ወቅትም ለማስቀጠል ፈለጉ፡፡ ተማሪዎቹ ክረምቱንም በተሻሎ የሰውነት ጥንካሬ እንዲያሳፉ በሚል በርካታ ሀሳቦች አስበው በኋላም ከበርካታ ሀሳቦች ውስጥ የባስኬት ቦልን በመምረጥ 10 ጫማ ወይም 3 ሜትር ከፍታ ያለው የባስኬት ቦል መረብ መስቀያ አዘጋጁ፡፡ ለባስኬት ቦል መጫወቻ ተብሎ የተዘጋጀው የመጀመሪያ ኳስ ብራውን ወይም ቡናማ ቀለም ሲኖረው እኤአ በ1950ዎቹ መጨረሻ ላይ ግን ቶኒ ሂንክል የተባለ ሰው ለተጫዋቾቹ ግልፅ ሆና መታየት አለባት በሚል የኳሷ ቀለም ወደ ብርቱካናማ ቀለም እንዲቀየር አደረገ የተቀየረውም ቀለም እስካሁን እያገለገለ ይገኛል፡፡ በ1892 ከገና እረፍት መልስ ለመጀመሪያ ጊዜ የባስኬት ቦልን የተጫወተው ፍራንክ ማሀን ሲሆን በወቅቱ ስያሜውን ምን እንደሚሉት ኒስሚዝን ጠየቃቸው እሳቸውም ውድድሩን የማስጀመር ሀሳብ እንጂ ስለስያሜው አላሰብኩበትም ሲሉ መለሱለት፡፡ ፍራንክ ለምን ኒስሚዝ ኳስ አይሉትም ሲል ሀሳብ አቀረበ፡፡ ኒሚዝም ከሳቁ በኋላ እንዲህ አይነት ስያሜዎች ጨዋታውን ይገድሉታል ብለው መለሱለት፡፡ ፍራንክም መልሶ ለምን ባስኬት ቦል አንለውም አለ፡፡ ኒስሚዝም ባስኬት አለን ኳስም አለን ስለዚህ ባስኬት ቦል መባሉ ለኔ ተስማምቶኛል፤ ጥሩ ይመስለኛል ብለው አፀደቁለት፡፡ የመጀመሪያው የባስኬት ቦል ውድድርም ኒዮርክ ውስጥ በሚገኝ YMCA ጂምዚየም ውስጥ እኤአ በጃንዋሪ 1892 በ9 ተጫዋቾ ተጀመረ፡፡ በወቅቱ የእግር ኳስ 10 ተጫዋቾ በ1 ቡድን የሚጫወቱበት ወቅት ስለነበር ሀይለኛ የበረዶ ግግር የእግር ኳስ ጨዋታቸውን እንዳያከናውኑ ስላስቸገራቸው ወደቤት ውስጥ ገብተው 10ሩ ተጫዋቾ በሁለት በመከፈል 5 5 ሆነው መጫወት ባስኬት ቦልን ወይም የቅርጫት ኳስን ጀመሩ፡፡ በ1897 -1898 በአንድ ቡድን የተጫዋቾ ብዛት 5 ሆኖ ፀደቀ፡፡ እኤአ በ1980ዎቹ እና በ1990ዎ ውስጥ ፕሮፌሽናል ውድድሮችን በማካሄድ የስፖርቱን ተወዳጅነትና እውቅና ከፍ እንዲል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረጉ እና የምንግዜም ምርጥ የቅርጫት ኳስ ተጫዋቾች የሚባሉት 3 ተጫዋቾ ላሪ በርድ፤ ኢረን ማጂክ ጆንሰን እና ማይክል ጆርዳን ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ ፌብርዋሪ 17፣1963 በአሜሪካዋ የኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው ማይክል ጆርዳን በአለማቀፍ ደረጃ ብዙ ሽልማቶችን ተቀዳጅቷል፡፡ ብዙ ሰዎች ከምርጥ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ሳይሆን መቼም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ተጫዋች ነው በማለት ያሞግሱታል፡፡ ከሴቶች እውቅ የባስኬት ቦል ተጫዋቾች ውስጥ አንዷ የሆነችው የአሜሪካ ፕሮፌሽናል ባስኬት ቦል ተጫዋች ማያ አፕሪል ሞኖር በርካታ የብሄራዊ ቻምፒየን ሺፕን በማሸነፍ የጆን ዎደን አወርድ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ እኤአ በ1932 ስምንት ሀገራት የብሄራዊ ባስኬት ቦል አሶሼሽን FYBA አቋቋሙ፡፡ ስምንቱ መስራች ሀገራት አርጀንቲና ፤ Czechoslovakia ፤ ግሪክ ፤ ጣሊያን ፤ lasiva፤ ፓርቹጋል ሮማንያ እና ሲውዘርላንድ ናቸው፡፡ ሴቶች በባስኬት ቦል ውድድር ላይ መሳተፍ የጀመሩት በ1892 በስሚዝ ኮሌጅ ውስጥ ነበር፡፡ በወቅቱ ሰንዳ በርሶን የተባለች የሰውነት ማጎልመሻ መምህር የኒስሚዝን የባስኬት ቦል ህጎች ለሴቶች እንዲሆኑ አድርጋ አስካከለቻቸው፡፡ በአጭሩ በአዲሱ ስፖርት በመማረኳ ስለውድድሩ ከኒሰሚዝ ብዙ ለመማር ትፈልግ ነበር፡፡ በመጋቢት 21 1893 የመጀመሪያው የሴቶች ባስኬት ውድድርን አዘጋጀች፡፡ \n \nጥያቄ: የቅርጫት ኳስ ጨዋታ በአምስት ተጨዋቾች እንዲሆኑ መቼ ተወሰነ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1897 -1898 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: ውለታ ለማ (ዶ/ር) ያሸነፉበት በህክምናው ዘርፍ ያለውን የወረቀት ሥራ ዲጂታል ለማድረግ የሚያስችል የሥራ ፈጠራቸው ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nታንዛኒያዊው ደራሲ አብዱልራዛቅ ጉራህ የ2021 የኖቤል የሥነ ጽሑፍ አሸናፊ መሆናቸውን የስዊድን አካዴሚ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡ እ.ኤ.አ. በ1986 ዎሌ ሾይንካ በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑ ከ35 ዓመታት በኋላ አብዱልራዛቅ ጉራህ ሁለተኛው ጥቁር አፍሪካዊ ያሰኛቸውን ክብር ተቀዳጅተዋል፡፡ በመላው አፍሪካ ደረጃ ስድስተኛ ተሸላሚ ናቸው፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ አብዱልራዛቅ ለአሸናፊነታቸው ከስዊድኑ የኖቤል ሽልማት ድርጀት 10 ሚሊዮን ክራውን ወይም 1.14 ሚሊዮን ዶላር ያገኛሉ፡፡ የ73 ዓመቱ አዛውንት ጉራህ ጎልተው የሚታወቁትን ‹‹ፓራዳይዝ›› (Paradise) እና ‹‹ዲዘርሽን›› (Desertion) ጨምሮ የ10 ልብ ወለዶች ደራሲ ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: ደራሲ አብዱልራዛቅ የኖቤል የሥነ ጽሑፍ ተሸላሚ ከመሆናቸው ከ35 ዓመት በፊት ይህንን ሽልማት ያገኙት አፍሪካዊ ማን ነበሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዎሌ ሾይንካ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ በየት የመምህራን ማሰልጠኛ ተመረቁ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በሐረር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው። በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ። በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ዋና ዋና ተፋሰሶች እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንጉሥ ኃይለ ሥላሴ የንጉሠ ነገስትነት ማዕረግ ያገኙት መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nግሥላ ግሥላ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኝ አጥቢ አውሬ ነው። በእስያ የተገኘው ነብር የግስላ ቅርብ ዘመድ ሆኖ፣ በአነጋገር «ግስላ»ና «ነብር» የሚሉ ስሞች ሊለዋወጡ ይችላሉ። የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደት ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ሲደርስ በርዝመት ከ90 ሴ.ሜ እስከ 1,60 ሜ.ና በአፍሪካ የሚገኘው ዘር እስከ 1,90 ሜ ይደርሳል ። ከመሬት እስከ ሆዱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖረው ጭራው ደግሞ እስከ 100 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያሳያል ። ሴቲቱ ከወንዱ አነስ ትላለች ። በዱር ሲኖር እስከ 10 አመት እንደሚኖር ሲታወቅ በሰው ተይዘው ሲኖሩ እስከ 20 አመት እድሜ ያስመዘገቡ ግሥሎች አሉ። \n \nጥያቄ: ግስላ በዱር ሲኖር ለምን ያህል ጊዜ ይቆያሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ እስከ 10 አመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየናሳ ተመራማሪዎች ሱፐር ኧርዝ ሲሉ የሰየሟትን አዲስ ፕላኔት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡ በመጠኗ የመሬትን እጥፍ ታክላለች የተባለችው አዲሷ ፕላኔት ከከዋክብቷ አንፃር ለህይወት ተስማሚ በሆነ ርቀት ውስጥ እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡ ይህም በፕላኔቷ ላይ ህይወት ሊኖር ይችላል የሚል ተስፋ አሳድሯል ነው የተባለው፡፡ ፕላኔቷ አለታማ አሊያም እንደኔፕቲዩን በጋዝ የበለፀገች ልትሆን እንደምትችል የናሳ ተመራማሪዎች የገለጹ ሲሆን ፕላኔቷ ያልተለመደችና ከቀድሞ ፕላኔቶች ልዩ እንደሆነች በመረጃው ተጠቅሷል፡፡ \n \nጥያቄ: የናሳ ተመራማሪዎች ሱፐርኧርዝ ብለው የሰሟት አንዲት ፕላኔት ከመሬት አንፃር መጠንዋ ምን ያህል ይሆናል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የመሬትን እጥፍ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: በሳውዲ አረቢያ ከሚኖሩት ምን ያህሉ የሳውዲ ዜጎች ይኖራሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 2ዐ ሚሊዬኑ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nቴክኖ ካሞን 17 በዘጋቢ ፊልም ታግዞ ወደ ገበያ መግባቱን ኩባንያው አስታወቀ :: በዓለም አቀፍ ደረጃ በአዲሱ ትውልድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ቴክኖ ሞባይል ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም በለቀቀው አዲሱ የCAMON 17 ተከታታይ ስልክ የብዙዎችን ቀልብ መሳብ መቻሉን ኩባንያው አስታውቋል:: ይህ ፈጠራ የታከለበት ቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ማጠንጠኛውን በሰልፊ ላይ ባደረገ ዘጋቢ ፊልም የተመረቀ ሲሆን ድርጅቱ ምርቱን ከማስተዋወቅ ባለፈ በኢንዱስትሪ፣ በማኅበራዊና በሰብዓዊነት ዘርፎች ላይ የበለጠ ጥረት ለማድረግ ያለውን ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል:: “The Rise of Selfie” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ዘጋቢ ፊልም ፊልም በማስመረቂያ ፕሮግራሙ ላይ የቀረበ ሲሆን ታዳሚዎቹ በእርግጥም ቴክኖ የዚህን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት በተጨባጭ እና በስሜት እየሰራ መሆኑን ስለመገንዘባቸው ድርጅቱ ገልጿል:: አዲሱ የቴክኖ የንግድ አምባሳደር ክሪስ ኢቫንስ “ሕያው እና በስሜት የተሞላ ምስል ትፈልጉ ይሆናል፣ ነገር ግን መልካም ምስል የሚያደርገው ‘እጅግ ግለሰባዊ’ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ ሁሌም ቴክኖ በፅኑ ከሚያምንበት እና ከሚታወቅበት ሃሳብ ጋር ይጣጣማል ብለዋል፡፡ የስማርት ስልክ ፅንሰ ሃሳብ ብራንዱ ላይ ሳይሆን ተጠቃሚው ላይ ማውጠንጠን እንዳለበትም ነው የንግድ አምባሳደሯ የጠቆሙት፡፡ የፋሽን ሞዴል የሆኑት ሣራ በፊልሙ ላይ እንዳሉት እንደ ቴክኖ ካሞን 17 ያሉ የሰልፊ ስልኮች ተጠቃሚዎች የራሳቸውን ምስል ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተወዳጅ ፎቶዎችን በማንሳት ምስላቸውን እንዲቆጣጠሩ ያስችላቸዋል:: በተጨማሪም የተሻለ ማንነት እንዲኖር ለማድረግ እዲሁም በደመነብስ ወደተሻለ እኛነት እንድንመጣ ለራሳችን የምንጠቁምበት መንገድ ነው ብለዋል:: ቴክኖ ካሞን 17 ሁልጊዜ “በልባቸው ወጣት” ለሆኑ እና ለአዳዲስ ነገሮች ራሳቸውን ለሚያነሳሱ ተጠቃሚዎች ምልክት ለመሆን የተሰራ ነው ያለው ድርጅቱ፥ ሰዎች ራሳቸውን በይበልጥ ለመግለጽ እንዲችሉ ያስችላቸዋልም ብሏል፡፡ ኮቪድ19 ባስከተለው ተጽዕኖ ሰዎች ከሚወዷቸው ሰዎች ጋር ለመገናኘት ሰልፊን ማዘውተራቸው የሰልፊን ተግባር ይበልጥ አስፈላጊ ያደረገው በመሆኑ ጉዳዩን ቴክኖ እና ሌሎች የስልክ አምራቾች በአጽንኦት እንዲያጤኑት አድርጓቸዋል:: በቴክኖ ካሞን 17 ስልክ ሰዎች ህይወት ያላቸው የሚመስሉ ፎቶዎችን ማጣጣም ብቻ ሳይሆን በFHD ስክሪን ላይ በጣም ግልጽ የሆነ ምስልን ማየት እንደሚያስችላቸው ነው የተገለጸው:: ይህ ከፍተኛ ጥራት ያለው ስክሪን ተጠቃሚዎች በቪዲዮ ጥሪዎች ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ተወዳዳሪ የሌለው ግልጽነት የሚሰጣቸው ሲሆን ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ተንቀሳቃሽ ምስሎችን መመልከት እና ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ጌሞችን መጫወት እንደሚችሉም ነው ኩባንያው የገለጸው፡፡ ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!   \n \nጥያቄ: በዓለም አቀፍ ደረጃ በአዲሱ ትውልድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈው ሞባይል አምራች ቴክኖ ኩባንያ አዲሱ ምረቱን መቼ አስተዋወቀ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ግንቦት 4 ቀን 2013 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ የት ነው የምትገኘው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በምዕራብ ኤዥያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: በጮቄ ወረዳ ምን ያህል የአባይ ገባሮች እና የውሃ ጅረቶች ይገኙበታል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ምን ምን ሃይማኖቶች በስፋት ይገኛሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ክርስትና እና እስልምና ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሊንጋላ ሊንጋላ (Lingala) ከባንቱ ቋንቋዎች ቤተሠብ አንድ ነው። የሚናገርበት በተለይ በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ስሜን-ምዕራብ ክፍል፣ በኮንጎ ሪፑብሊክም፣ እንዲሁም በአንጎላና በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ነው። ተናጋሪዎቹ 10 ሚልዮን ናቸው። የሊንጋላ መነሻ ቦባንጊ በተባለ ቋንቋ ነበር። ከኮንጎ ነጻ መንግሥት አስቀድሞ ቦባንጊ የአከባቢው መደበኛ ቋንቋ ይሆን ነበር። የቤልጅክ ንጉስ አገሩን ከያዙ በኋላ የቀኝ አገሩ መንግሥት ለማስተዳደርና ለመሰበክ ቋንቋውን ጠቃሚ ሆኖ አገኙት። ካለፈው ቦባንጊ እንዲለይ የአዲሱን ቋንቋ ስም ባንጋላ ብለው ጠሩት። ሚስዮናዊዎቹ ወዲያ (1900 አ.ም.) ባንጋላን ዳግመኛ ሲያሻሽሉ \"ሊንጋላ\" እንዲህ ተፈጠረ። ሊንጋላ ከፈረንሳይኛ ብዙ ቃሎች ተበድሮ ደግሞ ከፖርቱጊዝ ተጽእኖ አለ (ለምሳሌ \"ማንቴካ\" = ቅቤ፤ \"ሜሳ\" = ጠረጴዛ፤ \"ሳፓቱ\" = ጫማ) ከእንግሊዝኛም ተጽእኖ አለ (\"ሚሊኪ\" = ወተት፤ \"ቡኩ\" = መጽሐፍ)። \n \nጥያቄ: የሊንጋላ ምንጭ ምን ቋንቋ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ቦባንጊ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከአድዋ ሽንፈት በኋላ ጣሊያኖች ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራርመው አዲስ ገዢ፣ ፈርዲናንዶ ማርቲኒ፣ 1897 ላይ በመሾም ግዛታቸውን ማጽናት ጀመሩ። በዚህ ወቅት የቀደመው ወታደራዊ ስርዓት እንዲቋረጥ ተደርጎ አገሪቱ የብሔር ልዩነትን \"በሚያከበር\" አስተዳደር ተከፍሎ እንዲቋቋም ተደረገ። ዳህላክ፣ አፋር እና ሰምሃር አንድ ላይ \"ምስራቃዊ ክፍል\" ተብለው ከምጽዋ እንዲተዳደሩ ተደረገ። \"ምዕራባዊ ክፍል\" ከአቆርዳት እንዲተዳደር ሲደረግ ቤኒ አሚርን፣ ናራንና ኩናማ ምድርን ያጠቃልል ነበር። ከከረን ሆኖ የሚተዳደረው ደግሞ ሰሜናዊ ሐማሴን (የእስልምና ተከታይ የሆነ)፣ ቤት አሰገደና ዓድ ሼኽ ነበሩ። ቀሪው ሐማሴን ከአስመራ፣ ሰራየ ከመንደፈራ(አዲ ወግሪ) እንዲተዳደር ሲደረግ አካለ ጉዛይ ከሳሆ ጋር ተዋህዶ ከአዲ ቀይሕ ይገዛ ጀመር። ከላይ ወደታች በተዘርጋ መዋቅር የጣሊያን ባለስልጣኖች እያንዳንዱን ክፍል ያስተዳድሩ ጀመር። የአገሪቱ ዋና ከተማ ከምጽዋ ወደ አስመራ የተዛወረው በዚህ ወቅት፣ በ1898 ነበር። ከ1898 እስከ 1908 በተደረጉ ውሎች (ከኢትዮጵያ፣ ከአንግሎ-ግብጻዊ ሱዳንና ከጅቡቲ ጋር) መሰረት የቅኝ ግዛቱ ድንበር ታወቀ። ኢትዮጵያን ስለ ድንበሩ ለማሳመን 3 አመትና 5ሚሊዮን ሊሬ ፈጅቶባቸው ግንቦት 1900 ላይ ያሰቡት ሊሳካላቸው ቻለ። ድንበሩ ከሞላ ጎደል የመረብ፣ በለሳና ሙና ወንዞችን የታከከ ነበር። \n \nጥያቄ: በ1898 የኤርትራ ዋና ከተማ ወደ አስመራ የተዛወረው ከየት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከምጽዋ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: የቀድሞው የናዋትል ቋንቋ አጻጻፍ ከማን ጽሕፈት ጋር ይመሳሰል ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በህፃናት ልብ ህክምን ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱት ዶክተር በላይ አበጋዝ እና 30ኛ አመቱን በማክበር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል ያላቸውን አስተዋፅኦ በማድነቅ ሽልማት አበረከቱ። \n \nጥያቄ: ዶ/ር በላይ አበጋዝ በኢትዮጵያ ልብ ህክምና ማዕከል ላደረጉት አስተዋጽኦ በዶ/ር አብይ አህመድ የተሸለሙት ማዕከሉ ስንተኛ ዓመቱን ሲያከብር ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 30ኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: በአሪዞና ሕግ አውጪ አካል 60ዎቹ አባላት ምንድን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ምክር-ቤት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1981 ዓ.ም. ንጉሥ ሌቤንጉላ ዜግነቱ ምናዊ ለሆነ ሰው ነበር የማዕድን ማውጣት ፈቃድ የሰጠው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ብሪታኒያዊው ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በዚምባብዌ በስሚዝ አመራር ወቅት ሮበርት ሙጋቤ የሚመሩት ፓርቲ ምን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንግሥተ ነገስታት ዘውዲቱ መቼ ሞቱ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበጃኑዋሪ 1958 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋልና የፈረንሣይ ሱዳን ተቀላቅለው የማሊ ፌዴሬሽንን መሠረቱ። ይህም ፌዴሬሽን በአፕሪል 4፣ 1960 እ.ኤ.አ. ከፈረንሣይ ጋር በተፈረመው የሥልጣን ዝውውር ስምምነት አማካኝ በጁን 20፣ 1960 እ.ኤ.አ. ነጻነቱን አውጀ። በውስጣዊ የፖለቲካ ውዝግቦች ምክኒያት ፌዴሬሽኑ ክሁለት ወር በኋላ ተከፈለ። ሴኔጋልም ነጻነቱን በድጋሚ አውጀ። ሊዎፖልድ ሴንግሆርም የመጀመሪያው ፕሬዘዳንት ሆኖ በኦገስት 1961 እ.ኤ.አ. ተመረጠ። ፕሬዝዳንት ሊዎፖልድ ሴንግሆር ሀገሩን መምራት ከጀመረ በኋላ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ማማዱ ዲያ ጋር ባለው አለመስማማት ምክኒያት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተመራ መፈንቅለ-መንግሥት በዲሴምበር 1962 እ.ኤ.አ. ተካሄደ። ይህ መፈንቅለ-መንግሥት ያለ ደም ፍስሻ የከሸፈ ሲሆን ማማዱ ዲያም ታሰረ። ከዛም ሴኔጋል የፕሬዝዳነንቱን ሥልጣን የሚያጠነክር አዲስ ሕገ-መንግሥት አሳለፈች። በ1980 እ.ኤ.አ. ፕሬዝዳንት ሴንግሆር በራሱ ፍቃድ ከሥልጣኑ የወረደ ሲሆን በ1981 እ.ኤ.ኣ. በራሱ በሊዎፖልድ ሴንግሆር የተመረጠው አብዱ ዲዮፍ ፕሬዝዳንት ሆነ። በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ.፣ ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ የሴኔጋምቢያ ኮንፌዴሬሽንን መሠረተች። ከስምንት ዓመት በኋላ ግን በ1989 እ.ኤ.አ. ኮንፌዴሬሽኑ ፈረሰ። ከ1982 እ.ኤ.አ. ጀምሮ በደቡባዊ ሴኔጋል በካሳማንክ አካባቢ የሚገኙ አማጺዎች ከሴኔጋል መንግሥት ጋር በየጊዜው ተጋጭተዋል። ሴኔጋል ዓለም-አቀፍ ሰላም-አስከባሪ ሃይሎችን በመላክ ትታተወቃለች። አብዱ ዲዮፍ ከ1981 እስከ 2000 እ.ኤ.አ. ድረስ ፕሬዝዳንት ነበረ። በሥልጣን ጊዜው አብዱ የፖለቲካ ተሳትፎን አበረታትቷል፣ መንግሥቱ በኤኮኖሚው ላይ ያለውን ቁጥጥር አሳንሷል፣ እና ሴኔጋል ክውጭ በተለይም ከታዳጊ ሀገሮች ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን አጠናክሯል። አብዱ ለአራት የሥራ-ጊዜዎች ፕሬዝዳንት ሆኖ አገልግሏል። በ2000 እ.ኤ.አ. በዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ነጻና ዲሞክራሲያዊ በተባለ ምርጫ የአብዱ ዲዮፍ ተቀናቃኝ አብዱላይ ዋዲ አሸንፎ ፕሬዝዳንት ሆኗል። ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ሸቀጦች በተለይ አሣ፣ ጥጥ፣ ጨርቅ፣ ባምባራ ለውዝ (Vignea subterranea)፣ ካልሲየም ፎስፌት ናቸው። ሴኔጋል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ናት። ከ2001 እ.ኤ.አ. ጀምሮ ፕሬዝዳንቷ በየአምስት ዓመት የሚመረጥ ሲሆን ከዛ በፊት ደግሞ በየሰባት ዓመት ነበር። ያሁኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ዋዴ ሲሆኑ በማርች 2007 እ.ኤ.አ. እንደገና ተመርጠዋል። \n \nጥያቄ: ሴኔጋል ከጋምቢያ ጋር ተዋሕዳ ኮንፌደሬሽን የመሰረተችው መች ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በፌብሩዋሪ 1፣ 1982 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በማሊ በመቶኛ ምን ያህሉ መሬት በረሃማ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 65 ከመቶ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአፋር (ክልል) አፋር ክልል (ክልል 2) በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙት ዘጠኝ ክልሎች አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ዋና ከተማው ሰመራ ሲሆን የቀድሞዋ ከተማ ግን አሳይታ ነበረች። 96,707 ካሬ ኪ.ሜ. ሲሸፍን በ1999 እ.ኤ.አ. የሕዝብ ብዛቱ 1,188,000 ነው። የድንቅ ነሽ ወይም ሉሲ አጽም በአፋር ክልል ውስጥ በ, 1967 (Nov. 24, 1974 እ.ኤ.አ.) ነው የተገኘው። በማርች 5, 2005 ደግሞ ሌላ 3.8 ሚሊዮን ዓመት የሚገመት አጽምም በዚሁ ክልል ተገኝቷል። \n \nጥያቄ: በአፋር ክልል ከሉሲ በተጨማሪ አዲስ የተገኘችው የሰው ቅሪተ አካል መቼ ተገኘች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 3.8 ሚሊዮን ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻውን የተካው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ማሪያኖ ባሬቶ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቢል ክሊንተን ያደጉት በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው። የቢል ክሊንተን አባት ዊሊያም ጄፈርሰን ብላይዝ ጁኚየር፣ ቢል ክሊንተን ከመወለዱ ሶስት ወር በፊት በመኪና አደጋ ሞተዋል። የቢል ክሊንተን እናት ቨርጂኒያ ክሊንተን ኬሊ፣ በ1950 እ.ኤ.ኣ. ሮጀር ክሊንተን የሚባል ሰዉ አገባች። 14 ዓመቱ ሲሆን ቢል ክሊንተን የመጨረሻ ስሙን ወደ ክሊንተን ለወጠ። ክሊንተን በጆርጅታውን ዩኒቨርሲቲ፥ ዋሽንግተን ዲ.ሲ.፣ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፥ ኢንግላንድ፣ እና ዬል ዩኒቨርሲቲ፥ ኮነቲኬት ተምረዋል። በ1975 እ.ኤ.ኣ. ሂለሪ ሮድሃምን አገቡና በሊትል ሮክ፥ አርካንሳው መኖር ጀመሩ። ከዚያም በዩኒቨርሲቴ ኦፍ አርካንሳው የሕግ ፐሮፌሰር ሆነው አገልግለዋል። ቢል ክሊንተን የአርካንሳው አስተዳዳሪ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመረጡት በ1978 እ.ኤ.ኣ. ነው። በዛ ጊዜ ከአሜሪካ በዕድሜ ትንሹ አስተዳዳሪ ነበሩ። በ1980 እ.ኤ.ኣ. በፍራንክ ዲ ዋይት ከተሸነፉ በኋላ በ1982 እ.ኤ.ኣ. እንደገና ተመረጡ። ከዛ ጀምሮ እስከ 1992 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ለአራት ጊዜ አስተዳዳሪ ሆነው መርተዋል። በ1984 እ.ኤ.ኣ. የአስተዳዳሪ የስልጣን ዕድሜ ከ2 ዓመት ወደ 4 ዓመት አራዝመዋል። በ1992 እ.ኤ.ኣ. ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድርው አሸንፈዋል። በ1996 እንደገና ተወዳድረው አሸንፈዋል። \n \nጥያቄ: የቢል ክሊንተን የእድገታቸው ስፍራ የት ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሆት ስፕሪንግስ፣ አርካንሳው ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ የሚነገሩ ቋንቋዎች በስንት ይከፈላሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nፋሲለደስ ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው አፄ ሱሰኒዮስ እና እናታቸው ልዕልት ስልጣነ ምገሴ በመገዛዝ፣ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው። አፄ ፋሲል አዘዞ ተብላ በምትታወቀው ከጎንደር ከተማ 5 ማይል ርቃ በምትገኘው ከተማ ጥቅምት18፣1667 እ.ኤ.አ. (ጥቅምት 10፣ 1660) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አስከሬናቸውም የአገሪቱ መላ ህዝብ ባዘነበት ሁኔታ በቅዱስ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ጣና ሃይቅ ውስጥ ደጋ ደሴት ተብላ በምትታወቀው ደሴት የዘላለም እረፍት አገኘ። \n \nጥያቄ: አፄ ፋሲል መቼና የት ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ሸዋ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በተያዘው የበጀት ዓመት የመጀመርያው ሦስት ወራት፣ ከ12.2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ቢሮው እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ የሚዘልቅ ግብር የማሳወቅና የመሰብሰብ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጾ፣ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጨረሻ ሳምንት ባለው ጊዜ ከግብር አሰባሰቡ የተገኘው ገቢ ከታቀደው በላይ እንደሆነ አስታወቋል፡፡ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊነትን አዲስ በተመረጠው የከተማ አስተዳደር እንዲመሩ በድጋሚ የተመረጡት አቶ ሙሉጌታ ተፈራ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ ገቢዎች ቢሮው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የተጀመሩትን የከተማዋን ገቢ በተጠናከረ ሁኔታ የመሰብሰብ ሥራ ዘመናዊ በሆነ ሥርዓትና ቅንጅታዊ አተገባበር እየተከናወነ ነው፡፡ በተያዘው በሩብ ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ የታቀደው የግብር ገቢ 11.5 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ያስታወቁት ኃላፊው፣ ከሦስት ያላነሱ ቀናት የገቢ አሰባሰብ መረጃ ሳይካተት እስከ መስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ 12.26 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ዓመታዊ የግብር ማሳወቅና አሰባሰብ እስከ መቼ ይቆያል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nህንድ ፈጣን የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ሰርታለች፡፡ ሃገሪቱ የሰራችው መመርመሪያ ልክ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ውጤቱን በፍጥነት ሊያሳይ የሚችል ነው ተብሏል፡፡ በዚህም ከአንድ ሰዓት በታች በሆነ ጊዜ ውስጥ ውጤቱን እንደሚያደርስ ነው የተነገረው፡፡ በ2 ሺህ ህሙማን ላይ ምርመራ ተደርጎም ውጤታማነቱ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡ ፌሉዳ የተባለው ይህ መመርመሪ ኪት ዋጋው 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የህንድ መንግስት ዋና የሳይንስ አማካሪ ፕሮፌሰር ኬ ቪጃይ ራጋቫን እንዳሉትም ሙከራው ቀላል ፣ ትክክለኛ፣ አስተማማኝ እና ወጪ ቆጣቢ ነው ፡፡ ህንድ በአሁኑ ጊዜ ከ1 ሺህ 200 በላይ ላቦራቶሪዎች ያሏት ሲሆን በቀን 1 ሚሊየን ናሙናዎችን እየመረመረች ትገኛለች፡፡ \n \nጥያቄ: ፌሉዳ የተባለው የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ዋጋው ስንት ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 500 የህንድ ሩፒ ወይም ሰባት ዶላር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሜሪላንድ ሜሪላንድ (እንግሊዝኛ፦ Maryland) በአሜሪካ የምትገኝ ስቴት ስትሆን ምዕጻረ ቃሏ MD ወይም Md. ነው። ሜሪላንድ ከአሜሪካ አስራሶስት ጥንታዊ ስቴቶች አንዷ ናት። ከሜሪላንድ ጋር የሚገናኙ ስቴቶች ፔንስልቫኚያ ፣ ቨርጂኚያ ፣ ዌስት ቨርጂኚያ ፣ እና ዴላዌር እያሉ፤ ደግሞ በኮለምቢያ ክልል (ዋሽንግተን ዲ.ሲ.)ና በአትላንቲክ ውቂያኖስ ትወሰናለች። የቼሳፒክ ወሽመጥ ስቴቱን መሃል ለመሃል ይከፍለዋል። የሜሪላንድ ከፍተኛ ቦታ የባክቦን ተራራ ጫፍ ነው። የሜሪላንድ አየር ሁኔታ ከቦታ ቦታ ይለያያል። የምስራቅ ክፍሉ ሞቃታማ በጋና መካከለኛ ክረምት የአየር ሁኔታ ሲኖረው የምዕራብ ክፍሉ ደግሞ መካከለኛ በጋ እና በጣም ቀዝቃዛ ክረምት አለው። የሜሪላንድ ጠቅላላ ምርቶች በ2003 እ.ኤ.ኣ. ወደ 212 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመት ነው። በዚሁ ዓመት የአንድ ሰው የዓመታዊ ገቢ በኣማካይ 37,446 የአሜሪካን ዶላር ነበር ፣ ከአገሩ 5ኛ። ከፍተኛ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ወታደራዊ ካምፖች እና የሳይንስና የሕክምና ተቋማት በዚሁ ክፍላገር ይገኛሉ። የስቴቱ ዋና ያውሮፕላን ማረፊያ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ዓለም አቀፍ ያውሮፕላን ማረፊያ (BWI) ነው። በ1996 የሜሪላንድ ጠቅላላ የህዝብ ብዛት 5,558,058 ነው ተብሎ ይገመታል። ከዚሁ ውስጥም 583,900ቹ ወይም 10.6 በመቶ ሌላ ስቴት ወይም አገር የተወለዱ ነዋሪዎች ናቸው። አብዛኛው ህዝብ የስቴቱ መዓከላዊ ክፍል ውስጥ ይኖራል። \n \nጥያቄ: የሜሪላንድ ስቴት ዋና አውሮፕላን ማረፊያ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ባልቲሞር-ዋሽንግተን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ በሌላ አጠራሩ ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ በቀጰዶቂያ የቄሣርያ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። የንቂያን የሊቃውንት ጉባዔ የሚደግፍና አርያኒዝምንና የአፖሊናረስን ተከታዮችን የክርስትና አመለካከት ተቃውሞ ትክክለኛውን መንገድ ያስተማረ ታላቅ አሳማኝ የሃይማኖት ፈላስፋና መሪ ነበር ። ቅዱስ ባስሊዮስ ከሃይማኖት ፈላስፋነቱ ሌላ ድሆችንና ኑሮን ማሸነፍ ያቃታቸውን በመንከባከብ ይታወቃል ። በተጨማሪም የማኅበራዊ ኑሮ ፣ የሥርዐተ ጸሎትና የጉልበት ሥራ ለገዳማዊ ኑሮ መመሪያን መሥርቷል። ባስሊዮስ ከቅዱስ ጳኩሚስ ጋር የማኅበራዊ ገዳማዊነት አባት ተብሎ በምሥራቃዊ ክርስትና ይታሰባል ። ዳሮግን በምሥራቅም በምዕራብም በቅዱስ ደረጃ ነው የሚከበረው ። እነዚህ ሁለት ጎራዎች ታላቅ የቤተክርስቲያን አባት የሚለውን ስያሜ ከዮሐንስ አፍወርቅና ከግሬጎሪዮ ናዚያንዘስ ጋር ሰተውታል። ባስሊዮስ ከቀዳማዊ ባስሊዮስና ከኤሚልያ የቄሣሪያዋ በ፫፻፳ ዓም አካባቢ በቀጰዶቂያ ተወለደ ። እናትና አባቱ እግዚአአብሔርን በጣም የሚወዱና ጸሎተኞች የነበሩ ሰዎች ነበሩ ። የእናቱ አባት ከቆስጠጢኖስ ፩ኛ በክርስትና ማመን በፊት ሰማዕት ሆኖ ያለፈ ሰው ነበረ። ጸሎተኛ ባልቴቱ ማክሪናም የጎርጎርዮስ ታውማታርገስ (የኒዎ ቄሣርያን ቤተክርስቲያን በአቅራቢያው የመሠረተ) ተከታይ የነበረች ባስሊዎስንና አራቱን ወንድሞቹንና እህቱን ፣ ወጣትዋ ማክሪና ፣ ናውክራቲየስ ፣ ጴጥሮስ የሰባስቴውንና ፣ ጎርጎርዮስ የኒሳውን (ወደፊት ታላቅና የተከበሩ ቅዱሳን የሚሆኑ) በክርስትና ሃይማኖት ሥርዐት አሳደገች ። ባስሊዮስ በቄሣርያ ማዛካ ቀጰዶቂያ በአሁኑ ዘመን አጠራር ካይዜሪ (ቱርክ) ትምህርት ቤት በ፫፻፵፪ ፵፫ ዓ.ም.አካባቢ ተምሩዋል ። እዛም ጎርጎርዮስ ናዚያንዘስን የረጅም ጊዜ ጉዋደኛ የሚሆነውን ተዋውቋል። ባስሊዮስና ጎርጎርዮስ አንድላይ በመሆን ለከፍተኛ ትምህርትና በተጨማሪ የሊባኒየስን ትምህርታዊ ንግግር ለማጥናት ወደ ቁስጥጥኒያ አምርተዋል ። ሁለቱ በአቴንስ በ፫፵፪ ዓ.ም. አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል። በዛም ቆይታቸው ጁሊያን ዘአፖስቴት ወደፊት ንጉሥ የሚሆን ተማሪ ተዋውቀዋል። ባስሊዮስ አቴንስን በ፫፵፰ ለቆ ወደ ግብፅና ሶርያ ከተጉዋዘ በኋላ አገሩ ቄሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር ቆየ። \n \nጥያቄ: ቅዱስ ባስሊዮስ ዘቄሣርያ የትውልድ ስፍራቸው በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በቀጰዶቂያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nፐርል በክ ፐርል በክ በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ (1938) ለመሆን የበቃች አሜሪካዊት ደራሲ ናት። በክ ጁን 26 ቀን 1982 ዓ.ም በምእራብ ቨርጂኒያ ሂልዝቦሮ በተባለ ቦታ ተወለደች። ወላጆቿ ፕሬስብቴርያዊ ሚሲዮኖች የነበሩ ሲሆን ብዙውን የሚሲዮን ስራቸውን በቻይና ነው ያሳለፉት። በዚሁ የተነሳ በክ ከልጅነቷ ጀምሮ እንግሊዝኛን ብቻ ሳይሆን ቻይንኛንም አቀላጥፋ ትናገር ነበር። ትምህርቷን በ1914 እንዳጠናቀቀች ወደ ቻይና ነው ያቀናችው። በ1915 የወደፊት ባሏ ከሚሆነውን ከጆን ሎሲንግ በክ ጋር ተገናነች። በ1917 ጋብቻቸውን ከፈጸሙ በኋላ ኑሯቸውን ናንሹ በተባለችው የገጠራማዋ አንህዌ ግዛት አደረጉ። በዚሁ ቆይታዋ ነው ወደፊት የሥነ-ጽሁፍ ስራዋ ጉልላት ለመሆን የበቃውን ስሙር መሬት (The Good Earth) ለተባለው መጽሃፏ የሚሆናትን መረጃ የሰበሰበችው። በክ ጽሁፎቿን ማሳተም የጀመረችው ከ1920ዎቹ ጀምራ ሲሆን አጫጭር ስራዎቿ \"The Nation\"፣ \"The Chinese Recorder\"፣ \"Asia\" እና \"The Atlantic Monthly\" በተሰኙ መጽሄቶች ታትመውላታል። የመጀመሪያው ወጥ ልብ-ወለድ ድርሰቷ (East Wind, West Wind) በ1930 በጆን ዴይ ኩባንያ ታትሟል። የጆን ዴይ ኩባንያ አሳታሚ የነበረው ሪቻርድ ዋልሽ ኋላ ላይ (1935) የፐርል በክ ሁለተኛ ባሏ ለመሆን በቅቷል። በ1931 ጆን ዴይ ኩባንያ የፐርል በክን ሁለተኛ ወጥ ልብ-ወለድ ድርስት የሆነውን ስሙር መሬትን አሳተመ። ይኸው ሥራዋ በተከታታይ በ1931 እና በ1932 ዓ.ም በገበያ ላይ አንደኛ ተፈላጊ ሆኖ ለመዝለቅ የቻለ ሲሆን ለሷም በ1935 ዓ.ም የፑሊትዘር ሽልማት እና የሃዌልስ ሜዳልያ አስገኝቶላታል። ስሙር መሬት በ1937 ዓ.ም በኤም.ጂ.ኤም አማካይነት በፊልም መልክ ተቀናብሮ ለተመልካች ቀርቧል። ከዛ በተከታታይ ሌሎች ድርሰቶችን ለአንባቢ አቅርባለች። በክ በ1938 ዓ.ም በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን በመቀበል የመጀመሪያዋ (ሴት) አሜሪካዊት ሆናለች። ፐርል በክ በ1973 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ስትለይ ከ70 በላይ ስራዎቿ ታትመውላታል። መቃብሯም ፔንሲልቬንያ ውስጥ በክስ በተባለው ቀበሌ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ፐርል በክ የመጀመሪያ ድርሰቷ መቼ ታተመላት?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1930 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ካሉ ባህላዊ ስፖርታዊ ውድድሮች የሚወደደው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ትግል ግጥሚያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ብሪታንያ በ1945 ዓ.ም. የትኞቹን አካበቢዎች አንድ ላይ በማድረግ ነው የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን የፈጠረችው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት በሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ምን ያህል ስደተኞች ይገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ 23,800 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ በአሜሪካ ጎዳናዎች ላይ ሙከራ እንዲያደርግ ፈቃድ አገኘ። ተሽከርካሪው የአሽከርካሪ ወይም የሰው እገዛ ሳያስፈልገው አገልግሎት ይሰጣል ነው የተባለው። ኑሮ በተባለው ኩባንያ የተሰራው ተሽከርካሪ መሪን ጨምሮ ለመሽከርከር የሚያገለግሉት የነዳጅ መስጫና ፍሬን እንዲሁም የእይታ መስታወትን (ስፖኬ) ያለ አሽከርካሪ በራሱ ይጠቀማል። የአሜሪካ የትራንስፖርት ሚኒስቴርም ተሽከርካሪው በቴክሳስ ሙከራውን እንዲያደርግ ፈቃድ ሰጥቶታል። አር 2 የሚል ስያሜን ያገኘው ይህ የእቃ ማመላለሻ፥ የኩባንያው ሁለተኛው ትውልድ ተሽከርካሪ ሲሆን በሆስተን ቴክሳስ ሙከራ እንደሚያደርግ ነው የተነገረው። የእቃ ማመላለሻውን ለመሞከር ተሽከርካሪውን መቆጣጠር የሚያስችሉ ክፍሎችን ማሟላት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል። ሆኖም የእቃ ማመላለሻ ተሽከርካሪው ፍጥነት በሰዓት ከ25 ኪሎ ሜትር እንዳይበልጥ የአሜሪካ ትራንስፖርት ሚኒስቴር አስጠንቅቋል። ምንጭ፦ ቢቢሲ ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision \n \nጥያቄ: የመጀመሪያው ያለ አሽከርካሪ የሚሰራ የእቃ ማመላለሽ ተሽከርካሪ ሙከራ እንዲያገኝ በየት ሀገር ፍቃድ አገኘ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በአሜሪካ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nተቀማጭነቱ ካሊፎርኒያ ውስጥ ያደረገው ኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የተባለው የሶፍትዌር አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ ውስጥ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ፡፡ የኢ ኦ ኤን ኩባንያ መስራች ዳን ለጀርስካር ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደማርያም ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ማዕከሉን የመክፈት ፍላጎት መኖሩን ተናግረዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሂሩት በበኩላቸው የቴክኖሎጂውን አስፈላጊነትና ወቅታዊነትን በመገንዘብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኩባንያው ጋር በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የኢ ኦ ኤን ሪአሊቲ የሶፍትዌር አምራች ድርጅት መስራች ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ዳን ለጀርስካር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአቡነ ቴዎፍሎስ አቡነ ቴዌፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያርክ ጎጃም በሚገኝው በዝነኛው ደብረ ኤሊያስ አካባቢ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ማርያም ውቤ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ዘርትሁን አደላሁ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፲፱፻፪ ዓ/ም ተወለዱ። ሲወለዱም የተሰጣቸው ስም መልእክቱ ወልደ ማርያም ነበር። በልጅነታቸው ንባብ እና ዜማን በመምህር መሪ ጌታ ረዳኸኝ እና ግራ ጌታ ሣህሉ እዚያው የተወለዱበት አካባቢ ተምረዋል። ኋላ የቅኔ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ዝንባሌ ስላደረባቸው እዚያው ደብረ ኤሊያስ ደብር መምህር ገብረ ሥላሴ በሚባሉ ሊቅ ሥር መማር ጀመሩ። በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ መጥተው ፍትሐ ነገሥትና አዲስ ኪዳንን በመምህር ተክሌ (ነቡረ ዕድ በኋላ ቢትወደድ አቡነ ዮሐንስ) በመባል የሚታወቁት መሪነት ሲከታተሉ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥ የኃይማኖት ችግሮችን ለማወቅ ይፈልጉ እንደነበርና ሰፋ ያለ ዕውቀት እንደነበራቸው ይነገራል። በተጨማሪ የኃይማኖት ችግሮችን የሚመለከቱ መጻሕፍትን ሳይታክቱና ሳይሰለቹ ያነቡም ነበር። መልእክቱ ወልደ ማርያም በ፲፱፻፴ ዓ/ም ይህን ዓለም በቃኝ ብለው ደብረ ሊባኖስ ገዳም መንኩሰው ገቡ። ከጠላት ወረራ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀሳውስቱ በዘመናዊ የኃይማኖት ትምህርት እንዲሠለጥኑ በነበራቸው ሀሳብ መሠረት ፳ የሚሆኑ ሊቃውንት መርጠው በቤተ መንግሥቱ አካባቢ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። ከነኚህም አንዱ አባ መልእክቱ ወልደ ማርያም ናቸው። ቀደም ብሎ በኢትዮጵያና በግብጽ በተደረገው ስምምነት መሠረት ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ጳጳሶች ሲሾሙ ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ ወልደ ማርያም ለሹመት ከተመረጡት አምስት አባቶች አንዱ ሲሆኑ ወደግብጽ ተጉዘው በእስክንድርያው ፓትርያርክ ዳግማዊ አቡነ ዮሳብ እጅ በካይሮ በትረ ካና ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን እሑድ ሐምሌ ፲፰ ቀን ፲፱፻፵ ዓ/ም ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ “ብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ” ተብለው የሐረርጌ ጳጳስ ሆኑ። \n \nጥያቄ: አቡነ ቴዎፍሎስ በስንት ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ መጡ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በ፲፱፻፻፳ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአንጎላ አንጎላ፣ በይፋ የአንጎላ ሪፑብሊክ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ስትሆን ከናሚቢያ ፣ ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ፣ እና ከዛምቢያ ጋር ድንበር ትጋራላች። በምዕራብ ጫፍ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር ትገናኛለች። የፖርቹጋል ቅኝ-ተገዥ ነበረች። ነዳጅ እና አልማዝ ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የሚመደቡ ናቸው። የአንጎላ የሕግ-አስፈጻሚ ፕሬዝዳንቱን ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና የሚኒስትሮች ካውንስሉን ያጠቃልላል። ሁሉም ሚኒስትሮችና ምክትል ሚኒስትሮች የሚኒስተሮች ካውንስሉን ሲሰሩ በየጊዜው እየተሰበሰቡ ስለተለያዩ የፖለቲካ ጉዳዮች ውሳኔ ይሰጣሉ። የአስራ ስምንቱ ክልሎች መሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚመረጡት። በ1992 እ.ኤ.ኣ. የወጣ ሕገ-መንግስት የመንግስቱን አወቃቀር እና የዜጎችን መብትና ግዴታ ይዘረዝራል። ፕሬዝዳንቱ መንግሥቱ በ2006 እ.ኤ.ኣ. ምርጫ ለማድረግ ዕቅድ እነዳለው ገልጸዋል። ይህ ምርጫ ከ1992 አ.ኤ.ኣ. በኋላ የመጀመሪያው ምርጫ ነው የሚሆነው። አንጎላ ውስጥ ሶስት ዋና ብሔረሰቦች ይገኛሉ። ኦቪምቡንዱ 37% ፣ ኪምቡንዱ 25% ፣ እና ባኮንጎ 13%። ሌሎች ብሔረሰቦች ቾክዌ (ሉንዳ)፣ ጋንጉዌላ፣ ንሀኔካ-ሁምቤ፣ አምቦ፣ ሄሬሮ፣ እና ዢንዱንጋን ያጠቃልላሉ። በተጨማሪም ክልሶች (አውሮፓና አፍሪካዊ) 2% ይሆናሉ። ፖርቱጋሎች አንጎላዊ ካልሆኑ ሰዎች ብዙዎቹ ናቸው። ታሪክ በአንጎላ መጀመሪያ የሠፈሩት የኮይሳን ሰዎች ነበሩ። በባንቱ ፍልሰቶች ጊዜ እነዚህ ሰዎች ወደ ደቡብ አንጎላ ሄዱ። በ1483 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋሎች በኮንጎ ወንዝ አጠገብ ሠፈሩ። በ1575 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋል ካቢንዳ ጋር በባሪያ ንግድ ላይ ያቶከረ ግዛት መሠረተች። በ16ኛው ክፍለ ዘመን፣ ፖርቱጋል የአንጎላ የባህር ጠረፍን ተቆጣጠረች። በተለያዩ ውሎችና ጦርነቶች የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት አንጎላ ተስፋፋ። የፖርቱጋል መመለሻ ጦርነትን ምክኒያት በማድረግ የደች ሪፐብሊክ ሏንዳን ከ1641 እስከ 1648 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ተቆጣጠረች። \n \nጥያቄ: አንጎላ የማን ሀገር ቅኝ ተገዢ ነበረች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የፖርቹጋል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን ከመቼ ጀምሮ ወደ ስልጣን መጡ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: ለ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተደልድሎ የነበረው በምድብ ስንት ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሁለት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ቀድሞ በኢትዮጵያ የነበረ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለየትኛው ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለኢሊኖይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nግሥላ ግሥላ በእስያ፣ በአፍሪካ (ከነኢትዮጵያ) እና በመካከለኛው ምሥራቅ የሚገኝ አጥቢ አውሬ ነው። በእስያ የተገኘው ነብር የግስላ ቅርብ ዘመድ ሆኖ፣ በአነጋገር «ግስላ»ና «ነብር» የሚሉ ስሞች ሊለዋወጡ ይችላሉ። የአንድ ጎልማሳ ግሥላ ክብደት ከ35 እስከ 80 ኪ.ግ ሲደርስ በርዝመት ከ90 ሴ.ሜ እስከ 1,60 ሜ.ና በአፍሪካ የሚገኘው ዘር እስከ 1,90 ሜ ይደርሳል ። ከመሬት እስከ ሆዱ ከ50 እስከ 70 ሴ.ሜ ቁመት ሲኖረው ጭራው ደግሞ እስከ 100 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያሳያል ። ሴቲቱ ከወንዱ አነስ ትላለች ። በዱር ሲኖር እስከ 10 አመት እንደሚኖር ሲታወቅ በሰው ተይዘው ሲኖሩ እስከ 20 አመት እድሜ ያስመዘገቡ ግሥሎች አሉ። \n \nጥያቄ: የግስላ የጭራው ርዝማኔ ስንት ሴ.ሜ ይሆናል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 100 ሴ.ሜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nብጉር ብጉር ማለት የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከቆዳ ስር በሚገኙ የወዝ እጢዎች በሚመነጭ ቅባት ወይም ወዝ እና በሞቱ የቆዳ ህዋሳት በብዛት መከማቸትና በቀዳዳው መደፈን የሚፈጠር እባጭ ነው። በርካታ ጥናቶች ጭንቀት ብጉርን ከማባባሱም በላይ የቆዳ ጤንነት ችግር ላይ እንዲወድቅ ያደርጋል ይላሉ። ብጉር በጣም ከተለመዱት የቆዳ ችግሮች ውስጥ አንዱ ነው። ዕድሜ ዘርና ጾታ ሳይገድበው ሁሉንም ያጠቃል። ቆዳችን ላይ ብዙ ጥቃቅን ቀዳዳዎች አሉ። በነዚህ ቀዳዳዎች ውስጥ ደግሞ ቅባታማ ፈሳሽ የሚያመነጩ ዕጢዎች አሉ። የቅባታማ ፈሳሽና የቀዳዳዎቹ ጥቅም የሞቱ የቆዳችን ህዋሳትን ለማስወገድ ነው፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች እነዚህ ቀዳዳዎች ሲዘጉ ቅባታማ ፈሳሹ በቆዳችን ውስጥ ስለሚጠራቀም ብጉር ይፈጠራል፡፡ የተጠራቀመው ቅባትም ለህዋሳት መራባት ዕድል ስለሚከፍት አንዳነዴ መግል ይይዛል፡፡ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከ'ስቤሸስ ግላንድ' ጋር የተያያዙ ናቸው፡ እነዚህ እጢዎች ሴበም የሚባል ንጥረነገር ሲያመነጩ ንጥረነገሩም በጸጉር መውጫ ቀዳዳ ወደላይ ወደቆዳ የሚወጣ እና ቆዳችን ላይ የሚያርፍ ነው። የብጉር መፈጠር የቆዳ ህዋሳትን ያበዛል። ይህ እባጭ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎችን ግርግዳ በመግፋት ነጫጭ የብጉር ሽፍታዎች ሲፈጥር የቀዳዳዎችን ግርግዳ በመጎተት ደግሞ ጥቋቁር የብጉር ሽፍታዎች (blackheads) ቆዳችን ላይ ሊፈጥር ይችላል። ብጉር በብዛት ሊወጣ የሚችልባቸው ቦታዎች፣ ፊት ላይ፣ በደረት፣ በኣንገት፣ በትከሻ ፣ እና በጀርባ ላይ ነው። \n \nጥያቄ: ብጉርን ሊያባብስ የሚችል ነገር ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጭንቀት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዩናይትድ ኪንግደም ዩናይትድ ኪንግደም ማለት የተባበረው ግዛት በተለመደው እንግሊዝ አገር ሲባል፣ እንዲያውም እንግሊዝ አገር ወይም ደግሞ «ኢንግላንድ» ከዩናይትድ ኪንግደም ዋና ክፍላገሮች አንዱ ብቻ ነው። ሌሎቹም፦ ስኮትላንድ ዌልስ ሰሜን አይርላንድ ናቸው። ከነዚህም እንግሊዝ፣ ስኮትላንድና ዌልስ አብረው «ታላቋ ብሪታንያ» የምትባል ደሴት ናቸው። ከ1699 ዓ.ም. (1707 እ.ኤ.አ.) አስቀድሞ፣ እንግሊዝና ስኮትላንድ የተለያዩ ንጉዛት ነበሩ። ከ1595 ዓ.ም. ጀምሮ ግን 2ቱ አገራት አንድ ንጉሥ ነበራቸውና በ1699 በመዋሐዳቸው አንድ ላይ «ዩናይትድ ኪንግደም» ሆነዋል። \n \nጥያቄ: ዩናይትድ ኪንግደም ማለት ምን ማለት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የተባበረው ግዛት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቢል ክሊንተን ዊልያም ጄፈርሰን «ቢል» ክሊንተን (William Jefferson Bill Clinton) (የትውልድ ስም፦ ዊልያም ጄፈርስን ብላይዝ ፬ኛ፣ እንግሊዘኛ፡ William Jefferson Blythe IV) በነሐሴ 13 ቀን፣ 1938 ዓ.ም.(1946 እ.ኤ.አ.) በሆፕ አርካንሳው የተወለዱ ሲሆን ከ1993 እስከ 2001 እ.ኤ.ኣ. ድረስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ፕሬዝዳንት ከመሆናቸዉ በፊት አምስት ጊዜ የአርካንሳው ስቴት አስተዳዳሪ ነበሩ። \n \nጥያቄ: ቢል ክሊንተን ከ1993 – 2001 በአሜሪካ ምን ኃላፊነት ነበረው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአሪዞና አሪዞና (Arizona) በምዕራባዊ ዩናይትድ ስቴትስ የሚገኝ ክፍላገር ነው። ኒው ሜክሲኮ ፣ ዩታህ ፣ ኔቫዳ ፣ ካሊፎርኒያ እና ኮሎራዶ ያዋስኑታል። የአሪዞና ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ የ30 ሰው ሴኔት እና የ60 ሰው ምክር-ቤት አለው። የሪፑብሊካን ፓርቲ በስቴቱ ዋነኛው ፓርቲ ነው። በ2002 እ.ኤ.አ. የአሪዞና ስቴት ሕግ-አውጪ ቅርንጫፍ በጀት 14.3 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በጀት ደግሞ 13.8 ቢሊዮን ዶላር ነው። የስቴቱ ሴኔተሮች እና ምክር-ቤት ተወካዮች ለሁለት-ዓመት ጊዜ ላልተወሰነ ብዛት ይመረጣሉ። ከ4 ጊዜ በላይ በተካካይ መመረጥ ግን አይችሉም። የሕግ-አስፈጻሚ ቅርንጫፍ በአስተዳዳሪ የሚመራ ሲሆን ለ4 ዓመት ሥልጣን ላይ ይቆያል። ያልተወሰነ ጊዜ መወዳደር ሲቻል ከሁለት ጊዜ በላይ ግን በተካካይ መመረጥ አይፈቀድም። \n \nጥያቄ: አሪዞና በዩናይትድ ስቴትስ በየት አቅጣጫ የሚገኝ ግዛት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በምዕራባዊ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nመጠነ እንቅፋት የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት (ሬዚስታንስ) የሚባለው አንድ ኤሌክትሪክ አባል በውስጡ ሊያልፍ የሚሞክር የኤሌክትሪክ ጅረትን የሚያደናቅፍበት መጠን ልኬት ነው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት ከሰበቃ ጋር ተመሳሳይ ባህርይ አለው። የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት የተደረሰበት በ1819 ዓ፣ም በጆርጅ ኦም ሲሆን፤ በዚህ ሰው ጥናት መሰረት የአንድ ነገር ኤሌክትሪካዊ መጠነ እንቅፋት በዚያ ነገር ላይ ያለ የቮልቴጅ ለ በውስጡ የሚያልፍ ጅረት ሲካፈል ጋር እኩል ነው። በሒሳብ ቋንቋ፡ ለብዙ ቁሶችና ሁኔታዎች፣ የኤሌክትሪክ መጠነ እንቅፋት R ጸንቶ የሚቆይ ቋሚ ቁጥር ነው። ማለት በኤሌክትሪክ ጅረትና በቮልቴጅ መጠን አይቀየርም። እነዚህ ነገሮች ኦማዊ ቁሶች ይባላሉ። የአንድ ሽቦ መጠነ እንቅፋት መጠን በርዝመቱና በስፋቱ ይወሰናል። የሽቦው ርዝመት በጨመረ ቁጥር እንቅፋቱ እየጨመረ ይሄዳል፣ በአንጻሩ ስፋቱ ሲጨምር እንቅፋቱ ይቀንሳል። ልክ ውሃ በሰፊ ቱቦ ውስጥ በቶሎ ሊሄድ እንደሚችልና፣ በረጅም ቱቦ ውስጥ ብዙ ሰበቃ ስለሚገጥመው በቀስታ እንደሚጓዝ ሁሉ። ከዚህ በተጨማሪ የሽቦው መጠነ እንቅፋት ሽቦው ከተሰራበት ዕቃ ተፈጥሮ ጋር ይዛመዳል። ስለሆነም የአንድ ሽቦን መጠነ እንቅፋት በሒሳብ ለማስላት የሚከተለው ቀመር ይጠቅማል፡ ሽቦው የተሰራበት ቁስ ልዩ መጠነ እንቅፋት ሲሆን የሚለካውም በ ኦም-ሜትር ነው። \n \nጥያቄ: የአንድ ሽቦ መጠነ እንቅፋት በምን ይወሰናል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በርዝመቱና በስፋቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: ፲፰፻፺ ዓ/ም ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ የገደላቸው ጣልያናዊ ማን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ባቫ-በካሪስ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: የሴኔጋል ቱባ ከተማ በነዋሪ ብዛት ስንተኛው ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ሁለተኛው ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኃይሌ ገብረሥላሴ ኃይሌ ገብረሥላሴ በ ሚያዝያ ፲ ቀን ፲፱፻፷፭ (1965) ዓ.ም. በአሰላ ከተማ ፣ አርሲ ክፍለ ሀገር የተወለደ አቻ ያልተገኘለት ድንቅ የረጅም ርቀት ኢትዮጵያዊ ሯጭ ነው። ኃይሌ በሩጫ ዘመኑ በ ፲ ሺህ ፣ በ ፭ ሺህ፣ በግማሽ ማራቶን፣ በማራቶንና እንዲሁም በሌሎቹ የሩጫ ዓይነቶች ከ ፲፩ በላይ የዓለም ክብረ-ወሰን ሰብሯል። ኃይሌ በሩጫ ችሎታው ጠንካራ የሆነበት ምናልባትም ከመንደሩ ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ ነው ተብሎ ቢታመንም የተፈጥሮ ጥንካሬው ዓለምን ያስደነቀ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ነው። ኃይሌ ሦስት ጊዜ የኦሊምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ከመሆኑም በላይ በ፴፫ ዓመት ዕድሜው ፪ ሰዓት ከ፬ ደቂቃ በሆነ ጊዜ በመግባት የዓለምን ማራቶን ክብረ-ወሰን ሊሰብር ችሏል። ኃይሌ ገብረሥላሴ እስካሁን ድረስ ፳፮ የዓለም ክብረ-ወሰኖችን ሰብሯል። ሯጭ ኃይሌ ገብረሥላሴ በሲድኒ እና በአትላንታ ኦሊምፒኮች በ፲ ሺህ ሜትር ሩጫዎች ወርቅ አስመዝግቧል። በ ፲፱፻፺፪ (1992) ዓ.ም. ኤንዱራንስ (Endurance) የተባለ ስለ እራሱ የእሩጫ ድል ፊልም ተሠርቷል። \n \nጥያቄ: አትሌት ኃይሌ ስንት ጊዜ የኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳልያ አግኝቷል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሦስት ጊዜ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአንጎላ አንጎላ፣ በይፋ የአንጎላ ሪፑብሊክ በደቡብ-ምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ስትሆን ከናሚቢያ ፣ ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ ፣ እና ከዛምቢያ ጋር ድንበር ትጋራላች። በምዕራብ ጫፍ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጋር ትገናኛለች። የፖርቹጋል ቅኝ-ተገዥ ነበረች። ነዳጅ እና አልማዝ ከተፈጥሮ ሀብቶቿ የሚመደቡ ናቸው። የአንጎላ የሕግ-አስፈጻሚ ፕሬዝዳንቱን ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና የሚኒስትሮች ካውንስሉን ያጠቃልላል። ሁሉም ሚኒስትሮችና ምክትል ሚኒስትሮች የሚኒስተሮች ካውንስሉን ሲሰሩ በየጊዜው እየተሰበሰቡ ስለተለያዩ የፖለቲካ ጉዳዮች ውሳኔ ይሰጣሉ። የአስራ ስምንቱ ክልሎች መሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚመረጡት። በ1992 እ.ኤ.ኣ. የወጣ ሕገ-መንግስት የመንግስቱን አወቃቀር እና የዜጎችን መብትና ግዴታ ይዘረዝራል። ፕሬዝዳንቱ መንግሥቱ በ2006 እ.ኤ.ኣ. ምርጫ ለማድረግ ዕቅድ እነዳለው ገልጸዋል። ይህ ምርጫ ከ1992 አ.ኤ.ኣ. በኋላ የመጀመሪያው ምርጫ ነው የሚሆነው። አንጎላ ውስጥ ሶስት ዋና ብሔረሰቦች ይገኛሉ። ኦቪምቡንዱ 37% ፣ ኪምቡንዱ 25% ፣ እና ባኮንጎ 13%። ሌሎች ብሔረሰቦች ቾክዌ (ሉንዳ)፣ ጋንጉዌላ፣ ንሀኔካ-ሁምቤ፣ አምቦ፣ ሄሬሮ፣ እና ዢንዱንጋን ያጠቃልላሉ። በተጨማሪም ክልሶች (አውሮፓና አፍሪካዊ) 2% ይሆናሉ። ፖርቱጋሎች አንጎላዊ ካልሆኑ ሰዎች ብዙዎቹ ናቸው። ታሪክ በአንጎላ መጀመሪያ የሠፈሩት የኮይሳን ሰዎች ነበሩ። በባንቱ ፍልሰቶች ጊዜ እነዚህ ሰዎች ወደ ደቡብ አንጎላ ሄዱ። በ1483 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋሎች በኮንጎ ወንዝ አጠገብ ሠፈሩ። በ1575 እ.ኤ.አ. ፖርቱጋል ካቢንዳ ጋር በባሪያ ንግድ ላይ ያቶከረ ግዛት መሠረተች። በ16ኛው ክፍለ ዘመን፣ ፖርቱጋል የአንጎላ የባህር ጠረፍን ተቆጣጠረች። በተለያዩ ውሎችና ጦርነቶች የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት አንጎላ ተስፋፋ። የፖርቱጋል መመለሻ ጦርነትን ምክኒያት በማድረግ የደች ሪፐብሊክ ሏንዳን ከ1641 እስከ 1648 እ.ኤ.ኣ. ድረስ ተቆጣጠረች። \n \nጥያቄ: አንጎላ በአፍሪካ በየትኛው አቅጣጫ ትገኛለች?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በደቡብ-ምዕራብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nነሐሴ ፲፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፵፩ ኛው ቀን ሲሆን የክረምት ወቅት ፵፮ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፳፭ ቀናት ሲቀሩ፣ በዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፳፬ ቀናት ይቀራሉ። ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ። ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአገሪቱን የመጀመሪያ አየር-ዠበብ (አውሮፕላን) በዚህ ዕለት ተረከበ። ሁለተኛው አየር-ዠበብ ከጂቡቲ ወደብ እስከ ድሬዳዋ በባቡር ተጭኖ፤ ከድሬ ዳዋ ደግሞ እስከ አዲስ አበባ አሥራ ስምንት የአውሮፓ የፖስታ ቦርሳዎችን ጭኖ እየበረረ ነሐሴ ፴ ቀን ገባ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ከ ፲፰፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በፈረንሳይ ሥር በቅኝ ግዛትነት ትተዳደር የነበረችው ጋቦን በዚህ ዕለት ነፃ ወጣች። ሊዮን ምባ የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆኑ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ። ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦይንግ ኩባንያ ከገዛቸው አሥር ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አየር-ዠበቦች የመጀመሪያውና በሰሌዳ ቁጥር ET-AOQ የተመዘገበው አየር-ዠበብ በዚህ ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስቶ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በተወለዱ በ፳፫ ዓመታቸው በዚህ ዕለት አረፉ። \n \nጥያቄ: ፲፱፻፶፪ ዓ/ም በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለማስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ ያመጡት አምባሳደር ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ አምባሳደር ዳግላስ ራይት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየአሜሪካ ታላቅ ማኅተም የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የአሜሪካ ታላቅ ማኅተም ይባላል። መጀመርያው የተገለጸው በ1774 ዓ.ም. ነበር። እንዲያውም በይፋ 'አርማ' ሳይሆን 'ማኅተም' ነው። ነገር ግን ይፋዊ አርማ ስለማይኖር በዘልማድ ይህ ማኅተም እንደ አርማ ይጠቀማል። በአሜሪካ ዶላር ላይ (ከ1927 ዓ.ም. ጀምሮ) እንዲሁም በአሜሪካ ፓስፖርት ላይ ይታያል። በማኅተሙ ፊት ላይ ክንፎቹን የሚዘረጋ የመላጣ ንሥር ስዕል እሱም የአሜሪካ ምልክት ይታያል። በግራው ጥፍሩ (ከንሥሩ አንጻር) ውስጥ አሥራ ሦስት ፍላጻ ይዟል። እነርሱም ከእንግሊዝ ያመጹ የመጀመርያ 13 ክፍላገሮች ያመልክታሉ። በቀኙም ጥፍር የወይራ ቅርንጫፍ ይይዛል። ይህ 13 ቅጠልና 13 ፍሬዎች አሉበት። ፍላጻ የጦር ምልክትና ወይራ የሰላም ምልክት በመሆኑ የንሥሩ ራስ ወደሱ ቀኝ ሲዞር ስላምን ይመርጣል እንደ ማለት ነው። በመንቁራው ውስጥ ደግሞ E PLURIBUS UNUM የሚለውን መፈክር ይይዛል። ይህም በሮማይስጥ ማለት 'አንድ ከብዙ' ነው። ከራሱ በላይ 13 ከዋክብት በሰማያዊ በስተኋላ መደብ አለ። እኚህ ከዋክብት የዳዊት ኮከብ ይሠራሉ። በፍርምባው ላይ የሚሸክመው ጋሻ እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር ነው። በማኅተሙ ጀርባ ላይ ያልተጨረሰ ሀረም (ፒራሚድ) ይታያል። ይህ 13 ደረጃዎች ሲኖሩት በመሠረቱ ላይ MDCCLXXVI ይላል። ይህ በሮማይስጥ ቁጥሮች ማለት '፼፯፻፸፮' ወይም 1776 ሲሆን በአውሮጳውያን አቆጣጠር የአሜሪካ ነጻነት አዋጅ የተፈረመበት አመት (1768 ዓ.ም.) ለማመልከት ነው። በሀረሙ ጫፍ ፈንታ 'የእግዚአብሔር ጥበቃ ዓይን' የሚባል ምልክት ይታያል። በዚሁ ዙሪያ «ANNUIT CŒPTIS» የሚለው መፈክር አለ፤ ይህም በሮማይስጥ 'የተጀመረው ተስማምቶታል' ለማለት ነው። በግርጌው ደግሞ «NOVUS ORDO SECLORUM» የሚል መፈክር እያለ ይህ ትርጉም 'የዘመናት አዲስ ሥርዓት' ነው። \n \nጥያቄ: እንደ አሜሪካ ሰንደቅ አለማ ዝንጉርጉር የሆነውን አርማ የአሜሪካ ብሔራዊ ምልክት የቱ ጋር ይቀመጣል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በፍርምባው ላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዛሬው ዕለት ኡጋንዳ ገብተዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ በፕሬዝዳንት ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ በዓለ ሲመት ላይ ለመገኘት ኡጋንዳ መግባታቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለከተው፡፡ ፕሬዝዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ባለፈው ጥር ወር ላይ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ለ6ኛ ዙር ሀገሪቱን ለመምራት ዛሬ ቃለ መሃላ ይፈፅማሉ። \n \nጥያቄ: የኡጋንዳ ፕሬዝደንት ማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ዮዌሪ ካጉታ ሙሴቪኒ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ መደብ የሚካተቱ ቋንቋዎች ምሳሌ ስጥ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: የመስቀል በዓል በዩኔስኮ መቼና በየት ተመዘገበ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአዶልፍ ሂትለር አዶልፍ ሂትለር (ጀርመንኛ Adolf Hitler አዶልፍ ሂትለ) እ.አ.አ. ከ1933 ጀምሮ የጀርመን ቻንስለር እንዲሁም ከ1934 ጀምሮ ደግሞ የጀርመን መሪም (Führer) ጭምር የነበረ ሰው ነው። ሂትለር በሚያዝያ 13 ቀን 1881 ዓ.ም. (20 አፕሪይል 1889 እ.ኤ.አ.) በዛሬይቷ ኦስትሪያ ተወለደ። በሚያዝያ 22 ቀን 1937 ዓ.ም. (30 አፕሪይል 1945 እ.ኤ.አ.) በርሊን ውስጥ ከአንድ ቀን በፊት ካገባት ሚስቱ ኤቫ ብራውን ጋር የራሱን ህይወት አጠፋ። በ1925 ዓ.ም. መጀመርያ የሂትለር ናዚ ወገን ከጓደኞቹ ወገን ጋር በራይክስታግ ምክር ቤት ትብብር መንግሥት ለመሥራት በቂ መንበሮች አልነበራቸውም። ተቃራኒዎቻቸው የኰሙኒስት ወገን 17% መንበሮች ስለ ነበራቸው የሂትለር ወገኖች የድምጽ ብዛት ሊያገኙ አልተቻላቸውም ነበር። በዚያው ዓመት ግን ከምርጫው ትንሽ በፊት የራይክስታግ ሕንጻ በእሳት ተቃጠለ። ይህ የኰሙኒስቶች ሥራ ነው ብለው የሂትለር ወገን ኰሙኒስት ፓርቲ ቶሎ እንዲከለከል አደረጉ። ስለዚህ ከምርጫው በኋላ የኰሙኒስትን መንበሮች ስለ አጡ የሂትለርም ወገኖች አሁን ከ50% መንበሮች በላይ ስላገኙ፣ የትብብር መንግሥት ሠሩና ወዲያው በድንጋጌ አቶ ሂትለር ባለሙሉ ሥልጣን አደረጉት። ሂትለር የጻፈው የርዮተ አለሙ ጽሑፍ «የኔ ትግል» (Mein Kampf) ሟርት ብቻ ነው። ለመጥቀስ ያህል፦ «ትኩረቴ ወደ አይሁዶች ስለ ተሳበ፣ ቪየናን ከበፊት በሌላ ብርሃን ለማየት ጀመርኩ። በሄድኩበት ሁሉ አይሁዶችን አየሁዋቸው፤ በብዛትም እያየኋቸው፣ ከሌሎች ሰዎች ፈጽሞ እንድለያቸው ጀመርኩ።»... «የግዛቱ (ኦስትሪያ-ሀንጋሪ) ዋና ከተማ የከሠተውን የዘሮች ውሑድ ጠላሁት፤ የዚህን ሁሉ የቼኮች፣ ፖሎች፣ ሀንጋርዮች፣ ሩጤኖች፣ ሰርቦች፣ ክሮዋቶች ወዘተ. የዘሮች ድብልቀት፤ በሁላቸውም መካከል፣ እንደ ሰው ልጅ መከፋፈል ሻገቶ፣ አይሁዶችና ተጨማሪ አይሁዶች።» በነበረው ዘረኛ አስተዳደሩ 6 ሚሊዮን የአውሮፓ አይሁዶችን እና 5 ሚሊዮን ሌሎች የተለያዩ ሀገራት ህዝቦችን (በተለይም ስላቮችን) በገፍ (በሆሎኮስት) አስጨርሷል። በሂትለር ሥር የናዚዎች ፍልስፍና በሂንዱኢዝም እንደሚገኘው በዘር የተከፋፈለ ካስት ሲስተም መመሥረት አይነተኛ ነበር። «አርያኖች» የተባሉት ዘሮች በተለይም የጀርመናውያን ብሔሮች ከሁሉ ላዕላይነት እንዲገኙ አሠቡ። ይህ ዝብረት የተነሣ በርግ ቬዳ ዘንድ በ1500 ዓክልበ. ያህል ወደ ሕንድ የወረሩት ነገዶች «አርያን» ስለ ተባሉ ነው፤ በጥንትም «አሪያና» የአፍጋኒስታን አካባቢ ስም የዘመናዊው ኢራንም ሞክሼ ነበር። በናዚዎቹ እንደ ተዛበው ግን ታሪካዊ ባይሆንም የ«አርያኖች» ትርጓሜ ጀርመናውያን ብቻ ነበሩ፤ ስላቮች (በተለይ የሩስያና የፖሎኝ ሕዝቦች) ግን አርያኖች ሳይሆኑ እንደ ዝቅተኞች ተቆጠሩ። የሂትለር እብደት እየተራመደ በ1926 ዓም የሀንጋሪ ሕዝብ ደግሞ «አርያኖች» ተደረጉ፣ በ1928 ዓም የጃፓን ሕዝብ እንኳን በይፋ «አርያኖች» ተደረጉ፤ በ1934 ዓም የፊንላንድ ሕዝብ ወደ «አርያኖች» በሂትለር ዐዋጅ ተጨመሩ። በሙሶሊኒ ሥር የፋሺስት ጣልያኖች እኛም አርያኖች ነን ቢሉም ጣልያኖች አርያን መሆናቸው በናዚዎች ዘንድ መቸም አልተቀበለም ነበር። \n \nጥያቄ: የአዶልፍ ሂትለር መንግሥት የሀንጋሪ ሕዝቦችን መቼ ነበር እንደ አርያኖች ዘር የቆጠረው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1926 ዓም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጮቄ አስደሳቹ ስፊውና ማራኪው ጮቄ በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ የተፈጥሮ የቱሪስት መስህብ ሃብቶች መካከል አንዱና ዋነኛው ሲሆን ወረዳዋ በስፋት የምትታወቅበት አስደናቂና ከፍተኛ የሆነ ተራራማ ቦታ ነው። ጮቄ ከወረዳዋ ድጓ ፅዮን ከተማ 10 ኪ/ሜ ፣ ከዞን ዋና ከተማ ከደ/ማርቆስ 61 ኪ.ሜ፣ ከክልል ዋና ከተማ ከባህር ዳር 325 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ጮቄ በእፅዋት ብዝሀነት የታደለና ከ85 በላይ አገር በቀል እፅዋት የሚበቅልበት ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ፡- ጅባራ፣ ጓሳ፣ አስታ፣ ቅርቅሃ፣ አምጃ፣ አሸንግድየ፣ ዝግባ/ግምይ/ ተጠቃሽ ናቸው። አባይን ያረገዘ ጮቄ አካባቢው የአባይ ወንዝ የውሃ ምንጭ ሲሆን የአባይ ተፋሰስ የውሃ ማማ እንደሆናና ከአባይ 9.5% ተፋሰስ ድርሻ ያለው ተራራማ የውሃ ስፍራ ነው። እንደ አጠቃላይ ሲታይ የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ (East Africa water Tower) የሆነው ጮቄ የአባይ ገባር የሆኑ 273 ትናንሽ የውሃ ጅረትና ከ23 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ወንዞች መፍለቂያ ነው። ከታላላቅ ወንዞች መካከል እናት ሙጋ፣ ግልገል ሙጋ፣ ተምጫ፣ ዝምብል፣ ትልቁ አብያ፣ ትንሹ አብያ፣ ጨሞጋ፣ ጌደብ፣ ጥጃን፣ ጠፍ፣ ጦመ፣አዝዋሪ፣ ተጠቃሽ ሲሆኑ ከነዚህም ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙት፡- ዝምብል፣ ትልቁ አብያና ትንሹ አብያ ናቸው። የጮቄ ተራራ ከባህር ወለል በላይ 4088 ሜትር አካባቢ ከፍታ ያለው በመሆኑ የጎጃም ጣራ ( The roof of Gojjam) በመባል ይታወቃል። የጮቄ ተራሮች በምስራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ዘጠኝ ወረዳዎች ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ጠቅላላ ስፋቱም 53558 ሄክታር በላይ እንደሚደርስ ጥናቶች ያመለክታሉ። ጮቄ በጣም ሰፊ ከመሆኑም የተነሳ ገና ብዙ ያልታወቁ ዋሻዎች፣ ጥንታዊ መኖሪያዎችና ያልተዳሰሱ አስደሳች የተፈጥሮ መስህቦች አሉት ፡፡ የጮቄ አካባቢ፡- በስተ ምስራቅ እነማይና እናርጅ እናውጋ፣ በስተ ሰሜን ምስራቅ 2 እጁ እነሴ በስተ ሰሜን ቢቡኝ በምዕራብ ማቻከል፣ በስተ ደቡብ ስናን እንዲሁም በስተ ደቡብ ምስራቅ ደባይ ጥላት ግን ወረዳዎች ያዋስናል። ይህ ተራራ በዋናነት በቢቡኝ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ አምስት ቀበሌዎችን ያቀፈ ነው፡፡ እነሱም፡- አሩሲ መሰሳቢያ ደድ ደብረ ፅዮን ደብረ ጊዮርጊስና ወንበር ቅዱስ ዮሐንስ ቀበሌዎች በዋናነት ይገኛሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጮቄ ወረዳ ከባህር ዳር ከተማ ምን ያህል ይርቃል?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 325 ኪ.ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዋዝንቢት ዋዝንቢት የሦስት አጽቄ አይነት ነው። የፌንጣና የአንበጣ ዘመድ ነው። ሁለንተናው ትንሽ ለጥ ይላል፤ ረጃጅም አንቴኖችም አሉት። ዋዝንቢት የሚታወቀው በሚያሰማው ድምጽ ነው። ድምጽ ማውጣትና ማሰማት የሚችለው አውራው ዋዝንቢት ብቻ ነው። የተባዕቱ ዋዝንቢት ክንፍ እንደ \"ሚዶና ሞረድ\" የሚመስል ፍርግርግ ነው። ክንፎቹን በማፋተግ ድምጽ ይፈጥራል፤ የድምጹ ቅላፄ እንደየ ዋዝንቢቱ ወገን ይለያያል። ሁለት ዓይነት የዋዝንቢት ዘፈኖች አሉ፤ የጥሪ ዘፈንና የመርቢያ ዘፈን ናቸው። የጥሪ ዘፈን ዓላማ አንስት ዋዝንቢ ለመሳብ ሲሆን ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ ነው። ለመራባት ሲባል የሚዘፈነው ድምፅ አንስቲቱ እንስቲቱን ለማቅረብ ስለሆነ ቀስ ያለና ለስላሳ ነው። አንስት ዋዝንቢት መርፌ የሚመስል ረጅም የዕንቁላል መጣያ አላት። በምድር ላይ 900 የሚያሕሉ የዋዝንቢት ዝርያዎች ይገኛሉ። አንዳንድ ዝርያ ሣርና ተክል ብቻ ሲበላ፣ ሌሎች ዝርዮች ደግሞ ነፍሳት ያድናሉ። ዋዝንቢት ሌሊት የሚነቃ ፍጥረት ነው። ብዙ ጊዜ ከፌንጣ ጋር ይመሳሰላል፣ በተለይ የመዝለያ እግሮቹ ከፊንጣ እግሮች አይለዩም። በ1963 ዓ.ም. ዶ/ር ዊሊያም ከይድ ምርመራ አድርጎ አንዲት ተባይ ዝንብ ደግሞ በተባዕቱ ዘፈን እንደምትሳብ፤ ዕጯንም እንድታስቀምጥበት ቦታውን ለማወቅ እንደሚጠቅማት አገኘ። የመርባትን ድምጽ በመጠቀም የአስተናጋጇን ቦታ ለምታገኝ የተፈጥሮ ጠላት ይህች መጀመርያ ምሳሌ ሆነች። ከዚያ በኋላ ብዙ የዋዝንቢት ወገኖች ይህችን ተባይ ዝንብ ሲሸክሙ በምድር ላይ ተገኝተዋል። በእስያ በተላይም በቻይና ዋዝንቢት ዝነኛ ለማዳ እንስሳ ሆኖ መያዙ እንደ መልካም እድል ይቈጠራል። የተያዘ ዋዝንቢት ሁሉ ማናቸውም አትክልት ወይም ሥጋ ቢሰጥ ይበላል። በአንዳንድ ባሕል ደግሞ ዋዝንቢት እንደ ምግብ ሊበላ ይችላል። \n \nጥያቄ: የዋዝንቢት ነፍሳት መለያው ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሚያሰማው ድምጽ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nነሐሴ ፳፯ ነሐሴ ፳፯ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፶፯ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነሉቃስ ፱ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ዮሐንስ ደግሞ ፰ ዕለታት ይቀራሉ። ፲፮፻፶፰ ዓ/ም ለሦስት ቀናት የጋየውና አስር ሺህ ሕንጻዎችን ያወደመው የሎንዶን ትልቁ እሳት ተነሳ። ፲፯፻፵፬ ዓ/ም የምዕራብ አውሮፓ አገራት ዘመን አቆጣጠራቸውን በለወጡ በሁለት መቶ ዓመታቸው፣ ብሪታንያ የጎርጎራዊ ዘመን አቆጣጠርን ተቀበለች። ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በጠላት ወረራ ዘመን የሸዋ አርበኞች ቡልጋ ላይ ተሰባስበው የልጅ ኢያሱን ልጅ መልአከ-ፀሐይ ኢያሱን አነገሡ። አዲሱ 'ንጉሥ' ወዲያው የአርበኞች መሪ ለነበሩት ባላምባራስ አበበ አረጋይ የራስነት ማዕርግ ሰጠ። መልአከ-ፀሐይ ኢያሱ መስከረም ፳፬ ቀን ፲፱፻፴፩ ዓ/ም አረፎ አንኮበር አካባቢ በሚገኘው ዞማ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ጃፓን በተሸናፊነቷ እጇን ሰጠች። ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ነጻነትን አስከትሎ በጃዋሃርላል ኔህሩ ምክትል ፕሬዚደንትነት የሚመራ የሕንድ ጊዜያዊ መንግሥት ተመሠረተ። ፲፱፻፺ ዓ/ም የርዋንዳን ፍጅት አስከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያቋቋመው የወንጀለኛ ፍርድ ቤት ጃን ፖል አካዬሱ የተባለውን የቀድሞ ከንቲባ ላይ ፍርዱን የወንጀለኛነት ፍርድ ፈረደበት። \n \nጥያቄ: ነሐሴ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ/ም ሕንድ ከአንግሊዝ ነጻነቷን እንዳገኘች በማን የሚመራ ጊዜያዊ መንግሥት አቋቋመች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በጃዋሃርላል ኔህሩ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nእንደ ፕላቶ ዘገባ፣ የሶቅራጠስ እናት ፌናርት የተሰኘች አዋላጅ ነበረች። ሶቅራጠስ እናቱ ሴቶች ልጅ እንዲወልዱ እንደምትረዳ ሁሉ እርሱ ደግሞ ሰዎች አዳዲስ አሳቦችን እንዲወልዱ ለመርዳት እንደሚሞክር መናገሩ ይጠቀሳል። የሶቅራጠስ አባት ድንጋይ አናጢ የነበረው ሶፍሮኒስከስ እንደነበር ይጠቀሳል። ሶቅራጠስ በዘመኑ ድሃ የነበረ ሲሆን ለዚህ ምክንያቱ ከገንዘብ ይልቅ እውቀት ይበልጣል ብሎ ስለሚያምን ነበር። ሶቅራጠስ ስራ እንደማይሰራና በፍልስፍና ሃሳብና ክርክር ጊዜውን እንደሚያሳልፍ ፕላቶ ዘግቦት ይገኛል። ዛንቲፕ የተሰኘች ከርሱ በዕድሜ በጣም የምታንስ ሴትን አግብቶ ሶስት ልጆች እንደነበሩት ፕላቶ ጽፏል። ሶቅራጠስ 70 ዓመት በሞላው ጊዜ የአቴና መንግስት እንዲያዝና ለፍርድ እንዲቀርብ አደረገ። በወቅቱ ሁለት ክሶች ሲቀርቡበት አንደኛው \"በትምህርትህ ወጣቱን አበላሽተሃል\" የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ \"ለግሪክ ጣዖታት አልተገዛህም\" የሚል ነበር። እንደ ፕላቶ ዘገባ ግን ሶቅራጠስ የግሪክ ጣኦታት አምላኪ ነበር። በአንድ አንድ ተመራማርወች ዘንድ የአቴንስ መንግስት ያቀረባቸው ክሶች በውሸት ላይ የተመሰረቱ ናቸው። የሆኖ ሆኖ፣ ክሪቶ የተሰኘው የፈላስፋው ጓደኛ ለጠባቂወቹ ጉቦ በመስጠት እንዲያመልጥ ሁኔታውን አመቻችቶ ነበር። ሶቅራጠስ ግን እምቢ በማለት ቀረ እንጂ አላመለጠም። ሶቅራጠስ ለፍርድ በቀረበ ጊዜ ሰፊ የሆነ የመከላከያ ክርክር በማቅረብ የአቴናን መንግስት ክስ ውድቅ ለማደርግ ሞክሯል። ከዚህ በኋላ ዳኞቹ ምን አይነት ቅጣት እንዲበይኑበት እንደሚፈልግ ሲጠይቁት፣ ለአቴና ህብረተሰብ ካበረከተው ጥሩ ተግባራቱ አንጻር በቀሪው ዘመኑ ሁሉ ነጻ እራት እንዲያመጡለት ተናገረ። ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ወይ በቅጣት እንዲለቀቅ ወይንም ደግሞ እንዲገደል የእጅ ምርጫ አደረገ። ውጤቱም ሶቅራጠስ እንዲገደል የሚል ሆነ። ይሁንና ሶቅራጠስ ሞትን አይፈራም ነበር። ሞቱን ለማስቀረት ይቅርታም ሆነ ሌላ ማባበያ አላቀረበም። በርሱ ሥነ ምግባር መሰረት ላመነበት ነገር እስከመጨረሻ መቆሙ ሰናይ ድርጊት ነበር። ስለሆነም ሄምሎክ የተሰኘ መርዝ ጠጥቶ እንዲሞት ስለታዘዘ፣ መርዙን በመጠጣት አለፈ። \n \nጥያቄ: የሶቅራጥስ አባት ሙያ ም ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ድንጋይ አናጢ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጨኖ ጨኖ ግራጫ ቢጤ የሆነ፣ ፈርጠም ያለ፣ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እስከ ደቡብ አፍሪቃ፣ በተጨማሪም በኮንጎ ደኖች የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው ዓይነት ጨኖ የፀጉሩ ቀለም ግራጫና ጥቁር የሆነ፣ ፊቱ የጠቆረ ሰማያዊ የሆነ፣ አገጭና አንገቱ ነጭ ነው። የወንዶቹ ክብደት እስከ 12 ኪ.ግ. ሲሆን፤ አማካዩ 4.5 ኪ.ግ ይመዝናሉ። ጨኖ የደን ዝንጀሮ ነው። የደን ዝንጀሮች ብዙ ጊዜ ከዝናባማ ሥፍራዎች ደኖች ውጪ አይገኙም። ጨኖ ግን ከነዚህ ደኖች ውጪም በሚገኙ ደኖች ውስጥ ይኖራል። በኢትዮጵያ፣ በጎደሬ ደን ውስጥ፣ ቴፒ አጠገብ ሜጢ አካባቢ ይገኛሉ። በተራራማ ሥፍራዎች ደኖችም እስከ 3000 ሜትር ከፍታ ድረስ ይገኛሉ። እጅጉን በዛፍ ላይ የሚገኝ ዝንጀሮ ነው። የሚገኘው በደን ዛፎች ግማሽ ላይ ነው። በተለያዩ ዓይነት ተግባሮች መገለጫ የሚሆኑ ሰባት ዓይነት ድምፆች አሏቸው። በቡድናቸው ውስጥ የሚታየው አብዛኛው ፀብ፣ በዋናው ወንድና ለአካለ መጠን ባልደረሱና ጎረምሳ ወንዶች መሃል የሚታየው ነው። በሴቶቹና ሕፃናትን በሚገድሉ ወንዶች መኻከል ከባድ ግጭት ያድጋል። በቡድኖች መኻከል የሚደረግ ግጭት የሚሆነው አልፎ አልፎ ነው። እንዲህ ያለ ግጭት የሚነሳው በድንበር አካባቢ በምግብ ሽኩቻ የተነሳ ነው። የእርግዝና ጊዜአቸውን 140 ቀን ነው። የልጆቻቸውን እድገትም ቀስ ያለ ነው። ከወለዱ ወዲያ ለሚቀጥለው እርግዝና 15 ወራት መቆየት አለባቸው። \n \nጥያቄ: ጨኖዎች ከወለዱ በኃላ ለቀጣይ እርግዝና ምን ለያህል ጊዜ መቆየት አለባቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 15 ወራት ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎግል የተወሰኑ ደንበኞችን የግል ተንቀሳቃሽ ምስል በስህተት ለሌሎች በማጋራቱ ይቅርታ ጠይቋል። ችግሩ ደንበኞች የግል ገፃቸውን ለመለየት የሚስችለውን ምስል ለመጫን በሚያስችለው ክፍል ላይ የተፈጠረ መሆኑ መሆኑን ኩባንያው አስታውቋል። ስህተቱ ለአራት ቀናት ማለትም ካሳለፍነው ጥቅምት 21 እስከ 25 ቀን 2019 ድርስ የቆየ መሆኑ ነው የተገለጸው። በዚህ ወቅትም በችግሩ የተጠቁ ደንበኞች የራሳቸው ያልሆነ አሊያም ተገቢውን ጥራት ያላሟላ ተንቀሳቃሽ ምስል የደረሳቸው መሆኑ ተጠቁሟል። ይሁን እንጂ ኩባንያው ችግሩ በምን ያህል ደንበኞቹ ላይ ተከስቶ እንደነበር ከመግለፅ ተቆጥቧልል። አሁን ላይ ችግሩ መስተካከሉን የገለጹት የኩባንያው ቃል አቀባይ፥ለተፈጠረው ስህተት ደንበኞችን ይቅታ ጠይቀዋል። በቀጣይ መሰል ችግሮች እንዳይከሰቱ ጥልቅ ምርመራዎችን በማካሄድ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅ የሚደረግ መሆኑ ተጠቁሟል። ምንጭ፡-ቢቢሲ   \n \nጥያቄ: ከጥቅምት 21 እስከ 25 ቀን 2019 ባሉ ቀናት የደንበኞችን የግል ተንቀሳቃሽ ምስል በስህተት ለሌሎች ያጋራው ድርጅት ማን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጎግል ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nአባይ ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል። ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣ የጩኸቱን ግርማ፣ ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል”። ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው። ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል። የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር። ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀት መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል። ከግሸን ተራራ ስር፣ ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ, በግሸን ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል። አባይ ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል ቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም። በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም። \n \nጥያቄ: አባይ በኢትዮጵያ ምድር ሲጓዝ ምን ያህል ርቀት ይሸፍናል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 800 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: ከፀሀይ የመጠነ ቁስ ጥንቅሮች መካከል የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም መጠን ምን ያህል ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ 1% ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: በአርባ ምንች የሚገኘው ብሔራዊ ፓርክ የትኛው ነው ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ1930 እ.ኤ.አ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ አዲስ አበባ ተብላ የተሠየመችው እቴጌ ጣይቱ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፰፻፸፱ (1879) ዓ.ም. ፍልውሃ ፊን-ፊን ወደሚልበት መስክ ወርደው ሳሉ ከዚህ በፊት አይተዋት የማያውቋት አንዲት ልዩ አበባ አይተ ስለማረከቻቸው ቦታውን ‹‹አዲስ አበባ!›› አሉ ይባላል። አዲስ አበባ (ኣዲስ ኣበባ) ኢትዮጵያ ዋና ከተማ ስትሆን በተጨማሪ የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ እንዲሁም የብዙ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቅርንጫፎችና ሌሎችም የዓለም የዲፕሎማቲክ (የሰላማዊ ግንኙነት) ልዑካን መሰብሰቢያ ከተማ ናት። ራስ-ገዝ አስተዳደር ስላላት የከተማና የክልል ማዕረግ ይዛ ትገኛለች። አብዛኞቹን የሀገሩ ቋንቋዎች የሚናገሩ ክርስቲያኖች እና ሙስሊሞች የሚኖሩባት ከተማ ናት። ከባሕር ጠለል በ2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኘው ከተማ በግምት 2,757,729 በላይ ሕዝብ የሚኖርባት በመሆኗ የሀገሪቱ አንደኛ ትልቅ ከተማ ናት። ከተማዋ እቴጌ ጣይቱ በመረጡት ቦታ ማለትም በፍል ውሐ አካባቢ ላይ በባላቸው በዳግማዊ ምኒልክ በ፲፰፻፸፰ (1878) ዓ.ም. ተቆረቆረች። የሕዝቧ ብዛት በያመቱ 8% (ስምንት በመቶ) እየጨመረ አሁን አምስት ሚሊዮን እንደሚደርስ ይገመታል። ከእንጦጦ ጋራ ግርጌ ያለችው መዲና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መገኛ ሆናለች። ይህም በመስራቹ የቀድሞው ንጉሠ-ነገሥት ስም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል ነበር። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ ዋና መዲና ማናት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አዲስ አበባ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሚያዝያ ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፵ ኛው ዕለትና የወርኅ ፀደይ (በልግ) ፴፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፻፳፮ ቀናት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመን ማርቆስ ደግሞ ፻፳፭ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ። ፲፰፻፺ ዓ/ም - በጣልያ አበጋዙ ባቫ-በካሪስ ብዙ መቶ ሰልፈኞች በመድፍ ገደላቸው። ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ የእንግሊዝን አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ። ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ። ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በሩሲያኖች የተገነባው የአሰብ የነዳጅ ማጣሪያ ማዕከል የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ እራሳቸውን ከሥልጣናቸው አስወገዱ። ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - አቶ ለገሰ ዜናዊ አስረስ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር አድዋ ላይ ተወለዱ። \n \nጥያቄ: ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከስልጣን ራሳቸውን መቼ አገለሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: የብልሃርዝያ በሽታ አምጪ ትሎች ከምን ይመነጫሉ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሊቢያ ኦይል ከኢትዮጵያ የተሰናበተውን ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድ በመግዛት የኢትዮጵያን የነዳጅ ገበያ የተቀላቀለው በ2000 ዓ.ም. ነበር፡፡ ኩባንያው ኢትዮጵያ ውስጥ 143 የነዳጅ ማደያዎች ሲኖሩት፣ 24 በመቶ የገበያ ድርሻ አለው፡፡ ኩባንያው በየዓመቱ ዘጠኝ ማደያዎች በመክፈት እ.ኤ.አ. በ2020 የነዳጅ ማደያዎቹን ቁጥር 185 ለማድረስ፣ የገበያ ድርሻውን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኩባንያው ዓመታዊ ሽያጭ 13 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡ ሊቢያ ኦይል 50 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ የአቪዬሽን ነዳጅ ዲፖ ማስፋፊያና በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የነዳጅ ዲፖ የኤታኖል ማደባለቂያ ገንብቷል፡፡ ኩባንያው እስከዛሬ እንደ አዲስ የገነባቸው ስምንት የነዳጅ ኩባንያዎችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ለግንባታ የሚሆን ቦታ የማግኘት ችግር በመኖሩ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ዘካሪያስ፣ ከሼል ኩባንያ ግዢ ጋር የተፈጠረው የታክስ ክርክር የኩባንያውን ዕድገት እንደጎተተው ያስረዳሉ፡፡ የታክስ ክርክሩ እልባት ያገኘ በመሆኑ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋፋት ቆርጦ መነሳቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል ባለፈው ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ አዳዲስ የሞተር ዘይትና ቅባቶችን አስተዋውቋል፡፡ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ የሊቢያ ኦይል የነዳጅ ማደያ ባለቤቶች፣ የሊቢያ ኦይል ምርቶች አከፋፋዮችና የትራንስፖርት ኩባንያዎች የሊቢያ ኦይል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ሙስባሕ ኤልቤሽቲ ሽልማቶች አበርክተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሼል ኢትዮጵያ ሊሚትድን የገዛው ድርጅት ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሊቢያ ኦይል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: አሁን በዚምባቡዌ የሾና ሰዎች ስንት ስንተኛ ይሆናሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አራት አምስተኛ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nበምዕራቡ ዓለም ውስጥ ስለ ፀሓይ ሳይንሳዊ መግለጫ ለመስጠት ከቻሉ ቀዳሚ ሰዎች አንዱ ግሪካዊው ፈላስፋ አናክሳጎራስ ነበር። ፀሓይ በእሳታዊ ነበልባል የምትንቀለቀል እጅግ ግዙፍ የብረት ኳስ እንጂ የሄሊዮስ ሰረገላ እንዳልነበረች በምክንያት የተደገፈ ትንተና አቀረበ። ይህንን እንደ ኑፋቄ የተቈጠረ ሐተታ በማስተማሩም ታሰረ፤ በሞት እንዲቀጣም ተፈርዶበት ነበር፤ በፔሪክልስ አማላጅነት እንዲፈታ ተፈቀደለት እንጂ። የባለሥልጣናት መዓት የወደቀበት ሌላው የሳይንስ ሊቅ ኒቆላዎስ ቆጰርኒቆስ ነበር። በ16ኛው ምእት ውስጥ የኖረው ቆጰርኒቆስ ምድር ፀሓይን በቀለበትማ ምሕዋር ትዞራለች እንጂ፣ ፀሓይ ምድርን አትዞርም የሚል ኀልዮ አቅርቦ ነበር። በ17ኛው ምእት ጋሊሌዮ በቴሌስኮፕ ለታገዘ የፀሓይ ጥናት ፈር-ቀዳጅ ሊቅ ኾነ። አይዛክ ኒውተን ደግሞ በፕሪዝም አማካይነት የፀሓይ ብርሃን ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ብርሃናት የተጠናቀረ እንደኾነ አሳየ። 19ኛው ምእት ዊሊያም ኸርሽል የኢንፍራሬድ ጨረር ግኝት ባለቤት የኾነበት፣ በስፔክትሮስኮፕ ስለ ፀሓይ የሚደረገው ጥናትም እጅግ የመጠቀበት ምእት ኾነ። ዛሬ በብዙ አገሮች ልማድ ፀሓይ እንደ ባህላዊ ምልክት ትታያለች። ለምሳሌ በሜክሲኮ ኪነ ጥበብ አበክራ የምትታይ ሞቲፍ በመባል ትታወቃለች። በኛ ሥርዐተ-ፀሓይ ዋናዋ ትልቅ አካል ራሷ ፀሓይ ናት። በመላው ሥርዐተ-ፀሓይ ውስጥ ከሚገኘው ክብደት 99.86% የፀሓይ ነው። ለምሳሌ ከታላቁ ፈለክ ከጁፒተር ሲነጻጸር የፀሐይ ክብደት 1000 ዕጥፍ ይበልጣል። የፀሓይ ክብደት ከምድር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ ይበልጣል። በጣም ግዙፍ እና ከባድ የኾነችው ኮከብ ከምድር ያለችበት ርቀት በጣም የሚያስደንቅ ነው። በምድር እና በፀሓይ መካከል ያለው ርቀት የምድርን ዳያሜትር በ12,000 ጊዜ ይበልጣል። ብርሃን ይህን ርቀት ለመጓዝ 8.5 ደቂቃ ይፈጅበታል። \n \nጥያቄ: ፕሪዝም በመጠቀም የፀሓይ ብርሃን የልዩ ልዩ ቀለማት ጥርቅም መሆኑን ያወቀው ማን ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ አይዛክ ኒውተን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሮማንሽ ሮማንሽ ወይም ሩማንች (Rumantsch) ከስዊስ አገር 4 ብሔራዊ ቋንቋዎች 1ዱ ሆኖ ሌሎቹ 3 ጀርመንኛ ጣልኛና ፈረንሳይኛ ናቸው። ከሮማይስጥ የታደገ ቋንቋ በመሆኑ የሮማንስ ቋንቋ ቤተሠብ አባል ነውና በተለይ የሚመስለው ፈረንሳይኛ ወይም እጣልኛ ነው። የሚናገረው በግራውብውንደን (ግሪዞን) ካንቶን ስዊስ በሚኖሩ 60,000 ሰዎች ነው። ይህ ከስዊስ አገር ሕዝብ ብዛት 1% ብቻ ሲሆን ከስዊስ አገር ብሔራዊ ቋንቋዎች ሁሉ ትንሹ ነው። እንኳን በስዊስ አገር ከሚኖሩት ስርቦ-ክሮዌሽኛ ተናጋሪዎች ቁጥር ብዛት (111,000) በግማሽ ያንሳል። በስሜን እጣልያ አገር ዛሬ ለሚናገሩ ቋንቋዎች ለፍሪዩልያንና ለላዲን ቅርብ ዘመድ ነው። \n \nጥያቄ: ሮማንሽ ቋንቋ በስዊስ ምን ያህል ተናጋሪዎች አሉት?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 60,000 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ በሃገራችን ኢትዮጵያ ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ ጻድቅ ናቸው። ጻድቁ የተወለዱት በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ሲሆን ወላጆቻቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ቅድስት እድና ይባላሉ ። የተወለዱበት አካባቢም ሮም ነው ። ስማቸው ብዙ ዓይነት ነው። ወላጆቻቸው ዘሚካኤል ሲሏቸው በበርሃ ገብረአምላክ ተብለዋል። በኢትዮጵያ ደግሞ አረጋዊ ይባላሉ። አቡነ አረጋዊ ምንም የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በልጅነታቸው መጻሕፍትን ተምረው ነበርና ጠፍተው ገዳም ገቡ። በዚያም በገዳመ ዳውናስ (ግብጽ) የታላቁ ቅዱስ ጳኩሚስ ደቀ መዝሙር ሆነው ከነ አባ ቴዎድሮስ ጋር ሥርዓተ መነኮሳትን ተምረዋል። ከመነኮሱ ከዓመታት በኋላም ወደ ሃገራቸው ሮም ተመልሰው በማስተማር ሰባት ያህል የቤተ መንግሥት ሰዎችን ወደ ምናኔ ማርከዋል። \"የት ልሒድ?\" ብለው ሲያስቡም ቅዱስ መልአክ በክንፉ ጭኖ ወስዶ ኢትዮጵያን አሳያቸው። ተመልሰውም ለስምንት ባልንጀሮቻቸው \"ሃገርስ ባሳየኋችሁ! ሐዋርያ ሳያስተምራት በሕጉ በሥርዓቱ ጸንታ የምትኖር\" ብለው ከስምንቱ ጋር ከቃልኬዶን ጉባዔ በኋላ በ፬፻፶፩ ዓም ወደ ኢትዮጵያ መጡ ። ከዘጠኙ ቅዳሳን ወደ ኢትዮጵያ ከሮምና ከመካከለኛው ምሥራቅ ከፈለሱት አንዱ አቡነ አረጋዊ ናቸው ። በዚህ ጊዜም እናታቸው ቅድስት እድናና ደቀ መዝሙራቸው አባ ማትያስ አብረው ነበሩ። ወደ ሃገራችን የመጡ በአራት መቶ ሰባዎቹ አካባቢ ሲሆን አልዓሜዳ በክብር ተቀብሏቸዋል። በቤተ ቀጢን (አክሱም) ተቀምጠውም መጽሐፍትን እየተረጎሙ ወንጌልን እየሰበኩ ቆይተዋል ። አቡነ አረጋዊ ለብዙ ጊዜ በዓት ፍለጋ ደክመዋል ። በመጨረሻም ደብረ ዳሞ ማረካቸዋለች ። ዘጠና ዘጠኝ አመት ሲሞላቸው ጌታ በመንፈቀ ለሊት ተገልጾ ምድራዊ መንግስትህን ትተህ ስላገለገልከኝ ህልፈት ሽረት የሌለባት ሰማያዊ መንግስቴን አወርሰሃለሁብሎ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ በስምህ የተማጸነውን እስከ አስራ አምስት ትውልድ ድረስ እምርልሃለሁ አንተም ከሞት ገጽ ትሰወራለህ ብሎ ተስፋቸውን ነገራቸው፡፡ እሳቸው መነኮሳቱን ሰብስበው ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም ብለው ነግረዋቸው አበምኔት (የገዳም አባት ወይም አለቃ) ሾመውላቸው ጥቅምት አሥራ አራት ቀን በዚያው በደብረ ዳሞ ተራራ በስተምስራቅ አቅጣጫ እንደሄኖክ እንደ ኤልያስ ተሰውሯል ፡፡ \n \nጥያቄ: አቡነ አረጋዊ ከብዙ ፍለጋ በኋላ በስተመጨረሻ በየት ተቀመጡ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ደብረ ዳሞ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሳምሰንግ ኩባንያ በተጠናቀቀው የፈረንጆች ዓመት 6 ነጥብ 7 ሚሊየን አምስተኛ ትውልድ (5ጂ) ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ዘመናዊ ስልኮችን ለደንበኞቹ ሸጧል። ኩባንያው በዓመቱ 4 ሚሊየን 5ጂ ስማርት ስልኮችን ለመሸጥ አቅዶ 6 ነጥብ 7 ሚሊየን ስልኮችን በተሳካ ሁኔታ መሸጡን አስታውቋል። ይህን ተከትሎም ኩባንያው 5ጂ ኢንተርኔት የሚጠቀሙ ስልኮችን በደንበኞች እጅ በማድረስ ከተቀናቃኞቹ የተሻለው ሆኗል። በዓመቱ ለገበያ ከቀረቡ ዘመናዊ ስልኮች ውስጥ ሳምሰንግ ኤስ ኤስ ኤን አል ኤፍ የተሰኘው ሞዴል ብባዛት መሸጡ ተመላክቷል። እንዲሁም ሳምሰንግ ጋላክሲ ኖት 10ጂ፣ 10+5ጂ፣ ኤ90 5ጂ እና የመተጣጠፍ ችሎታ ያለው ጋላክሲ 5ጂ በዓመቱ ለገበያ የቀረቡ ሞዴሎች ናቸው። ሳምሰንግ በአዲሱ የፈረንጆች ዓመትም ለኩባንያው የመጀመሪያ የሆነውን ኤስ6 የተሰኘ 5ጂ ኢንተርኔት የሚጠቀም ታብሌት ለገበያ እንደሚያቀርብ ገልጿል።   ምንጭ፦ ሲ ኤን ኤን \n \nጥያቄ: ሳምሰንግ በዓመቱ ወደ ገበያ ይዟቸው የወጡት ሞዴሎች ምን ምን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሳምሰንግ ጋላክሲ ኖት 10ጂ፣ 10+5ጂ፣ ኤ90 5ጂ እና የመተጣጠፍ ችሎታ ያለው ጋላክሲ 5ጂ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየእብድ ውሻ በሽታ የእብድ ውሻ በሽታ የየቫይረስ በሽታ ሆኖ ከፍተኛ የየአንጎል መጉረብረብን በሰዎች እና በሌሎች ደመ-ሞቃት እንስሳት ላይ የሚያስከትል ነው። ቅድሚያ ምልክቶቹ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠልን ያካትታል። እነዚህ ምልክቶች ከሚከተሉት አንድ ወይም የበለጡ ምልክቶች አስከትለው ይመጣሉ- ሃይል የታከለባቸው የሰውነት እንቅስቃሴዎች፣ ከቁጥጥር ወጭ የሆ መሸበር፣ የውሀ ፍራቻ, የሰውነት ክፍለን ለማንቀሳቀስ አለመቻል፣ ግራ መጋባት፣ እና ህሊናን መሳት። ምልክቶቹ ከታዩ በኋላ፣ የእብድ ውሻ በሽታ በአብላጫው ሁልጊዜ ሞትን ያስከትላል። በበሽታው በመያዘዎ እና ምልክቶቹ መታየት የሚጀምሩበት የጊዜ ገደብ በአብዛኛውን ጊዜ ከአንድ እሰከ ሶስት ወራት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው። ሆኖም ግን፣ ይህ የጊዜ ገደብ ከሳምንት ባነሰ እና ከአመት በበለጠ ጊዜ ሊለያይ ይችላል። የጊዜ ገደቡ የሚወስነው የበሽታ አምጭው ረቂቅ ህዋስ ወደ የማዕከላዊ የነርብ ስርዓትለመድረስ በሚፈጅበት እርቀት ነው። የእብድ ውሻ በሽታ በአለም ዙሪያ በአመት ከ26,000 እሰከ 55,000 ሞቶች ምክንያት ነው። ከ95% በላይ እነዚህ ሞቶች የተከሰቱት በኢሲያ እና አፍሪቃነው። የእብድ ውሻ በሽታ ከ150 ሀገራት በላይ እና ከአንታርቲካ በቀር በሁሉም አሀጉራት ይገኛል። ከ3 ቢሊዮን ሰዎች በላይ የእብድ ወሻ በሽታ በሚከሰትበት የአለማችን ከፍሎች ውስጥ ይኖራሉ። እጅግ በአብዛኛው አውሮፓ እና አውስትራሊያ፣ የእብድ ወሻ በሽታ የሚገኘው በሌሊት ወፎች ላይ ነው። \n \nጥያቄ: እብድ ውሻ ምልክቱ ምንድን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ትኩሳት እና በተነከሱበት ቦታ ማሳከክ/ማቃጠል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nሚያዝያ ፲፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፳፰ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፳፫ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፴፰ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፴፯ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ። ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ታሽኬንት በትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ክስተት ስትወድም ሰብ ስምንት ሺ መኖሪያ ቤቶች በመጥፋታቸው ከሦስት መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎቿ መኖሪያ ቢስ ሆነዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በሼክ ሞሀመድ ማህሙድ ኤል ሳዋ የተመራ የሳዑዲ አረቢያ\tልዑካን ቡድን ለአጭር ጉብኝት አዲስ አበባ ገባ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ከደርግ በተላለፈ ትእዛዝ መሠረት፣ የፖሊስ አለቆች፤ የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ታሠሩ። ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር። \n \nጥያቄ: የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ፣ የፖሊስ አለቆች ከደርግ በተላለፈ ትህዛዝ መቼ ታሠሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጎፋ ብሔረሰብ ባህላዊ ምግብ ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሸንዴራ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኋንግ ዲ ኋንግ ዲ (ቢጫው ንጉሥ) በቻይና ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ የቻይና ሕዝብ አባትና ንጉሥ ነበረ። የቤተሠቡ ስም «ጎንግሱን» የተሰጠው ስም «ሽወንዩወን» ነበር ይባላል። አባቱ ሻውድየን ተባለ። የተወለደው ሾው ጪው በተባለ ሥፍራ በጩፉ ሲሆን በኋላ ነገዱን ወደ ዥዎሉ ወሰደው፤ በዚያ ገበሬ ሆኖ ድብ፣ ነብርና ባለክንፍ አንበሣ የመሰለ ፍጡር አንዳስለመደ የሚል ትውፊት አለ። ያንጊዜ የኋንግ ዲ ወገን እና የያንዲ (ዩዋንግ) ወገን ለቢጫው ወንዝ ሸለቆ ተወዳዳሪዎች ነበሩ። ሦስተኛ ወገን - የሊ ሕዝብና ንጉሣቸው ቺ ዮው - ደግሞ ጠላቶቻቸው ሆኑ። ሦስት ውግያዎች ተከተሉ። በመጀመርያው የቺ ዮው ሥራዊት ያንዲውን አሸነፈው። ከዚያ ያንዲው ተሸንፎ ወደ ኋንግ ዲ ሸሸ። በሁለተኛው የዥዎሉ ውግያ ኋንግ ዲ እና ቺ ዮው ተጋጠሙ። በዚህ ውግያ ቺ ዮው ጉምን በጥንቆላ ፈጥሮ ኋንግ ዲ እንደገና በተነው፣ ብዙም ሌሎች ጉድ ሥራዎች እንደ ተከሠቱ የሚል ትውፊት አለ። ቺ ዮው በዚህ ውግያ ቢሸነፍም፣ የኮርያ ሕዝብና የህሞንግ ሕዝብ ዛሬውንም እንደ ቅድማያታቸው ይቆጥሩታል። በሦስተኛው የባንጯን ውግያ፣ ኋንግ ዲ በያንዲው ላይ ድል አደረገ። ከዚያ በኋላ ወገኖቻቸው ተባብረው የኋሥያ ብሔር (የቻይና ሕዝብ ቅድማያቶች) ፈጠሩ። ኋንግ ዲ በይፋ የቻይና ንጉሥነት ማዕረግ ወሰደ፤ የዘውድና ቤተ መንግሥት ሥርዓት ጀመረ። ከዚህ በተረፈ ኋንግ ዲ ጋሪና መርከብ እንደ ፈጠረ ይጻፋል። ደግሞ ምኒስትሩ ጻንግችየ መጀመርያ የቻይና ጽሕፈት ፈጠረ፤ የኋንግ ዲ ሚስት ሌዙም ልብስ ከሃር ትል እንዴት እንደሚሠራ አሳየች። የህክምና መጽሓፍ ኋንግዲ ኔጂንግ ሌሎችንም መጻሕፍት እንደ ጻፈ ይታመናል። ከዚህ በላይ የቻይና ስነ ፈለክና የቻይና ዘመን አቆጣጠር ፈጠረ። ስለ ኋንግ ዲ ብዙ ሌሎች ትውፊቶች አሉ። መጀመርያ ሚስቱ ሌዙ ተከታዩን ሻውሃውን ወለደች። 3 ሌሎች ሚስቶች እነርሱም ፋንግሌ፣ ቶንግዩ እና ሞሙ ነበሩት። በተለመደው ታሪክ ዘንድ ለ99 አመት ነገሠ። ታላቅ መቃብሩ በያንአን ከተማ ሲገኝ እስከ ዛሬ ድረስ በየአመቱ በሥነ ስርአት ይከብራል። \n \nጥያቄ: ስለ ኋንግ ዲ የሚነገረው ትውፊት ምንድን ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ድብ፣ ነብርና ባለክንፍ አንበሣ የመሰለ ፍጡር አንዳስለመደ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nለሴት ልጆች ትምህርትን አጥብቃ በመስራቷ እ.ኤ.አ. በ 2003 በደቡብ አፍሪካ የተቀበለችውን የአማኒታሪ ሽልማትን (አፍሪካዊ አጋርነት ለወሲባዊ እና ስነተዋልዶ ጤና እና የሴቶች መብቶች ) ጨምሮ ለፀረ-ኤድስ እንቅስቃሴ ባገለገለችበት ወቅት በርካታ ብሔራዊ እና ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን አግኝታለች ። ፡፡ ወ / ሮ የትነበርሽ ከአካዳሚክ ህይወቷ ባሻገር በበጎፈቃደኝነት ከ 20 በላይ ድርጅቶች ውስጥ ያገለገለች ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በኢትዮጵያ ዓይነ ስውራን የሴቶች ክንፍ ማህበር ለ 4 ዓመታት (እ.ኤ.አ. ከ 2003 እስከ 2007) መርታለች ፡፡ ከዚያም በመቀጠል የአካል ጉዳተኞች ኢኮኖሚያዊ መብትን ጨምሮ በተለያዩ የልማት መርሃ ግብሮች ውስጥ እንዲካተቱ ለማበረታታት የኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞችና የልማት ማዕከል (ኢ.ሲ.ዲ.ዲ.) የተባለ አገር በቀል ድርጅት ለማቋቋም ወሰነች ፡፡ከ2016 ጀምሮ ደግሞ ቀደም ሲል በዓለምአቀፍ አምባሳደሮች ቦርድ አባልነት ወክላው ከነበረው የአካል ጉዳተኞች እና ልማት ብርሃን ለኣለም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ላይ ትሰራለች ፡ የትነበርሽ ንጉሴ የአካል ጉዳተኞችን መብትና ማካተት በማስተዋወቋ እና ሙሉ አቅማቸውን እንዲገነዘቡ የሚያስችላቸው አነቃቂ ሥራ በመስራት በማህበረሰቡ ውስጥ የአስተሳሰብ ለውጥ በመፍጠሯ እ.ኤ.አ. በመስከረም ወር 2017 ላይ የተባበሩት መንግስታት ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ ፣ “አማራጭ የኖቤል ሽልማት” ፡ እና የአሜሪካ የአካባቢ ጠበቃ ጋር በመጋራት ተሸላሚ ሆናለች። ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን በማሸነፏ እና በሄለን ኬለር ሽልማት መንፈስ የተበረታታችው የትነበርሽ ንጉሴ በህይወታቸው እና በስራ መስካቸው ታላቅ ውጤት ያስመዘገቡ የአካል ጉዳተኛ ሴቶችን ለማክበር ከብርሃን ለኣለም ጋር በመሆን ‹የእርሷ ችሎታዎች ሽልማትን› ኣስጀምራለች፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የዓይነ ስውራን የሴቶች ክንፍ ማህበር ውስጥ ለስንት አመት ሰራች?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ለ 4 ዓመታት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ለወጣት ለአዛውንት የሚመቹ ደግ እናት፡፡ በኢትዮጵያ የሚድያ ታሪክ ስም ያተረፉ፡፡ ለምርምር የማይደክሙ፡፡ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን እነሆ ታሪካቸውን አቀረበ፡፡ ጋዜጠኛዋ በ79 አመታቸው ሀምሌ 14 2013 ህይወታቸው አልፏል፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ በ1934 አመተ ምህረት ከአባታቸው ከአቶ መኩሪያ ወልደስላሴ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ ተወለዱ፡፡ እናታቸው ወይዘሮ ሶስና ወርቅነህ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ልጅ ናቸው፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ነበር የተከታተሉት፡፡ ወይዘሮ እሌኒ ያደጉት ካዛንቺስ አካባቢ ሲሆን የልጅነት ዘመናቸው በደስታ የተሞላ ነበር፡፡ በተለይ በሳንፎርድ ተማሪ ቤት ጥሩ የእንግሊዝኛ ችሎታቸውን ከማዳበራቸው በላይ ደስ የሚል የመዝናኛ ጊዜን አሳለፈው ነበር፡፡ ቴኒስ መጫወት ፤ ዋና መዋኘት ፣ ቴአትር ማየት እና መተወን ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እንዲያውም ለልኡል መኮንን ሆስፒታል ማሰሪያ የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ቴአትር መስራታቸውን ወይዘሮ እሌኒ በህይወት በነበሩ ጊዜ ተናግረዋል፡፡ በተለይ አያታቸው ክቡር ሀኪም ወርቅነህ እሸቴ ዳንስ ያለማምዷቸው እንደነበር አይዘነጉትም፡፡ ወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ፣ ማህበራዊ ሳይንስ የማጥናት ግብ ቢኖራቸውም ቤሩት የነጻ የትምህርት እድል አግኝተው ወደዚያ በ1951 ግድም ያቀናሉ፡፡ ነገር ግን የነርስነትን ትምህርት ቢጀምሩም አቋርጠው ወደ እናት ሀገራቸው ይመለሳሉ፡፡ በመቀጠልም ወደ ብስራተ ወንጌል ሬድዮ በማቅናት በእንግሊዝኛው ክፍል ተቀጠሩ፡፡ ያኔ በሬድዮ ከወይዘሮ እሌኒ ጋር ይሰሩ ከነበሩት ባለሙያዎች መካከልም ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ኩምሳ ይጠቀሳል፡፡ ወይዘሮ እሌኒና ጋዜጠኛ ልኡልሰገድ ዜና ሲያቀርቡ ያለበት ቪድዮ ከዚህ ጽሁፍ አዘጋጅ ዘንድ ይገኛል፡፡ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ቻርተር በግንቦት 18 1955 ሲፈረም ጋዜጠኛ ከነበሩት መካከል ወይዘሮ እሌኒ ይጠቀሳሉ፡፡ በወቅቱ ገና የ21 አመት ወጣት የነበሩት ወይዘሮ እሌኒ መሪዎች ሲመጡ የተደረገውን ታሪካዊ አቀባበል በፍጹም አይዘነጉትም፡፡ \n \nጥያቄ: ወ/ሮ እሌኒ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1934 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nየቅኝ ግዛት ጊዜ በ1648 እ.ኤ.ኣ. ፓርቱጋል ሏንዳን እንደገና ተቆጣጠረች። በ1650 እ.ኤ.አ. ደግሞ የተነጠቀችውን መሬት እንዳለ አስመለስች። በ1671 እ.ኤ.አ. ፑንጎ አንዶንጎ የሚባለው ቦታ ወደ ፖርቱጋል ቅኝ ግዛት ተጨመረ። ፖርቱጋል በ1670 እ.ኤ.አ. ኮንጎን እና በ1681 እ.ኤ.አ. ማታምባን ለመውረር ያደረገችው ሙከራ አልተሳካም። በ1885 እ.ኤ.አ. የበርሊን ጉባኤ የፖርቱጋል ቅኝ-ግዛት ድንበርን ከወሰነ በኋላ፣ በብሪታኒያ እና ፖርቱጋል ጥረት በኩል የባቡር-መንገድ፣ እርሻና ማዕድን ተሻሻሉ። እስከ ፳ኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ አካባቢው ሙሉ በሙሉ በፖርቱጋል አልተመራም ነበር። በ1951 እ.ኤ.አ. ቅኝ ግዛቱ የባህር ማዶ ክፍለ-ሀገር ሆኖ ፖርቱጊዝ ምዕራብ አፍሪካ ተባለ። ፖርቱጋል አካባቢውን ወደ አምስት መቶ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያህል ተቆጣጥራለች። ስለዚህም የአካባቢው ሕዝብ ነጻነት ለመውጣት ያለው ስሜት የተደበላለቀ ነበር። ነፃነትና የእርስ በርስ ጦርነት አንጎላ ነጻነቷን በኅዳር ፲፱፻፷፰ ከተቀዳጀች በኋላ ግን ለብዙ አሥርተ ዓመታት የሚቀጥል የእርስ በርስ ጦርነት ገጠማት። ይህ ውጊያ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለሞትና ስደት አብቅቷል። ከአልቮር ስምምነት በኋላ ሶስቱ ትልቅ የትግል ግንባሮች የሽግግር መንግሥትን ለማቋቋም በጃኑዋሪ 1975 እ.ኤ.አ. ተስማሙ። ነገር ግን በሁለት ወራት ውስጥ እነዚህ ግንባሮች ወደ ውጊያ ተመልሰው አገሯ ወደ ክፍፍል እያመራች ነበር። በዚህ ወቅት የቀዝቃዛው ጦርነት ኃያል አገራት የነበሩት የሶቭየት ሕብረትና አሜሪካ አንዱን ወይም ሌላውን ወገን ደግፈው ወደ ጦርነቱ ገብተዋል። ሌሎችም እንደ ፖርቱጋል፣ ብራዚል፣ ደቡብ አፍሪካና ኩባ የመሳሰሉት ሀገራትም ከማገዝ ወደ ኋላ አላሉም። ፖለቲካ የአንጎላ የሕግ አስፈፃሚ አካል ፕሬዝዳንቱን፣ ምክትል ፕሬዝዳንቱንና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱን ያጠቃልላል። ለብዙ ዓመታት አብዛኛው ሥልጣን በፕሬዝዳንቱ እጅ ነው ያተኮረው። የ፲፰ቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። የ1992 እ.ኤ.አ. ሕገ መንግሥት የመንግሥቱን አወቃቀርና የዜጎችን መብቶችና ግዴታዎች ይዘረዝራል። የሀገሩ ሕግ ተርጓሚ አካል የፖርቱጋል ሥርዓትን ይከተላል። ጦር ኃይል የአንጎላ ጦር ኃይሎች በመከላከያ ሚኒስቴር ስር ሲሆኑ በሦስት ይከፈላሉ። እነዚህም ምድር ኃይል፣ ባህር ኃይል እና አየር ኃይል ናቸው። የሀገሩ ጠቅላላ ሠራዊት ፻፲ ሺህ ይሆናል። የጦር ኃይሉ ንብረቶች መካከል በሩሲያ የተሰሩ ተዋጊ፣ ቦምብ ጣይና አጓጓዥ አውሮፕላኖች ይገኛሉ። አንዳንድ የጦር ኃይሉ ክፍሎች በኮንጎ ኪንሻሳና ኮንጎ ብራዛቪል ተመድበዋል። \n \nጥያቄ: በአንጎላ የሚገኙ አስራ ስምንቱ ክልሎች አስተዳዳሪዎች የሚሾሙት በማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በፕሬዝዳንቱ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበ1913 በፕሬዝዳንት ዋረን ሃርዲንግ ዘመን ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ሆኑ። በሃርዲንግ ተከታይ በፕሬዝዳንት ካልቪን ኩሊጅ ዘመን ደግሞ እንዲህ ያለን ማዕረግ ይዘው አገለገሉ። የንግድ ሚኒስትር እየሆኑ ሃይለኛ ሰው ነበሩ። የንግድ ዘርፍና መንግሥት አንድላይ ይሠሩ የሚለውን ተስፋ በመያዛቸው በዚህ አንጻር ብዙ አደረጉ። በማዶ ባሕርና በውጭ አገር ለባለጉዳዮች ምክርና እርዳታ የሚሰጡ መሥርያ ቤቶች በማስከፈቱ የአለም አቀፍ ንግድ በጉልበት አስለሙ። በተለይም የሆሊዉድ ፊልም ማዶ ባሕር ለመግፋፋት ጉጉ ነበሩ። ዜጎችም ቤት እንዲያገነቡና የራሳቸው መሬት ባለአባት እንዲሆኑ አበረታቷቸው። ስለ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የክላርክ ሰነድ በ1920 ተጽፎ ሁቨር ፕሬዝዳንት እየሆኑ በ1922 ግልጽ ሆኖ ወጣ። በዚህ ሰነድ ዘንድ፥ አውሮጳ በላቲን አሜሪካ ላይ ዛቻ ካልጣለች በተቀር አሜሪካ በውጭ አገር ጥልቅ ለማለት ሕጋዊ መብት አልነበራትም የሚል ማስታወሻ ነበር። በዚያን ጊዜ አሜሪካ ሠራዊት በኒካራጓና በሃይቲ ነበራት። ስለዚህ ሁቨር ከነዚህ አገራት የሠራዊቱን ቁጥር ቀነሱ። በላቲን አሜሪካ ውስጥ የጦርነት መሣርያ እንዳይደርስ ማዕቀብ ለመጣል አሠቡ። በ1924 ጃፓን ማንቹርያን በወረረ ጊዜ አዲስ ፖሊሲ አወጡ። እሱም በግፍና በወረራ የሚገኝ የመሬት ለውጥ ሁሉ አናከብርም የሚል ነበር። ከታላቁ ጭፍግግ የተነሣ ብዙ ባንክ ቤቶች ስለወደቁ አንዳችም ብድር ለማግኘት ከባድ ሆነ። ብዙ ሰዎች ሥራ ፈት ሆኑ። በአውሮፓም ምጣኔ ሃብቱ ችግር ውስጥ ስለ ገባ ሁቨር ጀርመን ስለመጀመርያው ጦርነት ለፈረንሳይ ከምትከፍል ካሣ ለአንድ አመት ይቅር ትበል የሚል ዕቅድ አዋጁ። በሚከተለውም አመት የጀርመን ዕዳ በሙሉ ተሰረዘ። በ1925 ምርጫ ተቃራኒው ፍራንክሊን ሮዘቨልት በሰፊ መጠን አሸነፉና በሳቸው ፈንታ ፕሬዚዳንት ሆኑ። ሁቨር ፕሬዚዳንት ከሆኑ በኋላ ረጀም ዕድሜ ነበራቸው። እስከ 1957 ዓ.ም. ድረስ ኖሩ። ከ2ኛ አለማዊ ጦርነት ቀጥሎ በ1939 ስለ ቀድሞው ልምዳቸው ፕሬዚዳንት ሃሪ ትሩማን የአውሮፓ ምግብ ፍላጎት ለመወሰን ወደ አውሮፓ ላኳቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር መቼ ስልጣናቸውን ለቀቁ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1925 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአኩሪ አተር አኩሪ አተር የአባዝርት አትክልት ዝርያ ነው። በየጊዜው አኩሪ አተርን መመገብ ለሴቶች ጉዳት ባያደርግም፣ ለወንዶች ጤናማ እንደማይሆን በሰፊ ቢታወቅም በአንዳንድ አገር ባሕል አመጋገብ በብዛት ይጨመራል። ከ20ኛዉ ክፍለ ዘመን አንስቶ በተለይ አሜሪካን ዉስጥ ወርቃማዉ ወይም ተዓምረኛዉ እህል የሚል ስያሜ አግኝቷል። አኩሪ አተር በፕሮቲን እና ቅባት ምንጭነቱ የሚወዳደረዉ የእህል ዘር የለም። ባለሙያ ካገኘም ለመጠጣትም ለመበላትም የሚችል የእህል ዘር ነዉ። ስለአኩሪ አተር ሲወሳ ብዙዎች የሚያስታዉሱት ለሕፃናት አካል ግንባታ ጠቃሚ መሆኑ ብዙ ጊዜ የተነገረለትን የአኩሪ አተር ወተት ሊሆን ይችላል። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን በኢትዮጵያዉያን የምግብ ጣዕም ለዛ ተላብሶ በተለያየ ምግብነት መቅረብ እንደሚችል እየታየ ነዉ። አኩሪ አተር ወደኢትዮጵያ የገባዉ በ1950ዎቹ መሆኑን ነዉ በእህሉ ላይ ምርምር የሚያደርጉት ባለሙያዎች የሚያስረዱት። በአኩሪ አተር ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተደረገዉ ዝርያ የማዉጣት ምርምርም 22 ዓይነት ዘሮች እስካሁን ተገኝተዋል። አኩሪ አተርን በሀገር ዉስጥ በ12 የምርምር ማዕከላት ላይ ከፍተኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ፤ መካከለኛ የዝናብ መጠን በሚያገኙ እና ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ምርምሩ ይካሄዳል። አኩሪ አተር ሀገር ዉስጥ በከፍተኛ ደረጃ የሚመረተዉ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በኦሮሚያ ክልል ነዉ። አኩሪ አተርን በብዛት ከሚያመርቱ ሃገራት ዩናትድ ስቴትስ፤ ብራዚል እና አርጀንቲና ቀዳሚዎቹ ናቸዉ። ከአኩሪ አተር ወተት ለማዘጋጀት ሲታሰብ እህሉን ከአንድ ቀን በፊት ለቅሞና አጥቦ ለ15 ደቂቃ ያህል መቀቀል ያስፈልጋል። ከዚያም አዉጥቶ ተዘፍዝፎ ያድራል። ከዚያም የራሰዉን አኩሪ አተር ልጣጩን በሚገባ በዉኃ አስለቅቆ በትንሽ በትንሹ እየቆነጠሩ ፈጭቶ እንደእህሉ መጠን ዉኃ ጨምሮ መቀቀልና መጭመቅ ነዉ። እንደባለሙያዉ ከሆነም ለአንድ ኪሎ አኩሪ አተር ስምንት ሊትር ዉኃ ያስፈልጋል። ተፈጥሮን ተከትሎ የማይበቅል እህልም ሆነ በተፈጥሮ ሥርዓት ያላደጉ እንስሳትን መመገብ ለጤና አደገኛ መሆኑን በተግባር የተረዳዉ ምዕራቡ ዓለም በአሁኑ ጊዜ ፊቱን ከእንስሳት ተዋፅኦ ወደተክሎችና ሰብሎች አዙሯል። በዚህ ምክንያትም ከአኩሪ አተር የሚገኙ የምግብ ተዋፅኦዎች ተመራጭነትን እያገኙ ነዉ። ከአኩሪ አተር ወተት እና አይቡ እንደሚገኝ ሁሉ የአኩሪ አተር ሥጋም አለዉ። \n \nጥያቄ: አሩሪ አተር ወደ ኢትዮጵያ መቼ ገባ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1950ዎቹ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nጎፋ የጎፋ ብሔረሰብ ቋንቋ ‹ጎፍኛ› ሲሆን፣ ቋንቋው ከማዕከላዊ ኦማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ውጤት የብሔረሰቡ ሕዝብ ብዛት 363ሺ9 ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ በጋሞጎፋ ዞን ውስጥ ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ብሔረሰቡ በዋናነነት በጎፋ ዙሪያ፣ ዛላ፣ ዑባ፣ ደብረፀሐይ እና መሎካዛ በሚባሉ ወረዳዎች ይገኛል፡፡ የብሔረሰቡ ዋና የሀብት መሠረት ጥምር ግብርና ሲሆን፤ የገቢ ምንጭ በሚያስገኙ ምርቶች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ነባር ባህላዊ አስተዳደር አለው፡፡ ጥንት በጎፋ ግዛት ክልል ሥር የነበሩ አካባቢዎች በሰባት የካዎ (ነጉሥ) ግዛቶች ተከፋፍለው የተደራደሩ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ከአዎ የአስተዳደር ማዕከል ቤተ-መንግሥት(ጋዶ) ነበረው፡፡ ማዕከላዊ አስተዳደሩ የተለየ ሥልጣንና የሥራ ድርሻ ያላቸውን አስፈፃሚ አካላትን የያዘ ነበር፡፡ ካዎ (ንጉሥ)- የባህላዊ አስተዳደሩ ቁንጮና ከፍተኛ የሥልጣን አካል ሲሆን፤ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገኙትን የሥልጣን አካላትንና አማካሪዎችን የመሾምና የመሻር ሥልጣን ነበረው። ጠንከር ያለ ውሳኔን የሚሹ ጉዳዮች የመጨረሻ ብይን የሚያገኙትም በካዎ ነበር፡፡ ብሔረሰቡ ጋብቻ የማፈጸመው የጎሣ አቻነትን፣ የሀብት ደረጃ በማስተያየትና የሥጋ ዝምድና አለመኖርን መሠረት በማድረግ ነው፡፡ ወንዶች ከ17-25፤ ሴቶች ደግሞ ከ14-19 ባለው የዕድሜ ክልል ጋብቻ ይፈጽማሉ፡፡ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ይገረዛሉ፡፡ ጋብቻ ከመፈጸማቸው በፊት ሴቷ ጥጥ ፈትላ አልባሳት ስታዘጋጅ ወንድም በፊናው የመኖሪያ ቤትና የራሱን የእርሻ ቦታ ያደራጃል፡፡ በብሔረሰቡ የተለያዩ የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች አሉት፡፡ በቤተሰብ ስምምነት፣ በጠለፋ የሚፈጸሙ ጋብቻዎች ኣሉት። በተጋቢዎችም ሆነ በቤተሰብ መካከል ያለመግባባት ሲከሰት ወይም የአግቢው ገቢ ሀብት አቅም ውሱንነት ሲከሰት ተጋቢዎቹ ሳይተዋወቁ የወንዱ አባት ሽማግሌ ይዞ የልጅቷን ቤተሰብ ከ1-2 ቀን ደጅ በመጥናት የሚፈጸም የሽምግልና ጋብቻም ኣለው። የምትክ ጋብቻ የሚባለው ደግሞ፤ ሚስት ከሞተች እህቷ ወይም የቅርብ ዘመዷ በምትክ ሚስትነት የምትሰጥበት የጋብቻ ኣይነት ነው፡፡ ወዶ ገብ ጋብቻ ደሞ ሌላው በብሔረሰቡ የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ ይኸውም፤ ሳታገባ የቆየች ሴት የራሷን ንብረት በመያዝ ወደ ወንዱ ቤት በፈቃዷ ሄዳ በመግባት የሚፈጸም የጋብቻ ዓይነት ነው፡፡ በብሔረሰቡ በበዓላት ቀናት ከሚዘጋጁት ምግቦች መካከል ሸንዴራ ይገኝበታል፡፡ ከበቆሎና ከገብስ ዱቄት የሚሠራ ሆኖ ቅመማቅመምና ቅቤ በማጣፈጫነት ገብቶበት የሚበላ ጥሩ ምግባቸው ነው፡፡ ቡላ በአይብ ጎመንና ቅቤ ገብቶበት የማሠራው ባጭራ የተባለው ምግባቸውና ቅንጬ በበዓላት ቀን ከሚያዘጋጇቸው ተጠቃሾች ናቸው፡፡ \n \nጥያቄ: የጎፋ ብሔረሰብ ህዝብ በ1999ዓ.ም በተደረገው የቤት ቆጠራ ምን ያህል ነበሩ?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ 363ሺ9 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቴሌቪዥን ቴሌቪዥን የስዕል እና ድምጽ ምልክቶችን ከማሰራጫ የሚቀበል የመገናኛ ዘዴ ነው። «ቴሌ-» የሚለው ክፍል በግሪክ «ሩቅ» ማለት ቢሆን «-ቪዥን» ደግሞ ከሮማይስጥ visio /ዊዚዮ/ «ማየት» («ትርዒት») ተወስዷል። በአጠቃላይ ቴሌቪዥን ማለት ተንቀሳቃሽ ምስልን (ብዙ ጊዜ ከድምፅ ጋር) ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለማስተላለፍ የሚረዳ የመልዕክት ማስራጫ መንገድ ነው። ይህ ከሆነ ዘንዳ ቴሌቪዥን ምስል መቅጃውንም ሆነ ምስል መቀበያውን መሳሪያ ሁሉ ያጠቃልላል ግን በተለምዶ ቴሌቪዥን የምንለው ምስል መቀበያውን ብቻ ነው። በ1873 እ.ኤ.አ. (1865 ዓም) የእንግላንድ ኤንጅኔር ውሎቢ ስሚስ ባደረገው ጥረት ጥንተ ንጥሩ ሴሌኒይም ብርሃን-አስተላልፎሽ መሆኑን ገለጸ። በ1884 እ.ኤ.አ. ፓውል ጎትሊብ ኒፕኮው የተባለ ጀርመናዊ ክብ የሆነ ዲስክን በስፓይራል በምብሳት ይህ ዲስክ በተሽከረከረ ቁጥር ከፊትለፊቱ የሚመጣውን ብርሃን በቀዳዶቹ በማሾለክ ከሴሌኒይም በተሰራ የካሜራ ግድግዳ ላይ እንዲያርፍ አደረገ። ግድግዳው ብርሃን ሲነካው ያንን ብርሃን ወደ ኮሬንቲ ሃይል በመቀየር ምስልን በኮሬንቲ መልክ በሽቦ ለመላክ ቻለ። ነገር ግን በዚህ ጊዜ አምፕሊፋየር ስላልነበር የሚላከው ምስል እምብዛም አመርቂ አልነበረም። ከ27 አመታት በኋላ በ1911 እ.ኤ.አ. የራሻው ቦሪስ ሮዚንግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሲርቲን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ አሁንም ለመጀመሪያ ጊዜ ተንቀሳቃሽ ምስልን ለመላክና ለመቀብል ቻለ። ነገር ግን የሚንቀሳቀሱት ምስሎች የጂዎሜትሪ ቅርጽ ነበራቸው ማለትም ሶስት ማዕዘን፣ አራት ማእዘን ወዘተ... ከ7 አመታት በኋላ በ1925 እ.ኤ.አ. ጆን ሎጂ ቤርድ የተሰኘው የስኮትላንድ ተመራማሪ 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለመላክ ቻለ ከዚያም በ1926 እ.ኤ.አ. ጥቁርና ነጭ የሆኑ ምስሎችን ለማስተላለፍ በቃ። በዚህ ጊዜ የሚላኩት ምስል ጥራት 30 መስመር በአንድ ጊዜ ነበር፣ በዚህም ምክንያት የሰውን ፊት ለመለየት አስቸጋሪ ቢሆንም ግን ይቻል ነበር። አቶ ቤርድ በ 1918 ዓ.ም. (26 January 1926 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የቴሌቪዥን መግለጫ ሰጠ። በ1927 እ.ኤ.አ. ኸርበርት አይቭስ የተሰኘው የቤል ላብራቷር ተቀጣሪ 16 የምስል ገጽታ በሰከንድ ከዋሽንግተን ዲሲ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በሽቦ መላክ ቻለ። ቀጠል አድርጎም በራዲዮ ወደ ዊፓኒ ኒው ጀርሲ ለመላክ በቃ። በዚያው አመት ፊሎ ፍራንስዎርዝ የመጀመሪያውን የተሟላና በኤሌክትሪክ ስካኒንግ ብቻ የሚስራውን የቴሌቭዥን ስርዓት በተግባር አዋለ።.በጥር 1928 እ.ኤ.አ. (1920 ዓም) መጀመርያው የቴሌቪዥን ማሰራጫ ጣቢያ በስከነክተዲ፣ ኒው ዮርክ ተከፈተ፤ እስከ ዛሬም ድረስ ያሰራጫል። \n \nጥያቄ: በ1925 እ.ኤ.አ. 2ቅጥ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎችን በቴሌቪዥን ለመላክ የቻለው ጆን ሎጂ ቤርድ የየት ሀገር ተመራማሪ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የስኮትላንድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዳምጠው አየለ ዳምጠው አየለ (23.11. 1944 አ/ም – 27.10. 2006 አ/ም) ባህላዊ የኢትዮጵያ ዘፋኝ ነበር። በሃምሌ 23 1944 አ/ም ከእናቱ ወይዘሮ ሸዋየ ተካና ከአባቱ አየለ ካሰኝ በመራቤቴ ሰሜን ሸዋ ተወለደ። ልጅነቱን በእረኝነት፥ በግብርና እንዲሁም በቆሎ ተማሪነት እንዳሳለፈ ይናገራል። እድሜውም ለትምህርት ሲደርስ ባቅራቢያው በሚገኘው መራኛ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብቶ ተምሯል። ዳምጠው ህይወቱ እስካለፈችበት ጊዜ ድረስ ለረዥም ጊዜ አብሯት የኖረው ባለቤቱ አልማዝ ይመር ትባላለች። ከአልማዝ ይመር አብዩ ዳምጠውና ቤቴልሄም ዳምጠው የሚባሉ ሁለት ልጆችን አፍርቷል። ዳምጠው መራቤቴ እያለ በየባእላቱ መዝፈን፣ ማቅራራት እንዲሁም መሸለል ይወድ እንደነበር ተናግሯል። በተለይም ጥምቀትን በማድመቅ ይታወቅ ነበር። የ 6ኛ ክፍል ተማሪ እያለ ክፍሌ ሞገስ የሚባል መምህሩ ወደ አዲስ አበባ ይዞት እንደመጣ ይናገራል። ባጋጣሚም የምድር ጦር ማስታወቂያ አውጥቶ ስለነበር ይፈተንና ያልፋል። የምድር ጦር ካምፕ ውስጥም እንዲኖር ይደረጋል። የዘፋኝነት ሙያው በዚህ አጋጣሚ ነበር የጀመረው። ዳምጠው ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማዉና መነሻ የሆነው አበበ ተሰማ እንደሆነ ይናገራል። ዳምጠው አየለ በምድር ጦር ከ 30 አመት በላይ አገልግሏል። የኢትዮዽያ ምድር ጦር በ1927 አ/ም ተመስርቶ በ1983 አ/ም የፈረሰ የሙዚቃ ቡድን ነበር። ዳምጠው በመንግስት ለውጥ ምክንያት እስከፈረሰበት ጊዜ ድረስ አብሮ እንደነበር ይናገራል። ምድር ጦርም እያለ ከነታምራት ሞላ፣ ሲራክ ታደሰ፣ ተክሌ ደስታ ፣ ጥላየ ጨዋቃ፣ ክፍሌ አቦቸር እንዲሁም ሌሎች የጦሩ አባላት ጋር ሰርቷል። ከሌሎች የሙዚቃ ቡድንም ጋር አብሮ ሰርቷል። ለምሳሌ ያክል ከነ ክቡር ጥላሁን ገሰሰ፣ ሙሃሙድ አህመድ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ ሙሉቀን መለስ፣ ፀሃየ ዮሃንስ፣ ቴድሮስ ታደሰ፣ቴድሮስ ካሳሁን እንዲሁም ሌሎችም ጋር ሰርቷል። የዳምጠው አየለ የመጀመሪያ የህትመት ስራው በ1963 አ/ም ሲሆን ወፌ ላላ የሚለው የሸክላ ስራ ነበር። ዳምጠው አየለ ባጠቃላይ 13 ሲዲዎችን ሰርቷል። ዳምጠው አየለ ኖርዌይ ሃገር በስደት ለ 8 አመት ያክል ኖሯል። ኢትዮጵያም ከገባ በኋላ አዲስ አበባ በሚገኘው በቅ/ገብራኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በተወለደ በ 62 አመቱ ሰኔ 27 2006 አ/ም ቀን ህይወቱ አልፏል። የቀብር ስነስርአቱም ወዳጅ፣ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: የዳምጠው አየለ ባለቤት ማን ይባላሉ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አልማዝ ይመር ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኤርትራ ኤርትራ በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ አገሮች አንዷ ስትሆን በስሜን-ምዕራብ ከሱዳን፣ በሰሜን-ምስራቅ ከቀይ ባህር፣ በደቡብ ከኢትዮጵያ፣ በደቡብ-ምስራቅ ጅቡቲ ጋር ድንበር ትካለላለች። ኤርትራ የሚለው ስም ከላቲን የተወሰደ እና ስረ-መሰረቱ የግሪክ ሐረግ ሲሆን ትርጉሙም ቀይ ማለት ነው። ይህን ስም ለአካባቢው የሰጡት ጣሊያኖች በጥር ፲፰፻፺ ቅኝ ግዛታቸውን ሲያውጁ ነበር (ተመሳሳይ ስም በጀርመኖች 1870 እና ግብጾች ፲፰፻፷ወቹ በጥቅም ላይ ውለዋል፣ ነገር ግን የትኛውን ክፍል ስሙ እንደሚመለከት ግልጽ አልነበረም)። ኤርትራ፣ እንደ ሐገር፣ በጣሊያኖች ከተመሰረተች በኋላ በ5 ልዩ ሂደቶች ውስጥ በማለፍ ነው ያሁኑን ቁመናዋን የያዘችው። ከ1890 በፊት የነበረው የአካባቢው ታሪክ በ«ኤርትራ» ስር የሚጠና ባህይሆንም ስለአዲሱ ኤርትራ ግንዛቤ ስለሚያስጨብጥ ታሪክ ተመራማሪዎች ከ፲፰፻፺ በፊት ያለውንም ታሪክ ማጥናት ተገቢ እንደሆነ ይስማማሉ። በ1860ዎቹ መጀመሪያ አካባቢ፣ የግብጹ መሪ ኢስማኤል ከዴቭ ፓሻ በናይል ተፋሰስ ላይ ሰፊ የግብጽ ቅኝ ግዛት ለማበጀት ተነሳ። ለዚህ አዲሱ ግዛቱ ካርቱምን ዋና ከተማው በማድረግ የሱዳን ግዛቱን አጸና። ቀጥሎም የቀይ ባህርን ጠረፎች በ1865 ከተቆጣጠረ በኋላ በ1870ዎቹ መጀመሪያ ሐረርንና ተሻግሮ ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ግዛቶችን አበጀ። እንግዲህ በኒህ ግዛቶቹና በሱዳን መካከል የነበረው ብቸኛ መገናኛ መንገድ ካርቱም-ከሰላ- ከረን -ምፅዋ ብሎ የሚዘልቅ ነበር። ስለሆነም በ1872 ይህን ስልታዊ መንገድ የክዴቭ ፓሻ ሰራዊቶች ተቆጣጠሩ። መቆጣጠር ብቻ አይደለም በየመንገዱ ምሽግ እየሰሩና የአውሮጳ ምስዮናውያንን እርሻ ቦታ እየሰጡ ቅኝ ግዛት አበጁ። በዚህ ሳይቆጠቡ፣ የመንገዱን ደህንነት ዋስትና ለማስጠበቅ ሲሉ የአካባቢውን ደጋማ ክፍል መያዝ ግድ አላቸው። ደጋማው ክፍል በዚህ ወቅት በአጼ ዮሐንስ ግዛት ስር ነበር። \n \nጥያቄ: ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የምትዋሰነው በየት አቅጣጫ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በደቡብ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2012(ኤፍቢሲ) ቻይና በዋና ከተማዋ ቤጂንግ እና በሀቤይ ግዛት ዘሃንግጃኩ መካከል የተዘረጋውን ፈጣን ባቡር ለገልግሎት ክፍት ልታደርግ መሆኑ ተሰምቷል። ቻይና የፈጣን ባቡሩን ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው በአውሮፓውያኑ 2022 የምታስተናግደውን የክረምት ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ እንደሆነም ተነግሯል። ፈጣኑ ባቡር በሰዓት 350 ኪሎ ሜትር የሚጓዝ ሲሆን፥ በዓለማችን ላይ የመጀመሪያው አሽከርካሪ አልባ ባቡር እንደሚሆንም ተነግሮለታል። የ 174 ኪሎ ሜትር ያለው የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቱ ለ2022 የክረምት ኦሎምፒክ እና የፓራሎምፒክ ታስቦ የተሰራ መሆኑም ታውቋል። የባቡር መስመሩ የክረምት ኦሎምፒኩን በሚያስተናግዱት በሁለቱ ከተሞች መካከል የነበረውን የ3 ሰዓት መንገድ ወደ 47 ደቂቃ የሚቀንስ መሆኑ የቻይና ባቡር ኮርፖሬሽን አስታውቋል። ምንጭ፦ newsus.cgtn.com \n \nጥያቄ: ቻይና በክረምቱ ኦሎምፒክ ምክንያት ለአገልግሎት ክፍት የምታደርገው ፈጣን ባቡር በሰዓት ምን ያህል ኪ.ሜ ይጓዛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 350 ኪሎ ሜትር ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nግንቦት ፳፮ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፷፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፷፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፺፱ ቀናት ይቀራሉ። ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኤር ፍራንስ ቦይንግ ፯፻፯ አየር ዠበብ ከፓሪስ ኦርሊ ማረፊያ ተነስቶ ወደ አትላንታ ለመብረር ሲነሳ በደረሰበት አደጋ ፻፴ መንገደኞችና የዓየር መንገዱ ባልደረቦች ሞተዋል። ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የአሜሪካው ‘ኖርዝ ዌስት ኤየርላይንስ’ ዲ-ሲ-፯ አየር ዠበብ በረራ በሰላማዊ ውቅያኖስ ላይ ውድቆ ሲሰምጥ ፻፩ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኮንኮርድ አየር ዠበብ አምሳል የተሠራው የሶቪዬት ቱፖሌቭ ቲ-ዩ-፻፵፬ ፈረንሳይ ላይ በደረሰበት የበረራ አደጋ ሲከሰከስ ፲፬ ሰዎች ሞተዋል። ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ የውሕደት ስምምነታቸውን በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት ሰረዙ። ፲፯፻፷፭ ዓ/ም - የዓፄ በካፋ ሚስት የነበሩት እቴጌ ምንትዋብ በዚህ ዕለት አርፈው በቁስቋም ደብረ ጸሐይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። \n \nጥያቄ: በሞንቴኔግሮ የሉዐላዊነት አዋጅ ምክንያት - የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ አካላት የነበሩት ሰርቢያ እና ሞንቴኔግሮ ስምምነታቸውን መቼ አፈረሱ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፲፱፻፺፰ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ የት ተወለደ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጅሩ ቆላ ውስጥ እምባጮ መግደላዊት በሚባል ሥፍራ መጋቢት ፲፯ ቀን በ፲፰፻፺፩ ዓ/ም ተወለዱ። በቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያ ትምህርታቸውን እስከ ዳዊት ድረስ ካጠናቀቁ በኋላ የዜማ ትምህርት ተከታትለው ጾመ ድጓ እና ድጓን ዘልቀዋል። ቀጥሎም የቅኔ ትምህርታችውን አጠናቀው በ ፲፱፻፭ ዓ/ም በአሥራ አራት ዓመት ዕድሜያቸው በወንበር ፀሐፊነት የመጀመሪያ ሥራቸውን ጀመሩ። የመጻሕፍተ ሐዲሳትን ትርጓሜ፤ የዮሐንስ አፈወርቅን ትርጓሜ፤ እንዲሁም የመቅድመ ወንጌልን ትርጓሜ ትምህርት ያጠናቀቁት እኝህ ታላቅ ሰው ብርሃንና ሰላም (ጋዜጣ) የተሰኘው ጋዜጣ ሲመሠረት የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ በመሆን፣ ቀጥለውም በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የግዕዝና የአማርኛ አስተማሪ በመሆን አገልግለዋል። ከፋሺስት ወረራ በኋላ ከ፲፱፻፴፫ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፷፫ ዓ/ም ድረስ በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በኃላፊነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ሥነ ጽሑፍንና ታሪክን በተመለከተ፣ አሥራ ሦስት መጻሕፍትን የደረሱ ሲሆን፣ ሰባት መጻሕፍት ደግሞ ተርጉመው አቅርበዋል። እንዲሁም የተለያዩ ጽሑፎችን አሰባስበው ከማዘጋጀታቸው ባሻገር፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ሥራዎችም ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በትብብር አዘጋጅተዋል። \n \nጥያቄ: ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ የመጀመሪያ ሥራቸውን በስንት ዓመታቸው ጀመሩ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በአሥራ አራት ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nአዳማ /ኢዜአ/መስከረም 23/2012 የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ስምንት የምርምርና የልህቀት ማእከላት እያደራጀ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ተሾመ አብዶ ለኢዜአ እንደገለጹት ግንባታቸው ከ90 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የምርምር ፓርኮችንና የልህቀት ማዕከላትን በመሳሪያ ለማደራጀት 86 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ተመድቦ እየተሰራ ነው ብለዋል። በዚህም ሁለት ሊትል ስታር የተባሉ ሳተላይቶች በደቡብ ኮሪያና ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች በመገጣጠም ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የፋርማቲካል የልህቀት ማእከሉ የባህል መድኋኒቶችን በመቀመምና በምርምር በማዘጋጀት ወደ ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ምርት እንዲገቡ የሚያስችል መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ተሾመ በተለይም በባህላዊ መድኋኒቶች ዙሪያ በትኩረት የምርምር ሥራ ለማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል። የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በ19 የትምህርት ፕሮግራሞች ከ6 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በኤክስቴሽን ፕሮግራም ተቀብሎ ማስተማር ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ዶክተር ተሾመ አብዶ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቺኑዋ አቼቤ በሙሉ ስሙ ሲጠራ አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ ይሰኛል። ምናልባትም ናይጄሪያ ካሉዋት ምርጥ ፀሃፍት ዝርዝር ውስጥ በአንደኛ ደረጃ የሚሰለፍ ሳይሆን አይቀርም። በ1930 እ.ኤ.አ. ኦጊዲ በተባለች የናይጄሪያ ግዛት ከአዜያህ ኦካፎ እና ከጃኔት አቼቤ ተወለድ። በ1953 እ.ኤ.አ. ከለንደን ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ለአቼቤ ድንቅ ሥራ የተባለለት \"Things Fall Apart\" 50 ወደሚሆኑ የአለም ቁዋንቁዋዎች የተተርጎመ ሲሆን ወደ 10,000,000 ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይነገራል። አቼቤ ከአፍሪካ ፀሃፍት ሁሉ ሥራው በበዙ ቁዋንቁዋዎች በመተርጎም ክብረ ወሰኑን እንደያዘ ነው። ብዙዎችም ይኸው ድርሰቱ በአለም እስከዛሬ ከተደረሱ ምርጥ ልበ-ወለዶች መካከል እንደሆነ ይስማማሉ። አቼቤ ከ30 ከሚበልጡ ዩኒበርስቲዎች የክብር ዶክትሬት የተቀበለ ሲሆን ብዙ ሽልማቶችንም ከተለያዩ ድርጅቶች አግኝቷል። ይሁንና እስከ አሁን ድረስ የኖቤል ሽልማት ለማግኘት አልታደለም። ይኸውም በብዙው ጽሁፉ የመራቡን አለም ዘረኛነት የሚተች በመሆኑ እንደሆነ ይነገራል። በ1990 ዓ.ም በደረሰበት የመኪና አደጋ ምክንያት ከወገቡ በታች መንቀሳቀስ የተሳነው ሲሆን ኒው ዮርክ ውስጥ በሚገኘው የባርድ ኮሌጅ የቋንቋና ሥነ-ፅሁፍ ፕሮፌሰር ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። \n \nጥያቄ: አልበርት ቺኑዋሉሞጉ አቼቤ የመጀመሪያውን ዲግሪ መቼ አገኘ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በ1953 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nመጋቢት ፳፮ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት የመጀመሪያው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፱ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል። ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅት መሠረቱ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (የዓለም የንግድ ማዕከል) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል። ፲፱፻፷ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በሜምፊስ ከተማ በነፍሰ-ገዳይ እጅ ተገደለ። \n \nጥያቄ: አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በማን ተገደለ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ ጄምስ ኧርል ሬይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nገንዘብ በአንድ አገር ወይም ማህበረሰብ ውስጥ ለሸቀጥ (አሰፈላጊ እቃ) ና አገልግሎት መግዢያ እንዲሁም እዳ መክፈያ የሚያገለግ ማንኛውም ነገር ሁሉ ገንዘብ ይባላል። የጥንቱ ገንዘብ ዋጋ ይመነጭ የነበረው ከራሱ ከተሰራበት እቃ ዋጋ ነበር (ለምሳሌ፡ ከወርቅ የተሰራ ሳንቲም) ። በዚህ ምክንያት እንዲህ አይነቱ ገንዘብ የኮሞዲቲ ገንዘብ ይባላል። በአሁኑ በአለማችን የሚሰራባቸው ገንዘቦች በራሳቸው የራሳቸው የሆነ ዋጋ የላቸውም (ለምሳሌ ከተልባ እግር የተሰራው ዶላር በራሱ ዋጋ የለውም) ። ይህ አይነት ገንዘብ ፊያት ገንዘብ ሲባል ዋጋው የሚመነጨው የአንድ አገር መንግስት ህጋዊ መገበባያ ብሎ ስላወጀው ብቻ ነው። ህጋዊ መገበባያ ሲባል ለማንኛውም በዚያ አገር ውስጥ ላለ እዳ ይህ የታወጀው ገንዘብ እንደ ክፍያ ሲቀርብ \"አይ! አልቀበልም\" ማለት ክልክል ነው። በዚህ ምክንይት የፊያት ገንዘብ ዋጋ ከመንግስት ሃይል ጋር ከፍተኛ ግንኙነት አለው። ያንድ ዘመናዊ ሃገር የገንዘብ አቅርቦት በሁለት ይከፈላል፣ ይኸውም ተጨባጭ የሆነው የታተመው ብርና በማይጨበጥ መልኩ በባንክ ቤት ተጠራቅሞ ያለው በቼኪንግ እና ሴቪንግ የሚከፈለው የባንክ ሒሳብ ነው። ባብዛኛው ጊዜ እኒህ የ ባንክ ሒሳቦች ታትሞ ከቀረበው ብር በላይ ናቸው። በምናባዊ አለም ውስጥ የተቀመጡት እነዚህ የቁጥር ሰነዶች ምንም እንኳ የማይታዩና የማይዳሰሱ ቢሆንም ልክ እንደ ጥሬ ብር እኩል ለመሸጥና ለመለወጥ ያገለግላሉ። \n \nጥያቄ: በአንድ አገር ወይም ማህበረሰብ ውስጥ ለሸቀጥ እና አገልግሎት መግዢያ እንዲሁም እዳ መክፈያ የሚያገለግ ማንኛውም ነገር ሁሉ ምን ይባላል?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ገንዘብ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nየሕገ መንግሥት ታሪክ የሱመር ከተማ ላጋሽ አለቃ ኡሩካጊና በ2093 ዓክልበ. ያሕል ያዋጀ ሕገ ፍትሕ በታሪካዊ መዝገብ እስከምናውቀው ድረስ መጀመርያ የሕገ መንግሥት ሰነድ ነው። ሰነዱ እራሱ ገና አልተገኘም፤ ነገር ግን ለዜጎቹ አንዳንድ መብት እንደ ፈቀደላቸው ይታወቃል። ለምሳሌ ለመበለትና ለደሀ አደጎች ቀረጥ እንዳስቀረላቸው ድሆችንም ከሃብታሞች አራጣ እንደጠበቃቸው ይታወቃል። ከዚህ በኋላ ብዙ መንግሥታት በተጻፈ ሕግ እንዲገዙ ልዩ ስርዓት ነበራቸው። ከተገኙት ሕግጋት ሁሉ ጥንታዊ የሆነው በ1983 ዓክልበ. የገዙ የኡር ንጉሥ የኡር-ናሙ ሕግጋት ነው። በተለይ ዕውቅ የሆኑ የጥንት መንግሥት ሕጎች የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት (1832 ዓክልበ.) ፤ የኤሽኑና ሕግጋት (ምናልባት 1775 ዓክልበ. ግድም)፤ የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ሕግጋት (1704 ዓክልበ.) እና፤ ሕገ ሙሴ ለእስራኤል (1661 ዓክልበ.) ናቸው። ሕገ ሙሴ በተለይ በኦሪት ዘጸአት 21 እና 22 ያህዌ አስተካክሎ ከነዚህ ሁሉ የተሻሸሉት ብያኔዎች ይጠቅልላል። በኋላ ኬጢያውያን (1488 ዓክልበ. ግድም) እና አሦር (1080 ዓክልበ. ግድም) በበኩላቸው ለራሳቸው ሕግጋት አወጡ። \n \nጥያቄ: የኢሲን ንጉሥ ሊፒት-እሽታር ሕግጋት መች ነበር የታወጀው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ 1832 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: የበፊቱ አራቱ ሳውዲ አረብያ ግዛቶች የትኞቹ ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1932 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘውድ እንደጫኑ የአገሪቱን የመጀመሪያ ሕገ-መንግሥት እንዲዘጋጅ አዝዘው በዘውዱ አንደኛ ዓመት በዓል ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. በአዲሱ ምክር ቤት (ፓርላማ) ለሕዝብ ቀረበ። ከዚህም በላይ ብዙ የቴክኖዎሎጂ ስራዎችና መሻሻያዎች ወደ ኢትዮጵያ ከውጭ አገር አስገቡ። በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. የሙሶሊኒ ፋሺስት ሠራዊት ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ጃንሆይ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከቀረጥ አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ከታገሉ በኋላ የጠላቱ ጦር ኅይል ግን በመጨረሻ ወደ እንግሊዝ አገር ለጊዜው አሰደዳቸው። ወደ ጄኔቭ ስዊስ ወደ ዓለም መንግሥታት ማኅበር ሄደው ስለ ጣልያኖች የዓለምን እርዳታ በመጠየቅ ተናገሩ። የዓለም መንግሥታት ግን ብዙ አላደረጉም። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ግን አውሮፓ ሁሉ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ተያዘ። የእንግሊዝ ሠራዊቶች ለኢትዮጵያ አርበኞች እርዳታ በመስጠት ጣልያኖች ተሸንፈው በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ተዉ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ አዲስ አበባን እንደገና የገቡበት ቀን ከወጡበት ቀን በልኩ ዕለት አምስት ዓመት በኋላ ነበረ። ከዚህ በኋላ በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የሕዝቦችን መብቶችና ተከፋይነት በመንግሥት አስፋፍቶ ሁለቱ ምክር ቤቶች እንደመረጡ አደረገ። በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ግርማዊነታቸው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በአዲስ አበባ እንዲመሠረት ብዙ ድጋፍ ሰጡ። በ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ወደ ካሪቢያን ጉብኝት አድርገው የጃማይካ ራስታዎች ተገኛኙ። በ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. በማርክሲስት አብዮት ደርግ ሥልጣን ያዙና እሳቸው በእሥር ቤት ታሰሩ። በሚከተለው ዓመት ከተፈጥሮ ጠንቅ እንደ አረፉ አሉ ፤ ሆኖም ለምን እንደ ሞቱ ስለሚለው ጥያቄ ትንሽ ክርክር አለ። ብዙ ራስታዎች ደግሞ አሁን እንደሚኖሩ ይላሉ። የዓፄ ኃይለ ሥላሴ የትውልድ ስም ልጅ ተፈሪ መኮንን ነው። ስመ-መንግሥታቸው ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ነበር። ሞዓ አንበሣ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ የሚለው የሰሎሞናዊ ሥረወ-መንግሥት ነገሥታት መጠሪያም በንጉሠ-ነገሥቱ አርማ እና ሌሎች ይፋዊ ጽሑፎች ላይ ከመደበኛው ማዕረግ ጋር ይጠቀስ ነበር። ጃንሆይ ፣ ታላቁ መሪ እና አባ ጠቅል በመባልም ይታወቁ ነበር። \n \nጥያቄ: የጣልያን ፋሺስት ጦር ከኢትዮጵያ ተሸንፎ ከወጣ በኋላ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወደ ሀገራቸው ከስደት የተመለሱት መቼ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nከ2009 ዓ.ም ህዳር ወር ጀምሮ ሲዘጋጅ የነበረው አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል፡፡ ዝርዝር እቅዱን ለመተግበር ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡ ገንዘቡ በኢትዮጵያ መንግስትና በአጋር ድርጅቶች እንደሚሸፈንም ተነግሯል፡፡ አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ ዕቅድ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ የሚቆይ ነው ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: አገራዊ የጤና ደህንነት ትግበራ እቅድ እስከመቼ ይቆያል?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nባሕር-ዳር ባሕር-ዳር በድሮ ስሙ ባሕር ዳር ጊዮርጊስ በሰሜን-ምዕራብ ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ስትሆን የአማራ ክልል ዋና ከተማ ናት። ከተማዋ በቀድሞው ጎጃም ክፍለ ሓገር ውስጥ ከጣና ሐይቅ ደቡባዊ ጫፍ ላይ ተቀምጣ ስትገኝ ባህር ዳር እንደ መቀሌና ደሴ የወረዳ ደረጃ ያላት ስፔሻል(ልዩ) ዞን ናት። በማዕከላዊ ስታትስቲክ ትመና የ167,261 ህዝብ ከነሱም መሃከል የ86,355 ወንዶችና የ80,906 ሴቶች መኖሪያ ከተማ ናት። 1700 ሜትር ከባሕር ወለል በላይ ትገኛለች። ባሕር-ዳር ከአዲስ አበባ 565 ኪ.ሜ ወደ ሰሜን-ሰሜን ምዕራብ ትገኛለች። ባህር ዳር ከጢስ አባይ በ30 ኪሎሜትር ስለምትርቅ ለጎብኚዎች አመቺ ቦታ ላይ ናት። ባህር ዳር የአንድ የአስፋልት ንጣፍ ያለው ኤርፖርት የሰፊ ገበያና የተለያዩ የመዝናኛ ቦታዎች እና ታሪካዊ እና ጥንታዊ ግዳማት መግኛ ቦታ ናት። ባሕርዳር ከተማ የምትገኘዉ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል፣ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ከአዲስ አበባ በ 565 ኪሜ ርቀት ላይ ነው፡፡ አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ በ 11º 38’ በሰሜን ላቲቲውድ እና በ37º15’ ምስራቅ ሎንግቲውድ ነው፡፡ በአፈ ታሪክ እንደሚነገረው የባሕር-ዳር ስያሜን ያወጡት አፄ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ እሳቸውም ይሕን ታቦት የት እናስቀምጥ ተብለው በተጠየቁ ጊዜ \"ከባሕሩ-ዳር\" አድርጉ የተባሉ ሰወች ለመንደሩ ባሕር-ዳር ብለው ስያሜ አወጡለት ይባላል። ባሕር-ዳር ከተማ የተቆረቆረችው በ1915 ዓ.ም ነው ፡፡ ባሕር-ዳር በክልሉ ከሚገኙ የሪፎርም ከተሞች አንድዋ ስትሆን፤ የከተማ አስተዳደር፣ 3 ሜትሮፖሊታን ክ/ከተማዎች፣ የከተማ አገልግሎት ጽ/ቤት፣ 9 የከተማ ቀበሌዎችና 4 የገጠር ቀበሌዎች አሏት፡፡ ከተማዋ በ1998 ዓ.ም የተቀናጀ ልማት ፕላን አላት፡፡ የተቆረቆረችበትን ዓመት፣ የቆረቆሩትን ቀደምት ሠዎች፣ የሠፈሮችን ስሞች፣ ለባሕር-ዳር የተገጠሙትና የተዘፈኑ ታሪካዊ ግጥሞችና ስነ ቃሎች፣ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጎጆ ቤት ወደ አሁኑ ይዞታው አመጣጥ (ባሕር-ዳርን ስናስብ ጊዮርጊስን ሚካኤልን እና ገበያውን ከገበያው አካባቢ የነበረውን ፍርድ ቤት ነጣጥሎ ማየት አይቻልም የሚል አስተያየት ስላለ ነው)፣ ባሕር-ዳር እንደባሕር ዳርነቱ ከመቆርቆሩ በፊት በሚካኤል እና በሽመምብጥ ሠፈር አካባቢ ስለነበረው አሰፋፈር፣ ስለማዘጋጃቤቱ፣ ስለ አውቶቡስ ተራው፣ ስለ ድባነቄ ተራራ፣ እና ስለ መሳሉት፣ ስለፖሊቴክኒክ፣ ስለዓባይ ወንዝና ድልድዩ፣ ስለዓባይ ወንዝና ስለጣና ሐይቅ መገናኛ እና ስለሌሎችም ቁልፍ ነገሮችን ማቅረብ የሚችሉ አፈታሪኮች አሉ። \n \nጥያቄ: ባሕር ዳር በኢትዮጵያ የየትኛው ክልል ዋና መዲና ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የአማራ ክልል ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ዶናልድ ጆን ትራንፕ መቼ ተወለደ?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nግብፅ ግብፅ ወይም ምጽር፣ ምሥር በሰሜን ምስራቅ ኣፍሪካ የምትገኝ አገር ናት። 77 ሚሊዮን ከሚሆነው ህዝቧ አብዛኛው ከናይል ወንዝ ዳርቻ በአንድ ኪሎሜትር ክልል ውስጥ ይገኛል። የግብፅ አብዛኛው መሬት በሰሃራ በረሃ ክልል ውስጥ ይገኛል። ዋና ከተማዋ ካይሮ ስትሆን ከአፍሪካም ትልቋ ከተማ ናት። ሌላ ትኩረት የሚሰጣት ከተማ አሌክሳንድሪያ (እስክንድርያ) ናት። አሌክሳንድሪያ የአገሪቱ ዋና ወደብ ስትሆን በህዝብ ብዛት ከአገሪቱ ሁለተኛ ናት። ግብፅ በሰሜን ከሜዴቴራኒያን ባሕር በምሥራቅ ከቀይ ባሕር፤ በደቡብ ከኖብያ፤ በምዕራብ ከምድረ በዳው አገር ይዋሰናል። ነጭ አባይ በግብፅ መካከል ያደርግና ከደቡብ ወደ ምሥራቅ ይሄዳል። የአባይ ወንዝ የሚሞላው በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው። በግብፅ የሚዘንበው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ስለ ሆነ ግብፅ በአባይ ለምቶ ይኖራል። \n \nጥያቄ: ካይሮ ለግብጽ ምኗ ናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ዋና ከተማዋ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nብጉር ብጉር ማለት የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከቆዳ ስር በሚገኙ የወዝ እጢዎች በሚመነጭ ቅባት ወይም ወዝ እና በሞቱ የቆዳ ህዋሳት በብዛት መከማቸትና በቀዳዳው መደፈን የሚፈጠር እባጭ ነው። በርካታ ጥናቶች ጭንቀት ብጉርን ከማባባሱም በላይ የቆዳ ጤንነት ችግር ላይ እንዲወድቅ ያደርጋል ይላሉ። ብጉር በጣም ከተለመዱት የቆዳ ችግሮች ውስጥ አንዱ ነው። ዕድሜ ዘርና ጾታ ሳይገድበው ሁሉንም ያጠቃል። ቆዳችን ላይ ብዙ ጥቃቅን ቀዳዳዎች አሉ። በነዚህ ቀዳዳዎች ውስጥ ደግሞ ቅባታማ ፈሳሽ የሚያመነጩ ዕጢዎች አሉ። የቅባታማ ፈሳሽና የቀዳዳዎቹ ጥቅም የሞቱ የቆዳችን ህዋሳትን ለማስወገድ ነው፡፡ ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች እነዚህ ቀዳዳዎች ሲዘጉ ቅባታማ ፈሳሹ በቆዳችን ውስጥ ስለሚጠራቀም ብጉር ይፈጠራል፡፡ የተጠራቀመው ቅባትም ለህዋሳት መራባት ዕድል ስለሚከፍት አንዳነዴ መግል ይይዛል፡፡ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎች ከ'ስቤሸስ ግላንድ' ጋር የተያያዙ ናቸው፡ እነዚህ እጢዎች ሴበም የሚባል ንጥረነገር ሲያመነጩ ንጥረነገሩም በጸጉር መውጫ ቀዳዳ ወደላይ ወደቆዳ የሚወጣ እና ቆዳችን ላይ የሚያርፍ ነው። የብጉር መፈጠር የቆዳ ህዋሳትን ያበዛል። ይህ እባጭ የጸጉር መውጫ ቀዳዳዎችን ግርግዳ በመግፋት ነጫጭ የብጉር ሽፍታዎች ሲፈጥር የቀዳዳዎችን ግርግዳ በመጎተት ደግሞ ጥቋቁር የብጉር ሽፍታዎች (blackheads) ቆዳችን ላይ ሊፈጥር ይችላል። ብጉር በብዛት ሊወጣ የሚችልባቸው ቦታዎች፣ ፊት ላይ፣ በደረት፣ በኣንገት፣ በትከሻ ፣ እና በጀርባ ላይ ነው። \n \nጥያቄ: ብጉር በብዛት ሊወጣ የሚችልባቸው ቦታዎች ምን ምን ናቸው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ፊት ላይ፣ በደረት፣ በኣንገት፣ በትከሻ ፣ እና በጀርባ ላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nናዋትል ናዋትል (nāhuatl, mexìcatlàtōlli, Nawatl) በኡቶ-አዝቴካዊ የቋንቋ ቤተሠብ የሚከተት በሜክሲኮ ኗሪዎች የሚናገር ቋንቋ ነው። በተለይ እስፓንያውያን በ16ኛው መቶ ዘመን ከወረሩ አስቅደሞ በጣም ትልቅና መደበኛ ቋንቋ ሆኖ ነበር። እስከ ዛሬ ግን በ1.5 ሚሊዮን ኗሪዎች በሜክሲኮ እየተናገረ ነው። የዛሬውኑ ናዋትል ከስፓንኛ ታላቅ ተጽኖ ተቀብሏል። ኣብዛኛው ተናጋሪዎቹ ስፓንኛ ደግሞ የሚችሉ ናቸውና። ስፓንያውያን በደረሡ ጊዜ ናዋትል የራሱ ጽሕፈት ነበረው። ይህ ጽሕፈት እንደ ጥንታዊ ግብጽ ስዕል ጽሕፈት ይመስል ነበር። ነገር ግን እነዚህ ጽሑፎች በአብዛኛው በካቶሊኮች ስለ ተቃጠሉ፣ ዛሬ ቋንቋው የሚጻፈው በላቲን ፊደል (አልፋቤት) ሆኗል። በናዋትል ሰዋስው አያሌ ባዕድ መነሻዎችና መድረሻዎች አንድላይ ሊቀጣጥሉ ይችላሉ። ስለዚህ አንድ ቃል እጅጉን እንዲረዝም ተችሏል። \n \nጥያቄ: የናዋትል ቋንቋ በሌላ በምን ቋንቋ ተጽእኖ ስር ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ስፓንኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nበኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ በጥሩ ጎናቸው ከሚነሱ የቅርብ ጊዜያት ተጫዋቾች መካከል አዳነ ግርማ ይገኝበታል።ተጫዋቹ በበርካታ የስፖርቱ ቤተሰቦች ልብ ውስጥ ትልቅ ቦታንም ይዟል።አዳነ ግርማ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን መነቃቃት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ተጫዋቹ በብሄራዊ ቡድኑ ውስጥ ለ10 ዓመታት በመጫወትም አንጋፋ ለመሆን በቅቷል። አዳነ ግርማን ስናስብ ሁለት ጨዋታዎች ሁሌም ከፊታችን ድቅን ይላሉ።ደቡብ አፍሪካ ላስተናገደ ችው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡደን ከሱዳን አቻው ጋር ሲጫወት በግንባሩ ገጭቶ ያስቆጠራት ግብ መቼም ቢሆን አዳነ እንዲታወስ ያደረገችም የምታደርግ ናት።ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ ያረገችው ወሳኝ ግብም ሆናለች። በአፍሪካ ዋንጫው ከ 39 ዓመታት በኋላ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛምቢያ ላይ ያስቆጠራት ግብም አዳነን ሁሌም እንድናስበው ያረገች ሌላዋ ግቡ ናት። ተጫዋቹ ከዋልያዎቹ ጋር ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎና በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጉዞ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳደረገና የቡድኑ ምሰሶ እንደነበርም ይታወቃል።በአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ዘመን አዳነ ቡድኑን በአምበልነት መርቷል። የአትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ከሰውነት ቢሻው የተረከቡት አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ቡድኑን እንደ አዲስ ሲያዋቅሩ አዳነ ግርማን መቀነሳቸው ሲሰማ በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ ቅሬታ ቢፈጠርም፣ ተጫዋቹ ግን ውሳኔውን አሜን ብሎ ነው የተቀበለው። በወቅቱም አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ማብራሪያ ለተጫዋቹ መቀነስ ምክንያታቸው ያደረጉት የተጫዋቹ «ብቃትና አቅም ወርዷል» የሚል ነው። ተጫዋቹ ግን በወቅቱ ለአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን ያረጋገጠው ምንም አይነት የአቋም መዋዠቅም እንደሌለበት ነው። የብቃት መውረድ እንዳላሳየም ገልጿል። የመቀነሱ ሚስጥር ለሱም እንቆቅልሽ እንደሆነበት ነበር ያስታወቀው። ይህን ተከትሎ ራሱን ከብሄራዊ ቡድን ያገለለው አዳነ በአዲሱ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ሰሞኑን ጥሪ ተደርጎለት ነበር:: የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአልጄሪያ ጋር ላለበት ወሳኝ ጨዋታ በአጥቂ እጥረት ላይ ቢገኝም አዳነ ግርማ ከቤተሰቦቼ ጋር ተመካክሬ የወሰንክይት ውሳኔ ነው በሚል ለብሔራዊ ቡድኑ እንደማይጫወት አስታውቋል:: በ2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በምድብ ሁለት የተደለደለውና በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአልጀሪያ አቻው ጋር ላለበት የምድቡ ሶስተኛ እና አራተኛ ጨዋታ 24 ተጫዋቾችን መጥራቱ ይታወሳል። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ሁለት ተጫዋቾችን ከአገር ውጭ ቀሪዎቹን 22 ደግሞ ከአገር ውስጥ ሊጎች የመረጡ ቢሆንም የአዳማ ከነማው አጥቂ ታፈሰ ተስፋዬ ባጋጠመው ጉዳት ከቡድኑ ውጭ ሆኗል። እርሱን ለመተካት ሳልሃዲንና አዳነን ቢጠሩም እምቢ ተብለዋል:: ሆኖም ግን አሰልጣኙ ከቅዱስ ጊዮርጊስ የመረጧቸውን አምስት ተጫዋቾችና ከአገር ውጭ ከሚጫወቱት ሕመልስ በቀለና ጌታነህ ከበደ በስተቀር 15 ተጫዋቾችን ይዘው ልምምዳቸውን ዛሬ ጀምረዋል። \n \nጥያቄ: ኢትዮጵያ በ29ኛው የእግር ኳስ የአፍሪካ ዋንጫ ከዛምቢያ ጋር ስትጨወት ግብ ያስቆጠረው ማነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አዳነ ግርማ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: የዚምባቡዌ ሀገር ቀድሞ ምን ተብሎ ይታወቅ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልስ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nኮረማሽ ኮረማሽ በአማራ ክልል ውስጥ፤ በሰሜን ሸዋ የምትገኝ ወረዳ ናት። ከአዲስ አበባ በምሥራቅ በኩል ሰማንያ አምሥት ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ሥፍራ ስትሆን፣ በስምጥ ሸለቆ ምሥራቃዊ ፍንጭ አናት ላይ ያላት ገዥ ይዞታ ከአፋር (የቀድሞው አዳል) እና ከሶማሌ በኩል በታሪክ ዘገባ ይመነጩ የነበረቱን እስላማዊ አጥቂዎች ለመከላከል የተመቸች ቦታ በመሆኗ የተመሠረተች ጥንታዊ ምሽግ ናት። ከፊት ለፊትዋ የመገዘዝ ተራራ፤ እንኮይ፤ ሰንበሌጥ፤ ቡልጋ እና ወደ ምሥራቅ የደረቂት እና አማሪት ወንዞች ከከሰም ወንዝ ጋር ሲቀላቀሉ እንዲሁም የመስኖ ዘንባባ ተራራ እና የመስኖ ማርያም ቤተ ክርስቲያን፤ ሜዳማው የሾላ ገበያ ወደደቡብ ምሥራቅ ደግሞ ከማዶ የክርስቶስ ሰምራ ትውልድ አገር እና ምንጃር ቁልጭ ብለው ይታያሉ። የአካባቢው ቃለ ታሪክ ሥፍራዋ በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አያት ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ እንደተመሠረተች ሲያረጋግጥ፤ የልጅ ልጃቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ደግሞ የሸዋ ንጉሥ በነበሩ ጊዜ እስካሁን ድረስ ያለውን ታላቅ የመሣሪያ ምሽግ እና በግቢው ውስጥ ያሉትን አሥራ አንድ ቤቶች እንዳሠሩ ብዙ የጽሑፍና የቃል ታሪኮች እንዲሁም ሕንጻዎቹ እራሳቸው ምስክር ናቸው። ከነኚህ አሥራ አንድ ሕንጻዎች ሁለቱ በ ፲፱፻፸፯ ዓ/ም በሉተራን ኃይማኖታዊ ተልዕኮ ልገሣ ታድሰው የ ጥራ ጥሬ እና የ እህል ምርት ማከማቻ ጎተራ ሆነዋል። ሌሎቹ ቤቶች የወረዳው ፍርድ ቤት፤ የቤተ ክህነት ጽ/ቤት ፤ የወረዳው የፖሊስ ጽ/ቤት እና የመሳሰሰሉ መንግሥታዊ ቢሮዎችን ይዘዋል። በጥቅምት ወር ፲፱፻፱ ዓ/ም አዲስ በተመሠረተው የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እና የራስ ተፈሪ መኮንን መንግሥት ላይ ጦርነት አውጀው ከወሎ የዘመቱትን የልጅ እያሱ አባት ንጉሥ ሚካኤልን ሊከላከል የተሰለፈው የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሠራዊት ጥቃቱን ያደራጀው እዚሁ ኮረማሽ ላይ ሲሆን፡ ኋላም ዓርብ ጥቅምት ፲፯ ቀን ራስ ተፈሪና ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሰገሌ ሜዳ ላይ ንጉሥ ሚካኤልን ድል ያደረጉት ከዚሁ ደጀን ቦታ ነው። በ፳፻፩ ዓ/ም ከ ዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የኤሌክትሪክ መሥመር ተዘርግቶ ለዚች መንደርና ለአካባቢው የቡልጋ ሕዝብ የልማት መስፋፊያ ጮራ ተገልጾለታል። በዘመናዊ መልክ የተገነባው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በተመረቀበት ዋዜማ፣ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ባለው የአሥራ ሦስት ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ ላይ በሳምንት ሁለት ጊዜ፤ ማለትም ሐሙስ እና ቅዳሜ ለገበያ የሚያመች የሕዝብ መመላለሻ የአውቶቡስ መሥመር አገልግሎቱን ጀምሮ፣ በተለይም ቆለኞቹ ምርታቸውን ወደ ገበያ በማቅረብ ላይ የነበረባቸውን የእግር ጉዞ እንግልት ቀንሶላቸዋል። ወደፊትም ገብያቸውን ሐሙስ ገበያ ድረስ ከመሄድ እዚችው ኰረማሽ ላይ ለመመሥረት ተስፋ ሰጥቷቸዋል። ለ የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምረቃ ሥነ ስርዐት የተጓዙ እንግዶች በዚሁ የአውቶቡስ አገልግሎት ከሐሙስ ገበያ እስከ ኮረማሽ ድረስ ቢያንስ የሦስት ሰዐት የእግር ጉዞ ቀርቶላቸዋል። \n \nጥያቄ: በኮረማሽ ወረዳ ፲፱፻፱ ዓ/ም በተደረገው ጦርነት ማን አሸነፈ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ራስ ተፈሪና ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: ሳርፌ ቢዝነስ የብረታ ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ለመትከል ያቀደው በየት ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በዱከም ከተማ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. የማሊ ፌደሬሽን የተፈጠረው ማሊን ከማን ጋር በማድረግ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ከሴኔጋል ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nቱርክመንኛ ቱርክመንኛ (Türkmen) የቱርክምኒስታን ብሔራዊ ቋንቋ ነው። በቱርክመኒስታን 3,430,000 ተናጋሪዎች ሲኖሩ ከቱርክመኒስታን ውጭ ደግሞ 3 ሚሊዮን የሚያሕሉ ተናጋሪዎች በተለይም በኢራን (2 ሚሊዮን) በአፍጋኒስታን (500,000) እና በቱርክ (1000) አሉ። ቱርክመንኛ በቱርኪክ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይከተታል። ይህም አንዳንዴ በትልቁ አልታይ ቋንቋ ቤተሰብ ውስጥ ይደመራል። ቀድሞ የተጻፈበት ወይም በቂርሎስ ወይም በ አረብ ፊደሎች ነበር፤ አሁን ግን የቱርክመኒስታን መሪ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በላቲን ፊደል እንዲጻፍ አዋጀ። በ1994 አ.ም. ደግሞ የሳምንት ቀኖችና የወር ስሞች ሁሉ እንደ አቶ ኒያዞቭ \"ሩህናማ\" የሚባል ይፋዊ መጽሐፍ ፍልስፍና በአዋጅ ተቀየሩ። \n \nጥያቄ: ቱርክመንኛ የየት ሀገር የሥራ ቋንቋ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የቱርክምኒስታን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nበ1913 በፕሬዝዳንት ዋረን ሃርዲንግ ዘመን ሄርበርት ሁቨር የአሜሪካ የንግድ ሚኒስትር ሆኑ። በሃርዲንግ ተከታይ በፕሬዝዳንት ካልቪን ኩሊጅ ዘመን ደግሞ እንዲህ ያለን ማዕረግ ይዘው አገለገሉ። የንግድ ሚኒስትር እየሆኑ ሃይለኛ ሰው ነበሩ። የንግድ ዘርፍና መንግሥት አንድላይ ይሠሩ የሚለውን ተስፋ በመያዛቸው በዚህ አንጻር ብዙ አደረጉ። በማዶ ባሕርና በውጭ አገር ለባለጉዳዮች ምክርና እርዳታ የሚሰጡ መሥርያ ቤቶች በማስከፈቱ የአለም አቀፍ ንግድ በጉልበት አስለሙ። በተለይም የሆሊዉድ ፊልም ማዶ ባሕር ለመግፋፋት ጉጉ ነበሩ። ዜጎችም ቤት እንዲያገነቡና የራሳቸው መሬት ባለአባት እንዲሆኑ አበረታቷቸው። ስለ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የክላርክ ሰነድ በ1920 ተጽፎ ሁቨር ፕሬዝዳንት እየሆኑ በ1922 ግልጽ ሆኖ ወጣ። በዚህ ሰነድ ዘንድ፥ አውሮጳ በላቲን አሜሪካ ላይ ዛቻ ካልጣለች በተቀር አሜሪካ በውጭ አገር ጥልቅ ለማለት ሕጋዊ መብት አልነበራትም የሚል ማስታወሻ ነበር። በዚያን ጊዜ አሜሪካ ሠራዊት በኒካራጓና በሃይቲ ነበራት። ስለዚህ ሁቨር ከነዚህ አገራት የሠራዊቱን ቁጥር ቀነሱ። በላቲን አሜሪካ ውስጥ የጦርነት መሣርያ እንዳይደርስ ማዕቀብ ለመጣል አሠቡ። በ1924 ጃፓን ማንቹርያን በወረረ ጊዜ አዲስ ፖሊሲ አወጡ። እሱም በግፍና በወረራ የሚገኝ የመሬት ለውጥ ሁሉ አናከብርም የሚል ነበር። ከታላቁ ጭፍግግ የተነሣ ብዙ ባንክ ቤቶች ስለወደቁ አንዳችም ብድር ለማግኘት ከባድ ሆነ። ብዙ ሰዎች ሥራ ፈት ሆኑ። በአውሮፓም ምጣኔ ሃብቱ ችግር ውስጥ ስለ ገባ ሁቨር ጀርመን ስለመጀመርያው ጦርነት ለፈረንሳይ ከምትከፍል ካሣ ለአንድ አመት ይቅር ትበል የሚል ዕቅድ አዋጁ። በሚከተለውም አመት የጀርመን ዕዳ በሙሉ ተሰረዘ። በ1925 ምርጫ ተቃራኒው ፍራንክሊን ሮዘቨልት በሰፊ መጠን አሸነፉና በሳቸው ፈንታ ፕሬዚዳንት ሆኑ። ሁቨር ፕሬዚዳንት ከሆኑ በኋላ ረጀም ዕድሜ ነበራቸው። እስከ 1957 ዓ.ም. ድረስ ኖሩ። ከ2ኛ አለማዊ ጦርነት ቀጥሎ በ1939 ስለ ቀድሞው ልምዳቸው ፕሬዚዳንት ሃሪ ትሩማን የአውሮፓ ምግብ ፍላጎት ለመወሰን ወደ አውሮፓ ላኳቸው። \n \nጥያቄ: ሄርበርት ሁቨር በይፋ ፕሬዝዳንት የሆነው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ1922 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nቶማስ ጄፈርሰን ቶማስ ጄፈርሰን (ሚያዝያ 7 ቀን 1735 ~ ሰኔ 28 ቀን 1818 ዓ.ም.) ከየካቲት 26 ቀን 1793 እስከ የካቲት 25 ቀን 1801 ዓ.ም. ድረስ የአሜሪካ 3ኛ ፕሬዝዳንት ነበሩ። ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኚያን ያቋቋሙት ጄፈርሰንም ነበሩ። ቶማስ ጄፈርሰን ከአባቱ ከፒተር ጄፈርስን እና ከእናቱ ጄን ራንዶልፍ ተወለዱ። ቶማስ በአሜሪካ አብዮት ጊዜ በ1768 ዓ.ም. ከእንግሊዝ ንጉሥ የአሜሪካ ነጻነት ዐዋጅ ጻፉ። በኋላ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ የመርከብ ሃያላት ወደ አልጀርስ ላኩ፣ ከናፖሌዎን ደግሞ ሰፊ መሬት በሚሲሲፒ ወንዝ አቅራቢያ (የሉዊዚያና አቅራቢያ የተባለው) ገዝተው ነበር። ይህ ድርጊት የአሜሪካ ስፋት በሁለት እጅ አስፋፋ። \n \nጥያቄ: ቶማስ ጄፈርሰን የአሜሪካ ስንተኛ ፕሬዝደንት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 3ኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: በኢትዮጵያ ስንት ቋንቋዎች ይነገራሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ ፹ በላይ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nጥንታውያን የግብጽ ባለሥልጣኖች በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ከማየ አይኅ ቀጥሎ መጀመሪያ የአፍሪካ ሕዝብ የኖኅ ልጅ የካም ዘሮች ናቸው፤ ይህ አገር ሰናዖር ለሚሉት ቅርብ ስለ ነበር የባብል ግንብ ከተሠራ በኋላ ከዚህ ተነስተው ወደ ግብፅ ወረዱ። የግብጽ ቀድሞ ዘመን መንግሥት ዋና ጥንታዊ ነው፤ የመሠረተውም ፈርዖን ሜኒስ የተባለው ነው። ጸሓፊው ጊዮርጊስ ስንቄሎስ (፰፻ ዓ.ም. አካባቢ የጻፈው) ይህ ፈርዖን ሜኒስ በዕውነት የካም ልጅ ምጽራይም እንደ ነበረ ገመተ። ዳሩ ግን አባ አውሳብዮስ በጻፉት ዜና መዋዕል ዘንድ (፫፻፲፯ ዓ.ም. ተጽፎ)፣ የድሮ ግብጻዊው ባለታሪክ ማኔጦን (፫ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ.) ስለ ኋለኞቹ ግብጻውያን ሲጽፍ፣ ይኮሩበት የነበረው የታላቁ ጥንት ዘመን ከማየ አይህ አስቀድሞ እንዳለፈ፣ በኋላም በዚያው አገር ዳግመኛ ከሠፈረበት ከካም ልጅ ምጽራይም በውኑ እንደ ተወለዱ ጽፎ ነበር። ተመሳሳይ ታሪክ በእስላም ጸሐፊዎች በግብጻዊው እብን አብድ ኤል-ሀከም እና በፋርሳውያን አል-ታባሪና ሙሐመድ ቈንዳሚር መጻሕፍት ሲገኝ፣ ፒራሚዶች፣ እስፊንክስ ወዘተ. ሁሉ የተሠሩ ከጥፋት ውኃ በፊት በኖሩት ክፉ ዘሮች ሆኖ፣ ከዚያ በኋላ ግን አገሩ ለካም ተወላጅ ለምጽራይም ('ማሣር' ወይም 'መሥር') ተሠጠ ብለው ጻፉ። \n \nጥያቄ: በመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት ካም የማን ልጅ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የኖኅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nፍራንክሊን ሮዘቨልት ፍራንክሊን ዴላኖ ሮዘቨልት (1874-1937 ዓ.ም.) የኒው ዮርክ አገረ ገዥና የአሜሪካ 32ኛ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ሮዘቨልት በቀድሞ ፕሬዚዳንት ዉድሮው ዊልሶን ዘመን የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነበሩ። በ1913 ምርጫ የምክትል ፕሬዚዳንት ዕጩ ሆኑ። ጄምስ ኮክስም የፕሬዚዳንት ዕጩ ነበሩ። ነገር ግን ኮክስና ሮዘቨልት በዋረን ሃርዲንግና በካልቪን ኩሊጅ ተሸነፉ። ሮዘቨልት በ1920 ዓ.ም. የኒው ዮርክ አገረ ገዥ ሆኑ። በታላቁ ጭፍግግ ሳቢያ ፕሬዚዳንት ሄርበርት ሁቨር በጣም ስላልተወደደ በ1925 ምርጫ ሮዘቨልት ሁቨርን አሸነፏቸው። ሮዘቨልት በጣም ስለተወደደ በ1929 ዓ.ም. ምርጫ ለሁለተኛ የ4 አመት ዘመን ተመለሱ። እንዲሁም በ1933 ምርጫ ለሦስተኛ ዘመንና በ1937 ምርጫ ለአራተኛ ዘመን ተመረጡ። በጠቅላላ 4 ዘመኖች ተቀበሉ። በ2ኛ አለማዊ ጦርነትም የአሜሪካ መሪ ነበሩ። ነገር ግን ፖሊዮ ከሚባል በሽታ የተነሣ አካለ ስንኩል ሆነው ባለ መንኮራኩር ወምበር ነበራቸውና በአራተኛው ዘመን መሃል ሞቱ። ምክትላቸው ሃሪ ትሩማን ወዲያው ፕሬዚዳንት ሆኑ። ፍራንክሊን ሮዘቨልት አራት ጊዜ በመመረጣቸው ከሁሉ ይልቅ ለረጅም ዘመን ገዙ። ከሳቸው በኋላ የመንግሥት አንደኛ ዘርፍ የሆነ የሕግ አማካሪ ቤት ወደፊት ሌላ ፕሬዚዳንት እንደሱ 3 ወይም 4 ዘመናት እንዳይቀብል አንፈልግም የሚል ድምጽ አሰሙ። ስለዚህ በ1943 ዓ.ም. የአሜሪካ መንግሥት 2ኛ ዘርፍ የሆኑት ፕሬዚዳንቶች ከ2 ጊዜ (እነሱም 8 አመታት) በላይ ሊያገለግሉ አይችሉም የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ ሕጋዊ ደንብ ሆነ። \n \nጥያቄ: ሮዘቨልት ወደ ፕሬዝዳንትነት ከመምጣታቸው ቀድሞ ገለግሉት የነበረው ምን ላይ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ የባሕር ኅይል ምክትል ሚኒስትር ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበሕንድ ንጉሥ አሾካ መንግሥት የአሾካ አዋጆች ሕግጋት በ264 አክልበ. መሠረቱ። ከምዕራቡ ሮማ መንግሥት ውድቀት ደግሞ ወደ ተረፈው ሕዋእ ውስጥ ከፈለሱት ጀርመናውያን ወገኖች አብዛኛው የራሳቸውን ሕጎች ዝርዝር በጽሑፍ አወጡ። በተለይ የሚታወቁም የቪዚጎቶች አለቃ ዩሪክ ሕግ (463 ዓ.ም.)፣ የቡርጎንዳውያን ሕግጋት (እኚህ ለጀርመናውያንና ለሮማውያን የተለያየ ፍትሕ ነበራቸው)፣ የአላማናውያን ሕግጋትና፣ የፍራንኮች ሕግጋት ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ የተጻፉት ከ492 ዓ.ም. ጀምሮ ነው። በ498 ዓ.ም. የቪዚጎቶች አለቃ 2ኛ አላሪክ መጽሐፈ ቴዎዶስዮስና አንዳንድ የተለያዩ የቀድሞ ሮማ ሐገጋት አከማችተው አዋጁአቸው። ከዚህም በኋላ የታዩ ሕጎች የሎምባርዶች ሕግጋት (635 ዓ.ም.)፣ የቪዚጎቶች አዳዲስ ሕግጋት (646 ዓ.ም.)፣ የአላማናውያን አዳዲስ ሕግጋት (722 ዓ.ም.) እና የፍሪዝያውያን ሕግጋት (777 ዓ.ም.) አሉ። በአውሮፓ አኅጉር ላይ የተጻፉት እነኚህ ፍትሖች ሁሉ በሮማይስጥ ቢጻፉም፣ በእንግሊዝ አገር ግን የተጠቀሙት ሕጎች ከኬንት ንጉሥ ኤጠልቤርት ሕጎች (594 ዓ.ም.) ጀምሮ በጥንታዊ እንግሊዝኛ የተቀነባበሩ ነበሩ። በ885 ዓ.ም. ታላቁ አልፍሬድ ይህንንና ሁለት የድሮ ፍትሖች ከሕገ ሙሴና ከሕገ ወንጌል ጋራ አጋጥመው የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ዶም ቦክ ሠርተዋል። \n \nጥያቄ: በ885ዓ.ም. የድሮ ሕጎችን፣ የኦሪትና የወንጌል ሕግጋትን በመጠቀም አዲስ የእንግሊዝ ሕገ መንግሥት ያዘጋጀው ንጉሥ ማን ይባላል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አልፍሬድ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየማይዳሰሱ (ኢንታንጀብል) ባህላዊ ቅርሶችን የሚመለከተው የዩኔስኮ አካል በይነ መንግሥታዊው ኮሚቴ 10ኛ ስብሰባውን ከኅዳር 20 እስከ ኅዳር 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በናሚቢያ መዲና ዊንድሆክ በተደረገው 10ኛ የዩኔስኮ ጉባዔ ለውሳኔ ከቀረቡት 35 (ሠላሳ አምስት) ባሕላዊ ቅርሶች መካከል የሲዳማ ብሔር የአዲስ ዓመት ዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ የ2003 የኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ ዓለም አቀፍ ስምምነት መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱ አባል አገሮች ውይይት ካደረጉበት በኋላ ፍቼ ጫምባላላ ተመዝግቧል፡፡ ይህም ከመስቀል በዓል ቀጥሎ የኢትዮጵያ ሁለተኛው የማይዳሰስ ዓለም አቀፍ የሰው ልጆች ወካይ ቅርስ ሆኖ ሕዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር 9፡40 በፋይል ቁጥር (01054) በውሳኔ ቁጥር 10.com.10.b.16 ተመዝግቧል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት የመስቀል በዓል አከባበርን በዩኔስኮ ማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከ ሲሆን በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ ከህዳር 23-28 ቀን 2006 ዓ.ም በተካሄደው 8ኛው የዩኔስኮ የኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃ የኢንተርገቨርንመንታል ኮሚቴ መደበኛ ጉባዔ ውሳኔ መሰረት የመስቀል በዓል አከባበር በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ተካቷል፡፡ በ2006 የበጀት ዓመት የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ፊቼ ጫምበላላን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ የሚያስችል የጥናት ሰነድ (ኖሚኔሽን ፋይል) ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ የተላከውና ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም የተመዘገበው የተደረገው ፊቼ ጫምበላላ ሰነዶች በሚከተለው የዩኔስኮ ድረ ገጽ ላይ ለመላው ዓለም ተለቀው ይገኛል፡፡ በተመሳሳይም በ2007 የበጀት ዓመት ኦሮሞ ህዝብ የማንነት መገለጫ የሆነው የገዳ ስርዓትን በሰው ልጆች ወካይ ኢንታንጀብል ባህላዊ ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ለማካተት የሚያስችል የኖሚኔሽን ሰነድ ተዘጋጅቶ ለዩኔስኮ መጋቢት 2007 ዓ.ም ተልኳል፡፡ \n \nጥያቄ: በዚህ ስብሰባ ላይ ስንት ባህላዊ ቅርሶች ለውሳኔ ቀረቡ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ 35 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣2012 (ኤፍቢሲ) ፌስቡክ ከግል መረጃ መጠበቅ ጋር ተያይዞ የአባላት የስልክ ቁጥሮች በጓደኞች ጥቆማ ሂደት ላይ መጠቀም ሊያቆም መሆኑ ተገለፀ ፡፡ የተጠቃሚዎች የፌስቡክ አድራሻ በጠላፊዎች በቀላሉ እንዳይገኝ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ኮድ እንዲላክ ምርጫ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ፌስቡክ የተጠቃሚዎችን ስልክ ቁጥር ለማስታወቂያ እና በጓደኛ ጥቆማ ሂደት ላይ ሲጠቀምበት እንደነበረ አስታውቋል፡፡ በአሁን ወቅት ከአሜሪካ አዲስ የቁጥጥር ስርዓት ጋር ተያይዞ ይሄን አሰራር ለማቆም ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡ \n \nጥያቄ: ፌስቡክ የተጠቃሚዎች አድራሻ እንዳይገኝ ምን አይነት ዘዴዎችን ሲጠቀም ቆይቷል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ኮድ እንዲላክ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሰቆጣ ሰቆጣ ከ1956 ጀምሮ የዋግ አውራጃ ማዕከል እና የሰቆጣ ወረዳ ዋና ከተማ ነው። ከሰቆጣ 6 ኪሎ ሜትር ወጣ ብሎ የውቅሮ መስቀል ክርስቶስ አለት ውቅር ቤ.ክ. ይገኛል። በዚሁ ቤተ ክርስቲያን ላስታን ከሰቆጣ ሆነው ያስተዳደሩ ዋግሹሞች ደረቅ ቅሪቶች ይገኛሉ። ከአክሱም መዳከም በኋላ በአረብ ጸሐፊዎች ዘንድ እንደ የኢትዮጵያ ዋና ከተማነት ብዙ ጊዜ የሚጠቀሰውኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል ሰቆጣ እንደነበር በታሪክ ግንዛቤ አለ። ስለሆነም ይመስላል፣ ላስታን በዋግ ሹም ማዕረግ ያስተዳደሩ ገዢዎች መቀመጫቸው ሰቆጣ ነበር። ከጥፋት በተረፉ መዝገቦች ዘንድ ሰቆጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠቅሶ የምናገኘው በ1738ዓ.ም. ሲሆን፣ ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ ወደ ላስታ ባደረጉት ዘመቻ ሰቆጣ ውስጥ በዋግ ሹም ነዓኩቶ ለአብ (የዋግ ሹም ቴዎድሮስ አባት) ቤት ለ5ቀን እንዳረፉ ዜና መዋዕላቸው በማተቱ ነው ። ከዚያም በ19ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ የአውሮጳ ተጓዦች ሰቆጣን ሲጎበኙ፣ ዋልተር ፕላውዴን ለምሳሌ በኢትዮጵያ ከሚገኙ 5 ብቻ ነጋድራሶች አንዱ በሰቆጣ ይገኝ እንደነበር መዝግቧል። ከዚያም በ1800ዎቹ መጨረሻ ሰቆጣን የጎበኘው ኤ.ቢ.ዋይልድ ሰቆጣን የላስታ ዋና ከተማ አድርጎ ሲጠቅስ፣ የሰቆጣ ቤተ መንግስት ባለ ሶስት ፎቅና በ1650ዎቹ የተገነባ እንደነበር ያትታል። ቤተ መንግስቱን የሰሩት የፋሲል ግቢን አናጺዎ እደሆኑም መላምት ያቀርባል። ይሄው የአውሮጳ ተጓዝ፣ በ1880ዎቹ የሰቆጣ ገበያ ከአካባቢው ካሉት ሁሉ ግዙፉ እንደነበር ፣ የዝሆን ጥርስ እና በቅሎ ገበያው የደራ እንደነበር፣ እንዲሁም 21፣000 በሬዎች፣ 2፣900 ላሞች፣ 10ሺህ ፍየሎች፣ 1፣500 በጎች በየአመቱ ለግብይት ይቀርቡበት እንደነበር ሳይጠቅስ አላለፈም። ጥር 2፣ 1929 ጣሊያኖች በሰቆጣ ላይ የመርዝ ጋዝ ቦምብ እንደጣሉ በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል። \n \nጥያቄ: ኩባር የተሰኘው የጥንቱ የኢትዮጵያ ገናና ማዕከል የት ይገኛል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሰቆጣ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የአማራ ፣ እና የኦሮሞ የትግራይ እንደሁም የሶማሌ ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የሀገሪቷ ሕዝብ ቁጥር ከ 3/4ኛ በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ። በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች ክርስትና እና እስልምና በስፋት የሚስተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እስልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች አማርኛ እና ኦሮምኛ ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች አፍሮ-ኤስያዊ እና ናይሎ ሳህራዊ በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም ኩሻዊ፣ ኦሞአዊ እና ሴማዊ የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ። ኩሻዊ ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ አፋን ኦሮሞ ፣ ሶማልኛ ፣ አፋርኛ ፣ ሲዳምኛ ፣ ሃዲያኛ እና ከምባትኛ ሲሆኑ ከአባይ-ሰሃራዊ የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት በርታኛ ፣ ኩናማኛ ፣ ጉሙዝኛ ፣ ሙርሲኛ እና የመሳሰሉት ናቸው። \n \nጥያቄ: የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ ምንድን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አማርኛ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nማሊ የማሊ ሪፐብሊክ (ማሊ) በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ የለሽ ሀገር ናት። ከምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች በስፋት ሁለተኛ ናት። ከአልጄሪያ፣ ኒጄር፣ ቡርኪና ፋሶ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ጊኔ፣ ሴኔጋል እና ሞሪታኒያ ጋር ድንበር ትዋሰናለች። ማንዴ ሕዝቦች አውራጃውን ሠፍረው ተከታታይ መንግሥታት አጸኑ። እነዚህም የጋና መንግሥት፣ የማሊ መንግሥትና የሶንግሃይ መንግሥት ያጠቅልላሉ። በነዚህ መንግሥታት ውስጥ ቲምቡክቱ ለትምርትና ለመገበያየት ቁልፍ ከተማ ነበረች። በ1583 ዓ.ም. በሞሮኮ በተካሄደ ወረራ የሶንግሃይ መንግሥት ኃይል ለማነስ ጀመር። ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በፈረንሣይ ቅኝ ተገዝታ «ፈረንሳያዊ ሱዳን» ወይም «የሱዳን ሪፐብሊክ» ትባል ነበር። ፈረንሳያዊ ሱዳን በኅዳር 16 ቀን 1951 ዓ.ም. በፈረንሳያዊ ማሕበረሠብ ውስጥ 'ራስ-ገዥ ሁኔታ' አገኝታ በመጋቢት 26 1951 ዓ.ም. ከሴኔጋል ጋር አንድላይ የማሊ ፌደሬሽን ሆኑ። ይህ የማሊ ፌዴሬሽን በሰኔ 13 ቀን 1952 ነጻነት አገኘ። ነገር ግን በነሐሴ 14 ቀን ሴኔጋል ከፌዴሬሽኑ ወጣች። በመስከረም 12 ቀን 1953 ዓ.ም. ፈረንሳያዊ ሱዳን በሞዲቦ ኪየታ ስር ራሷን 'የማሊ ሬፑብሊክ' አዋጀችና ከማሕበረሰቡ ወጣች። ሞዲቦ ኪየታ በ1968 እ.ኤ.ኣ. በተደረገው መፈንቅለ መንግሥት ከወረደ በኋላ እስከ 1991 እ.ኤ.አ. ድረስ ማሊ በማውሳ ትራዎሬ ተመራች። በ1991 እ.ኤ.አ. የተካሄዱ ተቃውሞች ወደ መፈንቅለ-መንግሥት አመሩ። ከዚያም የተሸጋጋሪ መንግሥት ተቋቋመና አዲስ ሥነ-መንግሥት ተጻፈ። በ1992 እ.ኤ.አ. አልፋ ዑመር ኮናሬ የማሊን የመጀመሪያ ዴሞክራሲያዊ ምርጫን አሸነፉ። ማሊ ከባሕር ጋር ግንኙነት የላትም። የሀገሩ አብዛኛው ክፍል በሰሐራ በረሃ ውስጥ ይገኛል። ከተፈጥሮ ሀብቶች ውስጥ ወርቅ፣ ዩራኒየም፣ ፎስፌት፣ ካዎሊን፣ ጨው፣ ኖራ (ላይምስቶን) ይጠቀሳሉ። የማሊ ፓርላማ 147 ሰዎች ሲኖረው እነዚህ ተወካዮች በህዝብ ብዛት ነው የሚመረጡት። ማሊ ከዓለም ደሀ ሀገሮች አንዷ ስትሆን 65 ከመቶ የሚሆነው መሬት በረሃ ነው። አብዛኛው የኤኮኖሚ እንቅስቃሴ በኒጅር ወንዝ አካባቢ ነው የሚካሄደው። 10 ከመቶ የሚሆነው ሕዝብ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ የሚኖር ሲሆን 80 ከመቶ የሚሆነው የሥራ ሃይል በእርሻና ዓሣ ማጥመድ ተሰማርቷል። የኢንዱስትሪው እንቅስቃሴ በእርሻ ምርቶች ላይ ያተኩራል። የሸክላ ሥራ በሴቶች የሚከናወን ሲሆን በነጋዴዎች በገበያዎች ይሸጣል። ሸክላዎቹ የሚሰሩበት ባሕላዊ ሂደት የቱሪስት መሳቢያ ነው። \n \nጥያቄ: ማሊ በ1880 እ.ኤ.አ. በማን ቅኝ ተገዛች?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በፈረንሣይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nየአመራር ክፍሎች ናይጄሪያ በሠላሳ ስድስት ክፍላገራት እና አንድ የፌዴራል ግዛት ተከፍላለች። እነዚህ ክፍላገራት ወደ ፯፻፸፬ የአካባቢ ግዛቶች ተከፍለዋል። ስድስት የናይጄሪያ ከተሞች ከአንድ ሚሊዮን በላይ ነዋሪዎች አሉባቸው። እነዚህም ሌጎስ፣ ካኖ፣ ኢባዳን፣ ካዱና፣ ፖርት ሀርኮርት እና ቤኒን ከተማ ናቸው። ሌጎስ ከ፰ ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሲኖሩባት ከሣህራ በታች በአፍሪካ ትልቁ ከተማ ናት። ብሔረሰቦች በናይጄሪያ ውስጥ ከ፪፻፶ በላይ ብሔሮች ይገኛሉ። ትልቆቹ ብሔሮች ፉላኒ ወይም ሀውዛ፣ ዮሩባ እና ኢግቦ ናቸው። ከእነሱ ቀጥሎ ደግሞ ኤዶ፣ ኢጃው፣ ካኑሪ፣ ኢቢብዮ፣ ኑፔ እና ቲቭ ይገኛሉ። በናይጄሪያ ውስጥ የተቆጠሩት ቋንቋዎች ፭፻፳፩ ይሆናሉ። ከእነዚህም ውስጥ ፭፻፲ቹ መደበኛ ተናጋሪዎች አሏቸው። ሁለት ቋንቋዎች እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ብቻ ነው የሚነገሩት። ዘጠኙ ደግሞ ተናጋሪ የሌላቸው የጠፉ ቋንቋዎች ናቸው። ከእንግሊዝኛ በኋላ ዋናዎቹ ልሳናት ዮሩብኛ፣ ሐውዝኛና ኢግቦኛ ናቸው። \n \nጥያቄ: በናይጄሪያ ተናጋሪ ያላቸው ስንት ቋንቋዎች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፭፻፲ቹ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጋና ጋና በአፍሪካ አትላንቲክ ጠረፍ ላይ የተገኘ አገር ሲሆን ከ24 ሚሊዮን ኗሪዎች በላይ አሉት። የጋና ስራ ቋንቋ እንግሊዝኛ ሲሆን፣ ሌሎች ኗሪ ቋንቋዎች በተለይም ትዊኛ (አካንኛ) በሰፊ ይነገራሉ። የ«ጋና» ስያሜ በታሪክ የድሮ «ጋና መንግሥት» ወይም «ዋጋዱጉ መንግሥት» ለማክበር በ1949 ዓም ተመረጠ። እንዲያውም ያው መንግሥት እስከ 1068 ዓም ድረስ ከጋና ወደ ስሜን-ምዕራብ በአሁኑ ማሊ ይገኝ ነበር እንጂ የዛሬውን ጋና መቸም አልገዛም። «ጋና» በትክክል የዋጋዱጉ መንግሥት አለቆች ማዕረግ ሆኖ ነበር። ዋጋዱጉ መንግሥት በ1068 ዓም ግድም ከወደቀ ቀጥሎ፣ የአካን ብሔሮች ከዚያው ፈልሰው በዛሬው ጋና ሠፈሩና መጀመርያ ግዛቶችን መሠረቱ። ከ1662 እስከ 1949 ዓም ድረስ የአሻንቲ መንግሥት ባካባቢው ቆየ፤ በ1894 ዓም ይህ የብሪታንያ አሻንቲ ጥብቅ ግዛት ሆነ። ከ1949 ዓም አስቀድሞ የዩናይትድ ኪንግደም ጥገኛ ግዛት ሲሆን በወርቅ ሀብቱ ምክንያት «የወርቅ ጠረፍ ጥገኛ ግዛት» (ጎልድ ኮስት ፕሮቴክቶሬት) በመባል ይታወቅ ነበር። ከ1984 ዓም ጀምሮ ዴሞክራሲያዊ እና ፓርላሜንታዊ መንግሥት ኖሮታል። አብዛኞቹ ኗሪዎች (70%) በተለይ በደቡቡ ክርስቲያን ሲሆኑ፣ በተለይ በስሜኑ 16% የእስልምና ተከታዮች ናቸው። የተረፉትም የኗሪ አረመኔነትን እምነቶች ይከተላሉ። የጋና ዋና ምርቶች ካካዎ፣ ዘይት፣ አልማዝ ናቸው። በአለሙ ከሁሉ ትልቅ የሆነው ሠው ሰራሽ ሐይቅ፣ ቮልታ ሐይቅ፣ በጋና ይገኛል። እግር ኳስ ከሁሉ የተወደደው እስፖርት ነው። የጋና አበሳሰል በተለይ በኮቤ፣ ጐርጠብ፣ የስኳር ድንች፣ ባቄላ፣ በቆሎ፣ ኦቾሎኒ፣ ባሚያና ሩዝ ይሠራል። \n \nጥያቄ: ቮልታ ሐይቅ በዓለም ካሉ ከሰው ሠራሽ ሐይቆች ሲነጻጸር መጠኑ እንዴት ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከሁሉ ትልቅ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአብርሀም ሊንከን (የካቲት ፮ ቀን ፲፰፻፩ ዓ.ም. - ሚያዝያ ፰ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም.) ድረስ የኖሩ ከ፲፰፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ነበሩ። ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. ከአሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ጆን ዊልክስ ቡዝ በተባለ ነፍሰ ገዳይ እጅ በጥይት ተመትተው ተገደሉ። የአብርሀም አባት ማሀይም ገበሬ ቢሆንም፣ አብርሀም ከልጅነት ጀምሮ እራሱን በትጋት ያስተምር ነበር። በ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. ለኢሊኖይ ክፍለ ሀገር ምክር ቤት መቀመጫ ተመረጡ። የሕግ ትምህርት በጠንካራ ትጉነት አጥንቶ የሕግ ባለሙያ ሆነ። ከ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ጀምሮ የባርነት ተቃዋሚ ሆነ። ከአፍሪካ የተወሰዱት ጥቁር ሕዝቦች በግብርና መሥራት እንዲገደዱ ትክክለኛ ወይም ጥሩ ሀሣብ አይደለም ብለው አመኑ። ዳሩ ግን በ1834 ብዙ ባርያዎች ባገለገሉበት ቤተሠብ ውስጥ ያደገችውን ሚስታቸውን ሜሪ ቶድን አገቡ። ሜሪ ያለ ባርያዎች ከባልዋ ጋር መኖር ትንሽ የተቸገሩ ቢሆነም ከጊዜ ብዛት ግን ለምደዉ 4 ወንድ ልጆችን በተከተሉት አመታት ወለዱ። በ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. የባርነት ተቃዋሚዎች ወገን ሪፐብሊካን ፓርቲ መሥርተው አብርሀም ከፍተኛ ሚና ተጫወቱ። በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ዘመቻ፣ እሳቸው የሪፐብሊካን ዕጩ ሆኑ። ምርጫው በተደረገበት ቀን በጥቅምት ፳፰ ቀን ፲፰፻፶፫ ዓ.ም.፣ ሊንከን አሸነፉ። በጦርነቱ የስሜን ሠራዊት ከብዛታቸው የተነሣ በአራት ዓመት ውስጥ አሸነፉ። በዚህ ጊዜ ላይ ሊንከን ለአመጸኖቹ ባርዮች ነጻነት አዋጁ። ያላመጹ ዜጎች ባርያዎች ግን በዚያን ጊዜ ነጻ አልወጡም። በ፲፰፻፶፮ዓ.ም.ምርጫ ሊንከን በቀላል ለሁለተኛ ጊዜ ለፕሬዚዳንትነት ተመረጡ። በሚያዝያ ፪ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ.ም. የኮንፌደራት ሠራዊት እጁን ሰጠ። ነገር ግን ሚያዝያ ፯ ቀን የመድረክ ትርዒት ሲያዩ በነፍሰ ገዳዩ በጆን ዊልክስ ቡዝ እጅ በጥይት ተመትተው በማግሥቱ ሞቱ። ከዚህም ትንሽ በኋላ ባርነት በሕግ በሙሉ ተክለክሎ የተረፉት ባርያዎች ነጻነት አገኙ። \n \nጥያቄ: አብርሃም ሊንከን ለመጀመሪያ ጊዜ ለፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ዕጩ የሆኑት መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ በ፲፰፻፶፪ ዓ.ም. ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nቀጭኔ ቀጭኔ በአፍሪካ የሚኖር ባለሙሉ ጣት ሸሆኔ ጡት አጥቢ አራዊት ሲሆን በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ የመጀመሪያውን ደረጃ ይዞ ይገኛል። ወንዱ ከ 4.4 እስከ 5.5 ሜትር ርዝማኔና 1,360 ኪሎግራም ክብደት ያስመዘግባል። እስካሁን በሪኮርድ የተያዘው የ 5.87ሜና የ2000ኪ.ግ ቀጭኔ ነው። ሴቶቹ በጥቁቱ አነስ ብለው ይታያሉ። እነዚህን ፍጥረታት በአራዊት ማቆያ ቦታዎች አንገታቸውን ከታጠሩበት አጥር በላይ ወጣ አድርገው የተመለከተ ሰው በአፍሪካ ቁጥቋጦዎች ነፃ ሆነው ሲሮጡ ያላቸውን ውበትና ግርማ መገመት ያስቸግራል። የቀጭኔ እንቅስቃሴ ትልቅ ግርማ ያለውና እንደ ውኃ ሙላት የሚፈስ ነው። በገላጣው የግጦሽ መስክ ላይ በሚጋልቡበት ጊዜ ቁመናቸው ትንሽ እንቅፋት ቢነካቸው ወድቀው የሚሰባበሩ ያስመስላቸዋል። ይሁን እንጂ እስከ 1, 300 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደት ያላቸው ወንድ ቀጭኔዎች ቀልጣፋና ምንም የማያደናቅፋቸው ሯጭ ከመሆናቸውም በላይ በሰዓት እስከ 60 ኪሎ ሜትር ሊሮጡ ይችላሉ። ይህች አስደናቂ ፍጡር የምትገኘው በአፍሪካ ብቻ ነው። እርጋታዋና ሰላማዊ ተፈጥሮዋ ዓይን ይስባል። የቀጭኔ ፊት በዓይነቱ ልዩ የሆነና ቆንጆ ሊባል የሚችል ሲሆን ረዥምና ጠባብ ጆሮዎች፣ ሁለት ትናንሽ ቀንዶች እንዲሁም ጠቆር ያለ ለስላሳ ጠጉር አላት። ዓይኖቿ በጣም ትላልቅና ጥቁር ሲሆኑ ረዣዥም በሆኑ ቅንድቦች ይጠበቃሉ። ቀጭኔ ያን በመሰለ ከፍታ ላይ ሆና ሩቅ ስትመለከት ፊቷ ላይ የየዋህነት ገጽታ ይታይባታል። በጥንት ዘመናት ቀጭኔ ባላት አስደሳች ቁመና እንዲሁም ጨዋ፣ ዓይነ አፋርና ሰላማዊ ባሕርይ ያላት በመሆኑ በጣም ተወዳጅና ትልቅ ግምት የሚሰጣት ነበረች። በብሔራት መካከል ሰላምና በጎ ፈቃድ መኖሩን ለማመልከት የቀጭኔ ግልገሎች ለነገሥታትና ለገዥዎች በገጸ በረከትነት ይሰጡ ነበር። ጥንታዊ በሆኑት የአፍሪካ አለቶች ላይ ቀለማቸው የደበዘዘ የቀጭኔ ሥዕሎች እስከ ዛሬ ይታያል። ከእንስሳት ሁሉ ቀጭኔን በቁመት የሚወዳደር የለም። ሙሉ ዕድሜ ላይ የደረሱ ወንድ ቀጭኔዎች ከእግራቸው ኮቴ አንስቶ እስከ ቀንዳቸው ድረስ ከ5.5 ሜትር የሚበልጥ ርዝመት አላቸው። በግብፃውያን ጥንታዊ ሥዕላዊ የአጻጻፍ ዘዴ ቀጭኔ በረዥም ቁመቷና አርቆ በመመልከት ችሎታዋ ምክንያት “መተንበይ” የሚለውን ግሥ ትወክል ነበር። ቀጭኔ በአፍሪካ መስኮች በሚሰማሩት የሜዳ አህዮች፣ ሰጎኖች፣ አጋዘኖችና ሌሎች እንስሳት መካከል ስትቆም እንደ ማማ ሆና ትታያለች። ቁመቷና አርቆ የማየት ችሎታዋ ማንኛውንም አደጋ ገና ከሩቅ ለማወቅ ያስችላታል። ስለዚህ የቀጭኔ መኖር ለሌሎች እንስሳት የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር ጥርጥር የለውም። \n \nጥያቄ: ቀጭኔ በምድር ከሚገኙ እንሰሳት በርዝማኔ ስንተኛ ደረጃ ይዞ ይገኛል?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የመጀመሪያውን ደረጃ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nኤንመርካር ኤንመርካር በሱመር (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የኡሩክ (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የኡቱ ልጅ መስኪያጝካሸር ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከኤአና ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል። የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። «ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ» በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የጸሓይ አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በኤሪዱም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ አራታ እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል። በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት ሹቡር፣ ሐማዚ፣ ሱመር፣ ኡሪ-ኪ (የአካድ ዙርያ) እና የማርቱ አገር ናቸው። ከዚህ በላይ የኤንመርካርን መንግሥት የሚገልጹ ሦስት ተጨማሪ ጽሑፎች አሉ። «ኤንመርካርና ኤንሱሕጊርዓና» የሚባል ተረት የኤንመርካርና የአራታ መቀያየም ሲገልጽ፣ ሐማዚ ተሸንፎ እንደ ነበር ይጠቅሳል። በ«ሉጋልባንዳ በተራራ ዋሻ»፣ ኤንመርካር በአራታ ላይ ዘመቻ ሲመራ ይታያል። አራተኛውና መጨረሻውም ጽላት፣ «ሉጋልባንዳና የአንዙድ ወፍ» ኤንመርካርና ሠራዊቱ በአራታ ዙሪያ ለ1 አመት እንደ ከበቡት ይላል። ለመሆኑ ኤንመርካር 50 አመት ከነገሰ በኋላ፣ የማርቱ ሕዝብ (አሞራውያን) በሱመርና በአካድ ሁሉ ተነሥተው ኡሩክን ለመጠብቅ ግድግዳ በበረሃ መስራት እንደ ነበረበት ይጠቅሳል። በነዚህ መጨረሻ 2 ጽላቶች፣ ከኤንመርካር ጦር አለቆች አንድ የሚሆን ሉጋልባንዳ የሚባል ሰው ይተረታል። በሱመር ነገሥታት ዝርዝር ዘንድ፣ ይህ ሉጋልባንዳ «እረኛው» ኤንመርካርን ወደ ኡሩክ ዙፋን ተከተለው። ይህ ሉጋልባንዳ ደግሞ በጊልጋመሽ ትውፊት በተባለው ግጥም ዘንድ የኋለኛው ኡሩክ ንጉሥ የጊልጋመሽ አባት ነበረ። ዴቪድ ሮኅል የሚባል አንድ የታሪክ ሊቅ የኤንመርካርና የናምሩድ ተመሳሳይነት አመልክቷል። «-ካር» የሚለው ክፍለ-ቃል በሱመር ቋንቋ ማለት «አዳኝ» ነው። ኡሩክ ከተማ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ነበር ሲባል፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በሌላ ትውፊቶች ዘንድ ይህ ናምሩድ የባቢሎን ግንብ መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪም አቶ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም «ባቤል» እንደ ነበር ያምናል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ። «ባቢሎን» ማለት የኤሪዱ መጠሪያ እንደ ነበር የሚል ማስረጃ በሌሎችም ጥናቶች አለ። ሮማዊው ጸሐፊ ክላውዲዩስ አይሊያኑስ በጻፈ አንድ ትውፊት ዘንድ (200 ዓ.ም. ግድም)፣ የባቢሎን ንጉስ «ኤወኮሮስ» የተከታዩን «ጊልጋሞስ» አያት ይባላል። ይህ «ጊልጋሞስ» ማለት የኡሩክ ንጉስ ጊልጋመሽ መሆኑን የአሁኑ ሊቃውንት ስለ ገነዘቡ፣ እንዲሁም «ኤወኮሮስ» ማለት ኤንመርካር ሳይሆን አይቀርም የሚል አስተሳሰብ ያቀርባሉ። ከዚህ በላይ የከላውዴዎን ታሪክ ጸሐፊ ቤሮሶስ በጻፈው ዝርዝር መሰረት፣ ከማየ አይህ ቀጥሎ የከላውዴዎንና የአሦር መጀመርያው ንጉስ «ኤወኮዮስ» ይባላል፤ ስለዚህ የዚሁ «ኤወኮዮስ»ና የናምሩድ መታወቂያ አንድ ናቸው የሚለው አሳብ ለረጅም ዘመን የቆየ ነው። \n \nጥያቄ: “የኤንመርካርና የአራታ ንጉስ” በሚል ተረት ውስጥ ከሱመር ነገስታት መካከል ኤንመርካር የማን ልጅ ነው?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የኡቱ ልጅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፓርጦሎን ፓርጦሎን በአየርላንድ ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ ከማየ አይኅ ጥቂት ክፍለ ዘመናት ቀጥሎ መጀመርያው በአይርላንድ ደሴት ላይ የደረሱት ሰፈረኞች መሪ ወይም ንጉሥ ነበር። የፓርጦሎን ስም በታሪክ መጻሕፍት መጀመርያው የሚታወቅ በ820 ዓ.ም. አካባቢ በሮማይስጥ በተጻፈው ሂስቶሪያ ብሪቶኑም («የብሪታንያውያን ታሪክ») ሊገኝ ይችላል። በዚሁ ጽሁፍ መሠረት፣ «ፓርጦሎሙስ» ከ1 ሺህ ሠፈረኞች (ወንዶችና ሴቶች) ጋር ደረሰ፣ እስከ 4 ሺህም ድረስ ቶሎ ተባዙ፣ ነገር ግን ድንገት በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁላቸው ከቸነፈር ሞተዋልና አገሩ እንደገና ባዶ ሆነ። ይኸው መጽሐፍ በአየርላንድኛ ትርጉም ደግሞ ቸነፈሩ በፓርጦሎን ሕዝብ ላይ የመጣበት ጠንቅ ፓርጦሎን ከኗሪ አገሩ ገና ሳይወጣ ወላጆቹን ገድሎአቸው ስለ ነበር የአምላክ ፍርድ ነው በማለት ይጨምራል። ከዚህ በላይ የፓርጦሎን መነሻ አገር እስኩቴስ እንደ ነበር፣ የማጎግ ተወላጅ እንደ ነበር ይታመን ነበር። የስኮት (በስኮትላንድና ቀድሞ በአይርላንድ የተገኘ) ብሔር ስም ከዚህ እስኩቴስ እንደ መጣ በድሮው መጻሕፍት በሰፊው ይጻፍ ነበር። \n \nጥያቄ: ፓርጦሎን የምን ሃገር ንጉስ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ አይርላንድ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nአራት ማዕዘን አራት ማዕዘን ማናቸውም አራት ቀጥተኛ መስመር የሆኑ \"ጎኖች\"ና አራት መገናኛወች ያላቸውን የሚወክል የሂሳብ ስያሜ ነው። እኒህ ጎኖች መነባበር ወይም አንዱ ባንዱ ላይ መንሳፈፈ የለባቸውም አለዚያ አራት ማዕዘን አይባሉም። የአራት ማዕዘን አራቱ ውስጣዊ ማዕዘኖች ሲደመሩ ምንጊዜም ውጤታቸው 360 ዲግሪ ነው። ፓራላሎግራም ሁለቱ ጎኑ ትይዩ የሆነ አራት ማዕዘን ፓርላሎግራም ይባላል። በፓራላሎግራም ስር የሚተድዳደሩ እንግዲህ ካሬ፣ ሬክታንግል፣ ሮምበስና ሮምባቶይድ ይባላሉ። ሮምበስ ማለት አራቱም ጎኑ እኩል የሆነ ፓራልላሎግራም ነው። በሌላ አነገጋገር ተጻራሪ ጎኖቹ ትይዩ ሲሆኑ ተጻራሪ ማዕዘኖቹ ደግሞ እኩል ናቸው፣ ወይም ደግሞ ዲያጎናሎቹ በ90 ደጊሪ እኩል ለኩል ይቋረጣሉ። ወይም በሌላ አባባል ወደጎን የተገፋ ካሬ ማለት ነው። ሮምባቶይድ ማለት ፓራሎግራም ሆኖ ተነካኪ ጎኖቹ እኩል ያልሆኑና ማዕዘኖቹ ኦብሊክ የሆኑ ማለት ነው። በሌላ አባባል የተገፋ ሬክታንግል ማለት ነው። ሬክታንግል ማለት አራቱም ማዕዘኖቹ 90ዲግሪ የሆነ አራት ማዕዘን ማለት ነው። በሌላ አባባል ዲያጎናሎቹ እኩል ሆነው እኩል የሚቋረጡ ማለት ነው። ካሬ አራቱም ጎኖቹ እኩል የሆኑ እንዲሁም አራቱም ማዕዘኖቹ 90 ዲግሪ የሆኑ ማለት ነው። በአንድ ጊዜ ሮምበስ እና ሬክታንግል የሆነ አራት ማዕዘን ምንጊዜም ካሬ ነው። \n \nጥያቄ: ፓራሎግራም ሆኖ ተነካኪ ጎኖቹ እኩል ያልሆኑና ማዕዘኖቹ ኦብሊክ የሆኑ አራት መአዘን ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ሮምባቶይድ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጁፒተር እና ሳተርን ጁፒተር እና ሳተርን ከ4 መቶ አመት በሆላ ትላንት ምሽት በአንድ ላይ ገጥመው አንድ ፕላኔት መስለው ታይተዋል፡፡ ፕላኔቶቹ ከቀን ቀን እየተቀራረቡ መጥተው ትላንት ምሽት በአንድ ላይ በመግጠም ደማቅ ብርሃን ፈንጥቀዋል፡፡ የሁለቱ ግዙፍ ፕላኔቶች ምህዋር በየ20 ዓመቱ የሚገናኙ ሲሆን ክስተቱ በብዛት በቀን ውስጥ ስለሚሆን በዓይን ለማየት ከባድ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ‘ዘ ስታር ኦፍ ቤቴልሄም’ ወይም የቤቴልሄም ኮከብ ተብሎ በሚጠራው በዚህ ክስተት ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ሰማይ ላይ እጅግ ደማቅ ብርሃን ታይቶ እንደነበር ሳይንቲስቶች መናገራቸውን ዘ ጋርዲያን አስነብቧል፡፡ \n \nጥያቄ: ጁፒተር እና ሳተርን ከስንት አመት በኋላ ነው የገጠሙት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ከ4 መቶ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዶናልድ ጆን ትራምፕ ዶናልድ ጆን ትራምፕ (ጁን 14 ቀን 1946 እ.ኤ.አ. ተወለደ) አሜሪካዊ ነጋዴ ፣ ፖለቲከኛ ፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቹ ታዋቂ እና 45ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ፕሬዚደንት ነው። ሥልጣኑንም እ.ኤ.አ. በጃኑዌሪ 20 ቀን 2017 ተረክቧል። በክዊንስ ኒው ዮርክ ከተማ የተወለደው አቶ ትራምፕ በሪል እስቴት ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የፍሬድ ትራምፕ ልጅ ነው። በኮሌጅ እያለም ኤሊዛቤት ትራምፕ ኤንድ ሰንስ በተባለው ድርጅት ይሠራ ነበር። በእ.ኤ.አ. 1968 ከኮሌጅ ከተመረቀ በኋላ ያንን ድርጅት ተቀላቀለ። በእ.ኤ.አ. 1971 ደግሞ ሙሉ ሥልጣን ከተሠጠው በኋላ የድርጅቱን ስም ወደ \"ዘ ትራምፕ ኦርጋናይዜሽን\" ለወጠው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ካሲኖዎችን ፣ የጎልፍ ሜዳዎችን ፣ ሆቴሎችን እና ሌሎች በእርሱ ስም የሚጠሩ ንብረቶችን አፍርቷል። እ.ኤ.አ. ከ2005 እስከ 2015 ድረስ ዘ አፕሬንቲስ የተባለ ፕሮግራምን በኤን ቢ ሲ ላይ ያቀርብ ነበር። እ.ኤ.አ. በ2000 ላይ፣ ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንትነት ተወዳድሮ ሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነትን አሸንፎ ነበር። በእ.ኤ.አ. ጁን 16 2015 ላይ ደግሞ ለፕሬዚደንትነት እንደሚወዳደር አሳወቀ። ይህን ጊዜ ግን የሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ነው። በስደት፣ በነፃ ገበያ እና በጦር ጣልቃ ገብነት ላይ ባለው ተቃውሞ ምክንያት ታዋቂ ሆኗል። በእነኚህ አነጋጋሪ አስተያየቶቹ በመላው ዩናይትድ ስቴትስ የተቃውሞ እና የድጋፍ ሰልፎች እንዲካሄዱ ምክንያት ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ሜይ 2016 ከሪፐብሊካን የፕሬዚደንታዊ እጩነት ውድድሮች ውስጥ 28ቱን ውድድሮች ካሸነፈ በኋላ እና የተቀሩት ተቀናቃኞቹ እነ ቴድ ክሩዝ እና ጆን ካሲች ከውድድሩ ራሳቸውን ስላገለሉ፥ ትራምፕ ለሪፐብሊካን ፓርቲ እጩ መሆኑ የተረጋገጠ ሆኗል። በእ.ኤ.አ. ከጁላይ 18 እስከ 21 በተካሄደው የ2016ቱ የሪፐብሊካኖች አገር አቀፍ ስብሰባ ላይ እጩ መሆኑ በይፋ ታወጀ። በእ.ኤ.አ. ኖቬምበር 8 ቀን 2016 ላይ የፕሬዚደንትነት ምርጫውን አሸነፈ። ማሸነፉንም ተከትሎ ብዙ የተቃውሞ ሠልፎች በተለያዩ የአሜሪካ ከተሞች ውስጥ ተካሂዶ ነበር። በ70 ዓመቱም ሥልጣን ላይ በመውጣቱ ከእርሱ በፊት ከነበሩት ፕሬዚደንቶች ሁሉ በዕድሜ ትልቁ ያደርገዋል። \n \nጥያቄ: ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዮናይትድ ስቴትስ ፕሬዘዳንትነት ተወዳዳሪ ለሁለት የሪፎርም ፓርቲ እጩነት ያሸነፈው መቼ ነበር?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ እ.ኤ.አ. በ2000 ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nናጊብ ማህፉዝ ናጊብ ማህፉዝ በ1988 እ.ኤ.አ. በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ሽልማትን የተቀዳጀ ግብጻዊ ደራሲ ነው። ማህፉዝ ካይሮ ውስጥ ገማልያ በተባለው ሰፈር ዲሴምበር 11፣ 1911 እ.ኤ.አ. ተወለድ። የመጠሪያ ስሙን የወረሰው ሲወለድ አዋላጅ ሃኪም ከነበሩት ከፕሮፌሰር ናጊብ ማህፉዝ ፓሻ ነው። ማህፉዝ ለረጅም ዘመን በመንግስት መስሪያቤቶች ውስጥ ያገለገል ሲሆን በስነ-ጽሁፉም ዘርፍ 34 ወጥ ልብ-ወለዶች፣ ከ350 የሚዘሉ አጫጭር ታሪኮች፣ ከደርዘን በላይ የሲኒማ ድርሰቶች፣ እና አምስት ተውኔቶችን አበርክቷል። በ1971 ያሳተመው «ጭውውት በአባይ ወንዝ ላይ» የተሰኘው ድርሰቱ ተወዳጅነትን ካተረፉለት ስራዎቹ መካከል ሲሆን የገማል አብድል ናስር አገዛዝ በግብጽ ማህበረሰብ ላይ ያደረሰውን ዝቅጠት የሚተች ነው። የገብላዊ ልጆች የተሰኘው ሌላው ልብ-ወለዱ ተምሳሌታዊ በሆነ መልክ እግዚአብሄርን እና የታላላቆቹን እምነቶች መስራቾች (ሙሴን፣ እየሱስን እና መሃመድን) በገጸባህርይነት የቀረጸበት በመሆኑ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ ታግዶ ቆይቷል። በ1989 ሳልማን ሩሽዲ ሰይጣናዊ ጥቅሶች (Satanic Verses) የተሰኘ መጽሃፉን በማሳተሙ የኢራኑ መሪ አያቶላህ ሮላህ ኾሚኒ የግድያ ትእዛዝ ካስተላለፉበት በኋላ ግብጻዊው የስነ-መለኮት መርማሪ ኦማር አብዱል ራህማን ለጋዜጠኞች በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ላይ «ማህፉዝ 'የገብላዊ ልጆች'ን ሲያሳትም ተገቢው ቅጣት ተሰጥቶት ቢሆን ኖሮ ሩሽዲ 'ሰይጣናዊ ጥቅሶች'ን ለማሳተም ባልደፈረ ነበር» በማለቱ ይህንኑ ቃሉን እንደ ግድያ ትእዛዝ የወሰዱ ጽንፈኞች በ1994 ዓ.ም ማህፉዝን በስለት አንገቱ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሰውበታል። አጥቂዎቹ አላማቸው ማህፉዝን መግደል ነበር ቢባልም እሱ ግን በህይወት ለመትረፍ ችሏል። ይኽ መጽሃፍ ከ2006 መጀመሪያ ወሮች አንስቶ እንደ አዲስ ግብጽ ውስጥ ታትሞ መሰራጨት ጀምሯል። ማህፉዝ የአንዋር ሳዳት መንግስት ደጋፊነቱ የታወቀ ሲሆን ግብጽ ከእስራኤል መንግስት ጋር በካምፕ ዴቪድ ያደረገችው የሰላም ስምምነት ደጋፊም ስለነበር ድርሰቶቹ ለብዙ ዓመታት በአረብ አገራት ታግደው ቆይተው እገዳው የተነሳላቸው የኖቤል ሽልማትን እንዳሸነፈ ከተሰማ በኋላ ነው። ማህፉዝ የኖቤልን ሽልማት ለመቀበል ለግብጽም ሆነ ለአረቡ ዓለም የመጀመሪያው ሲሆን በስነ-ጽሁፍ የኖቤል ተሸላሚ ከሆኑት ሰዎች ሁሉ የረጅም እድሜ ባለቤት በመሆን ሶስተኛ ደረጃን የያዘ ሰው ነው። ማህፉዝ ኦገስት 30 ቀን፣ 2006 አርፎ ቀብሩ በኦገስት 31 ቀን ካይሮ ውስጥ በሚገኘው የአል ረሽዳን መስጊድ ተፈጽሟል። \n \nጥያቄ: ናጊብ ማህፉዝ አምላክን በመገዳደር አስወንጅሎት መጽሃፉም በግብጽ ውስጥ እንዳይሰራጭ ለረጅም ጊዜ የታገደወው ድርሰቱ ምን ይባላል?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ የገብላዊ ልጆች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nበቁርጥራጭ ብረትና ያገለገሉ ማሽኖች ንግድ የተሰማራው ሳርፌ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ የግንባታ ብረታ ብረቶች ማምረቻ ፋብሪካ በዱከም ከተማ ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሆነ አስታወቀ፡፡ የሳርፌ ቢዝነስ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ክብርይስፋ ተክሌ ለሪፖርተር እንደተናገሩት፣ ኩባንያው እስካሁን ቁርጥራጭ ብረቶች ከውጭ በማስመጣትና ከአገር ውስጥ በመግዛት ለብረት አቅላጮች ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ የብረት ማቅለጫው ማሽኖች ከህንድ ተገዝተው የሚመጡ ሲሆን፣ የብረት መዋቅሩ ደግሞ ከቻይና ይገዛል፡፡ የፋብሪካው ጠቅላላ የኢንቨስትመንት ወጪ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚገመት የተናገሩት አቶ ክብርይስፋ፣ ፋብሪካው ለ300 ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡ ሳርፌ ቢዝነስ ለብረት ፋብሪካው ግንባታ የሚሆን 30,000 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከዱከም ከተማ አስተዳደር በቅርቡ መረከቡን ገልጸው፣ ኩባንያቸው ተገቢውን የአዋጭነት ጥናት ማሠራቱን አስረድተዋል፡፡ \n \nጥያቄ: የሳርፌ ብረታ ብረት ማምረቻ ፋብሪካ እውን ለማድረግ ምን ያህል ብር ያስፈልገዋል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአማራ (ክልል) አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ሲሆን ከ 1994 በፊት አራት የሀገሪቱን ዋና ወና ክፍለ ሀገራት የ ካትት ነበር እነሱም በጌምድር ጐጃም ወሎና ሸዋ ነበሩ ።የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ ይገኛል። በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል። የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል። የክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም 20,875,456 እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ 33.9% አካባቢ ድርሻ ይይዛል ተብሎ ይገመታል። ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው። የአማራ፣ የአገው፣ የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው። እንዲሁም የአማራ ክልል አሁን ላይ የክልል ከተማው ባህር ዳር ነው። በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣ በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮ፣ ዋልያ፣ ጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳና ነብር፣ ሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል። ክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎ በአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም። \n \nጥያቄ: በአማራ ክልል ስንት የከተማ አስተዳደሮች ይገኛሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፴፰ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በዚምባብዌ በስሚዝ አመራር ወቅት በጆሱዋ ንኮሞ የሚመራው ፓርቲ ምን ይባል ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሚስተር ኤልቤሽቲ ባደረጉት ንግግር፣ ሊቢያ ኦይል ለአፍሪካ ልዩ ትኩረት በመስጠት በመሥራት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ በኢነርጂ መስክ አፍሪካ ውስጥ አስተማማኝ አጋር ሆኖ መሥራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ ሊቢያ ኦይል በ18 የአፍሪካ አሮች 1,015 የነዳጅ ማደያዎች አሉት፡፡ ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ በሊቢያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን እ.ኤ.አ. በ2004 የተመሠረተ ኩባንያ ነው፡፡ አፍሪካ ውስጥ ያሉትን ቢዝነስ የገዛው ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው፡፡ በቅርቡ ናሽናል ኦይል ኢትዮጵያ (ኖክ) ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን በ450 ሚሊዮን ብር መግዛቱን አስታውቋል፡፡ ሊቢያ ኦይል የጂቡቲ ንብረቱን አለመሸጡንና ኖክ ኩባንያውን የገዛው ከጂቡቲ መንግሥት እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ሊቢያ ኦይል ወደ ጂቡቲ ከመግባቱ ከብዙ ዓመታት በፊት በተፈጠረ የባህር ውኃ ብክለት ምክንያት የጂቡቲ መንግሥት ከፍተኛ የካሳ ክፍያ በመጠየቁ በተፈጠረ አለመግባባት፣ የጂቡቲ መንግሥት የኦይል ሊቢያ ጂቡቲና የቶታል ጂቡቲ ንብረቶችን ወርሷል፡፡ የጂቡቲ መንግሥት የሊቢያ ኦይልና የቶታል ንብረቶችን ለሽያጭ አቅርቦ ሊቢያ ኦይል ጂቡቲን ኖክ፣ ቶታልን ደግሞ አንድ የፈረንሣይ ኩባንያ መግዛታቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ \n \nጥያቄ: ሊቢያ ኦይል ሆልዲንግ ኩባንያ አፍሪካ ውስጥ ያለውን ቢዝነስ የገዛው ከእነማን ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከሼልና ከኤክሶን ሞቢል ኩባንያዎች ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳህሌ ደጋጎ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከእናታቸው ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ አብራክ በ1923 ዓ/ም በምዕራብ ወለጋ ልዩ ስሙ ነጆ ከተባለው ሥፍራ ተወለዱ። እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በነቀምት አንደኛ ደረጃ እና በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ዘመናዊ ትምህርቱን ከተከታተለ በኋላ በነበረው ልዩ የውትድርና ፍቅር በቀድሞ 1ኛ ክፍለ ጦር በኋላም ማዕከላዊ ዕዝ ተብሎ በተጠራው የክ/ዘበኛ የጦር ክፍል ውስጥ በ1942 ዓ/ም ተቀጥሯል። በነበረው ሙያዊ ብቃትና ወታደራዊ ሥነ ሥርዓት አክባሪነት ከተራ ወታደርነት በአንድ ጊዜ የሃምሳ አለቅነት ማዕረግ ማግኘት የቻለው ሣህሌ፤ በሂደት እስከ ኮሎኔል ደረጃ ደርሷል። ወደ ሙዚቃ ቀማሪነት፣ ዜማና ግጥም ደራሲነት እንደዚሁም ወደ የማዕከላዊ ዕዝ የሙዚቃ ባንድ ኃላፊነት ከመሸጋገሩ በፊት በእግረኛ ባንድ ውስጥ “ክላርኔት” የተሰኘው የሙዚቃ መሣሪያ ተጫዎች የነበረው ሣህሌ ደጋጎ፣ የሙዚቃን ትምህርት የቀሰመው ከፈረንሣዊው መምህሩ ሙሴ ኒኮ መሆኑን የሕይወት ታሪኩ ላይ ተጠቅሷል። ከክላርኔት በተጨማሪ “አኮርዲዮን፣ አልቶ-ሳክስ፣ ፒያኖ” የተሰኙትን የሙዚቃ መሣሪያዎችንም በብቃት ይጫወት ነበር። በጠቅል ራዲዮ ጣቢያ (በተቋቋመ ጊዜ ) በአኮርዲዮን ጥዑም ዜማ ለጣቢያው አድማጮች ሲያንቆረቁር ከነበሩት የሙዚቃ ሰዎች መካከል ሣህሌ ደጋጎ የመጀመሪያው ነበር። ከእነ ሻለቃ ግርማ ይህደጎ፣ ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ እና ከሻለቃ ባሻ ገብረዓብ ተፈሪ ጋር በመሆን የክቡር ዘበኛ ኦርኬስትራን ስም እፁብ ድንቅ በማድረጉ በኩል የበኩሉን ሚና ተጫውቷል። ግጥምና ዜማ ደራሲ ከመሆኑም ባሻገር የአጫጭር እና ረዣዥም ድራማዎች ፀሐፊ የነበረው ሣህሌ፣ «ሁለገብ የታሪክ ማኅደር» ያሰኘውን ተግባር በሕይወት ዘመኑ አከናውኗል። \n \nጥያቄ: ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ ከወላጆቻቸው ከእነማን ተወለዱ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ከወይዘሮ ደጊቱ ፈይሣ እና ከባላንባራስ ደጋጎ አለቤ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nዩናይትድ ኪንግደም ዩናይትድ ኪንግደም ማለት የተባበረው ግዛት በተለመደው እንግሊዝ አገር ሲባል፣ እንዲያውም እንግሊዝ አገር ወይም ደግሞ «ኢንግላንድ» ከዩናይትድ ኪንግደም ዋና ክፍላገሮች አንዱ ብቻ ነው። ሌሎቹም፦ ስኮትላንድ ዌልስ ሰሜን አይርላንድ ናቸው። ከነዚህም እንግሊዝ፣ ስኮትላንድና ዌልስ አብረው «ታላቋ ብሪታንያ» የምትባል ደሴት ናቸው። ከ1699 ዓ.ም. (1707 እ.ኤ.አ.) አስቀድሞ፣ እንግሊዝና ስኮትላንድ የተለያዩ ንጉዛት ነበሩ። ከ1595 ዓ.ም. ጀምሮ ግን 2ቱ አገራት አንድ ንጉሥ ነበራቸውና በ1699 በመዋሐዳቸው አንድ ላይ «ዩናይትድ ኪንግደም» ሆነዋል። \n \nጥያቄ: እንግሊዝና ስኮትላንድ ተዋህደው «ዩናይትድ ኪንግደም» የፈጠሩት መቼ ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ በ1699 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የሴቶች የስራ ፈጠራ ፕሮጀክትን ለማገዝ የሚውል የ100 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነት ተፈራረሙ። ከባንኩ ትዊተር ገጽ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ድጋፉ ሴት ስራ ፈጣሪዎችን ስራዎቻቸውን ለማሳደግ የሚችሉበት ገንዘብ፣ ክህሎትና አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል ተብሏል፡፡ \n \nጥያቄ: የሴቶችን የሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ለማገዝ የሚውል የ100 ሚሊዮን ብር ስምምነት የፈረመው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሚያዝያ ፲፰ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፳፰ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፳፫ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፴፰ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፴፯ ቀናት ይቀራሉ። ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ። ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ታሽኬንት በትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ክስተት ስትወድም ሰብ ስምንት ሺ መኖሪያ ቤቶች በመጥፋታቸው ከሦስት መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎቿ መኖሪያ ቢስ ሆነዋል። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በሼክ ሞሀመድ ማህሙድ ኤል ሳዋ የተመራ የሳዑዲ አረቢያ\tልዑካን ቡድን ለአጭር ጉብኝት አዲስ አበባ ገባ። ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ከደርግ በተላለፈ ትእዛዝ መሠረት፣ የፖሊስ አለቆች፤ የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ታሠሩ። ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር። \n \nጥያቄ: የሳዑዲ አረቢያ ልዑካን ቡድን በሼክ ሞሀመድ ማህሙድ ኤል ሳዋ እየተመራ ለአጭር ጉብኝት በስንት ዓመተ ምህረት አዲስ አበባ ገባ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፱፻፷፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nሮማንሽ ሮማንሽ ወይም ሩማንች (Rumantsch) ከስዊስ አገር 4 ብሔራዊ ቋንቋዎች 1ዱ ሆኖ ሌሎቹ 3 ጀርመንኛ ጣልኛና ፈረንሳይኛ ናቸው። ከሮማይስጥ የታደገ ቋንቋ በመሆኑ የሮማንስ ቋንቋ ቤተሠብ አባል ነውና በተለይ የሚመስለው ፈረንሳይኛ ወይም እጣልኛ ነው። የሚናገረው በግራውብውንደን (ግሪዞን) ካንቶን ስዊስ በሚኖሩ 60,000 ሰዎች ነው። ይህ ከስዊስ አገር ሕዝብ ብዛት 1% ብቻ ሲሆን ከስዊስ አገር ብሔራዊ ቋንቋዎች ሁሉ ትንሹ ነው። እንኳን በስዊስ አገር ከሚኖሩት ስርቦ-ክሮዌሽኛ ተናጋሪዎች ቁጥር ብዛት (111,000) በግማሽ ያንሳል። በስሜን እጣልያ አገር ዛሬ ለሚናገሩ ቋንቋዎች ለፍሪዩልያንና ለላዲን ቅርብ ዘመድ ነው። \n \nጥያቄ: በስዊስ ከሮማንሽ በተጨማሪ ምን ምን ብሔራዊ ቋንቋዎች አሉ?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ጀርመንኛ ጣልኛና ፈረንሳይኛ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሺስቶሶሚሲስ ሺስሰቶሶሚያሲስ (ቢልሃርዚያ እና ካታያማ ትኩሳት በመባል ይታወቃል፡፡) በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትላትሎች በሆነው የ ሺስቶሶማ የህዋስ አይነት ነው፡፡ የ ሽንት መተላለፊያ ወይም አንጀት ሊያጠቃ ይችላል። የህመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል። ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትብ ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል። ቢልሃርዝያ በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ ያሉበት ውሀ ላይ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው። እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በታዳጊ ሀገራት በሚነኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱም ልጆቹ በተበከለ ውሃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ በእለት ከእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለውን ውሀ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠቃልላቸው ቡድኖች ናቸው። ሄልመንት በሽታዎች በሚባለው ቡድን ውስጥ ይጠቃለላሉ። ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች በሽንት ወይም ሰገራ ላይ በመመርመር ነው፡፡ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ ማረጋገጥም ይቻላል። በሽታውን የመከላከያ መንገድ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ያጠቃል፣ እንዲሁም የሚገመተው ከ 12 000 እስከ 200,000 የሚሆነው ሕዝብ በአመት ውስጥ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በ አፍሪካ ፣ እንዲሁም በ እስያ ና ደቡም አሜሪካ ነው። ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ፣ ከ70 በላይ ሃገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚሲሰ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀፅሎ በሁለተኛነት ያለ፣ እንደ ትላትል ትልቅ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው። ከጥንት ጀምሮ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ፣ ሲስቶሶሚሲሰ የ በሽንት ውስጥ ያለ ደም ምልክት የሚታየው በስሕተት እንደ የወንድ አይነት ወር አበባ እየተባለ በ ግብፅ እናም ለወንዶች ልጆች እንደ rite of የአምልኮ መተላለፊያ ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ የሚመደበው ችላ ከተባሉት የትሮፒካል በሽታ ስር ነው። \n \nጥያቄ: በሽታውን እንዴት መከላከል ይቻላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ንፁህ ውህ አቅርቦትን ማሻሻልና የቀንድኣውጣ ቊጥርን መቀነስ ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሴኔጋል ከ፹ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሏት። ፓርላማዋ ሁለት ምክር ቤቶች አሉት። አንዱ ፻፳ መቀመጫዎች ያሉት የብሔራዊ ስብሰባ (እንግሊዝኛ፦ National Assembly) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ፻ መቀመጫዎች ያሉት ሴኔት ነው። ሴኔጋል ራሱን የቻለ ህግ ተርጓሚ አካል አላት። ዳኛዎቹ የሚሾሙት በፕሬዝዳንቱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ሴኔጋል የዴሞክራሲ ሂደት ስኬታማ ነው ከሚባሉት የቀድሞ ቅኝ ተገዢ ሀገራት መካከል የምትጠቀስ ናት። የአካባቢ አስተዳዳሪዎች በፕሬዝዳንቱ ነው የሚሾሙት። ማራባውት የሚባሉ የእስልምና ሃይማኖት መሪዎችም በሴኔጋል ጠንካራ የፖለቲካ ተፅእኖ አላቸው፡ ከ፪ ሚሊዮን ነዋሪዎች ያሉበት የሴኔጋል ዋና ከተማ ዳካር የሀገሩ ትልቁ ከተማ ነው። ሁለተኛው ፭፻ ሺህ ሰዎች የሚኖሩበት ቱባ ከተማ ነው። ሴኔጋል ከ12.5 ሚልዮን በላይ የሚሆን ሕዝብ አላት። ከዚህ ውስጥም ወደ ፵፪ ከመቶ በገጠር ነው የሚኖረው። የአሜሪካ የስደተኖች ኮሚቴ ባቀረበው የ2008 እ.ኤ.አ. የዓለም ስደተኞች አጠቃላይ ቅኝት መሠረት ሴኔጋል በ2007 እ.ኤ.አ. ወደ 23,800 የሚገመቱ ስደተኞች ይኖሩባታል። ከዚህ አብዛኛዎቹ የመጡት ከሞሪታኒያ ነው። ስደተኞቹ በንድዮም፣ ዶዴል እና በሴኔጋል ወንዝ አቅራቢያ በሚገኙ ሠፈሮች ይኖራሉ። የአገር ይፋዊ ብሔራዊ ቋንቋ ፈረንሳይኛ ሲሆን ከብዙ ኗሪ ቋንቋዎች 11ዱ በተለይም ዎሎፍኛ አገራዊ ዕውቅና አላቸው። ሌሎቹ ባላንታኛ፣ ማንዲንክኛ፣ ፑላርኛ (ፉላኒኛ)፣ ሰረርኛ፣ ሶኒንክኛ፣ ኖንኛ፣ ማንካኛኛ፣ ማንጃክኛ፣ ጆላኛ እና ሀሣኒያ አረብኛ ናቸው። ፖርቱጊዝኛም በትምህርት ቤት ይማራል፣ የካቦ ቨርዴ እና የጊኔ-ቢሳው ኅብረተሠቦችም ፖርቱጊዝኛ ክሬዮል ይናገራሉ። ከሴኔጋል ሕዝብ 94% የእስልምና አማኞች፣ 5% ክርስትና (ባብዛኛው ካቶሊክ)፣ 1% የኗሪ አርመኔነት ተከታዮች ናቸው። የመንግሥት ሃይማኖት የለውም። በሴኔጋል ልማዳዊ ባሕል ግሪዮት የተባሉ ሽማግሎች ታሪኮቻቸውን በአፍ ቃል ይደግማሉ። ሴኔጋል ለሙዚቃዊ ስልቶቹ ይታወቃል፤ በተለይ የሚወድደው ዘመናዊው ስልት ምባላክስ ተብሏል። በሴኔጋል አበሳሰል በተለይ አሣ፣ ዶሮ፣ በግ፣ አተር፣ ዕንቁላል፣ በሬ ይጠቀማሉ፤ እስላም አገር እንደ ሆነው መጠን ግን አሳማ አይበላም። ኩስኩስ፣ ሩዝ፣ ስኳር ድንች፣ ምስር፣ ጥቁር-ዐይን አተር ደግሞ በሴኔጋል አበሳሰል በሰፊ ይገኛሉ። በእስፖርት በኩል፣ ከሁሉ የሚወደደው ባህላዊው የሴኔጋል ትግል ግጥሚያ ሲሆን፣ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ ደግሞ እጅግ ይወደዳሉ። \n \nጥያቄ: በሴኔጋል ፓርላማ ውስጥ ካሉት ምክር ቤቶች አንዱ የብሔራዊ ስብስብ ምን ያህል መቀመጫዎች አሉት?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ ፻፳ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nጣይቱ ብጡል «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ» በሚል ቅፅል ስም የታወቁት እቴጌ ጣይቱ ከአባታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም እና ከእናታቸው ወይዘሮ የውብ ዳር ነሐሴ ፲፪ ቀን ፲፰፻፴፪ዓ/ም በጌምድር ውስጥ ደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ። በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት መሠረት በተወለዱ በ ፹ ቀናቸው ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፰፻፴፫ ዓ/ም በደብረ ታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሡ። እናታቸው ወይዘሮ የውብዳር ከባለቤታቸው ደጃዝማች ብጡል ኃይለ ማርያም ከሞቱ በኋላ በጅሮንድ መዩ የተባሉትን የዓፄ ቴዎድሮስን ባለሟል አግብተው ነበር። እሳቸውም ጣይቱ ብጡል ትምህርት እንዲቀስሙ ለማድረግ ልዩ መምህር ቀጥረውላቸው እንደነበር ይታወቃል። እቴጌ ጣይቱ በማኅደረ ማርያም ሆነው ሲማሩና መፃሕፍትን ይቀጽሉ በነበሩበት ጊዜ ለቤተክርስቲያን መጋረጃ መሥሪያ በትርፍ ጊዜያቸው ፈትል እየፈተሉ ያቀርቡ ነበር። በበገና ቅኝትና ድርደራም በኩል የታወቁ ባለሙያ እንደነበሩ ይተረክላቸዋል። የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በሸዋ የዓፄ ቴዎድሮስ እንደራሴ ከነበሩት አቶ በዛብህ ጋር ነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፰፻፶፯ ዓ/ም በጋዲሎ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ድል አድርገው ወደ አንኮበር ገብተው በነሐሴ ፳፬ ቀን ነገሡ። በነገሡም በአሥራ ሁለት ዓመታቸው በጣይቱ ብጡል እናት በወይዘሮ የውብዳር ቤት ከጣይቱ ብጡል ጋር ተጫጭተው ስለጋብቻቸው ተነጋገሩ። ከተጫጩ ከሁለት ዓመት በኋላ ወይዘሮ ጣይቱን ለማስመጣት በቤተ መንግሥቱ በተደረገው ምክር መሠረት አለቃ ተክለማርያም ወልደ ሚካኤል ደብዳቤ ተሰጥቷቸው ተላኩ። በዚያም አስፈላጊው ሁሉ በተፋጠነ ሁኔታ ተሟልቶ በጐጃም በኩል ደንገጡሮችና አሽከሮች አስከትለው ጉዞውን ጀመሩ። ደብረ ብርሃንም በገቡ ጊዜ ንጉሡ /ምኒልክ/ ታላቅ አቀባበል አደረጉላቸው። ከዚያም ጣይቱ ወንድማቸው ራስ ወሌ ብጡል ዘንድ ለጥቂት ዓመታት ተቀምጠው ከቆዩ በኋላ የጋብቻቸው ስነ-ሥርዓት የፋሲካ ዕለት ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም በአንኮበር መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን ተቀብለው ተጋቡ። \n \nጥያቄ: እቴጌ ጣይቱ ከንጉስ ምኒልክ ጋር በስንት ዓ.ም ተጋቡ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፲፰፻፸፭ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nሳምሱ-ዲታና ሳምሱ-ዲታና ከ1538 እስከ 1507 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር) ድረስ የባቢሎን ንጉሥ ነበር። የአሚ-ሳዱቃ ልጅና ወራሽ ሲሆን፣ ሳምሱ-ዲታና የባቢሎን (የሃሙራቢ ሥርወ መንግሥት) መጨረሻ ንጉሥ ነበረ። የዘመኑ አመት ስሞች ምንም ዘመቻ ስለማይጠቅሱ ሰላማዊ ዘመን ይመስል ነበር፣ ወደ ደቡቡ ግን የባሕር ምድር ሥርወ መንግሥት ንጉሥ ጉልኪሻር ከሳምሱ-ዲታና ጋር እንደ ታገለ በአንድ ታሪክ ጽላት ተቀረጸ። በ1507 ዓክልበ. የሐቲ (ኬጥያውያን) ንጉሥ 1 ሙርሲሊ እስከ ባቢሎን ድረስ ዘመተና ከተማውን ዘርፎ አቃጠለው። የኬጥያውያን ሠራዊት የባቢሎን ምስሎች (ጣኦታት) ወደ ሐቲ አገር ወሰዱ፤ ሳምሱ-ዲታናም እንደ ተገደለ ይመስላል። ይህ የሚታወቀው ከባቢሎን ዜና መዋዕል «በሳምሱ-ዲታና ዘመን፣ ኬጥያውያን ወደ አካድ መጡ» ሲዘገብ፣ ደግሞ በኬጥኛ የተለፒኑ ዜና መዋዕል እንደሚለው «እርሱ (ሙርሲሊ) ወደ ሐላብ ሔዶ አጠፋው፤ የሐላብን ምርኮ ወደ ሐቱሻ ወሰደ፤ ከዚያም እስከ ባቢሎን ድረስ ሔዶ አጠፋው፣ ሑራውያንንም አሸነፋቸው፣ የባቢሎንን ምርኮ ወደ ሐቱሻ ወሰደው።» \n \nጥያቄ: ሳምሱ-ዲታናም እንደ ተገደለ የመሰለው መቼ ነበር?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ 1507 ዓክልበ. ነው።" }, { "inputs": "ለሚከተለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከዚህ በታች የቀረበውን አውድ ተጠቀም፡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ የመጀመሪያ ዲግሪዋን በምን የትምህርት ዘርፍ ተመረቀች?", "targets": "ለጥያቄው መልሱ በሕግ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nአዳም ረታ አዳም ረታ ልቦለድና ግጥም በአማርኛ የሚጽፍ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነው። አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተመው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ”፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። ይህ የአጻጻፍ ስልቱ ሕጽናዊነት የሚባል ሲሆን ደራሲው በሌሎቹ መጻሕፍቱም ውስጥ በስፋት ተጠቅሞበታል፡፡ በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየዓመቱ አንዳንድ መፅሐፍ ለአንባቢያ ያደረሰ ሲሆን በ2002 ዓ.ም “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ በ2003 ዓ.ም “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” እና በ2004 ዓ.ም “ሕማማት እና በገና” ታትመው ለንባብ በቅተዋል። “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር” በተሰኘው መፅሀፉ ድንቅ የፋንታሲ (“ፈንጠዚያ”) ሥራዎች የተካተቱ ሲሆን በ”ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ” ለመጀመሪያ ጊዜ መቼቱን ከሀገር ውጭ በማድረግ የውጭውን ሕይወት በስሱ የዳሰሰ ሲሆን ከሌሎቹ ስራዎቹ በተለየ መልኩ ስለሀገራችን ፖለቲካ ወጣ-ገባ መንገድ በታዛቢ አይን ምልከታው፣ ትውስታውን … አስፍሯል፡፡ ሕማማትና በገና የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ ሲሆን ለየት ያለ ቅርፅ ያላቸው አንዳንድ ልቦለዶች ተካተውበታል። ፍልስፍናውና ስልቱ ሕፅናዊነት በሚል ስያሜው ይፋ ሆኗል። \n \nጥያቄ: የአዳም ረታ የመጀመርያ መፅሃፍ ምንድን ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nመጋቢት ፳፮ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት የመጀመሪያው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፷ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶፱ ቀናት ይቀራሉ። ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል። ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲክ የውል ድርጅት መሠረቱ። ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ። ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (የዓለም የንግድ ማዕከል) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል። ፲፱፻፷ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ በሜምፊስ ከተማ በነፍሰ-ገዳይ እጅ ተገደለ። \n \nጥያቄ: የአፍሪካ ሀገር የሆነችው ሴኔጋል ከ ፈረንሳይ ቅኝ ግዛት የተላቀቀችውና ነጻነቷን ተቀዳጀች መቼ ነው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ፲፱፻፶፪ ዓ/ም ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nሳዑዲ አረቢያ የሣውዲ አረቢያ ግዛት 28.7 ሚሊዬን የሚሆን ህዝብ ብዛት የያዘ ሲሆን 2ዐ ሚሊዬኑ የሣውዲ ዜጎች ሲሆኑ 8 ሚሊዬኑ የሌላ አገር ዜጎች ናቸው፡፡ ሳውዲ አረቢያ በምዕራብ ኤዥያ ከሚገኙ አገሮች በሙሉ በቆዳ ስፋቷ አንደኛ ናት፡፡ የአገሪቱ መሬት ስፋት 2,15ዐ,ዐዐዐ ኪሎ ሜትር ስኩኤር ነው፡፡ ጆርዳን እና ኢራቅ በሰሜን፣ ኩዌት ደግሞ በሰሜን ምስራቅ ኳታር ባህሬን እና የዩናይትድ አረብ ኤምሬት በምስራቅ ኦማን በደቡብ ምስራቅ እና በስተመጨረሻ የመን በደቡብ በኩል ሣውዲ አረቢያ ያዋስኗታል፡፡ የቀይ ባህር እና የፐርዢያን ገልፍ ባህርን የያዘ ብቸኛ አገር ሲሆን የሣውዲ መሬት ለመኖር በሚያስቸግር በረሃ የተከበበ ነው፡፡ አሁን ያለው የሣውዲ ግዛት በፊት ጊዜ አራት ቦታዎችን ያጠቃለለ ነበር፡፡ ሄጃዝ፣ ናጅድ፣ አል አሻ እና አስርን የያዘነው፡፡ የሣውዲ አረቢያ ግዛት ተመሠረተው በ1932 እ.ኤ.አ. በኢብን ሣኡድ በተባለ ሰው ነው፡፡ ኢብን ሣኡድ ቀድሞ በ1894 ዓም (1902 እ.ኤ.አ.) ከብሪታንያ ግዛት ከኩወይት ዘምቶ ሪያድን ያዘ። ኢብን ሳኡድ አራት የነበሩትን የተለያዩ ግዛቶች አንድ በማድረግ ሣውዲ አረብያን ከተመሠረተ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ሀገሪቱ በዘውድ አገዛዝ እና በእስልምና ሃይማኖት መሠረት እየተዳደረች ትገኛለች፡፡ እስልምና ሃይማኖትን በተመለከተ ዋሀቢ እስላም የሣውዲ አረቢያ አንደኛ እምነት ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለእስልምና እምነት ትልቅ ቦታ የሚይዙት ቅዱስ ስፍራ ተብለው መካ እና መዲና በሣውዲ ስለሚገኙ ሣውዲ አረቢያ አብዛኛው ጊዜ የተቀደሱትን ሁለት መስጊዶች የያዘው መሬት ተብሎ ይታወቃል፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ትልቅ የነዳጅ አምራች ሀገራት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በተጨማሪም ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ካሉ ሀይድሮ ካርቦን ክምችት ካላቸው አገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ በሀገሪቱ ባለው የተፈጥሮ ሀብት ከፍተኛ ክምችት ምክንያት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ እና የህዝብ ቁጥር እድገት ከያዙ ሀገራት ጋር ትመደባለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ G-2ዐ ተብለው ከሚታወቁት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አቅም ካላቸው የሀገራት ቡድን ውስጥ ብቸኛዋ የአረቡ ዓለም አገር ናት፡፡ ይህም ቢሆን የሣውዲ ኢኮኖሚ በአብዛኛው በአንድ ቡድን የተያዘ ነው፡፡ የሣውዲ አረብያን ፈላጭ ቆራጭ በሆነ የመንግስት ስርዓት በመመራት “ነጻነት የለም” በሚል “ነጻነት ቤት” በሚል በሚታወቀው ድርጅት ተሰይማለች፡፡ ሣውዲ አረቢያ በዓለም ላይ ለጦር ሀይል ከፍተኛ ገንዘብ ከሚያወጡ አገሮች ዝርዝር በአራተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ እ.ኤ.አ. ከ2ዐ1ዐ-2ዐ14 በስኘሪ ተብሎ በሚታወቅ ድርጅት በተደረገው ጥናት ሣውዲ አረቢያ ዓለም ላይ ከሚገኙ የጦር መሣሪያዎች በከፍተኛ ደረጃ በማስገባት ሁለተኛዋ ሀገር ናት፡፡ ሣውዲ አረቢያ በአካባቢው ካሉ ሀገሮች በዓለም ላይ ከፍተኛ አስተዋጾኦ በማድረግ ላይ ያለች አገር ናት፡፡ የኦፔክ፣ ጂሲስ እና የእስላም ግሩፕ አባል ናት፡፡ \n \nጥያቄ: ሳውዲ አረብያ በሰሜን የሚያዋስኑዋት የትኞቹ ሀገራት ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ጆርዳን እና ኢራቅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nየትነበርሽ ንጉሴ የትነበርሽ ንጉሴ በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ እና የአካል ጉዳተኛ መብትቶች ተሟጋች ናት ፡ እ.ኤ.አ በ 2017 \"የአካል ጉዳተኞችን መብቶችን እና ማካተቶችን በማስተዋወቅ እንዲሁም በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉየአእምሮ ውቅርን መለወጥ የሚያበረታታ ሥራዋ\" ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድን ተሸልማለች። የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው በ 5 ዓመቷ ነበር ። ይህ አጋጣሚ በተወለድችበት በአማራ ክልል በስፋት ይተገበር ከነበረው ያለ አድሜ ጋብቻ አንድታመልጥ እድሉን እንደፈጠረላት ትናገራለች። ፡፡የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሻሸመኔ ካቶሊክ የዓይነ ስውራን ት/ቤት ተከታትላ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (አካታች ትምህርት ቤት) ገብታ እስከ 12 ኛ ክፍል እዚያ ተማረች። በትምህርት ቤቱ ካላት አካዳሚክ ተሳትፎ በተጨማሪ የተማሪዎችን አማካሪ ጨምሮ ከ 6 በላይ የክለቦችን ክበባት መርታለች ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን በመቀላቀል የመጀመሪያ ዲግሪ በሕግ ሁለተኛ ዲግሪ በማኅበራዊ ሥራ አግኝ ታለች፡፡ ከመደበኛ ትምህርት ውጭ በልዩ ልዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተከታታይ ትሳተፋለች በዚህም የመኢአድ የፀረ ኤድስ እንቅስቃሴን ከ2004 - 05 በመምራት በ 2006 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (አአዩ) ሴት ተማሪዎች ማህበርን በመመስረት እንዲሁም የማህበሩ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን አገልግላለች ፡፡ \n \nጥያቄ: የትነበርሽ ንጉሴ የአይን ብርሃኗን ያጣችው መቼ ነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በ 5 ዓመቷ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየፀሓይ አካል ለፍጹም ሉል የቀረበ ቅርጽ አለው፤ ዋልታዎቿን የሚያገናኘው ዳያሜትር ከወገቧ ዳያሜትር የሚያንሰው በ10 ኪሎ ሜትር ብቻ ነውና። ኮከባችን ፀሓይ በሥነ ፈለክ ሊቃውንት እጅግ ብዙ ጥናት ተደርጎባታል። ኾኖም ኮከቢቱን በተመለከተ ብዙ ጥያቄዎች ገና አልተመለሱም። ለምሳሌ በገሃድ የሚታየው የፀሓይ ገጽ ስኂን 6,000 ኬ (ኬልቪን) ኾኖ ሳለ፣ የዳርቻ ከባቢ አየሯ ስኂን ከሚሊዮን ኬ በላይ እንዴት ሊኾን እንደቻለ አይታወቅም። የፀሓይ ዕድሜ በአንዳንድ ሊቃውንት እሳቤ 4.6 ቢሊዮን ዓመት ገደማ ነውና በዕድሜ እኩሌታዋ ላይ የምትገኝ ኮከብ ተደርጋ ትታያለች። የኮከቢቱ መጠነ-ቁስ ጥንቅር 74% ሃይድሮጂን፣ 25% ሂሊየም ሲኾን፣ ቀሪው 1% ደግሞ ክብደት ያላቸው ርዝራዥ የብረቴ ንጥረ-ነገሮች ጥርቅም ነው። ስለ ፀሓይ የሰው ልጅ ቀዳሚ መሠረታዊ ግንዛቤ ብርሃን-ሰጭ ሰማያዊ ጻሕል መኾኗን፣ ደግሞም ከአድማስ በላይ እና በታች በመኾን ለመዓልትና ሌሊት መኖር ምክንያት መኾኗን መረዳት ነበር። በብዙ የቅድመ-ታሪክ እና የጥንት ዘመን ባህሎች ፀሓይ እንደ ብርሃናዊ አምላክ ወይም እንደ ዲበ-ተፈጥሯዊ ክሥተት ትታይ ነበር። የፀሓይ አምልኮ ለምሳሌ የ-ኢንካ (ደቡብ አሜሪካ) እና አዝቴክ (የዛሬዋ ሜክሲኮ) ጥንታዊ ሥልጣኔዎች ዐይነተኛ ገጽታ ነበር። ከፀሓያዊ ክሥትቶች ጋር የተያያዙ ብዙ ጥንታዊ ሐውልቶች ተገንብተው እንደነበር ለማሰብ የሐጋይ ሶልስቲስን ለማስታወቅ የተገነቡትን የድንጋይ ሜጋሊት በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። ከችንክር ከዋክብት አንጻር ስትታይ ፀሓይ የግርዶሽ መስመርን ተከትላ በዞዲያክ ውስጥ በዓመት አንድ ዑደት የምታደርግ ትመስላለች። ስለዚህ በጥንት የግሪክ የሥነ-ከዋክብት ሊቃውንት ዘንድ ፀሓይ ታዋቂ ከነበሩ ሰባት ፈለኮች እንደ አንዱ ትቈጠር ነበር። በአንዳንድ ቋንቋዎች ሰባቱ የሳምንት ዕለታት በነዚህ ፈለኮች ይጠራሉ። \n \nጥያቄ: የፀሀይ ቅርጽ ምን ይመስላል?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ለፍጹም ሉል የቀረበ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nበርግጥም የመጀመሪያው በሰፊው ተግባራዊ የሆነ የቴሌቭዥን ስርዓት ስራ ላይ የዋለው በጀርመን አገር ሲሆን ይኸውም በ1929 እ.ኤ.አ. ነው። በ1936 እ.ኤ.አ. (1928 ዓም) ጀርመን ሃገር ተደርጎ የነበረውን የኦሎምፒክ ውድድር በቴሌቭዥን ሊሰራጭ ቻለ፣ ህዝቡም ውድድሩን እቤቱ ሆኖ ቀጥታ ሲካሄድ ለማየት ቻለ። ከዚያ መጀመርያው ጥቁርና-ነጭ ፕሮግራሚንግ በዩናይትድ ኪንግደም 1928 ዓም፤ በአሜሪካ 1933 ዓም ተደረገ። በአፍሪካ መጀመርያው ጣቢያዎች በ1952 ዓም በናይጄሪያና ደቡብ ሮዴዝያ (አሁን ዚምባብዌ) ተሰራጩ፣ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ስርጭት አገልግሎት (ኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን) የጀመረው በ1956 ዓም ሆነ። ሁለት አገራት - እነርሱም ቱቫሉና ኪሪባስ - ምንም የራሳቸውን ቴሌቪዥን አሁን አያሰራጩም፤ ሆኖም የሌላ አገር ስርጭት እዚያ ሊታይ ይችላል። ከዚያ ቤርድ በግንቦት 26 ቀን 1920 (ጁላይ 3, 1928 እ.ኤ.አ.) የመጀመሪያውን የከለር ቴሌቪዥን ስርጨት ሙከራ አደረገ። ነገር ግን ከለር ቴሌቪዥን ቢፈጠረም ለሚከተሉት ብዙ ዓመታት ስርጭት ባብዛኛው ጥቁርና ነጭ ብቻ ሆኖ ቀረ። ይሄው ቴክኖዎሎጂው በጣም ውድ፣ በጣም ከባድና በትክክል ያልተስተካከለ ስለ ሆነ ነው። በየጥቂቱ ከ1946 ዓም (1954 እ.ኤ.አ.) ጀምሮ አገራት ወደ ከለር ስርጭትና ከለሩን ማሳየት የሚችል ቴሌቪዥን ወደ መሸጥ ይዛወሩ ጀመር። በጥር ወር 1946 ዓም NBC የተባለው አሜሪካዊ ስርጭት ጣቢያ በከፊሉ ወደ ከለር ተሸጋገረ፤ ብዙ ሰዎች ግን ያንጊዜ ከለር ማሳያ ቴሌቪዥን ለመግዛት ገና አልቻሉም ነበር። ከ1955 እስከ 1959 ዓም ድረስ ሌሎቹ ትልልቅ አሜሪካዊ ጣቢያዎች ABC እና CBS ደግሞ ወደ ከለር ተዛወሩ፣ የከለርም ተቀባዮች ዋጋ እየተቀነሰ የሚይዩት ሕዝብ ቁጥር ደግሞ ከዚህ በኋላ እየተጨመረ ሄደ፤ ከረጅሙ ጥቁርና-ነጭ ዘመን ቀጥሎ ከለርም በኅብረተሠብ ያመጣው ለውጥ ለግዙፍነቱ በኋላ ኢንተርኔት እንደ ሆነ ያሕል ነው። ጃፓን በ1952 ዓም፣ ሜክሲኮ በ1955፤ ካናዳ በ1958፣ የአውሮፓ ኅብረትና የሶቪዬት ሕብረት በ1959፣ ኮት ዲቯር በ1962፣ አውስትራሊያ በ1967 ከለር ስርጭትን ጀመሩ። በኢትዮጵያም ከለር ስርጭት ከ1976 ዓም ጀምሮ ተገኝቷል። በ1977 ዓም ሮማኒያ ከጥቁርና-ነጭ ስርጭት ወደ ከለር ማሰራጨት የለወጠ በዓለም መጨረሻው ሃገር ሆነ። \n \nጥያቄ: በዓለም የመጨረሻው ወደ ቀለም ቴሌቭዥን ስርጭት የገባው ሀገር ማነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ሮማኒያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ (ቀ.ኃ.ሥ.) ከጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ተፈሪ መኰንን ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም. ከአባታቸው ከልዑል ራስ መኰንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺ እመቤት ኤጀርሳ ጎሮ በተባለ የገጠር ቀበሌ ሐረርጌ ውስጥ ተወለዱ። በ፲፰፻፺፱ የሲዳሞ አውራጃ አገረ ገዥ ሆኑ። በ፲፱፻፫ ዓ.ም. የሐረርጌ አገረ ገዥ ሆኑ። የሐረርጌ አገረ ገዥ ሲሆኑ ፣ በጣም ብዙ ሺህ ተከታዮች ነበሩዋቸውና ልጅ እያሱን ከእንደራሴነት በኅይል እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ተፈሪን ከሐረር አገረ ገዥነት እንዳይሽሯቸው የሚል ስምምነት ተዋዋሉ። ዳሩ ግን እያሱ ሃይማኖታቸውን ከክርስትና ወደ እስልምና እንደቀየሩ የሚል ማስረጃ ቀረበና ብዙ መኳንንትና ቀሳውስት ስለዚህ ኢያሱን አልወደዱዋቸውም ነበር። ከዚህም በላይ እያሱ ተፈሪን ከሐረር ከአገረ ገዥነታቸው ለመሻር በሞከሩበት ወቅት ስምምነታቸው እንግዲህ ተሠርዞ ተፈሪ ደግሞ ለወገናቸው ከስምምነቱ ተለቅቀው በዚያን ጊዜ እሳቸው እያሱን ከእንደራሴነት አስወጡ። እንግዲህ በ፲፱፻፱ ዓ.ም. መኳንንቱ ዘውዲቱን ንግሥተ ነገሥት ሆነው አድርገዋቸው ተፈሪ ደግሞ እንደራሴ ሆኑ። ከዚህ ወቅት ጀምሮ ተፈሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ባለሙሉ ሥልጣን ነበሩ። በመስከረም ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. የንጉሥነት ማዕረግ ተጨመረላችው። በ፲፱፻፳፪ ዓ.ም ንግሥት ዘውዲቱ አርፈው ንጉሠ ነገሥት ሆኑና ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. ብዙ የውጭ ልዑካን በተገኙበት ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ቅብዓ ቅዱስ ተቀብተው እሳቸውና ሚስታቸው እቴጌ መነን ዘውድ ጫኑ። በንግሥ በዓሉ ዋዜማ ጥቅምት ፳፪ ቀን የትልቁ ንጉሠ-ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ-ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለዘውድ በዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት ፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ። ለንግሥ ስርዐቱ ጥሪ የተደረገላቸው የውጭ አገር ልኡካን ከየአገራቸው ጋዜጠኞች ጋር ከጥቅምት ፰ ቀን ጀምሮ በየተራ ወደ አዲስ አበባ ገብተው ስለነበር ሥርዓቱ በዓለም ዜና ማሰራጫ በየአገሩ ታይቶ ነበር። በተለይም በብሪታንያ ቅኝ ግዛት በጃማይካ አንዳንድ ድሀ ጥቁር ሕዝቦች ስለ ማዕረጋቸው ተረድተው የተመለሰ መሢህ ነው ብለው ይሰብኩ ጀመር። እንደዚህ የሚሉት ሰዎች እስከ ዛሬ ድረስ ስለ ፊተኛው ስማቸው «ራስ ተፈሪ» ትዝታ ራሳቸውን «ራስታፋራይ» (ራሰተፈሪያውያን) ብለዋል። \n \nጥያቄ: ንግሥተ ነገሥታት እቴጌ ዘውዲቱ ሲሞቱ የተኳቸው ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ላይ የሚሰራውን የተ.መ.ድ አካል (UNAIDS) ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ እና የዩኤን ኤድስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊኒ ቢያንዩማን በኢትዮጵያ የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከል በተያዙ ዕቅዶች ላይ መምከራቸውን ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ \n \nጥያቄ: የተ.መ.ድ አካል ዩኤን ኤድስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማን ነው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ዊኒ ቢያንዩማን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nሄርበርት ሁቨር (1866 - 1957 ዓ.ም.) ከ1921 እስከ 1925 ዓ.ም. ድረስ 31ኛ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ነበሩ። የሁቨር ቤተሠብ ከስዊስና ጀርመን ትውልድ ሲሆን ሃይማኖቱ የክዌከር ('የሚንቀጠቀጡ' ማለት ነው) ቤተ ክርስቲያን ነበረ። ወላጆቹ በልጅነቱ ጊዜ ካረፉ አንስቶ ድሃ አደግ ሆነና ከአጎቱ ጋር አደገ። በስታንፎርድ ዩኒቨርሲቴ መጀመርያ ክፍል በመሆኑ ትምህርቱ በነጻ ተቀበለ። ከዚያ በላይ የዩኒቬርሲቴው የቤስባልና የፉትቦል ቡድኖች አለቃ ሆነ። በ1887 ዓ.ም. የጂዮሎጂ ዲግሪ ይዘው ተመረቁ። ለ20 ዓመት የማዕደን ሊቅ ሲሆኑ እንኳን በአውስትራልያና በእንግሊዝ በማዕደን ዘርፍ የሠሩት ሥራ ስመ ጥሩ ሆነ። መጀመርያው ታላቅ አለማዊ ጦርነት በ1906 ዓ.ም. በጀመረበት ወቅት ሁቨር ከራሳቸው ኪስ ለጋሥነት አውጥተው 120,000 አሜሪካውያን ቱሪስቶችና ሠራተኞችን ከአውሮፓ ወደ አገራቸው አስመለሷቸው። ከዚያ በጀርመኖች በተወረረው በቤልጅግ ውስጥ የኖሩት ረሃብተኞች ምግብ እንዲደርሳቸው ብዙ አደረጉ። በዚህ አይነት ሥራ በጦርነት ጊዜ የሁቨር ስም ጀግና እንዳለው ሁኔታ በመገኘት ላይ ሄዶ ነበር። ጦርነቱም ከተጨረሰ በኋላ ለምሥራቅ አውሮጳ ድሃ ሕዝብ እስከ ሩስያም ድረስ በረሃብ ላሉት ሰዎች ምግብ አደረሷቸው። \n \nጥያቄ: የሄርበርት ሁቨር የትውልድ ቦታው የት ነው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ ከስዊስና ጀርመን ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር (1906-2001) የሴኔጋል የመጀመሪያው መራሄ መንግስት በመሆን ከ1960 እስከ 1980 ድረስ ያገለገሉ፣ ኔግሪቲዩድ የሚባለው ፍልስፍና ዋነኛ አቀንቃኝ የነበሩ እና በግጥሞቹም አድናቆትን ያተረፉ አፍሪካዊ የሥነጽሁፍ ሰው ናቸው። ሴንጎር የሴኔጋል ዋና ከተማ ከሆነችው ዳካር 70 ማይልስ ያህል በምትርቅ እና ጆአል ላ ፖርቱጊዝ (ጆአል ፖርቱጊዛዊቱዋ) በምትባል ትንሽ የአሳ አጥማጆች መንደር በ1906 ተወለዱ። አባታችው ነጋዴ ከሆኑ ሴሬር ከሚባሉ ጎሳ የተወለዱ ሲሆን እናታቸው ግን ፔውል ከተባለ የሙስሊም ዘላን አርብቶአደሮች ጎሳ የተወለዱ ሴት ናቸው። ሴንጎር ኋላ ላይ ሲጽፉ «ተወልጄ ያደኩት በአፍሪካ መኸል፣ የጎሳዎች እና ዘሮች መገናኛ ላይ ነው» ብለዋል። በ12 ዓመታችው የካቶሊክ ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተመዝግበው ትምህርታቸውን የጀመሩ ሲሆን ከዛ በኋላ በሌሎች ትምህርት ቤቶችም በመማር በ1928 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ከዚያም ፓሪስ ከሚገኘው ሊሴ ፓሪ ለግራንድ ከተባለው ትምህርት ቤት በ1931 ተመርቀዋል። \n \nጥያቄ: ሊኦፖልድ ሴዳር ሴንጎር በትንሻ የአሳ አጥማጆች መንደር መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ1906 ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nየላሊበላ ግሎባል ኔትወርክስ ድርጅት ተባባሪ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ (ዶ/ር) ዓለም አቀፉን ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ አዲስ የስራ ፈጣራ ውድድር አሸነፉ። ኢትዮጵያዊቷ በየዓመቱ የሚካሄደውን ዓለም አቀፉን ፒአይቲሲኤች (PITCH) አዲስ የስራ ፈጠራ ውድድር በትላንትናው እለት ማሸነፉቸው ይፋ ሆኗል። ውድድሩ 2500 ስራ ፈጣሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ወደ መጨረሻው ዙር ያለፉት ደግሞ 700 የሚሆኑ አዲስ ፈጣሪዎች ነበሩ። ከዚህ ውስጥ ኢትዮጵያዊቷ ውለታ ለማ(ዶ/ር) በጤና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያቀረቡት አዲስ የስራ ፈጠራ በቅርበት ተፎካካሪ ከነበሩት የአሜሪካና የእንግሊዝ የስራ ፈጣሪዎችን በመብለጥ የዓመቱ ውድድር አሸናፊ ሆኗል። ውለታ ለማ (ዶ/ር) ለውድድሩ ያቀረቡት የስራ ፈጠራ አባይ ሲ ኤች አር (ABAY CHR) የተባለ በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ህክምና ዘርፍ ያለውን ሰፊ የወረቀት ስራ ወደ ዲጂታል በመቀየር ስራን የሚያቀልና የሚያቀላጥፍ እንዲሁም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወጪን የሚያስቀር የሥራ ፈጠራ ነው ተብሏል። \n \nጥያቄ: በጤና ቴክኖሎጂ አዲስ የሥራ ፈጠራ አሸናፊ የሆኑት ኢትዮጵያዊት ማን ይባላሉ?", "targets": "ለጥያቄው መልስ ውለታ ለማ(ዶ/ር) ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nጋሞጐፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ከ1955 እስከ 1993 ዓ.ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛት፣ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር አካባቢና ከዚያም የሰሜን ኦሞ ርዕሰ ከተማ በመሆን ለቀድሞዎቹ የጋሞ፣ የጐፋ፣ የጋርዱላና ሐመር ባኮ አውራጃዎች ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ማዕከል ሆና ያገለገለች ስትሆን ከ1993 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ አስራ አምስት ወረዳዎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን አቅፎ ለያዘው ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን እያገለገለች የምትገኝ ከተማ ነች፡፡ በዞኑ ውስጥ የሚገኙ የጋሞ፣ የጎፋ፣ የዘይሴ ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሄረሰቦችን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ ሌሎች የሀገራችን ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጆች ተከባብረውና ተቻችለው በፍቅርና በሰላም የሚኖሩባት አርባ ምንጭ ከተማ በቀለማት አደራደሩ ትኩረትና ተወዳጅነት የማይለየው የጋሞ ብሔረሰብ የክብርና የማዕረግ ልብስ እንዲሁም መታወቂያው የሆነውንና ዱንጉዛ በመባል የሚታወቀው ባህላዊ ልብስ ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ የሸማ ጥበብ አልባሳት ሥራዎች መፍለቅያ አካባቢዎች እምብርት ከመሆኗም በተጨማሪ በባህላዊ ቤት አሰራራቸው በለቅሶና ሠርግ ስርዓታቸው በባህላዊ የማምረቻና የመገልገያ ቁሳቁሶቻቸው የብዙዎችን አድናቆትና አግራሞትን ላስጫሩት የጋሞ፣ የጐፋ፣ የዘይሴ፣ የጌዲቾና የኦይዳ ብሔረስብ ህዝቦች መዲና ነች፡፡ ከባህር ወለል በላይ ከ1,300 እስከ 1,500 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ የአርባ ምንጭ ከተማ አየር ንብረት በተለምዶ ቆላማ የሚሉት አይነት ሲሆን፤ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የሙቀት መጠኗ 240c ነው፡፡ የከተማዋ ዓመታዊ አማካይ የዝናብ መጠኗ 900 ሚሊ ሜትር ሆኖ ግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረምና ጥቅምት ወራት ከፍተኛ የዝናብ መጠን በዓመቱ ውስጥ የሚመዘግብባቸው ወራት ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ስፍራ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን መንትያዎቹ የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ፤በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያ እና የተፈጥሮ ደኖችን ሌሎች ከህሊና ጓዳ የማይፋቅ ትዝታን ጥለው የሚያልፉ ሃብቶች ባለቤት ናት በተፈጥሮ ውበት በታደለው ድንቅ ከተማ እንደመከተሟ አርባዎቹ ምንጮች የሚመነጩባትን የአባያና ጫሞ አስደናቂ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ያለሀሳብ የሚፈነጩባትን ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክ፤ የአዞ እርባታ ጣቢያ፤ የአዞ ገበያን በአካባቢው ታይተው የማይጠገቡ የዱር እንሰሳት እና የተፈጥሮ ደኖችን ይገኛሉ፡፡ የዞኑን አስደናቂ የቱሪስት መስህቦች እንግዶቻችንን በማስጎብኘት ከታዋቂ የዓሳ ምርታችን ፣ ከማንጎ ፤ ከሙዝ እና በአፕል ማሳችን እየተንሸራሸርን የማይረሱ ትዝታዎችን ጥለው ያልፋሉ፡፡ \n \nጥያቄ: የጋሞ ጎፋ ዞን ዋና ከተማ ማናት?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ አርባ ምንጭ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች በየትኛው ዘመን ወደ አካባቢው መጡ?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ በብረት ዘመን ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ከዚህ በታች በተሰጠው አውድ መሰረት መልሱ፡ \nአፄ ዘርአ ያዕቆብ አጼ ዘርአ ያዕቆብ በዘውድ ስማቸው ቆስጠንጥንዮስ ከአባታቸው ቀዳማዊ ዳዊት እና ከእናታቸው ንግስት ክብረ እግዚእ በ1399 እ.ኤ.አ. ከአዋሽ ወንዝ አጠቀብ ትገኝ በነበረው ትልቅ ተብላ በምትጠራው መንደር የድሮውፈተገር ክፍለ ሐገር ተወለዱ(ከቀኝ ያለውን ካርታ ይመልከቱ) ። የነገሡበትም ዘመን 1434 - 1468 እ.ኤ.አ. ነበር። ያረፉትም በደጋ ደሴት፣ ጣና ሃይቅ ነው። የዘርዓ ያዕቆብ አባት ቀዳማዊ ዳዊት ባረፉ ጊዜ፣ እንደ ጥንቱ የኢትዮጵያ ባህል ወግ መሰረት፣ ታላቅ ወንድማቸው የነበሩት ቀዳማዊ ቴወድሮስ በ1414 ሲነግሱ ታናሽ ወንድማቸውን በግዞት ወደ አምባ ግሽን እንዲሄድ አደረጉ። አጼ ዘርዓ ያእቆብ ቆየት ብለው በጻፉት መጽሀፈ ብርሃን በተሰኘው ድርሰታቸው መሰረት እስከ ነገሱበት ሰኔ 20 ፣ 1434 ዓ.ም. ድረስ በግዞት ግሸን ተራራ (አምባ ግሸን) ላይ ለሚቀጥሉት 20 አመታት በእስር ኖሩ። ሆኖም ግን በግዞት እያሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ የደጋፊያቸው መጠን እየበዛ ሄደ። በነዚህ አመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከዓመት ወደ ዓመት እይተበላሸ ሂዶ በመጨረሻ ከአምባው ላይ ለሹመት ሲወርዱ አገሪቱ በእርስበርስ ሽኩቻ እየታመሰች፣ በሃይማኖት በኩልም መከፋፈል ተፈጥሮ የውጭ ሀይሎችም ከነገ ዛሬ አጠቁን እየተባለ ይሚፈራበት ሁኔታ ገጠመው። የወደፊቱ ንጉስ ብዙ እድሜውን ያሳለፈው ከሰው ተለይቶ አምባ ላይ ስለነበር፣ የዲፕሎማሲ ጥቅሙ አልተረዳውም ነበር። ይልቁኑ ፊት ለፊት የተጋረጡትን የሃገሪቱን ችግሮች በሚያስፈራ ድፍረት እና ምንም በማያወላዳ ጽናት ተጋፈጠው። ዓፄ ዘርአ ያእቆብ ንጉስ ከሆኑ በኋላ ንግስት እሌኒን በ1434 አገቡ፣ ከዚያም በ1436 ዘውዳቸውን ጫኑ። በ1442 በሰንበት ላይ ተነስቶ የነበረውን የቤተክርስቲያን ክፍፍል ለማብረድ ቢችሉም እስከ 1450 ነገሩ ሲሰክን ቆይቱ በደብረ ምጥማቅ ጉባኤ (ተጉለት) ፣ የግብጾቹ ጳጳሳተ በተገኙበት ችግሩን ሊፈቱ ችለዋል ። ሌላው በዘመናቸው የተከሰተው ሃይማኖታዊ ንቅናቄ የደቀ እስጢፋ ወገኖች እምነት ነው። እነዚህ እስጢፋኖስ የተባለ መነኩሴ ባስተማራቸው መሰረት ለመስቀል መስገድና ለስእል አድኅኖ ለድንግል ማርያም መስገድ አይገባም የሚሉ ነበሩ።ተከራክረው አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አሸንፈዋል። በ1445 እና ከዚያ በኋላ በተነሱ ጦርነቶች ላይ በመሳተፍ ሁሉን በድል በማጠናቀው ግዛታቸውን ያሁኒቷን ሶማልያን ሁሉ ያቅፍ ነበር። በ1456 ዓ.ም አጼ ዘርዓ ያዕቆብ በነበሩበት ቦታ ታላቅ ብርሃን ስለታየ የነበሩበትን ቦታ ደብረ ብርሃን በማለት የሃገሪቱ ዋና ከተማ አድርገው ቆርቁረዋል። እስከ እለት ህልፈታቸውም ደብረ ብርሃን የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ነበረች።ኢትዮጵያዊ መንፈሳዊ ፈላስፋ። አጼ ዘርአ ያዕቆብ በጦር ውሎአቸው ብቻ ሳይሆን የሚታወቁት፣ ከ 20 በላይ መጻህፍትንም በመድረስና ለትውልድ በማቅረብ ጭምርም ነው። \n \nጥያቄ: የአጼ ዘርአ ያዕቆብ ሚስት ማን ናቸው?", "targets": "ለጥያቄው ትክክለኛው ምላሽ ንግስት እሌኒ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ዝርዝር መረጃ በመጠቀም ለሚከተለው ጥያቄ መልስ ይስጡ፡ \nዚምባብዌ የዚምባብዌ ሪፐብሊክ ከዚህ በፊት የሮዴዢያ ሪፐብሊክ በመባል የምትታወቅ ስትሆን፣ በደቡብ አፍሪካ የምትገኝ ወደብ-የለሽ ሀገር ናት። ዚምባብዌ ደቡብ አፍሪካ ፣ ቦትስዋና ፣ ዛምቢያ እና ሞዛምቢክን ትዋሰናለች። የዚምባብዌ ስም የመጣው ከ«ድዚምባ ድዜማᎆ» ሲሆን በሾና ቋንቋ «የድንጋይ ቤቶች» ማለት ነው። የድንጋይ ዘመን አዳኞች በቦታው ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደነበሩ የሚጠቁም ብዙ መረጃ አለ። እነዚህ ሰዎች ከዛሬው ኮይሳን ብሔር ጋር የሚዛመዱ ሲሆን በባንቱ ብሔር ተተክተዋል። ህይወታቸውን የሚያሳዩ ሥዕሎች በዚምባብዌ ባሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ዋሻዎች ይገኛሉ። በብረት ዘመን የነበሩ የባንቱ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ አካባቢው ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት ፈልሰት ጀመሩ። ዛሬ የሀገሩን አራት አምስተኛ ሕዝብ ብዛት የሚሆኑት የሾና ሰዎች የዘር-ሐረጋቸው ወደ ጥንታዊው ሰዎች ያመለክታል። የታላቅ ዚምባብዌ ፍርስራሾች በመካከለኛው ዘመናት የባንቱ ስልጣኔ እንደ ነበረ ያመለክታሉ። ወደ 10ኛው ክፍለ-ዘመን አካባቢ ከሙስሊም ነጋዴዎች ጋር በኢንዲያን ባህር ላይ ንግድ ተጀመረ። ይህም ታላቅ ዚምባብዌ በ11ኛው ክፍለ-ዘመን አንድትሻሻል ረድቷል። ወርቅ ፣ የዝሆን ጥርስ እና መዳብ ይሸጡ ነበር። በ1828 ዓ.ም.፣ በደቡባዊ ዚምባብዌ የነበሩ የሾና ህዝቦች በንዴቤሌ ብሔር ተወረው ግብር ለመክፈልና ወደ ሰሜናዊ ዚምባብዌ ለመሰደድ ተገደዱ። በ1881 ዓ.ም. ብሪታኒያዊው ሴሲል ሮድስ ከንዴቤሌ ንጎሥ ሎቤንጉላ የማዕደን ማውጣት ፈቃድ አገኘ። ሴሲል ሮድስ በሊምፖፖ ወንዝና ታንጋኒካ ሐይቅ መካከል ያለውን ቦታ (ዛምቤዚያ ብሎ ሰይሞት) ተመሳሳይ ፈቃድ እንዲሰጡ አበረታቷል። ይህም ቦታው በብሪታኒያ ቅኝ-እንዲገዛ መንገድ ከፍቷል። በ1887 ዓ.ም.፣ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ የዛምቤዚያን ስም ወደ ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ለወጠ። ከዛም በ1891 ዓ.ም. ከዛምቤዚ በታች ያለው ቦታ 'ደቡባዊ ሮዴዢያ ተብሎ' በኩባኒያው ተሰየመ። ደቡባዊ ሮዴዢያ ወደፊት ዚምባብዌ ሆነ። ከዛምቤዚ በላይ ያለው ክልል ሰሜናዊው ሮዴዢያ ከተባለ በኋላ አሁን ዛምቢያ ነው። የንዴቤሌና ሾና ሕዝቦች የሮድስ አመራር ቢቃወሙም አልተሳካም ነበር። ከዛም ነጮች በስፍራው በብዛት ሰፈሩ። ነጮችን የሚጠቅምም የቦታ ክፍፍል ተጀመረ። የዚምባብዌ የቦታ ውዝግብ እስከዛሬ ድረስ ይቀጥላል። ደቡባዊ ሮዴዢያ እራሱን የሚያስተዳድር የብሪታኒያ ግዛት በ1916 ዓ.ም. ሆነ። በ1945 ዓ.ም. ብሪታኒያ ሁለቱን ሮዴዢያዎች ከኒያሳላንድ (አሁን ማላዊ) ጋር አገናኝታ በአንድላይ የሮዴዢና ኒያሳላንድ ፌዴሬሽን ተባሉ። ረብሻና የአፍሪካዊ ሰሜት ብሪታኒያ ፌዴሬሽኑን በ1956 ዓ.ም. እንድታፈርስ አደረጉ። በ1958 ዓ.ም. ኢያን ስሚዝ ከብሪታኒያ ነጻነት አወጀ። ከዛም በ1962 ዓ.ም. ደቡባዊ ሮዴዢያ የሮዴዢያ ሪፐብሊክ ሆነች። በኢያን ስሚዝ የሚመራው የነጮች መንግሥት የሮዴዢያን ነጻነት በኖቬምበር 11፣ 1965 እ.ኤ.አ. አወጀ። የብሪታኒያ መንግሥት ከስሚዝ አመራር ጋር በ1966 እና 1968 እ.ኤ.አ. ያደረገው ንግግሮች ስኬታዊ ስላልነበሩ ዩናይትድ ኔሽንስን በሮዴዢያ ላይ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲጣልባት ጠየቀች። የስሚዝ አመራር የሪፕብሊክ መንግሥት መሆኑን በ1970 እ.ኤ.አ. ቢያስታወቅም እውቅና የሰጠው ሀገር ግን የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ብቻ ነበር። የደፈጣ ተዋጊዎች ነጮችን ማጥቃት ጀመሩ። የስሚዝ አመራር በሮበርት ሙጋቤ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ብሔራዊ ሕብረት እና በጆሱዋ ንኮሞ ከሚመራው የዚምባብዌ አፍሪካዊ ሕዝብ ሕብረት ጋር የድርድር ንግግሮችን ጀመረ። በማርች 1978 እ.ኤ.አ. የስሚዝ አመራር ሊወድቅ ሲደርስ በሊቀ ጳጳስ አቤል ሙዞርዋ በሚመሩ ሶስት ጥቁር መሪዎች ጋር የነጭ ዜጎች ደህንነት እንዲጠበቅ ስምምነት ፈረመ። በ1979 እ.ኤ.አ. ሁሉም ፓርቲዎች በለንደን ተገናኝተው የእርስ-በርስ ጦርነቱን ለማቆም የላንካስተር ቤት ስምምነትን ፈረሙ። \n \nጥያቄ: በ1887 ዓ.ም. የዛምቤዚያን ስም ሮዴዢያ (ለሴሲል ሮድስ) ብሎ የቀየረው ማነው?", "targets": "ከጥያቄው አንጻር ትክክለኛው መልስ የብሪታኒያ ደቡብ አፍሪካ ኮባኒያ ነው።" }, { "inputs": "የተሰጠውን ጥያቄ ለመመለስ ከዚህ በታች የቀረበውን መረጃ ይመልከቱ፡ \nኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የዓለም አቀፍ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየም ልታካሂድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ። ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት ሲምፖዚየምና የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የምክክር መድረክ ከመስከረም 26-30 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህን አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ እንደተብራራው በሁለቱ መድረኮች ከ30 አገራት ከ200 በላይ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች፣ ኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎችና ባለድርሻ ተቋማት ስለ አስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ይመክራሉ። በኢንስቲትዩቱ የአስትሮኖሚና አስትሮፊዚክስ ምርምር ክፍል ኃላፊ ዶክተር ማሪያና ፖቪች እንዳሉት በዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ኅብረት በተለያዩ አገራት በየዓመቱ የሚዘጋጁ ሲምፖዚየሞች አሉ። ኅብረቱ መቶኛ ዓመቱን እያከበረ ይህንንም ክብረ በዓል ያከናወናቸውን ስራዎችና ስኬቶች እየገመገመ በተለያዩ ሁነቶች እያከበረ ነው። እስካሁን 355 ሲምፖዚየሞች የተካሄዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ሲምፖዚየሙን የምታካሂድ ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር ስትሆን በደቡብ አፍሪካና ቡርኪናፋሶ መሰል ሲምፖዚየም ተካሂዷል። ሲምፖዚየሙ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያካበቱ ተመራማሪዎች ልምዳቸውን የሚያጋሩበትና ኢትዮጵያ ብሎም አፍሪካ በሳይንስ ዘርፍ እየከወኗቸው ያሉ ተግባራትን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስገንዘብ የሚያስችል ነው ብለዋል። የምስራቅ አፍሪካ አስትሮኖሚ ለልማት ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ዳይሬክተር አቶ አለምዬ ማሞ በበኩላቸው እንደገለጹት የአፍሪካ አስትሮኖሚ ማኅበር የሚያዘጋጀው የአፍሪካ አስትሮኖሚ የሳይንስ ምክክር መድረክ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2012 ዓ.ም ይካሄዳል። መድረኩ በአፍሪካ አስትሮኖሚ ምን አይነት አስተዋፅኦ ማበርከት እንደሚችል የሚያመላክት ራዕይና ስትራቴጂ ሰነድ የሚነደፍበት ይሆናል ነው ያሉት። የማኅበሩን እንቅስቃሴ ለሳይንስና ለጠቅላላ ማኅበረሰቡ ማስተዋወቅ፣ የአህጉሪቱ ወጣት ተመራማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማስቻል፣ በአፍሪካ በአስትሮኖሚና ስፔስ ሳይንስ ዘርፍ የሚሰሩ ሳይንሳዊ ምርምሮችን ማጎልበት የመድረኩ ዓላማዎች መሆናቸውን አንስተዋል። መድረኩ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብርና ትስስር መፍጠር ያስችላልም ነው ያሉት። ነገና ከነገ በስቲያ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ካምፓስ በዘርፉ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እየሰሩ ላሉ ተማሪዎች የእውቀትና ክህሎት ስልጠናም ይሰጣል። ከሁለቱ መድረኮች ጎን ለጎን በተመረጡ 10 የህዝብ ትምህርት ቤቶች በተግባር የታገዘ አስትሮኖሚን የማስገንዘብ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል። ለበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎች ስለ አስትሮኖሚ ሳይንስ ግንዛቤ የመፍጠር እንዲሁም ለሁለተኛ ደረጃ መምህራን የሚሰጥ ስልጠና መኖሩም ተጠቁሟል።     \n \nጥያቄ: በአዲስ አባባ ዩኒቨርስቲ በየትኛው ካምፓስ ለሚገኙ 2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች ነው ስልጠና ለመስጠት የታሰበው?", "targets": "ለተጠቀሰው ጥያቄ ትክክለኛው ምላሽ አራት ኪሎ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nአሸናፊ ከበደ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ አዲስ አበባ ግንቦት ፰ ቀን ፲፱፻፴ ዓ/ም ተወለዱ። አባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ክልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትንና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወይዘሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እናየንግሥት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅርን ገና በልጅነታቸው ያሳደሩባቸው እናታቸው ሲሆኑ ታዳጊው አሸናፊ ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ እኒህ የሚያፈቅሯቸውና ዕድሜ ልካቸውን በኀዘን የሚስታውሷቸው እናታቸው ሞተውባቸዋል። መሠረታዊ ትምህርታቸውን በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት እና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ኮከበ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኋላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለ-ሀገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርሲቲ፣ “ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት” በ፲፱፻፶፬ ዓ/ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ የያሬድ ሙዚቃ ትምሕርት ቤትን መሠረቱ። የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክቶር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባው የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማኅበር (ወ.ወ.ክ.ማ Y.M.C.A.)፤ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ-ዕውራን ትምህርት ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማኅበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምህርት ይሰጡ ነበር። \n \nጥያቄ: የፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ እናት የሞቱት ፕሮፌሰር ስንት ዓመት እያሉ ነበር?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ የዘጠኝ ዓመት ልጅ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nራስ መኮንን ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል የሸዋ ንጉሥ የነበሩት የሣህለ ሥላሴ ልጅ የልዕልት ተናኘወርቅ እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት ፩ ቀን ፲፰፻፵፬ ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ ፲፬ ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የንጉሥ ኃይለ መለኮት ልጅ ዳግማዊ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተ መንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ። በ፲፰፻፷፰ ዓ.ም ዕድሜያቸው ሀያ አራት ዓመት ሲሆን ከወይዘሮ የሺ እመቤት ጋር ተጋብተው ሐምሌ ፲፮ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም የወደፊቱን ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ወለዱ። \n \nጥያቄ: ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል ከስንት ዓመታቸው ጀምሮ የዳግማዊ ምኒልክ ባለሟል ሆነው ሰሩ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ ፲፬ ዓመት ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች ያለውን ጽሑፍ በማጣቀስ እባክዎን ለሚከተለው መልስ ይስጡ \nላይቤሪያ ላይቤሪያ (እንግሊዝኛ፦ Liberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒ፣ ኮት ዲቯር፣ ሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች። የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳ፣ ክሩ፣ ጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ። መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ። በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ። የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል። ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ። በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር። በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ። አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው። የላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው። ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲ በየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል። \n \nጥያቄ: ላይቤሪያ ከውቅያኖሶች በየትኛው ትዋሰናለች?", "targets": "ለጥያቄው መልስ በአትላንቲክ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nዕዝራ ዕዝራ ወይም ሱቱኤል በብሉይ ኪዳን ዘንድ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ የአይሁድ ካህን ነበረ። የሠራያ ልጅ ሲሆን በፋርስ ንጉስ አርጤክስስ 7ኛው አመት (464 ክ.በ.) ከ5000 ከወገኖቹ ጋራ ወደ ኢየሩሳሌም ለመመለስ ፈቃድ ተቀበለ። ከዚህ 13 አመት በኋላ ነህምያ የከተማውን ቅጥር ሲጠግነው ዕዝራ ኦሪት በሙሉ ለሕዝብ አነበበ (መጽሐፈ ነህምያ ምዕ. 8)። በአይሁዳዊው ታሪክ ጸሐፊ በዮሴፉስ ዘንድ ይህ የፋርስ ንጉስ አርጤክስስ ሳይሆን አሕሻዊሮስ ነበረ። አርጤክስስ የአሕሻዊሮስ ልጅ ሲሆን እነዚህ 2 ነገስታት ስሞች ብዙ ጊዜ በተለያዩ ቅጂዎች ተደናገሩ። ዮሴፉስ ደግሞ ዕዝራ የሞተበት ወራት ኤልያሴብ ታላቁ ካህን በሆኑበት ወቅት ገደማ እንደ ነበር ይመሰክራል። የአሕሻዊሮስ ዘመን ከሆነ 7ኛው አመት 486 ክ.በ. ነበር። ዕዝራ መጽሐፈ ዕዝራንና መጽሐፈ ነህምያ ከመጻፉ በላይ በዲዩትሮካኖኒካል መጽሐፍት ክፍል የሚገኙት መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤልና መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ እንደ ጻፈ ይባላል። መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ ለመጽሐፈ ዕዝራ በጣም ተመሳሳይ በመሆኑ በዕዝራ ካልዕ 81 ግን ሠራያ ሳይል በግድፈት የአዛርያስ ልጅ ይለዋል። ዕዝራ ሱቱኤል በሚባለው ትንቢት ደግሞ በ11 የጻፈው ኢየሩሳሌም ከጠፋች 30 አመት በባቢሎን መሆኑን ይላል። ይህም 565 ክ.በ. ማለት ነው። በዚህ መጽሐፍ 1344 መሠረት 24 መጻሕፍት በ40 ቀን ውስጥ ጻፈ ቢለን፥ በሌሎች ልሣናት ሕትመት ግን ስለ 94 መጻሕፍት እየተናገረ ከነዚህ መሀል ተጨማሪው 70 መጻሕፍት በምስጢር እንዲቆዩ ነበረባቸው ይላል። \n \nጥያቄ: ዕዝራ የጻፋቸው መፅሐፍት እነማን ናቸው?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ መጽሐፈ ዕዝራንና መጽሐፈ ነህምያ ነው።" }, { "inputs": "ከዚህ በታች በተገለጸው አውድ ተከታዩን ጥያቄ ይመልሱ፡ \nፕሮፌሰር ሙሃመድ ዩኑስ ትውልድ በ28 ጁን 1940 እ.ኤ.አ. የባንግላዴሽ የባንክ ባለሞያና ኤኮኖሚስት ናችው። ማይክሮክሬዲት ተብሎ የሚታወቀውን የአነስተኛ የብድር አገልግሎት በችግር ለሚኖሩ ወገኖች የመስጠትን ስራ የጀመሩትና የስፋፉት ሰው ናችው። ፕሮፌሰሩ እንነኝህ ባንክ አላስተናግድ ብሎ የተዋቸውን ድሆች የሚያገለግለውን ግራሚን ባንክን አቋቁመዋል። በጥቅምት 1999 ፕሮፈሠሩና ባንኩ የሰላም የኖቤል ተሸላሚ ለመሆነ በቅተዋል ይህም ሽልማት የልማት እድገትና ማህበረሰባዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል በማስመስከራቸውና ይህ ደግሞ ለሰላም ወሳኝነት ያለው መሆኑን ሽልማት ሰጭው ኮሚቴ ስላመነበት ነው። ፕሮፌሰር የበርካታ ሽልማቶች ባለቤት ሲሆኑ ከነዚህም የአለም የምግብ ሽልማት ይገኝበታል። የድሆች አበዳሪ በሚል ርዕስ አንድ የስራሳቸውንና የስራቸውን ታሪክ የሚያትት መጽሐፍ ደርሰዋል። \n \nጥያቄ: የባንግላዴሽ የባንክ ባለሞያና ኤኮኖሚስት የሆኑት ፕሮፌሰር ሙሃመድ ዩኑስ መቼ ተወለዱ?", "targets": "ከጥያቄው ጋር የሚስማማው ምላሽ በ28 ጁን 1940 እ.ኤ.አ ነው።" } ]